Sheger Times Media️

@shegrtimesmedia


በማትሪክስ ኢንተርቴይመንትና የፕሬስ ስራዎች ኃ.የተ.የግ.ማ እየታተመ በየ15 ቀኑ ለአንባቢያን የሚደርሰው የ #ሸገር_ታይምስ መፅሄት ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው።

Sheger Times Media️

21 Oct, 23:39


https://youtu.be/OcqcOVVRCUI?si=Lx0mwpcqCxrIE5HF

Sheger Times Media️

21 Oct, 18:32


‼️በመርካቶ ሸማ ተራ አካባቢ የተከሰተውን የእሳት አደጋ ለመቆጣጠር ሄሊኮፕተር በመጠቀም ጥረት እየተደረገ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
***************
በመርካቶ ሸማ ተራ አካባቢ የተከሰተውን የእሳት አደጋ ለመቆጣጠር እሳት አደጋ እና ስጋት መከላከል እንዲሁም ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመሆን ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለፁ፡፡

ከንቲባዋ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባስተላለፉት መልእክት፤ በመርካቶ ሸማ ተራ አካባቢ በተከሰተው የእሳት አደጋ በንብረት ላይ ለደረሰው ጉዳት እጅግ አዝነናል ብለዋል።

አደጋውን ቶሎ ለመቆጣጠር እየተደረገ ባለው ጥረት የአካባቢው መንገድ የእሳት አደጋ መኪና በተሟላ ሁኔታ ለመንቀሳቀስ አስቸጋሪ በመሆኑ ሄሊኮፕተር ለመጠቀም ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

ይህንን አደጋ ለመቀነስ ርብርብ እያደረጋችሁ ያላችሁ አካላት ሁላ ጥረታችሁን አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ አሳስባለሁ ብለዋል ከንቲባዋ በመልእክታቸው።
👀 https://www.youtube.com/c/ShegerTimesMedia

Sheger Times Media️

21 Oct, 18:27


‼️በሸማ ተራ የተነሳውን የእሳት አደጋ ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር ጥረት እየተደረገ ነው።

ዛሬ ጥቅምት 11 ቀን 2017 ዓ.ም ማምሻዉን በመርካቶ ሸማተራ አየተባለ በሚጠራዉ አካባቢ በንግድ ሱቆች ላይ የተነሳዉን የእሳት አደጋ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር ለማዋል የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል የአደጋ ጊዜ ሰራተኞችና ባለድርሻ አካላት ርብርብ እያደረጉ ነዉ።

አካባቢው የተጨናነቀ እና ለተሽከርካሪ አስቸጋሪ በመሆኑ እሳቱን በፍጥነት ለመቆጣጠር አስቸጋረ አድርጎታል ሲሉ የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ተናግረዋል።

የአደጋ ገዜ ባለሙያዎች እና ተሽከርካሪዎች በስፍራው ከሚገኘው ቅርንጫፍ በተጨማሪ ከሌሎች ቅርንጫፎች መላካቸውን ለማወቅ ተችሏል።
👀 https://www.youtube.com/c/ShegerTimesMedia

Sheger Times Media️

21 Oct, 12:23


ዛሬ ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩትና በ2016 የከሸፈዉን የቱርክ መፈንቅለ መንግስት በማሴር የተከሰሱት የ83 ዓመቱ ፋቱላህ ጉለን ማናቸው?

ሙሉ ታሪኩን በተከታዩ ሊንክ ይመልከቱት!
👇👇
https://yt.psee.ly/6l9u54

Sheger Times Media️

20 Oct, 22:53


‼️በእሳት የተፈተነው …

ከአደገኛ ወንበዴነት ወደ አንፀባራቂ ኮከብነት!
📍📍📍
https://youtu.be/ILQJRexcKL0?si=i9mlYJgGgIZNfRKM

Sheger Times Media️

20 Oct, 08:41


የሁለት አመቱን ህፃን ሰርቆ የወሰደዉ ተጠርጣሪ መያዙን በካፋ ዞን የጊምቦ ወረዳ ፖሊስ ገለፀ።

ወላጆች ህፃናት ልጆቻቸዉን በየጊዜዉ ክትትል ማድረግ እንዳለባቸዉ ፖሊስ አሳስቧል።

በካፋ ዞን የጊምቦ ወረዳ ፖሊስ የማህበረሰብ አቀፍ ወንጀል መከላከል ዲቪዥን ኃላፊ ዋና ሳጅን ተሾመ ወልደስላሴ እንደገለፁት ጥቅምት 8 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12:00 ከዲሪ ከተማ ወደወረዳዉ ዋና ከተማ ዑፋ በባጃጅ ይዞት መምጣቱንና ከባጃጅ ወርዶ አቆፎት ወደጫቃ እየወሰደ ህብረተሰቡ የግለሰቡ ሁኔታ ስላጠራጠራቸዉ ለፖሊስ ጥቆማ መስጠቱን ተናግረዋል።

ፖሊስ ግለሰቡን በቁጥጥር ስር አድርጎ ባደረገዉ ምርመራ ወባ ታሞብኝ ለማሳከም ማምጣቱን ቢገልፅም ህፃኑ የእሱ እንዳልሆነ ጥሪጣሬ በመፈጠሩ ከቀበሌ ፖሊስ ህፃን ስለመጥፋቱ መረጃ መድረሱን አስረድተዋል።

ህፃኑ ለወላጆቹ የተመለሰ ሲሆን ግለሰቡ ከዚህ ቀደም በስለት ሰዉ ወግቶ ሁለት አመት ተፈርዶበት ማረሚያ ገብቶ እንደነበር ያመለከቱት ዋናሳጅን ተሾመ ወላጆች ህፃናትን ወደ ትምህርት ቤት በሚሄዱበት ወቅት ወላጆች ተገቢውን ክትትል እንዲያደርጉ መልዕክታቸዉን አስተላልፈዋል የደቡብ ምዕራብኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ዘግቧል።

Sheger Times Media️

19 Oct, 22:12


‼️ሙስና ህጋዊ የሆነባት ሀገር!

👀የመንግስት ቢሮዎችን ወደ ፔንሲዮንነት…
📍
https://youtu.be/0-GQR2O7MQE?si=9lIs3t1AE8ffUJ4K​⁠@Meshualekia

Sheger Times Media️

18 Oct, 17:26


ℹ️ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ከተመድ ምክትል ዋና ጸሐፊ ጋር ተወያዩ።

ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) ምክትል ዋና ጸሐፊ እና የፖለቲካ እና የሠላም ግንባታ ጉዳዮች ኃላፊ ሮዝመሪ ዲካርሎ ጋር ተወያዩ፡፡

በውይይታቸውም በአፍሪካ ቀንድ ጉዳዮች በተለይም በሶማሊያ ሰላም እና ፀጥታ ላይ መምከራቸውን ፕሬዚዳንቱ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልጸዋል፡፡

በዚህም ሽብርተኝነትን በመዋጋት የተገኘው ውጤት መቀልበስ እንደሌለበት ለማረጋገጥ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ርምጃ እንደሚያስፈልግ ማስገንዘባቸውን ነው ያመላከቱት፡፡
👀https://www.youtube.com/c/ShegerTimesMedia

Sheger Times Media️

18 Oct, 14:30


ከኮሪደር ልማት ጋር ተያይዞ በሚነሡ የተዛቡ መረጃዎች ላይ ግልፅነት ተፈጥሯል-ከንቲባ አዳነች አቤቤ

"በአዲስ አበባ እየተተገበረ ካለው የኮሪደር ልማት ጋር ተያይዞ በሚነሡ የተዛቡ መረጃዎች ላይ ከነዋሪዎቹ ጋር ግልፅነት ፈጥረናል" ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡

ከንቲባ አዳነች ከተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች፣ ከከተማዋ ነዋሪዎችና ከልማት ተነሺ ተወካዮች፣ ከታዋቂ እንዲሁም ከሐይማኖት አባቶች ጋር በኮሪደር ልማት ሥራ ሂደት ላይ ተወያይተዋል።

በውይይታቸውም ÷ ከኮሪደር ልማት አስፈላጊነት ጋር ተያይዞ ያሉ ጥንካሬዎች፣እጥረቶች ፣የተለያዩ ሀሳቦች እና ጥያቄዎች መነሳታቸውን ከንቲባዋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስታውቀዋል፡፡

"ከልማት እና የህዝብን ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ ዉጪ ምንም ድብቅ አጀንዳ ስለሌለን ሁሉንም መረጃ እና አሰራር በዝርዝር አቅርበን ግንዛቤያቸውን የሚጨምሩ እና የመረጃ ክፍተቶችን የሚሞሉ እንዲሁም ላነሱዋቸው ጥያቄዎች ምላሽ የሚሆኑ ማብራሪያዎች ሰጥተናል" ሲሉም ገልጸዋል።

ከኮሪደር ልማት ጋር ተያይዞ በሚነሡ የተዛቡ መረጃዎች ላይም ግልፅነት ፈጥረናል ነው ያሉት ከንቲባ አዳነች ።

ከድህነት አረንቋ ውስጥ ለመውጣት ቆርጠን እየሰራን እና ያረጁ ቤቶችን እየቀየርን የዜግነት ክብርን ማረጋገጥ ላይ ስለመሆናችን የግንዛቤ ችግር ባይኖርም የልማት ፍላጎቱ ግን ዕለት በዕለት በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ መሆኑን ተገንዝበናል ብለዋል፡፡

የለዉጥ መንገድ አልጋ በአልጋ ስለማይሆን ጊዜያዊ ችግሮችን ተቋቁመን መሰረታዊ ለወጥ ለማምጣት በጋራ መትጋት እንዳለብን ተግባብተናል ሲሉም ገልጸዋል፡፡

በልማቱ ትብብር እያደረጉ ላሉ የከተማዋ ነዋሪዎች ምስጋና ያቀረቡት ከንቲባዋ "ለከተማችን ብልፅግና ያለ እረፍት በፍጥነት መስራታችንን አጠናክረን የምንቀጥል ይሆናል" ሲሉ አስገንዝበዋል፡፡

Sheger Times Media️

18 Oct, 14:05


‼️በጫሞ ሐይቅ ላይ የደረሰውን የጀልባ መስጠም አደጋ ተከትሎ የነፍስ አድን ሥራ እየተከናወነ ነው

በጋሞ ዞን ከአቡሎ አርፋጮ ወደ አርባምንጭ ከተማ 16 ሰዎችን እና ሙዝ ጭና ስትጓዝ የነበረች ጀልባ ጫሞ ሐይቅ ላይ መስጠሟን የጋሞ ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል፡፡

ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜም ሶስት ሰዎች በሕወት መገኘታቸውን መምሪያው ገልፆአል።

አደጋው ትናንት 10 ሠዓት ከ20 ገደማ መከሰቱን የገለጹት በመምሪያው የሕዝብ ግንኙነትና ገጽታ ግንባታ ዲቪዥን ኃላፊ ኮማንደር ረታ ተክሉ÷ አሁንም የነፍስ አድን ሥራው ተጠናክሮ መቀጠሉን ተናግረዋል፡፡

የአደጋው መንስኤ ከልክ በላይ መጫን ሳይሆን እንዳልቀረ ጠቁመው÷ በጀልባዋ ላይ የነበሩት ተሳፋሪዎች የቀን ሠራተኞች መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡
ኤፍቢሲ
👀https://www.youtube.com/c/ShegerTimesMedia

Sheger Times Media️

18 Oct, 13:58


‼️ከ350 በላይ የክላሽንኮቭ ጥይት ለመሸጥ ይዞ ሲንቀሳቀስ የነበረ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ዋለ።
**
358 የክላሽንኮብ ጥይት ይዞ ለመሸጥ ሲንቀሳቀስ የነበረ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ እንደገለፁት በካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ አስተዳደር 03 ቀበሌ ጥቅምት 08 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ሰዓት አንድ ተጠርጣሪ 358 የክላሽንኮብ ጥይት ፍሬዎችን በባለሶስት እግር ባጃጅ ተሽከርካሪ ይዞ ሲንቀሳቀስ በክልሉ ፖሊስ፣ፀጥታ፣የዞን ፖሊስ የመረጃ ደህንነት ክትትል ባለሙያዎች በቁጥጥር ስር መዋሉን ተናግረዋል።

ህገወጥ የተተኳሽ ጥይት በህገወጦች እጅ ቢገባ ለሰዉ ህይወት መጥፋትና ለአከባቢ ሰላም መናጋት የሚያስከትል መሆኑን ያመለከቱት ኢንስፔክተር ደጀኔ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ 1 ተጠርጣሪ ተይዞ ምርመራ እየተጣራበት እንደሚገኝ ጨምረዉ አስረድተዋል።

የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ከሰላም ወዳዱ ህዝብ ጋር በመሆን የክልሉ ሠላምና ደህንነት ለመጠበቅ የፀጥታ መዋቅሩ የተሰጠዉን ኃላፊነት እየተወጣ መሆኑን አመልክተዉ የባለሶስት እግር ባጃጅ አሽከርካሪዎች የሚጭኑትን ዕቃዎች አጣርተው እንዲጭኑ አሳስበዉ ህብረተሰቡም ለፀጥታ አካላት በጦር መሳሪያ ዝዉዉር የተሰማሩ አካላትን ጥቆማ በመስጠት እንዲተባበር ጥሪአቸዉን አቅርበዋል ሲል የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሚንኬሽን ዘግቧል።
👀https://www.youtube.com/c/ShegerTimesMedia