BBC News አማርኛ ️

@bbc_amharic_news1


━━⊱✿⊰━━
እንኳን ወደ BBC News አማርኛ መጡ

ቢቢሲ ከሌሎች ድረ-ገጾች እና ቴሌግራም ገጾች ለሚመጡ መረጃዎች ሀላፊነት አይወስድም. 

ድረ-ገፅ:- https://www.bbc.com/amharic

የቴሌግራም ገፅ:- https://t.me/BBC_Amharic_News1

የፌስቡክ አድራሻ:- https://m.facebook.com/BBCnewsAmharic/

@BBC_Amharic_News1

BBC News አማርኛ ️

13 Jun, 08:55


📌ማሳወቂያ

ይህ የቴሌግራም ገፅ ለብዙሀን ተደራሽ መሆን ስላልቻለ 20ሺ አባላት እስኪደርስ ድረስ መረጃዎች እንደማንለቅ ልናሳውቅ እኖዳለን። ስለሆነም የቢቢሲ አማርኛ ዜናዎችን በእየለቱ ለማግኘት እስከዛው እነዚህን አማራጮች እንዲጠቀሙ በአክብሮት እንጠይቃለን።


ድረ-ገፅ:- https://www.bbc.com/amharic

የፌስቡክ አድራሻ:- https://m.facebook.com/BBCnewsAmharic/

@BBC_Amharic_News1

BBC News አማርኛ ️

13 Jun, 07:50


የአሜሪካ ፖለቲከኞች የጦር መሳሪያ ቁጥጥር ላይ ከስምምነት ደረሱ

በአሜሪካ የጦር መሳሪያ ቁጥጥርን በተመለከተ ልዩነት ያላቸው ሪፐብሊካን እና ዲሞክራቶች በአዲሱ መመሪያ ላይ ከስምምነት መደረሳቸው ተገለጸ። ሆኖም የምክረ ሃሳባቸው ሂደት የሚጠበቅበትን ያህል አልተጓዘም ተብሏል።

ፍሎሪዳ ውስጥ በአንድ ትምህር ቤት ላይ ከተከፈተ ተኩስ የተረፉት ዴቪድ ሆግ “ምንም እንኳን ይህ ስምምነት ትንሽ ቢሆነም ጠቃሚ እርምጃ ነው” ብለዋል።

ሌላዋ የቀድሞ ሕግ አውጪ እና እንደ አውሮፓውያኑ በ2011 በአሪዞና ግዛት ውስጥ ከተፈጸመ ጥቃት ጉዳት ደርሶባቸው የተረፉት ጋብሬል ጊፎርድስ ስምምነቱን “ጠቃሚ እርምጃ ነው” ብለውታል።

ተቀናቃኞቹ ከስምምነት የደረሱበት አዲሱ እቅድ የጦር መሳሪያ ገዢዎች ጠንካራ ምርመራ የሚደረግባቸው ሲሆን ከ 21 ዓመት በላይ መሆን እና ከሕገ ወጥ የመሳሪያ ግዢ ጋር በተያያዘ ምረመራ ይደረገባቸዋል።

ይህ የጦር መሳሪያ ቁጥጥር ምክረ ሀሳብ ትላንት ዕሁድ ነበር ይፋ የተደረገው። ታዲያ 10 የሪፐብሊካን አባላት ሕጉን የደገፉ ሲሆን ይህ ማለት ወደ ሕግ ለመቀየር የሚስፈልገው ቁጥር ተሟልቷል ማለት ነው።

ፕሬዝዳነት ጆ ባይደን ዕቅዱ በትክክለኛ መንገድ ላይ እየሄደ ነበር ያሉ ሲሆን፣ ሆኖም እሳቸውም ይሁን ሌሎች ዲሞክራቶች እንዲሆንከሚፈልጉት እጅግ የራቀ ነው።

https://www.bbc.com/amharic/articles/c1wl701nx19o

@BBC_Amharic_News1
@BBC_Amharic_News1

BBC News አማርኛ ️

13 Jun, 07:49


አብዛኞቹ አፍሪካውያን ወጣቶች ከአህጉሪቱ መሰደድ እንደሚፈልጉ ጥናት አመለከተ

አብዛኞቹ አፍሪካውያን ወጣቶች በአገራቸውና በአህጉሪቱ ላይ ብሩህ ተስፋ እንደማይታያቸው አንድ ጥናት አመለከተ።

በጥናቱ ውስጥ ከተካቱት አፍሪካውያን ወጣቶች መካከል ሁለት ሦስተኛው ስለ እራሳቸው የወደፊት ተስፋ አውንታዊ ምልከታ ቢኖራቸውም፣ አገራቸውና አህጉራቸው አፍሪካ እየሄዱበት ባለው አቅጣጫ ላይ ተስፋ ሰጪ ነገር እንደማያዩ ተናግረዋል።

‘አፍሪካን ዩዝ ሰርቬይ’ በተባለው በዚህ ጥናት ውስጥ ከ15 የአፍሪካ አገራት የተወጣጡ ከ4,000 በላይ ወጣቶች ከአጥኚዎቹ ጋር የፊት ለፊት ቃለ ምልልስ አድርገው ነው፤ ስለአገራቸውና አህጉራቸው ያለቸውን አመለካከት ለአጥኚዎች የገለጹት።

https://www.bbc.com/amharic/articles/cxr67p3y0xko

@BBC_Amharic_News1
@BBC_Amharic_News1

BBC News አማርኛ ️

13 Jun, 07:47


ታዋቂው የትግርኛ ድምፃዊ ዳዊት ነጋ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

ታዋቂው ድምጻዊ ዳዊት ነጋ ትናንት እሁድ ሰኔ 5 ቀን 2014 ዓ.ም. አመሻሹ ላይ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን የቅርብ ወዳጆቹና ዘመዶቹ ለቢቢሲ ገለጹ።

ዳዊት ነጋ ባደረበት ድንገተኛ ህመም ዓርብ ዕለት አዲስ አበባ ውስጥ በሚገኘው አዲስ ህይወት ሆስፒታል መግባቱን ተናግረዋል።

ባለፈው ሳምንት ሰኞ ዕለት በጉንፋን መልክ የጀመረ ህመሙ ከተባባሰ በኋላ ዓርብ ወደ ሆስፒታል ተወስዶ እስከ ቅዳሜ ድረስ ህክምና ሲደረግለት ቆይቷል።

ትናንት እሁድ ከሰዓት በኋላ ህመሙ ሲጸናበት ወደ ጽኑ ህሙማን ክትትል ክፍል መግባቱን እና ማታ 1፡00 ሰዓት አካባቢ ህይወቱ ማለፉን ጓደኞቹ እና ዘመዶቹ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ዳዊት ወደ ሆስፒታሉ ከመምጣቱ በፊት ህመሙን ለማስታገስ በቤት ውስጥ ግሉኮስ ይወስድ እንደነበረም ተነግሯል።

ህመሙ ሲበረታበት ወደ ሆስፒታል ከተወሰደ በኋላ የስኳር መጠኑ መጨመሩን እና ህመሙ ወደ የሳንባ ምች (ኒሞኒያ) መቀየሩን ተነግሮታል።

በትላንትናው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት በተለየው የዳዊት አስከሬን ላይ ተጨማሪ ምርመራ እንደሚደረግም ሲያስታምሙት የሰነበቱት ጓደኞቹና አብሮ አደጎቹ ለቢቢሲ ገልፀዋል።

https://www.bbc.com/amharic/articles/cp9nz07x94eo

@BBC_Amharic_News1
@BBC_Amharic_News1

BBC News አማርኛ ️

13 Jun, 06:51


ለዩክሬን ሲዋጋ የነበረው የቀድሞ የብሪታኒያ ወታደር ተገደለ

የቀድሞው የእንግሊዝ ጦር አባል የነበረው ግለሰብ ዩክሬን ውስጥ መገደሉን ቤተሰቦቹ አሳወቁ።

ጆርዳን ጋትሊ ከብሪታኒያ ጦር በመውጣት ባለፈው መጋቢት ነበር በሩሲያ ከተወረረችው ዩክሬን ጎን ለመሰለፍ ወደ ጦር አውድማ ያቀናው።

የወታደሩ አባት ልጄ "ጀግና" ነው ሲሉ በማኅበራዊ ትስስር ገፃቸው ፅፈዋል።

በምሥስራቃዊቷ የሰቨሮዶኔስክ ከተማ ውስጥ በነበረው ጦርነት ነው የተገደለው።

ከተማዋ ባለፉት ጥቂት ቀናት ከበድ ያለ ጦርነት እያስተናገደች ትገኛለች።

የብሪታኒያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር "ዩክሬን ውስጥ የተገለደውን ወታደር ቤተሰቦች እንደግፋለን" ብሏል።

የወታደሩ አባት በፌስቡክ ገፃቸው በፃፉት መልዕክት ልጃቸው የዩክሬን ወታደሮችን እያሠለጠነ እንደነበረ ገልጠዋል።

አክለው ውጊያ ላይ እያለ ክፉኛ ቆስሎ ሕይወቱ ማለፉን አርብ ዕለት እንደሰሙም ጽፈዋል።

ወታደሩ ልጃቸው ወደ ዩክሬን ያቀናው ከራሱ ጋር "ብዙ ከመከረ" በኋላ እንደነበርም አባት አስታውሰዋል።

የቤተሰቡ መግለጫ እንደሚያትተው ወታደሩ በዩክሬን ተወዳጅነት አትርፎ ነበር።

https://www.bbc.com/amharic/articles/cv29e4w4nnyo

@BBC_Amharic_News1
@BBC_Amharic_News1

BBC News አማርኛ ️

13 Jun, 05:20


ተቃዉሞን ተከለትሎ ሕንድ የበርካታ ታዋቂ ሙስሊሞችን ቤት አፈረሰች

በነብዩ መሐመድ ላይ የተቃጡ ናቸው በተባሉ አሉታዊ አስተያየቶች ምክንያት ከተቀሰቀሰ ረብሻ ጋር ግንኙነት አላቸው ያሏቸውን የበርካታ ሙስሊሞች ቤቶችን የሕንድ የፀጥታ ኃይሎች አፍረሱ።

በኡታር ፕራዴሽ ግዛት የሚገኙት የቤቶቹ ባለቤቶች ቤታቸውን ለቀው እንዲወጡ አስቀድሞ ማስጠንቀቂያ ተስጥቷቸው ነበር።

ሁለት የሕንድ ገዢ ፓርቲ ቢጄፒ ፓርቲ አመራሮች ፀረ እስልምና አስተያየቶችን ከሰጡ በኋላ ባለፈው ሳምንት ሕዝበ ሙስሊሙ ተቃውሞውን ሲያሰማ ቆይቷል።

ከሁከቱ ጋር በተያያዘ ፖሊስ ከ300 በላይ ሰዎችን በቁጥጥር ስር አውሏል።

እነዚህ አስተያየቶች የተሰጡት በግንቦት ወር በቲቪ ክርክር ወቅት የቢጄፒ ቃል አቀባይ በሆኑት ኑፑር ሻርማ ነው። የግለሰቧ አስተያየት አጸያፊ በመሆኑ ምክንያት ቢቢሲ ላይደግመው ወስኗል።

አስተያየቱ በሕንድ ያሉ የእስልምና እምነት ተከታዮችንና በርካታ እስላማዊ መንግሥታትን አስቆጥቷል። የፓርቲው የደልሂ ሚዲያ ክፍል ኃላፊ የሆኑት ናቪን ኩማር ጂንዳል ይህንን አሉታዊ አስተያየት በትዊተር ገጻቸው በማጋራታቸው ተባረዋል።

https://www.bbc.com/amharic/articles/c973ej608gjo

@BBC_Amharic_News1
@BBC_Amharic_News1

BBC News አማርኛ ️

13 Jun, 05:19


ዕድሜያቸው 40 የሞላ እና ጥቁር ወንዶች ሊያውቁት የሚገባ የካንሰር ዓይነት

ለበርካቶች ፕሮስቴት ሲባል ሁለቱ የወንድ ልጅ የዘር ፍሬዎች አካባቢ ወይም የዘር ፍሬ ከረጢቱ ውስጥ ያለ አካል እንደሆነ ነው የሚያስቡት።

የኩላሊት፣ የፕሮስቴት፣ የሽንት ፊኛ እና ቧንቧ ቀዶ ጥገና ስፔሻሊስት የሆኑት ዶ/ር ፍፁም ሠለሞን ግን ፕሮስቴት ከሽንት ፊኛ በታች ያለ አካል ነው ይላሉ።

እንደ ዶ/ሩ ገለጻ ከሆነ ፕሮስቴት በወንድ ልጅ ብልት እና ፊኛ መካከል የሚገኝ እጢ ነው።

ፕሮስቴት የዘር ፈሳሽ የማመንጨት ጥቅም አለው። የወንድ ልጅ የዘር ፈሳሽ ወደ ውጪ ሲፈስ ሰባ በመቶ ያህሉን የሚያመነጨው ፕሮስቴት መሆኑን ዶ/ር ፍፁም ያብራራሉ።

የወንድ ልጅ የዘር ፈሳሽ ሀዋስ የሚዋኘው እንዲሁም ምግቡን የሚያገኘው ከዚህ ፈሳሽ መሆኑን አክለው ይጠቅሳሉ።

ታድያ የፕሮስቴት ችግር ያለበት ወንድ የዘር ፈሳሹ ወደ ውጪ መፍሰሱን ትቶ የሚመለሰው ወደ ፊኛው ነው።

ስለዚህ ይላሉ ዶ/ር ፍፁም ፕሮስቴት፣ የዘር ፈሳሹ ወደ ፊኛ እንዳይመለስ እና ወደ ውጪ እንዲወጣ ይረዳል።

ፕሮስቴት ልክ እንደ ምራቅ አመንጪ እና ታይሮይድ እጢዎች ሁሉ እጢ (ግላንድ) ነው።

የፕሮስቴት እጢ የሚገኘው ወንድ ላይ ብቻ ነው።

https://www.bbc.com/amharic/articles/cndxlne6nk9o

@BBC_Amharic_News1
@BBC_Amharic_News1

BBC News አማርኛ ️

13 Jun, 05:16


የነዳጅ ድጎማው ሲነሳ ምን ሊያስከትል ይችላል?

መንግሥት የውጭ ምንዛሬን በስስት ነው የሚያየው። እንደ ስእለት ልጅ።

የዶላር ጥሪት እንደዋዛ አይቋጠርማ። በብዙ አበሳ፣ በብዙ የወጭ ንግድ፣ በብዙ ተጋድሎ ነው የሚመጣው።

እንዲያም ኾኖ ጥሎበት ከአራት ቢሊዮን ዶላር አይዘልም። እሱም ቢኾን መጥቶ አይበረክትም፤ አብዛኛውን ነዳጅ ይጠጣዋል።

ይሁን እንጂ፣ እስከዛሬ ድረስ ለነዳጅ የሚከፈለው ዶላር በወጭ ንግድ ከሚገኘው ዶላር በልጦ አያውቅም ነበር።

አሁን ግን ታሪክ ተቀየረ፤ ነገሩ ከፋ።

ይህ በይፋ የታወቀው ከኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ነው። ለ2015 ነዳጅ መግዣ የሚያስፈልግህ ስንት ነው ሲባል 5.6 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልገኛል አለ።

እንዲህ ያለ አሃዝ ተሰምቶ አይታወቅም ነበር፤ ይህም የመርከብና የነዳጅ ዋጋ መናር ያመጣው ነው ይባላል።

ታዲያ ይህ ገንዘብ ከየት ይመጣል?

አንደኛ ከውጭ ንግድ እንዲህ ዓይነት ገቢ በጭራሽ ኖሮን አያውቅም። ቡናው፣ ሌጦው፣ ሰሊጡ ተረባርበው ከአገር ወጥተው እንኳ እንዲህ ዓይነት ገቢን አያመጡም።

https://www.bbc.com/amharic/articles/cyd3yjlr0rgo

@BBC_Amharic_News1
@BBC_Amharic_News1

BBC News አማርኛ ️

12 Jun, 20:20


🟥 BBCን ለወዳጅ ዘመዶ ያጋሩ

━━⊱✿⊰━━
📌 BBC News አማርኛ

ቢቢሲ ከሌሎች ድረ-ገጾች እና ቴሌግራም ገጾች ለሚመጡ መረጃዎች ሀላፊነት አይወስድም. 

ድረ-ገፅ:- https://www.bbc.com/amharic

የቴሌግራም ገፅ:- https://t.me/BBC_Amharic_News1

የፌስቡክ አድራሻ:- https://m.facebook.com/BBCnewsAmharic/

@BBC_Amharic_News1

BBC News አማርኛ ️

12 Jun, 17:58


ከዩኬ ወደ ሩዋንዳ የሚደረገው የስደተኞች ጉዞ ጉዳይ ይግባኝ ሊጠየቅበት ነው

የዩኬ መንግሥት ስደተኞችን ወደ ሩዋንዳ ማጋዝ መጀመሩን የተቃወሙ ሰዎች ጉዳዩን ሰኞ ዕለት ወደ ፍርድ ቤት በመውሰድ ይግባኝ ሊጠይቁ ነው።

ከፍተኛው ፍርድ ቤት የመጀመሪያው ዙር ስደተኞችን የማጓጓዝ ሥራ እንዲካሄድ ፈቃድ መስጠቱ ተሰምቷል።

31 ሰዎች ማክሰኞ ዕለት በአውሮፕላን ተጭነው ወደ ሩዋንዳ እንደሚወሰዱ ተነግሯቸዋል።

በዚህ ዓመት ተጨማሪ አውሮፕላኖች ስደተኞችን ጭነው ወደ ሩዋንዳ ይሄዳሉ።

የዌልሱ ልዑል ቻርልስ በዚህ የመንግሥት ዕቅድ ደስተኛ እንዳልሆኑ የዩኬ ጋዜጦች አስነብበዋል።

ልዑሉ በያዝነው ወር ወደ ምስራቅ አፍሪቃዊቷ ሃገር ንግሥቷን ወክለው እንደሚያቀኑ ታውቋል።

የልዑሉ ጉዞ ዓላማ ኪጋሊ ውስጥ የኮመንዌልዝ ሃገራት መሪዎች ስብሰባ ላይ ለመሳተፍ ነው።

የልዑሉ ተወካይ እንደሚሉት ልዑሉ "ፖለቲካዊ አስተያየቶችን" ከመስጠት ይቆጠባሉ።

አዲሱ የመንግሥት ፖሊሲ እንደሚለው በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ ዩኬ የገቡ ሰዎች ወደ ሩዋንዳ ተወስደው እንደ አዲስ ጥገኝነት ይጠይቃሉ።

የቦሪስ ጆንሰን መንግሥት ይህን የሚያደርገው ስደተኞች በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ ዩኬ የሚያደርጉትን ጉዞ ለመግታት ነው።

በዚህ ዓመት ብቻ ኢንግሊሽ ቻናል የተሰኘውን የባሕር መንገድ ተጠቅመው 10 ሺህ ሰዎች ድንበር አቋርጠዋል።

https://www.bbc.com/amharic/articles/cld26qry5nqo

@BBC_Amharic_News1
@BBC_Amharic_News1

BBC News አማርኛ ️

12 Jun, 17:57


በአሜሪካ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ጠበቅ ያለ የመሳሪያ ህግ እንዲተገበር ለተቃውሞ ወጡ  

በቅርቡ የተፈጸሙ ሁለት የጅምላ ግድያዎችን ተከትሎ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ አሜሪካውያን ነዋሪዎች ጠበቅ ያለ የጦር መሳሪያ አጠቃቀም ህግ እንዲተገበር ለተቃውሞ ወጡ።

በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰልፎች የሚል ስያሜ በተሰጠው በዚህ የተቃውሞ ሰልፍ ላይ የተሳተፉ አብዛኛዎቹ እንዲተኮስብኝ አልፈልግም የሚሉ መፈክሮችን ይዘው ነበር።

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ተቃውሞውን ደግፈው ኮንግረሱ “በጦር መሳሪያ አጠቃቀም ላይ የደህንነት ህግ እንዲያወጣ” ጠይቀዋል።

ምንም እንኳን የህግ ለውጥ ይመጣል ተብሎ ተስፋ ቢደረግም በሌላ በኩል የጦር መሳሪያ የህግ ለውጥ በማይፈልጉ ሪፐብሊካኖች ሊቀለበስ ይችላል።

በባለፈው ወር በኡቫልዴ፣ ቴክሳስ በሚገኝ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት  በተፈጸመ ጥቃት 19 ህፃናት እና ሁለት ጎልማሶች ተገድለዋል።

https://www.bbc.com/amharic/articles/c4n3ld1jndjo

@BBC_Amharic_News1
@BBC_Amharic_News1

BBC News አማርኛ ️

12 Jun, 06:00


“የልጃችንን ገዳይ ሳናውቅ አናርፍም”

ወቅቱ እንደ አውሮፓውያኑ 1984 ነው።

የ15 ዓመቱ ማርክ ቢሊንግተር በእንግሊዟ በርሚንግሃም ቤቱ አቅራቢያ በአየር ላይ የሚበረውን ‘ካይት’ ይዞ ብስክሌቱን እያሽከረከረ ወጣ።

ያችም ዕለት በሕይወት የታየበት የመጨረሻ ቀን ነበረች። ከሳምንታት በኋላ አስክሬኑ ከዛፍ ላይ ተንጠልጥሎ ተገኘ።

በመጀመሪያ ራሱን አጥፍቷል ተብሎ ቢታይም ከዓመታት በኋላ ግን የግድያ ምርመራ ተከፈተ።

ሆኖም አሥርት ዓመታት የፈጀ ምርመራ ቢደረግም እስካሁን በታዳጊው ግድያ የተከሰሰ ሰው የለም።  

የልጃችንን ገዳይ ሳናውቅ አናርፍም ያለው ቤተሰቡ ከ38 ዓመት በኋላ ገዳዩን ለማግኘት የራሳቸውን ምርመራ ጀምረዋል።

የማደጎ ቤተሰቦቹ ሮይ እና ዊንፍሬድ ቢሊንግተን ማርክን ወደ ቤታቸው ያመጡት ገና በጨቅላነቱ ነው። ጊዜው ረዥም ቢሆንም ትናንት የሆነ ይመስል ያስታውሱታል። 

"እዚያ ተቀመጠ እና ክፍሉን ዘወር ዘወር ብሎ ተመለከተ። እጆቼን ለማቀፍ ዘረጋሁለት እሱም በምላሹ አቀፈኝ፤ የኔም መሆኑን አወቅኩ” ትላለች እናቱ።

“እኔ የማደጎ ልጅ ነኝ። እሱንም በማደጎ እንዳሳደግነው ያውቃል። ሁልጊዜም የተለየን ነን እላለሁ ምክንያቱም የተመረጥን ስለሆንን።

“እንዲህ ዓይነት አሰቃቂ ነገር በሕጻን ላይ ሲከሰት፤  በሱ ላይ ሊደርስ ይችላል ብለን በሕልማችንም ቢሆን የምናስበው አልነበረም” ትላለች።

https://www.bbc.com/amharic/articles/cd167vmqdjdo

@BBC_Amharic_News1
@BBC_Amharic_News1

BBC News አማርኛ ️

12 Jun, 06:00


'ጠጅ' ኢትዮጵያ ምን ትሠራለች?

ጠጅ ትባላለች። በርግጥ ወላጆቿ ተዥ ወይም ተጅ-ሬይ ብለው ነው የሚጠሯት። ኑሮዋን ኢትዮጵያ ካደረገች ወዲህ ግን ስሟ ጠጅ ሆኗል እርሷም አልተቃወመችዉም።

እንደውም እ.አ.አ በ70ዎቹ በአሜሪካ ያሳደጓት ወላጆቿ ከ8 ዓመቷ ጀምሮ በተደጋጋሚ ወደ ኢትዮጰያ ምግብ ቤት አዘውትረው ይወስዷት እንደነበር በፈገግታ ታሰታውሳለች። ዕድሜዋም ከፍ ካለ በኋላ ጠጅ ይታዘዝላት አንደነበርም ትናገራለች።

የያኔዋ ተጅ ሬይ ስሟ ከሌሎች ሁሉ ይለይ እንደነበር ታስታውሳለች።

የጓደኞቿ ስም በመጻሕፍት ውስጥ ገፀባሕሪ ሆኖ ሲመጣ፣ በልብስ ላይ ታትሞ ሲለበስ፣ መጫወቻዎች ላይ በቀላሉ ሲገኝ የእርሷ ግን በኢትዮጵያ ምግብ ቤት ውስጥ ብቻ ነበር የሚገኘው።

በኢትዮጵያ ምግብ ቤት ውስጥ በብርሌ ተሰይሞ በልጅነቷ ያየችው ጠጅ እና የእርሷ የአትዮጵያ ቁርኝት በዚህ መንገድ ይሰምራል ብላ አስባ ታውቅ ይሆን?

https://www.bbc.com/amharic/articles/crg7dzj781qo

@BBC_Amharic_News1
@BBC_Amharic_News1

BBC News አማርኛ ️

12 Jun, 06:00


ሩሲያ በዩክሬን በተቆጣጠረቻቸው ከተሞች ፓስፖርት መስጠት ጀመረች

ሩሲያ በደቡባዊ ዩክሬን በተቆጣጠረቻቸው ሁለት ከተሞች ኬርሶን እና ሜሊቶፖል ውስጥ ለሚገኙ ነዋሪዎች የሩሲያ ፓስፖርት መስጠት መጀመሯንን የአካባቢው ባለስልጣናት ተናግረዋል።

ዩክሬን በግዛቷ ላይ እየተከናወነ ያለው ተግባር የሩሲያውን ዜጎች መፈጠር ወይም “ሩሲፊኬሽን” ነው ስትል አውግዛለች።

ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን አሰራሩን በፍጥነት እየተከታተሉት እንደሆነም ተገልጿል።

የሩሲያው ታስ የዜና ወኪል እንደገለጸው ቅዳሜ እለት በተካሄደው ሥነ ሥርዓት የመጀመሪያዎቹ 23 የኬርሶን ከተማ ነዋሪዎች የሩሲያ ፓስፖርት አግኝተዋል።

የዜና ወኪሉ አክሎ እንደዘገበው በሺዎች የሚቆጠሩ የኬርሶን ከተማ ነዋሪዎች የሩሲያ ፓስፖርት እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል። ነገር ግን ይህንን ከገለልተኛ አካል ማረጋገጥ አልተቻለም።

https://www.bbc.com/amharic/articles/c80wlnygjwpo

@BBC_Amharic_News1
@BBC_Amharic_News1

BBC News አማርኛ ️

11 Jun, 14:19


ታይዋንን ነጻ አገር ለማድረግ መሞከር ጦርነት እንደሚቀሰቅስ ቻይና አስጠነቀቀች

አሜሪካ ታይዋንን ነጻ አገር ለማድረግ ማንኛውንም አይነት ሙከራ የምታደርግ ከሆነ ወታደራዊ እርምጃ ለመውሰድ እንደምትገደድ አስጠነቀቀች።

ታይዋንን ከቻይና እንድትለይ መሞከር የቻይና ጦር ሠራዊት “የትኛውንም ዋጋ ከፍሎ ከመዋጋት ውጪ” ምንም ምርጫ አይኖረውም ሲሉ የቻይና መከላከያ ከፍተኛ ባለሥልጣን መናገራቸው ተዘግቧል።

ይህ የተነገረው የቻይናው የመከላከያ ሚኒስትር ዌይ ፌንግ ሴንጋፖር ውስጥ እየተካሄደ በሚገኘው የእስያ ደኅንት ጉባኤ ጎን ለጎን ከአሜሪካው አቻቸው ሎይድ ኦስቲን ጋር ተገናኝተው መወያየታቸውን ተከትሎ ነው።

ቀደም የአሜሪካው የመከላከያ ኃላፊ ሎይድ ኦስቲን ቻይና እያካሄደች ያለው ወታደራዊ እንቅስቃሴ “ጠብ ጫሪ፣ ሰላምን የሚያናጋ” ሲሉ ተችተው ነበር።

ጨምረውም ከደሴቲቱ ታይዋን አቅራቢያ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የቻይና የጦር አውሮፕላኖች በየዕለቱ መብረራቸው “የአካባቢውን መረጋጋት የሚሸረሽር ነው” ብለዋል።

ቻይና እራሷን የምታስተዳድረውን ታይዋንን የግዛቷ አንድ አካል አድርጋ የምትመለከት ሲሆን፣ በዚህ አቋሟ የተነሳም የቻይናው የመከላከያ ሚኒስትር አሜሪካ ለታይዋን የምታደርገውን የጦር መሳሪያ ሽያጭ አውግዘዋል።

https://www.bbc.com/amharic/articles/ceq80gy9l58o

@BBC_Amharic_News1
@BBC_Amharic_News1

BBC News አማርኛ ️

11 Jun, 08:21


ኢትዮጵያዊቷ የእጽዋት ተመራማሪ ረዳት ፕሮፌሰር መሠረት ተሰማ

ለመጨረሻ ጊዜ ያያችሁት እንስሳ ምንድን ነበር? ቀለሙ፣ ቅርጹ ትዝ ይላችሁ ይሆን? ከሌሎች እንስሳትስ በምን ትለዩታላችሁ?

መልካም፤ አሁን ደግሞ አብዛኛውን ጊዜ ምግብ እና ሥነ መአዛ እንዲሁም መድኃኒት የሚሰጡን እና ህይወታችን ውስጥ በብዙ መልኩ አስተዋጽኦ ስላላቸው እጽዋት እናንሳ።

በቅርቡ - ምናልባት ትናንት ማታም ሊሆን ይችላል - ያያችሁት እጽዋት ምንድን ነው?

በዚህ መካከል፣  ከእጽዋቱ ምስል ይልቅ ወደ አእምሮአችሁ የእንስሳቶቹ ቀድሞ የሚመጣ ከሆነ ችግሩ የእናንተ ብቻ አይደለም።

አብዛኞቻችን አካባቢያችን ያሉ እጽዋትን የማስተዋል ችግር አለብን። ተመራማሪዎች ይህንን ‘plant blindness’ ብለው ይጠሩታል።

ረዳት ፕሮፌሰር መሠረት ተሰማ ግን ከልጅነቷ አንስቶ እስከ ዛሬ ድረስ ከአእምሮዬ አይጠፋም የምትለው፣ ሽታው ሳይቀር ውልብ የሚልባት አንድ እጽዋት አለ - ጠጅ ሳር።

https://www.bbc.com/amharic/articles/cw98je5jv2yo

@BBC_Amharic_News1
@BBC_Amharic_News1

BBC News አማርኛ ️

11 Jun, 08:19


ኮንሰርቱን የሰረዘው ጀስቲን ቢበር ፊቱ ፓራላይዝድ እንደሆነ ተናገረ

ባለፈው ሳምንት ሊያካሂድ የነበረውን ኮንሰርት የሰረዘው የ28 ዓመቱ ድምጻዊ ጀስቲን ቢበር፣ ከፊል ፊቱ ፓራላይዝድ እንደሆነ ተናግሯል።

ኢንስታግራም ላይ በለቀቀው ቪድዮ “እንደምታዩት ይህኛው ዓይኔ አልገለጥ ብሏል። በዚህኛው የፊቴ ክፍል ፈገግ ማለት አልችልም። ያኛው የፊቴ ክፍል ደግሞ ሙሉ በሙሉ ፓራላይዝድ ሆኗል” ብሏል።

ድምጻዊው የገጠመው ራምዚ ሀንት የተባለ ሕመም ነው።

ሕመሙ ጆሮ አቅራቢያ የሚገኙ የፊት ነርቮችን ያጠቃል።

‘ጀስቲስ ወርልድ ቱር’ በሚል በተለያዩ አገራት ኮንሰርት እያቀረበ የነበረው ጀስቲን፣ ላለፈው ሳምንት ታቅደው ከነበሩ ኮንሰርቶቹ ሦስቱን ሰርዞ፣ ለሌላ ጊዜ አሸጋግሯቸዋል።

ትውልደ ካናዳዊው ጀስቲን ቢበር፣ በቀኝ የፊቱ ክፍል በገጠመው የነርቭ ጉዳት ምክንያት ኮንሰርቶቹን እንደሰረዘ ገልጾ፣ ሲሻለው ወደ ኮንሰርቶቹ እንደሚመለስ ለአድናቂዎቹ ቃል ገብቷል።

ኢንስታግራም ላይ ላሉት 240 ሚሊዮን ተከታዮቹ፣ የሕመሙን ክብደት ለማሳየት ቪድዮ ለቋል።

https://www.bbc.com/amharic/articles/cv29x53305do

@BBC_Amharic_News1
@BBC_Amharic_News1

BBC News አማርኛ ️

11 Jun, 08:18


አሜሪካ ለአውሮፕላን ተጓዦች የኮቪድ-19 ምርመራ ግዴታን አስቀረች

አሜሪካ በአውሮፕላን ከውጭ አገራት የሚገቡ ተጓዦች ወደ ዩናይትድ ስቴትስ ከመግባታቸው በፊት ሲጠየቅ የነበው የኮቪድ-19 ምርመራ ማረጋገጫ እንዲቀር አደረገች።

ባለሥልጣናቱ አገሪቱ ቫይረሱን ለመዋጋት ባደረገችው “ከፍተኛ መሻሻል” ምክንያት ከቫይረሱ ነጻ የመሆን የምርመራ ውጤት ማቅረብ አስፈላጊነት እንዲያበቃ ማድረጓን አሳውቀዋል።

ይህ ቅድመ ሁኔታ እንዲቀር የጉዞ አገልግሎት ዘርፉ ግፊት ሲያደርግ ቆይቷል። በፖሊሲው ምክንያት ብዙዎች መጓዝ ስለሚፈሩ እንግልት ተፈጥሯል ብለዋል። 

ለውጡ ከነገ እሁድ ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል።

የአሜሪካ በሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል (ሲዲሲ) ፖሊሲውን በ90 ቀናት ውስጥ እንደገና ይገመግመዋል። አስተዳደሩ አዳዲስ ዝርያዎች ስጋት ከፈጠሩ ግን ደንቡን ወደነበረበት ከመመለስ “ወደኋላ እንደማይል” ገልጿል።

"ይህን እርምጃ መውሰድ የቻልነው ቫይረሱን በመዋጋት ባደረግነው ከፍተኛ መሻሻል ነው። ህይወት አድን የሆኑ ክትባቶች እና ህክምናዎችን በስፋት እንዲሰራጭ አድርገናል። እነዚህ መፍትሔዎች ከባድ ህመም እና ሞትን ለመከላከል እያገለገሉ ናቸው። በበሽታው ላይም ውጤታማ ሆነዋል። በዩናይትድ ስቴትስ እና በዓለም ዙሪያ በስፋት እየተሰራጩ ያሉ ዝርያዎች አሉ" ሲሉ አንድ ከፍተኛ ባለሥልጣን ለጋዜጠኞች ተናግሯል።

https://www.bbc.com/amharic/articles/cl7gvdjq1l9o

@BBC_Amharic_News1
@BBC_Amharic_News1

BBC News አማርኛ ️

11 Jun, 08:16


ማክሰኞ ስደተኞች ከዩኬ ወደ ሩዋንዳ የሚወሰዱበት በረራ በፍርድ ቤት ፈቃድ አገኘ

በመጪው ማክሰኞ ጥገኝነት ጠያቂዎችን ከዩናይትድ ኪንግደም ወደ ሩዋንዳ ለመውሰድ የሚደረገው በረራ እንዲከናወን በከፍተኛ ፍርድ ቤት ይሁኝታ ተሰጥቶታል።

የጉዞው ተቃዋሚዎች ወደ ሩዋንዳ የሚደረጉትን በረራዎች ለማስቆም ያደረጉት የመጀመሪያ ሕጋዊ ሙከራ አልተሳካላቸው። ጉዳዩን ሰኞ ወደ ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት እንደሚወስዱት አረጋግጠዋል።

በተዘጋጀው ፖሊሲ መሠረት በሕገ ወጥ መንገድ ወደ ዩኬ ከሚገቡት ስደተኞች መካከል የተወሰኑት የጥገኝነት ጥያቄያቸውን ከሩዋንዳ ይከታተላሉ።

ወደ 31 የሚጠጉ ሰዎች በመጀመሪያው በረራ ሊሳፈሩ እንደሚችሉ ተነግሯቸዋል።

ከፍተኛው ፍርድ ቤት ከቀጣዩ ወር መጨረሻ በፊት ፖሊሲው ላይ የቀረበውን ተቃውሞ ያዳምጣል።

ውሳኔውን የሰጡት ዳኛ ስዊፍት እንዳሉት  “ለሕዝብ ጥቅም" ሲባል የአገር ውስጥ ሚንስትር ፕሪቲ ፓቴል ፖሊሲዎችን መተግበር አለባቸው።

ፓቴል ውሳኔውን በማድነቅ መንግሥት ዕቅዶቹን መተገበር ይቀጥላል ብለዋል።  ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን ደግሞ ውሳኔውን “በደስታ የተቀበልኩት ዜና” ሲሉ ገልጸዋል ።

ጥያቄውን ያቀረቡት ቡድኖች “በግዳጅ ሊባረሩ” የተዘጋጁት ሰዎች ደኅንነት እንደሚያሳስባቸው አስታውቀዋል።

ታይምስ ጋዜጣ እንደዘገበው የዌልሱ ልዑል የመንግሥትን ፖሊሲ በግላቸው ሲተቹ ነበር። ምንጮችን ጠቅሶ እንደዘገበውም  አቀራረቡ "አስደንጋጭ” ነው ብለው እንደሚያስቡ አስታውቋል።

ልዑል ቻርለስ በዚህ ወር መጨረሻ በሚካሄደው የኮመንዌልዝ ስብሰባ ንሥቲቱን ወክለው በሩዋንዳ ዋና ከተማ ኪጋሊ ይገኛሉ። ጽሕፈት ቤቱ “ከፖለቲካዊ ጉዳዮች ገለልተኛ” እንደሆነ በድጋሚ ተናግሯል።

https://www.bbc.com/amharic/articles/c84970d2p94o

@BBC_Amharic_News1
@BBC_Amharic_News1

BBC News አማርኛ ️

11 Jun, 08:14


በ1 ቢሊየን ፓወንድ የታክስ ማጭበርበር በጥብቅ ስትፈለግ የነበረችው ግለሰብ ተያዘች

በማጭበርበር ወንጀል ለዓመታት በጥብቅ ስትፈለግ የነበረችው ግለሰብ ተይዛ የስምንት ዓመት እስር ተፈረደባት።

በዩናይትድ ኪንግደም ከፍተኛ የወንጀል ተፈላጊዎች ዝርዝር ውስጥ የነበረችው የ48 ዓመቷ ሳራ ፓንቲዝክ፣ ጉዳዩዋ በፍርድ ቤት እየታየ ሳለ እአአ በ2013 ጠፍታ ነበር።

ለፍርድ የቀረበችው አንድ ቢሊዮን ፓውንድ በስልክ በታገዘ የገንዘብ ማጭበርበር ድርጊት በቁጥጥር ሥር ከዋለች በኋላ ነው።

ከፍርድ ካመለጠች በኋላ ለስምነት ዓመታት ስትፈለግ ቆይታ ሳንታ ባርብራ፣ ስፔን ውስጥ ውሻዋን እያንሸራሸረች ሳለች ተይዛ ታስራለች።

ለዩናይትድ ኪንግደም ተላልፋ ከተሰጠች በኋላ ለንደን በሚገኘው ኪንግስተን ፍርድ ቤት ቀርባለች።

በ2010 ተጨማሪ እሴት ታክስ ከማጭበርበር ጋር በተያያዘ በሚሊዮን የሚቆጠር ፓውንድ አጭበርብራለች ተብላ ተከሳ፣ በ2013 በሌለችበት የስምንት ዓመት እስር ተፈርዶባት ነበር።

ይህ ውሳኔ ከተያዘችን ጊዜ አንስቶ እንደሚጸና ዳኛ ሳራ ፓልሽክስ ተናግረዋል።

https://www.bbc.com/amharic/articles/c4n2d00v01zo

@BBC_Amharic_News1
@BBC_Amharic_News1