Ethiopian Enterprise Development (የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት)

@ethiopianenterprisedevelopment


Ethiopian Enterprise Developmen (የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት)

Ethiopian Enterprise Development (የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት)

22 Oct, 18:19


በመቀሌ ከተማ የሚገኙ አምራች ኢንተርፕራይዞች የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እያደረገላቸው መሆኑን ገለፁ፡፡

Ethiopian Enterprise Development (የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት)

22 Oct, 06:32


በጨርቃጨርቅ ፓተርንና ስፌት ዙሪያ በሁለት ዙር ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ

EED ጥቅምት 11/2017 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ጨርቃጨርቅና ቆዳ ውጤቶች ዘርፍ ለተውጣጡ 40 አመራሮችና ባለሙያዎች በአልባሳት ፓተርን ዝግጅትና ስፌት ዙሪያ በሁለት ዙር ሲሰጥ የነበረውን ስልጠና አጠቃለለ፡፡
በማጠቃለያ ፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ስራ አመራር ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ከላሊ ወ/ገብርኤል እንደገለፁት በስልጠናው የተሳተፉ ባለሙያዎች በፅንሰ ሀሳብና በተግባር ልምምድ ያገኙትን ዕውቀትና ክህሎት ለአምራች ኢንተርፕራይዞች እንዲያስተላልፉ ጠይቀዋል፡፡

በጨርቃጨርቅ አልባሳት ፓተርን ዝግጅትና ስፌት ዙሪያ ሲሰጥ የነበረው ስልጠና መሬት ላይ ያለውን የአምራች ኢንተርፕራይዞች ችግር ከመፍታት አንፃር ትልቅ አስተዋፆ እንዳለው የገለፁት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ የጨርቃጨርቅ አልባሳትና ቆዳ ውጤቶች ድጋፍ ዳሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሙሉሃብት ገነቴ ገለፁ፡፡

ስልጠናው አምራቾች ከፖተርን ዝግጅት ጋር በተያያዘ የሚያጋጥማቸውን ብክነት እና የምርት ጥራት ችግሮች እንዲቀርፉ የሚሰጠውን የቴክኒክ ድጋፍ ደረጃ እንደሚያሳድገው የገለፁት አቶ ሙሉሃብት በቀጣይ ተከታታይነት ያለውና የአምራቾችን ችግር የሚፈቱ ስልጠናዎችን የልማት መስሪያ ቤቱ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

#ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት

Ethiopian Enterprise Development (የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት)

19 Oct, 14:06


የልማት መስሪያ ቤቱ የተቋም ሀብት ዕቅድ ስርዓት - ERP ለመተግበር የሚያግዝ ስልጠና ሰጠ

EED ጥቅምት 9/ 2017 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት በሰው ሃብት አስተዳደር ፣ በመኪና ስምሪት አስተዳደር እና በመረጃ አስተዳደር ዘርፎች ላይ የተቋም ሀብት ዕቅድ ስርዓት (Enterprise resource planning) ለመተግበር የሚያስችለውን ስልጠና ዛሬ ጀመረ፡፡

የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አለባቸው ንጉሴ በመክፈቻ ስነ ስርአቱ ላይ እንደተናገሩት ተቋሙ ከሳይበር ሶፍት ጋር በመተባበር የተቋም ሀብት ዕቅድ ስርዓት ትግበራ ላይ ሲሰራ ቆይቷል፡፡

የስልጠናው አላማ ለተቋም ሀብት ዕቅድ ስርዓት በተዘጋጁት ሞጁሎች ላይ የተግባር ልምምድ  በመስጠት የስራ ክፍሎቹን  ወደ ሙሉ  ትግበራ በማስገባት ወቅቱ የሚጠይቀውን ዘመናዊ አሰራር ተግባራዊ ለማድረግ እንደሆነ ዋና ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡

የተቋም ሀብት ዕቅድ ስርዓት (ERP) መተግበር ወጪ ቆጣቢ በሆነ መልኩ  ፈጣን ፣ትክክለኛና ቀልጣፋ የሰው ሀብት እና የተሽከርካሪ ስምሪት አስተዳደር ፣ የመረጃ፣የማህደር እንዲሁም የኦንላይን የአይቲ ድጋፍ እንዲኖር በማድረግ በተቋሙ ያለውን የመረጃና የዶክመንት አያያዝ ችግር ይቀርፋል ብለዋል፡፡

በተጨማሪም ሰልጣኞች የተግባር ስልጠና ልምምዱን በአግባቡ በመረዳት እና በመያዝ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት መወጣት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል፡፡

Ethiopian Enterprise Development (የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት)

18 Oct, 10:52


🟩 ቤሬ ሐር

HANDMADE ETHIOPAN SILK

ኢንተርፕራይዙ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አርባ ምንጭ ከተማ የሚገኝ ሲሆን የሐር ትሎችን ከማራባት ጀምሮ ጨርቅ ሆኖ እስኪወጣ ድርስ ሂደቶችን ጠብቆ የሚሰራ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ድርጅት ነው፡፡ የሚያመርታቸውን የሐር አልባሳትን በአርባ ምንጭና በአዲስ አበባ ከተማ በጥራት ተደራሽ በማድርግ ላይ ያለ ድርጅት ነው፡፡

Ethiopian Enterprise Development (የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት)

18 Oct, 10:49


ቤሬ ሐር

HANDMADE ETHIOPAN SILK

ኢንተርፕራይዙ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አርባ ምንጭ ከተማ የሚገኝ ሲሆን የሐር ትሎችን ከማራባት ጀምሮ ጨርቅ ሆኖ እስኪወጣ ድርስ ሂደቶችን ጠብቆ የሚሰራ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ድርጅት ነው፡፡ የሚያመርታቸውን የሐር አልባሳትን በአርባ ምንጭና በአዲስ አበባ ከተማ በጥራት ተደራሽ በማድርግ ላይ ያለ ድርጅት ነው፡፡

የቤሬ ሐር ኢንተርፕራይዝ መስራችና ስራ አስኪያጅ አቶ ገለታ ሐይሉ እንደተናገሩት ስራውን ከመጀመራቸው በፊት በዕህል ንግድ ላይ ተሰማርተው እንደነበርና በአንድ ወቅት ሳይንስና ቴክኖሎጅ ምርምር ከመልካሳ ምርምር ማዕከል በራዲዩ በሐር ልማት ዙሪያ ሲተላላፍ በመስማት ወደ ስራው እንደገቡ ያስታውሳሉ፡፡

ድርጅቱ በ1997 ዓ.ም በ200 ካሬ ሜትር ቦታ፣ በ600 ሺህ ብር ካፒታልና በአምስት የሰው ሐይል እንደተጀመረ የሚናገሩት ስራ አስኪያጁ በወቅቱ መንግስት ለዘርፉ ትኩረት በመስጠት አሁን ያሉበትን የመስሪያ ቦታ እንደሰጣቸው ተናግረዋል፡፡

ከዚህ ቀደም የሐር ክሩን ብቻ በማምረት ለሚሸምኑ ድርጅቶችና ግለሰቦች ሲሸጡ እንደነበርና አሁን ላይ ባካበቱት ልምድ የራሳቸውን ዲዛይነርና የሽመና ባለሙያዎችን በመቅጠር ያለቀለት በእጅ የተሰሩ የሐር ልብሶችን በማምረት ለገበያ እንደሚያቀርቡ አቶ ገለታ ተናግረዋል፡

የሐር ክር ለቀዶ ጥገናና ለፓራሹት መውረጃነት አገልግሎት ላይ ሲውል ልብሱ ደግሞ የሰውነትን ሙቀት በመቆጣጠር ምቾት የሚሰጥ እንዲሁም ፕሮቲን ያለው በመሆኑ በዓለም ደረጃ እጀግ ተፈላጊ ምርት አድርጎታል ያሉት ስራ አስኪያጁ በኢትዮጵያ በሐር ልማት ላይ የተሳተፉ ባለሀብቶች የሉም ብለዋል፡፡

የስራውን ሁኔታና የዘርፉን አዋጭነት ለማስገንዘብ ቤሪ ሐር ልማት ድርጅት እንደ አንድ የምርምር ተቋም ሆኖ እያገለገለ እንደሚገኝና ከስራው ስፋት አንጻር በራሱ ማሳ ላይ የሚያመርተው ምርት አልበቃ ብሎት በአካባቢው ያሉ 200 አርሶ አደሮችን በማሰልጠን ምርት እንደሚወስድ አብራርተዋል፡፡

የሐር ምርት በውጭ ሐገር ደረጃ ካለው ተፈላጊነት አንጻር ኤክስፖርት ለማድረግ ፍላጎት ቢኖርም በምርት አቅርቦት፣በዘርፉ የሰለጠነ የሰው ሐይል፣ ፋይናንስ፣ የቦታና የማሽን አቅርቦት ችግር ምክንያት በስፋት ኤክስፖርት ማድረግ እንዳልተቻለና እነዚህ ችግሮች የሚቀረፉ ከሆነ በስፍት በማምረት የውጭ ገበያውን መቆጣጠር እንደሚቻል ተናግረዋል፡፡

ቤሬ ሐር ኢንተርፕራይዝ ከ80 በላይ ለሚሆነ ዜጎች የስራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን አጠቃላይ ካፒታሉም ከ30 ሚሊየን ብር በላይ ነው፡፡

👉አድራሻ፡- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አርባ ምንጭ ኤርፖርት 800 ሜትር ገባ ብሎ ና አዲስ አበባ ከተማ ቦሌ መድሐኒዓለም ገልፍ አዚዝ 1ኛ ፎቅ

☎️ ስልክ፡- 09 77 07 85 15

🌐 BER HAR፡- በማለት በሁሉም የሶሻል ሚዲያ አማራጮች ማግኘት ይችላሉ

Ethiopian Enterprise Development (የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት)

18 Oct, 10:39


ዓለም አቀፍ ኮንፈረንሱ ኢትዮጵያ በግብርና፣ ኢንዱስትሪው እና ቱሪዝም ዘርፍ ያስመዘገበቻቸውን ስኬቶች ለዓለም የምታስተዋውቅበት ዕድል  ይፈጥራል
፡፡፡፡፡፡፡፡
EED ጥቅምት 8/2017 ዓ.ም

ኢትዮጵያ  የምታስተናግደው ርሀብ አልባ ዓለምን እውን ማድረግ ይቻላል (WORLD WITH OUT HUNGER IS POSIBLE)  አለም አቀፍ ኮንፍረንስ  በአዲስ አበባ ከጥቅምት 26 እስከ 28 ቀን 2017 ዓ.ም ይካሄዳል፡፡ 
  
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሀሰን መሀመድ  አፍሪካን  እየፈተነ ያለው የምግብ ዋስትና አለመረጋገጥ  ለከፋ ችግር እና እንግልት እየዳረገ መሆኑን ገልጸው  በተለይም የሀገር ኢኮኖሚን ከማረጋጋት እና አምራች ዜጋን ከመፍጠር አኳያ  የሚፈጥረው ጫና ከፍተኛ በመሆኑ የዓለም ሀገራት  በጋራ መምከር እንደሚያስፈልግ አንስተዋል፡፡

ኢትዮጵያ  የምታስተናግደው ርሀብ አልባ ዓለምን እውን ማድረግ ይቻላል (WORLD WITH OUT HUNGER IS POSIBLE)  አለም አቀፍ ኮንፍረንስ  የምግብ ዋስትና አለመረጋገጥ  ችግርን  በዘላቂነት ሊፈታ የሚችል የመፍትሄ ሀሳቦችን እንደሚያስቀምጥ  ይጠበቃልም ብለዋል፡፡ 

ኮንፈረንሱ ኢትዮጵያ በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በቱሪዝም ዘርፍ የተገኙ ስኬቶችን ለአለሙ ማህበረሰብ የምታስተዋውቅበት እድል እንደሚፈጥር ገልጸዋል፡፡

ለኮንፈረንሱ አስፈላጊው  ቅድመ ዝግጅት እየተካሄደ መሆኑንም አክለዋል፡፡

#ኢትዮጵያ_ታምርት
#እኛም_እንሸምት

Ethiopian Enterprise Development (የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት)

16 Oct, 15:48


የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እና የተባበሩት መንግስታት የንግድ እና ልማት ኮንፈረንስ በአፍሪካ ያደጉ ሀገራት ልዩ ፕሮግራሞች የአፍሪካ ክልላዊ ቢሮ በጋራ ለመስራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አካሄዱ፡፡
=====
EED ጥቅምት 06/2017 ዓ.ም

የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል የተባበሩት መንግስታት የንግድ እና ልማት ኮንፈረንስ በአፍሪካ ያደጉ ሀገራት ልዩ ፕሮግራሞች የአፍሪካ ክልላዊ ቢሮ ኃላፊ ዳያን ሳይንዞጋን በፅ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል ።

የአምራች ኢንዱስትሪውን ዘርፍ ለማሳደግ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን ለመደገፍ ፍላጎት እንዳላቸው እና አብሮ ለመስራት ዕቅድ ማውጣቸውን ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡

በተለይም በንቅናቄው የአቅም ግንባታ ዘርፍ ድጋፍ ለማድረግ እና ያሉትን ክፍተቶች ለመሙላት ፍላጎት እንዳላቸው ያነሱት አቶ መላኩ አለበል በቅርቡ ባለሙያ ከውጪ በመላክ ይህን ስራ እንደሚጀምሩ ውይይት ማድረጋቸውን ገልፀዋል፡፡

የተባበሩት መንግስታት የንግድ እና ልማት ኮንፈረንስ በአፍሪካ ያደጉ ሀገራት ልዩ ፕሮግራሞች የአፍሪካ ክልላዊ ቢሮ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የአቅም ግንባታ ዘርፍ ድጋፍ በማድረግ በጋራ በትብብር ለመስራት ተስማምተዋል፡፡

#ኢትዮጵያ_ታምርት
#እኛም_እንሸምት