በ9.46 ሄክታር ጠቅላላ ስፋት ላይ የሚገነቡት ቤቶቹ በሁሉም መስመሮች ለከተማዋ መግቢያ የተመቹ መንገዶች ያሉት ነዉ ተብሏል።
ኦቪድ ሪል እስቴት በአዲስ አበባ የሚስተዋለዉን የቤት ችግር ለመቅረፍ ለዝቅተኛና ለመካከለኛ ነዋሪዎች በተመጣጣኝ ዋጋ መኖሪያ ቤቶችን እያቀረበ እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን ፣ ይህ ፕሮጀክትም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ አነሳሽነት የተጀመረዉ የጫካ ፕሮጀክት አንዱ አካል እንደሆነ ነዉ የተነገረዉ።
መሠረቱን የካ ተራራ ላይ ያደረገዉ ፕሮጀክቱ እስከ መሀል ከተማዋ የሚዘረጋ እንዲሁም ከእንጦጦ አንስቶ እስከ የካ አባዶ የሚደርስ ሲኾን፣ በ5 አመት ለማጠናቀቅም ዕቅድ እንደተያዘ ተነግሯል።
#ትርታ 97.6 FM #ከልብዎ_የቀረበ