Últimas publicaciones de Tirita 97.6 FM Radio (@tiritaradio) en Telegram

Publicaciones de Telegram de Tirita 97.6 FM Radio

Tirita 97.6 FM Radio
ትርታ 97.6 ኤፍ ኤም ''ከልብዎ የቀረበ''

ትርታ ሚዲያ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ያለ የንግድ መዝናኛ፣ ዜና እና ቢዝነስ ጭብጥ ያለው ሚዲያ ነው።
1,271 Suscriptores
955 Fotos
7 Videos
Última Actualización 09.03.2025 15:19

El contenido más reciente compartido por Tirita 97.6 FM Radio en Telegram

Tirita 97.6 FM Radio

07 Mar, 16:59

117

እናት ባንክ ለሴት ተማሪዎች የንጽህና መጠበቂያ ድጋፍ አደረገ!
***

እናት ባንክ የአለም አቀፍ የሴቶች ቀን በዓለን በማስመልከት የ200ሺህ ብር ወጪ በማድረግ የንፅህና መጠበቂያና ተያያዥ የንፅህና መጠበቂያዎችን በአዲስ አበባ ቂርቆስ ከፍለ ከተማ ወረዳ ስምንት ለምስራቅ ጎህ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለሚማሩ 400 ሴት ተማሪዎች ድጋፍ አድርጓል፡፡

ድጋፉን የእናት ባንክ የሥራ ሃላፊዎችና የባንኩ የብራንድ አምባሳደር አርቲስት ሐረገወይን አሰፋ  ለቂርቆስ ከፍለከተማ የወረዳ ስምንት የሥራ ኃላፊች፣ የትምህርቤቱ ርዕስ መምህራን፣ መምህራንና ተማሪዎች በተገኙበት በዛሬው እለት አስረክበዋል፡፡ 

በወቅቱም የእናት ባንክ የስራ ሃላፊዎች ባስተላለፉት መልክት ፣ ባንኩ የሴቶችን ኢካኖሚያዊ አቅም ከማጎልበትና ለሁሉም  ማህበረሰብ የተሟላ የባንክ አገልግሎት ከመስጠት ጎን ለጎን ማህበራዊ  ሃላፊነቱን እየተወጣ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡

በዚህም ለሴቶች የቢዝነስ  አሰራር ሥልጠና በመስጠት ፣የብድር ዋስትና ማቅረብ የማይችሉ ሴቶች ብድር የሚያገኙበት አሰራር በመዘርጋት ሀሳባቸውን እውን እንዲያደርጉ በማመቻቸትና የሥራ ዕድል በመፍጠር የበኩሉን እየተወጣ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

እናት ባንክ ሴቶችን በማብቃት  ተጠቃሚ ለማድረግ ከሚሰሩ  አካላት ጋር በትብብር መስራቱን አጠናክሮ  እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡

#ትርታ 97.6 FM #ከልብዎ_የቀረበ
Tirita 97.6 FM Radio

07 Mar, 16:40

101

በሴት ባለሞያዎች ብቻ የሚመራ በረራዎችን እንደሚያደርግ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታወቀ
***
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአለም አቀፉን የሴቶች ቀን ምክንያት በማድረግ በሴቶች ብቻ የሚመራ በረራዎችን ሊያደርግ ነው።

በሴቶች ባለሞያዎች ብቻ ስድስት በረራዎች የሚካሄዱ ሲሆን ፣
ከአዲስ አበባ ወደ አቴንስ ዴሊሂ ዱባይ ዊንድሆክ ሳኦፖሎና ባህርዳር ከተሞች ላይ በረራ እንደሚደረጉ ለማወቅ ተችሏል።

አየር መንገዱ ከ2015 ጀምሮ አለምአቀፉን የሴቶች ቀን ምክንያት በማድረግ በረራውን ሲያካሂድ የቆየ ሲሆን: በኮቪድ አማካኝነት ለሁለት አመት መቋረጡ ይታወሳል።

#ትርታ 97.6 FM #ከልብዎ_የቀረበ
Tirita 97.6 FM Radio

07 Mar, 15:50

88

እናት ባንክ ለደንበኞቹ በልዩ የዋጋ ቅናሽ የህክምና አገልግሎት እንደዱያገኙ አደረገ!
***

እናት ባንክ በአለም ዐቀፍ ደረጃ ለ114ኛ ጊዜ፤ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ49ኛ ጊዜ የሚከበረውን የሴቶች ቀን አስመልክቶ በአጋርነት አብረውት ከሚሰሩት የጤና ተቋማት ጋር በመተባበር ለደንበኞቹ በልዩ የዋጋ ቅናሽ ለአንድ ወር የሚቆይ የሕክምና አገልግሎት ማዘጋጀቱን አስታወቀ።

የእናት ባንክ ኮርፖሬት ሰርቪስ ምክትል ፕሬዘዳንት ገነት ሀጎስ እንደገለፁት፤ የሴቶችን ቀን ለደንበኞቻችን ጤና በሚል መሪ ቃል ከየካቲት 29 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ከአጋር የሕክምና ተቋማት ጋር: ለአንድ ወር ያህል የሚቆይ በልዩ የዋጋ ቅናሽ የሕክምና አገልግሎት ማግኘት የሚያስችል ነው።

አጋር የሕክምና ተቋማቱ ዋሽንግተን የሕክምና ማዕከል፣ መቅረዝ ሆስፒታል፣ አዲስ ህይወት ሆስፒታል እንዲሁም ስዊዝ ዲያጎነስቲክስ ናቸው።

የባንኩ ደንበኞች ''እናት ጤና'' የቁጠባ ሒሳብን ተጠቅመው  ኢትዮጵያ በልዩ ቅናሽ የተለያዩ በሽታወችን ለመከላከል አስቀድመው የህክምና ምርመራ ማድረግ እንዲሁም ጥራት ያለው ቀልጣፋ የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ እንደሚያስችል ተነግሯል።

በእናት ጤና የቁጠባ ሒሳብ ከፍተኛ የወለድ ምጣኔ ከማግኘት በተጨማሪ በልዩ የዋጋ ቅናሽ የሕክምና አገልግሎት ተጠቃሚ ለመሆን የሚያስችል ሲሆን ከተመረጡ አጋር የጤና ተቋማት ጋር ቀጣይነት እንደሚኖረው ተገልጿል።

(በንጉሱ በሪሁን)

#ትርታ 97.6 FM #ከልብዎ_የቀረበ
Tirita 97.6 FM Radio

07 Mar, 15:45

81

ግራንድ ኢትዮ - አፍሪካ ሩጫ በዱባይ ይካሄዳል።

Grand Ethio–Africa Run በዱባይ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄድ  ሲሆን በኢትዮጵያ እና በሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች እንዲሁም በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መካከል ያለውን  ማህበራዊና ዲፕሎማሲያዊ ትስስር  ለማጠናከር ያለመ ነው ተብሏል፡፡

ይኸው ሩጫ በዱባይ በመጪው የፈረንጆቹ ወር ሚያዚያ 5 – 6  2025 በልዩ ልዩ ዝግጅቶች በደማቅ ሁኔታ እንደሚካሄድ  ነው አዘጋጆቹ በዛሬው እለት  በሰጡት መግለጫ ያስታወቁት፡፡

ሩጫው FAS Business Group ከዱባይ ስፖርት ካውንስል ጋር በመተባበር ነው ያዘጋጀው።

ዝግጅቱ የተሳታፊ ሀገሮችን የባህል የስፖርትና የፋሽን እንዲሁም የማህበራዊ አንድነትን በማጉላት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን ወደ ላቀ ደረጃ ከፍ ያደርጋል ሲሉ የገለፁት የዝግጅቱ አስተባባሪና በኢትዮጵያ  የፊፋ ማች ኤጀንት  ፍፁም አድነው ናቸው፡፡ 

ዝግጅቱ ታላላቅ የስፖርት ባለሙያዎችን፣ በዘርፉ ከፍተኛ ልምድ ያላቸው እና ተፅእኖ ፈጣሪ የሆኑ ግለሰቦች እንዲሁም ለዘርፉ ልዩ ፍቅር ያላቸው ተሳታፊዎችን ያካተተ እንደሚሆን ተነግሯል፡፡

በዝግጅቱ ከኢትዮጵያ ከተለያዩ የአፍሪካ  ሀገሮች እና ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የተውጣጡ ዲፕሎማቶች፣ ታላለቅ ሰዎች እና መሪዎችም ይገኛሉ የተባለ ሲሆን  በተጨማሪም የባህል አጥኚዎች፣ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ የማሕበራዊ ጉዳዮች ምሁራን እንዲሁም የንግድ ባለሙያዎች የሚሳተፉበትም ነው፡፡ 

ከሩጫውና ከሩጫው  ጎን ለጎን ከሚካሄዱ ፌስቲቫሎች ከሚገኘው ገቢ 50 በመቶው ያህሉ ለሜቄዶኒያ አረጋውያን መርጃ ማእከል እንደሚለገስም አዘጋጆቹ አስታውቀዋል።

(በራህማ መሐመድ)

#ትርታ 97.6 FM #ከልብዎ_የቀረበ
Tirita 97.6 FM Radio

07 Mar, 15:40

93

"መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዮጲያ" በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ ነገ እና ከነገ በስቲያ መንፈሳዊ መርሀ ግብር ይካሔዳል።

የቢሊ ግርሀም ኢቫንጀሊስቲክ አሶሴሽን ባዘጋጀው እና በመዲናዋ መስቀል አደባባይ በሚካሄደው በዚሁ ፕሮግራም ላይም ዝማሬዎች ፤ የቃል አገልግሎትና ሌሎችም መንፈሳዊ ሁነቶች ይኖራሉ ተብሏል።

የቢሊ ግርሀም ወንጌል ማህበር በ1952 ዓ.ም ወንጌላዊ ቢሊ ግርሀም በአዲስ አበባ ስታዲየም ወንጌል ከሰበኩና በንጉሰ ነገስት ኃይለ ሥላሴ በቤተ መንግስታቸው ተጋብዘው ከተሸለሙ ከ 65 ዓመት በኋላ የሚካሄድ መሆኑ ታሪካዊ እንደሚያደርገውም ተመላክቷል፡፡

የኢትዮጲያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ዋና ጸሀፊ ቄስ ደረጀ ጀንበሩ ‹‹አሁን ኢትዮጲያ በእውነት በእግዚአብሄር የምትጎበኝበት ጊዜ ነው››ሲሉም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
‹‹መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዮጲያ›› በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀውን መንፈሳዊ መርሀ ግብር አስመልክቶም፤ በዛሬው ዕለት ለመገናኛ ብዙሀን እና ጥሪ ለተደረገላቸው እንግዶች በሸራተን አዲስ ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰጥቷል። በመድረኩም
የካቲት 29 እና 30 በመስቀል አደባባይ በሚካሄደው በዚህ ኮንፍራንስ ላይም ዜጎች እንዲታደሙ ጥሪ ተላልፏል፡፡

(በትባረክ ኢሳያስ)

#ትርታ 97.6 FM #ከልብዎ_የቀረበ
Tirita 97.6 FM Radio

06 Mar, 20:50

145

የአሜሪካ መንግስት በጤናው ዘርፍ ያቋረጠው ድጋፍ ክፍተት እንዳይፈጠር የአጭርና የረጅም ግዜ  የመፍትሄ አማራጮች ላይ መስራት ያስፈልጋል ተባለ።

የተዋልዶ ጤና አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች ማህበር 5ኛውን የተዋልዶ ጤና ጠቅላላ ጉባኤውን ዛሬ በስካይ ላይት ሆቴል አካሂዷል።

የዘንድሮው ጉባኤ በተለየ ሁኔታ ከወቅታዊው የአሜሪካን መንግስት የጤናው ዙርፍ ድጋፍ መቋረጥ የሚያስከትለውን ጫና ለመከላከል በሚያስችሉ አማራጮች ላይ ትኩረት በመስጠት ባለድርሻ አካላት ውይይት ተደርጎበታል።

ማህበሩ ከ85 በላይ በጤናው ዘርፍ የሚሰሩ ድጅቶችን በአባልነት የያዘ ሲኾን፣ የማህበሩ ስራ አስኪያጅ አበበ ከበደ በተለይ ለትርታ እንደተናገሩት፣ ጉባኤው ድንገተኛ በሆነውና በትራምፕ አስተዳደር በተላለፈው የጤና ዘርፍ ድጋፍ ማቋረጥ ውሳኔ በሚፈጥረው ተጽእኖ ላይ ትኩረት አድርጓል።

ከድጋፉ መቋረጥ ጋር በተያያዘም
የችግሩን ጥልቀትና ስፋት በመረዳት የአጭርና የረጅም ግዜ የመፍትሄ እርምጃዎች በአፋጣኝ ሊወሠዱ እንደሚገባም አሳስበዋል።

ትርታ ያናገራቸው በጉባኤው ላይ የተሳተፉ የማህበሩ አባል ድርጅቶችም የአሜሪካ መንግስት ድጋፍ መቋአጥ በተዋልዶ ጤና እየተሰራ ያለውን ስራ እጅጉን እንደሚጎዳው ገልጸዋል። በቀጣይ በሀገር ውስጥ ድጋፍ እና ትብብር ላይ ያተኮረ ስራ ሊሰራ እንደሚገባ ነው ያስረዱት።

በተለይም መንግስት ፈጣን የሆነ የፖሊሲ ማሻሻያ ማድረግና የጤና ዘርፉ በተለይም ደግሞ በተዋልዶ ጤና ዙሪያ የሚሰሩ ስራዎች በገንዘብም ሆነ በቁሶች እንዲሁም በሰለጠነ የሰው ኃይል ክፍተት ሳይኖር ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ማድረግ እንዳለበት አንስተዋል።

ከመንግስት ጋር በቀጣይ በሚደረግ ምክክር የመፍትሔ አማራጮች ይፋ እንደሚሆን ተገልጿል።

(ቆንጂት ተሾመ)

#ትርታ 97.6 FM #ከልብዎ_የቀረበ
Tirita 97.6 FM Radio

06 Feb, 13:59

116

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት የሀገራዊ ምክክር አጀንዳዎቹን ለኮሚሽኑ አስረከበ
***
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት በሀገራዊ ምክክር ሂደት ውስጥ ሊካተቱ ይገባሉ ያላቸውን አጀንዳዎች በዛሬው ዕለት ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በይፋ አስረክቧል፡፡

በርክክብ ሥነሥርዓቱ ላይ ኮሚሽኑን ወክለው ንግግር ያደረጉት ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መሥፍን አርአያ፤ የመገናኛ ብዙኃን ምክር ቤቱ ለኮሚሽኑ ዓላማ መሳካት ከፍተኛ እገዛ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ማኅበረሰቡ ስለኮሚሽኑ ተግባራት መረጃ እንዲያገኝ በማድረጉና የሚዲያ ተቋማትን ሀገራዊ አጀንዳዎች አደራጅቶ በማስረከቡ ለምክር ቤቱ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

በቀጣይ የምክክር ሂደትም ምክር ቤቱ ከኮሚሽኑ ጋር በትብብር እንዲሰራ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ አማረ አረጋዊ በበኩላቸው ምክር ቤቱ በሥነ-ምግባር የታነጸ ሚዲያ በሀገራችን እንዲጎለብት የሚሠራ ተቋም ነው ብለዋል፡፡

አክለውም በምክር ቤቱ በስድስት ርዕሰ ጉዳዮች የተከፋፈሉ የሀገራችንን እንዲሁም የሚዲያ ኢንዱስትሪውን መሠረታዊ ችግሮች የሚፈቱ አጀንዳዎች መዘጋጀታቸውን አብራርተዋል፡፡

ምክር ቤቱ ከሀገራዊ ምክክሩ ጋር የሚተሳሰሩ ጉዳዮችን ወደ ሕዝብ ለማስረጽ በትኩረት መሥራቱን እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል፡፡

በአጀንዳ ርክክብ ሥነ-ሥርዐቱ ላይም የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነሮች፣ የመገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት የሥራ አስፈጻሚ አባላትና ጋዜጠኞች መገኘታቸውን ከኮሚሽኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

#ትርታ 97.6 FM #ከልብዎ_የቀረበ
Tirita 97.6 FM Radio

05 Feb, 17:20

155

የሳፋሪኮም ቅድሚያ ለሴቶች የ 5 ኪሎ ሩጫ ምዝገባ የፊታችን የካቲት 3 ቀን ይጀመራል።

<<ሁሉም መብቶች፤ለሁሉም ሴቶች>> በሚል መሪ ቃል 22ኛዉ የሳፋሪኮም ቅድሚያ ለሴቶች የ 5 ኪሎ ሩጫ መጋቢት 07 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚካሄድ አዘጋጁ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ትናንት በሀያት ሬጀንሲ ሆቴል በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።

በዘንድሮው መድረክ ከ16 ሺህ በላይ ተሳታፊዎች እንደሚገኙበትና ከ200 በላይ አትሌቶች እንዲሁም ከ30 በላይ በተለያዩ ዘርፎች ላይ በጎ ተፅዕኖን መፍጠር የቻሉ እንስቶች ይታደሙበታል ተብሎ እንደሚጠበቅ የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ዋና ስራ አስኪያጅ ዳግማዊት አማረ ገልጸዋል።

የካቲት 3 ቀን 2017 ዓ.ም በM-Pesa መተግበሪያ እና በተመረጡ የሳፋሪኮም እና ዳሸን ባንክ ቅርንጫፎች ምዝገባ እንደሚጀመርም አስታውቀዋል።

የምዝገባ ዋጋው 540 ብር ሲሆን M-Pesa'ን ተጠቅመው ለሚመዘገቡ ተሳታፊዎች ልዩ የ30 በመቶ ቅናሽ እንደሚኖረውና ለተማሪዎችም ልዩ ቅናሽ እንዲሁም አቅም ለማይፈቅድላቸው ሴቶች አማራጮችን መመቻቸቱን ገልጸዋል። ተሳታፊዎች ሲመዘገቡ በቀጥታ የመወዳደሪያ ቲሸርት እንደሚሰጣቸው ተናግረዋል።

የቅድሚያ ለሴቶች 5ኪ.ሜ. ሩጫ አምባሳደር የሆነችው መሰረት ደፋር በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን ምክትል ፕሬዝዳንትነት መመረጧን ተከትሎ በታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ልዩ ስጦታ ተበርክቶላታል።

የሳፋሪኮም ቅድሚያ ለሴቶች የ 5 ኪሎ ሩጫም በተለይ ሴቶች በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተፅዕኖ መፍጠር እንዲችሉ በራስ መተማመን እንዲጎለብት እና የሴቶችን ብቃት እንዲሁም ችሎታ አንፀባራቂ መድረክ ነዉም ተብሏል።

(በትባረክ ኢሳያስ)

#ትርታ 97.6 FM #ከልብዎ_የቀረበ
Tirita 97.6 FM Radio

05 Feb, 15:04

143

አየር መንገዱ የሀገር ውስጥ ተርሚናል አገልግሎቱ ለጊዜው መቋረጡን አስታወቀ
***
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሀገር ውስጥ ተርሚናል አገልግሎቱ ለጊዜው መቋረጡን አስታውቋል፡፡

በዚህም የሀገር ውስጥ መንገደኞች በዓለም አቀፍ መንገደኞች ማስተናገጃ ተርሚናል በኩል እንዲስተናገዱ አሳስቧል፡፡

አየር መንገዱ ጉዳዩን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ፤ ዛሬ ከቀኑ 6:30 በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የሀገር ውስጥ መንገደኞች ማስተናገጃ ሕንፃ ውስጥ ወደ በረራ ይዞ መግባት ከሚከለከሉ ቁሳቁሶች መካከል ከመንገደኞች የሚሰበሰብ የሲጋራ መለኮሻ (ላይተር) ጊዜያዊ የማስቀመጫ ስፍራ ውስጥ ጭስ በመከሰቱ ለመንገደኞች ደህንነት ሲባል ሕንፃው ለጊዜው አገልግሎት አቋርጧል ብሏል፡፡

በመሆኑም በዛሬው ዕለት ወደ ሀገር ውስጥ መዳረሻዎች የሚጓዙ መንገደኞች በዓለም አቀፍ መንገደኞች ማስተናገጃ ተርሚናል በኩል ወደ በረራቸው እንዲሳፈሩ አሳስቧል፡፡

ለተፈጠረው መጉላላት መንገደኞችን ይቅርታ የጠየቀው አየር መንገዱ፤ ከነገ ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በተለመደው የሀገር ውስጥ ተርሚናል አገልግሎት መስጠት እንደሚቀጥል አስታውቋል።

#ትርታ 97.6 FM #ከልብዎ_የቀረበ
Tirita 97.6 FM Radio

05 Feb, 14:58

483

ጎዶ ሃውሲንግ ኤንድ ስማርት ሪል እስቴት ለመኖርያ ቤትና ለሱቆች ለአንድ ሳምንት የሚቆይ ኤክስፖ ማዘጋጀቱን ገለፀ።

አፍሪካን ሆልዲንግ ግሩፕ በ10 አመት ውስጥ 150 ኩባንያዎችን ለማቋቋም እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል።

ከዚህ መካከል አንዱ በሆነው ጎዶ ሃውሲንግ ኤንድ ስማርት ሪል እስቴት የመንግስትና የግል አጋርነት 70/30 እሴትን ከአፍሪካዊ ማንነት ጋር አጣምሮ እየሰራ እንደሚገኝ የድርጅቱ የስራ ኃላፊዎች በዛሬው እለት በዋና መስሪያ ቤታቸው በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።

ጎዶ ሃውሲንግ ኤንደ ስማርት ሪል እስቴት ቤቶችን ከ50ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ የቤት ባለቤት ለማድረግ በሰንጋተራና በተክለሃይማኖት መካከል ከጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ፊት ለፊት ከአስተዳደሩ ከተረከበው አስር ሺ ካሬ ሜትር ይዞታ ላይ ከየካቲት 14 እስከ የካቲት 16 ቀን 2017 ዓ.ም ለመኖርያ ቤትና ለሱቆች ለአንድ ሳምንት የሚቆይ ኤክስፖ ማዘጋጀቱን ገልጿል።

በተጠቀሱት የኤክስፖ ቀናት ምዝገባ የሚያደርጉ ቅድሚያ የቤት ባለቤትነት እድል ይኖራቸዋልም ብሏል።

#ትርታ 97.6 FM #ከልብዎ_የቀረበ