Sefere Selam Primary School

@sefereselamprimaryschool


Dear Parents and Students, the Main Objective of This Channel is to Make Students able to learn & have:
Lecture Notes,
Worksheets and
Related teaching aid materials.
And also the school messages will be accessible to all parents & staffs.

Sefere Selam Primary School

18 Sep, 04:17


"ተማሪዎቻችን ኑ ወደ ትምህርት ቤታችሁ የዕውቀት ብርሃንን ለመቅሰም" በትምህርት ቤታችን ለሚማሩ የነገ ሀገር ተረካቢ ብቁ ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጅቱን አጠናቋል። "ትምህርት ቤታችሁ ኑ ላስተምራችሁ ትላለች" የ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የትምህርት ማስጀመሪያ መርሃግብር "የጋራ መግባባት ለውጤታማ መማር ማስተማር" በሚል መሪ ሀሳብ ከአጠቃላይ ተማሪዎች ጋር ውይይት ይደረጋል። ስለሆነም ውድ ተማሪዎቻችን በ07/01/2016ዓ.ም 2:30 ሰዓት ላይ በትምህርት ቤቱ ቅጥር ግቢ እንድትገኙ እናሳስባለን።
ሰፈረ ሠላም ቅድመ አንደኛ፣አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት "መልካም የትምህርት ዘመን ይሁንላችሁ" መስከረም 2016ዓ.ም

Sefere Selam Primary School

15 Sep, 15:49


ቀን 04/01/2016ዓ.ም ማስታወቂያ
 ለተከበራችሁ የተማሪ ወላጆች በሙሉ
እንኳን ለ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሠላም አደረሳችሁ አደረሰን እያልን የ2016 ዓ.ም ትምህርት የሚጀመረው መስከረም 7/2016 ዓ.ም መሆኑ ይታወቃል። በመሆኑም በትምህርት ዘመኑ አጠቃላይ ተግባራት ማለትም በሰላማዊ መማር ማስተማር ሂደት የተማሪዎች ውጤት እና ስነ ምግባር መሻሻል ዙሪያ እንዲሁም በት/ቤቱ የ2015 ዓ.ም እቅድ አፈፃፀም እና የ2016 ዓም እቅድ ዝግጅት ዙሪያ ላይ ውይይት ስለምናደርግ ነገ ማለትም በ05 /01/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 በት/ቤቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ እንድትገኙ እናሳውቃለን። "ትምህርት ቤቶች የብቁ ዜጎች መፍለቂያ እና በሁለንተናዊ ስብዕና የሚገነቡበት ማዕከል ናቸው"
ሰፈረ ሠላም ቅድመ አንደኛ፣አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት

Sefere Selam Primary School

14 Sep, 12:56


ቀን 03/01/2016ዓ.ም
ማስታወቂያ
የሰፈረ ሠላም ቅደመ አንደኛ፣አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ያልተመዘገባችሁ ነባር ተማሪዎች የመጨረሻ የማጣሪያ ምዝገባ የሚደረገው እስከ ነገ ማለትም አርብ በ04/01/2016ዓ.ም እስከ 6:00 ብቻ መሆኑን አውቃችሁ በሰዓቱ በመገኘት እንድትመዘገቡ እያሳሰብን ከተጠቀሰው ቀን እና ሰዓት ውጪ የሚመጣ ማንኛውንም ተማሪ የማናስተናግድ መሆኑን እናሳውቃለን። ማሳሰቢያ:- ት/ቤቱ ካወጣው የምዝገባ ኘሮግራም ውጪ የሚመጣ ተማሪን የማናስተናግድ መሆኑን እየገለጽን ተቋሙ ኃላፊነት የማይወስድ መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን።

ትምህርት ቤቱ

Sefere Selam Primary School

13 Sep, 13:16


Share '4_5766907984827388195.pdf'

Sefere Selam Primary School

13 Sep, 12:36


ቀን 02/01/2016 ዓ.ም
ለትምህርት ቤታችን መምህራን በሙሉ
እንኳን ለ2016ዓ.ም አዲስ አመት በሰላም አደረሳችሁ፣አደረሰን። አርብ ማለትም በቀን 04/01/2016ዓ.ም በከተማ ደረጃ የተዘጋጀ አጠቃላይ የመምህራን ስብሰባ ስላለ የትምህርት ቤታችን መምህራን በሙሉ በዕለቱ ጠዋት 2:00 ላይ በት/ቤቱ ቅጥር ግቢ እንድትገኙ እናሳውቃለን::
👉ጥብቅ ማሳሰቢያ፡-
1. በጥብቅ ዲስኘሊን የሚመራ መድረክ ስለሆነ መቅረትም ሆነ ማርፈድ የማይቻል መሆኑን እየገለጽን ለሚፈጠረው ተጠያቂነት ተቋሙ ኃላፊነት የማይወስድ መሆኑን እናሳስባለን።
2. ስብሰባው ላያ ላለመገኘት ማስፈቀድ አይቻልም፡፡
3.የመሰብሰቢያ ቦታ በወረዳ ደረጃ በአንድ ማዕከል ሲሆን (ሰፈረ ሠላም)

ትምህርት ቤቱ

Sefere Selam Primary School

23 Jul, 17:14


ቀን 16/11/2015ዓ.ም

ለትምህርት ቤታችን መምህራን በሙሉ
በክፍለ ከተማ መምህራን ማህበር በኩል በመጣ የስልጠና መረጃ
መምህራን በተለያዩ የሙያ ዘርፎች በነፃ  ለ3 ወር ስልጠና ስለሚሰጥ ስልጠናውን መውሰድ የምትፈልጉ ያልተመዘገባችሁ ሰኞ በ17/11/2015 የመጨረሻ ስለሆነ ትምህርት ቤት በመገኘት  መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
የት/ቤቱ አስተዳደር

Sefere Selam Primary School

21 Jul, 13:28


የመምህራን፣የር/መምህራንና የሱፐርቫይዘር የቤት መረጃ አሰባሰብ ላይ ባልና ሚስት መምህር የሆኑ ላይ የመረጃ መዛባት ስላለ ሁለቱም መምህር ከሆኑ ፎርም የሚሞላው በአንዱ በባል ወይም በሚስት ብቻ በሚለው አስተካክላችሁ እንድትሞሉ፡፡
ሌላው አገልግሎት አያያዝ ላይ ለምሣሌ 9 ዓመት ከ8ወር አገልግሎት ያለው ወይም መሠል የአገልግሎት ሁኔታ ባሉበት ይቀመጡ እንጂ በማጠጋጋት መሙላት እንደማይቻል እናሳውቃለን።

Sefere Selam Primary School

21 Jul, 12:59


ቀን 14/11/2015
ለትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ እና ለተማሪ ወላጆች በሙሉ
ከላይ የተቀመጠዉን ሊንክ(ማስፈንጠሪያ) በመጫን አዲሱን ቻናል በመቀላቀል መረጃ ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።

Sefere Selam Primary School

21 Jul, 12:47


https://t.me/Sefereselam2015

Sefere Selam Primary School

20 Jul, 14:37


ውድ የተከበራችሁ መምህራን  በራሳችሁ ወይም በትዳር አጋራችሁ ስም ምንም አይነት የመኖሪያ ቤት የሌላችሁ መምህራን  የአዲስ አበባ መምህራን ማህበር ባዘጋጀው ቅፅ መሰረት ነገ በ14/11/15ዓ.ም በአካል ት/ቤት ተገኝታችሁ እንድታመለክቱና ትክክለኛ መረጃ እንድትሰጡ እየገለፅን ከተቀመጠው ቀነ ገደብ ዘግይታችሁ ብትመጡና ስማችሁ ለሚመለከተው አካል ባይተላላፍ ኃላፊነቱን የማንውስድ መሆኑን ከወዲሁ መግለፅ እንወዳለን
                                   የት/ቤቱ አስተዳደር

Sefere Selam Primary School

20 Jul, 00:16


The owner of this channel has been inactive for the last 11 months. If they remain inactive for the next 7 days, they may lose their account and admin rights in this channel. The contents of the channel will remain accessible for all users.

Sefere Selam Primary School

19 Jul, 14:00


Addis media network news