እንጠይቃለን::
7. ከዚህም ጋር ተያይዞ፣ ሁሉም የፋኖ ኃይሎች ልዩነቶቻቸውን አቻችለው፣ ከግለሰብ ወይም የቡድን ፍላጎት በላይ የሕዝባቸውን ህልውና በማስቀደም፣ በአስቸኳይ ኅብረት ለመመሥረት የሚያስችል ውይይት እንዲያደርጉ አጥብቀን እንጠይቃለን:: በዚህ ረገድ፣ የዐማራ ዲያስፖራ ግሎባል ፎረም እስካሁን ሲያደርግ የቆዬውን ያላሰለሰ ጥረት እንደሚቀጥልና ወደፊትም የሚጠየቀውን ማንኛውንም ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁነቱን የሚገልጸው በታላቅ ቁርጠኝነት ነው::
8. በዓለም ዙሪያ የሚኖሩት የዐማራው ሕዝብ የህልውና ትግል ደጋፊ ዲያስፖራ አባሎች፣ ብዙ መስዋዕትነት ተከፍሎ የተደረሰበት እድገት ተጨናግፎ፣ የዐማራ ሕዝብ ሰቆቃ እንዳይቀጥል፣ ማንኛውንም ከፋፋይ እርምጃ አንዲቃወሙ፤ ከመሳተፍም እንዲቆጠቡ፤ አጥብቀን እናሳስባለን። ይልቁንም፣ በአንድ ጃንጥላ ሥር ተሰባስበው፣ የፋኖ አደረጃጀቶችም በህበረት ተናብበው ትግሉን እንዲያራምዱ፣ የሚያስፈልግውን የገንዘብ፣ የቁሳቁስ፣ የዲፕሎማሲ እና የገንቢ ሃሳብ ድጋፍ በማድረግ፣ ታሪካዊ ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ እንጠይቃለን።
የዐማራ የህልውና ትግል ያሸንፋል!
ድል ለፋኖ!