ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy @qdist Channel on Telegram

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

@qdist


የግጥም ተሰጥዖ ያላችሁ አድሚን እናደርጋችኋለን በቦቱ ተመዝገቡ ግጥም ብቻ ሳይሆን መነባንብ ሆነ ሌሎችም ተሰጥዖ ያለው መሳተፍ ይችላል
For any comment👉 @e_t_l_bot

Buy ads: https://telega.io/c/qdist

የህይወት ፍልስፍና ethio philosophy (Amharic)

የህይወት ፍልስፍና ethio philosophy is a Telegram channel that explores the rich and diverse philosophical tradition of Ethiopia. Led by a team of passionate scholars and thinkers, this channel delves into the various schools of thought, ideas, and beliefs that have shaped Ethiopian philosophical discourse over the centuries. From ancient wisdom to contemporary debates, የህይወት ፍልስፍና ethio philosophy offers a platform for intellectual exchange and critical reflection. Whether you are a student of philosophy, a curious mind, or simply interested in Ethiopia's cultural heritage, this channel provides an invaluable opportunity to engage with profound ideas and deepen your understanding of the world. Join us on this enlightening journey as we uncover the essence of Ethiopian philosophy and its enduring relevance in today's world.

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

11 Feb, 17:22


ሰዉ እምድላድር ላይ
አንጋጦ ወደ ላይ
ሲመራመር ውሎ
ሰማይን ከምድር ሊያስተሳስር ምሎ
አውጥቶ አውርዶ
በምስራች መርዶ
በመሰለው ሁሉ
ስምን የሚያወጣው መላክት ነው ሲሉ
ከት ብዬ ሳኩኝ ስለመጣራቸው
አንቺን እስካገኝሽ ውሸት ነው ብያቸው

ዮርዳኖስ ያሉሽን ሳለምድልሽ ገና
ቤት ለቤት ሊያ ነሽ ሲባል ሰማሁና
እስኪ ልፈራረድ ብሂሉን ብዬልሽ
ቀልቤን ጥዬ ገባው ልቤን አንግቤልሽ
አወይ የኔስ እዳ የኔው ሞኝነት
ታሪኬን ሳወጋ አመታት አልፎት
እንደ አዲስ ትዝታ ዛሬም ይሰማኛል
ሰላምታዬ ሳይቀር ዘንድሮም ወርሶኛል
በንባሽ የታጠቡ ያለፉት ቀኖቼ
ፅዱ  ሆነው ቀርተው ቢሳሉ ካይኖቼ
ባየሁት ብሌን ውስጥ ሁሌ ነው ማያቸው
ህመሜን ሚሽሩት አይኖችሽ ናፍቋቸው

ኡኡታን ለሚያውቅ እህህንም እንዲያ
ፍቅርሽ ያባክናል ካበገነ ወዲያ
አለምን አምላክሽ ቢያረግልኝ ደብተር
ፅፌ ብጨርሰው አይወጣልኝ ነበር

ናፍቀሺኛል እሺ…ስምሽ ጋር ልመለስ
በጣም ተናፍቀሻል ሀሞቴ እንኳ ቢፈስ
ስላንቺ ማንሳቱን ይፍታህ ላሉኝ አባ ባላቆምም እኔ
በመሸልሽ ቁጥር ጭሴን ተከትዬ
አለሁኝ ለምትል አለሁልሽ ብዬ
ያንተ ነኝ ለምትል ያንቺ ነኝ እያልኩኝ
አንቺን እያሰብኩኝ
ተአምር እያለምኩኝ
ትመጫለሽ ብዬ እያበድኩኝ እኔ
የሆዴን በሆዴ እርዳታ ለምኔ
አምላክ እንኳ አልቻለም
ብዬ ስለፎከርኩ
ለእኔና አንቺ አለም
ምስክር ስላጣው
ይኼንን ፅፍያለው
ስላንቺ ለመፃፍ ብፈርጥ እንኳ እንደ እንቧይ
ቃላት አይበቃኝም ብባንን ሰማይ ላይ
ደመናን ሚቀዝፉ መላክቶች ጋር ካለው
ኼጄ ዝም አልልም እኔ ጠይቃለው
ለምን ካልጠፋ ስም በሞላ ባገሩ
የሷን በኔ ጣሉት አልገባኝም ውሉ
ለካ ስቼ ኖሯል መሳቄ የዛኔ
በማልቀስ ስተካው ገባኝ አሁን እኔ

ዬርዳኖስ ብለዋት በገላዬ ፈሳ
ህማሜን ተረድታ አክማው አድሳ
ታድጋኝ ከራሴ ለኔ ፈውስ ሆና
ማግኘቴን በማጣት እንዴት ብዬ ላውሳ

ደግሞም ሊያ ሆናኝ ስሟን ተደግፌ
ካምላኬ አርፌ በርሱ ተንሳፍፌ
ዘውድ ሆናኝ የአልማዝ አንፀባራቂዋ
በርትታ አበርትታኝ ጠንክራ በእምነትዋ
የኖህ ውሀ ቢሆን ጌታ ለኔ ያላት
ግራዬን እጉድላ በለጋ እድሜ ባያት
ነገር ባልገባኝ ለት
አጥሚት ባኘኩበት
ትዝታ ሆነና ታሪካችን ሁሉ
ብቻዬን ካየሺኝ እንደ እድልሽ ሆኖ
አንቺ ነሽ ሀሳቤ ጫጫታው ተከድኖ
ከእኔና አንቺ ውጪ ላሉት ቢሆን ሚስጥር
ባርስተ ሰላምታ ህመሜን ብናገር
መቼም እንዳትረሺ ፀሎቴ ፀሎትሽ ሆኖ እንደሚቀር
ይቅናሽ እንጂ አንቺን ኑሮሽ ይሳካና
አለኝ የምሰጥሽ  የኑሮዬን ዳና
አሳትመሽ ሽጪው ወይ ካንቺው አስቀሪው
መድብል ሞልቶልሻል ልቤን ስታዝዪው

እሺ ታዲያ ጊዜ የተራረፋቹ
የኔን ስሜት የተካፈላቹ
በትዳር በፍቅር አብራቹ ላላቹ
በፍፁም አእምሮን ደርሶ እያመናቹ
ልባቹን አትግፉት ትሰቃያላቹ



#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመዶ ያጋሩ #share @Qdist
Join and share👇👇
@qdist
@qdist
@qdist
For any question& comment ለማንኛውን
ጥያቄ&አስተያየት @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

10 Feb, 19:01


ወደድኩሽ ካለኝ በኃላ...

ስደዉል ስልኩን ቢዘጋም
ስቀጥረዉ ቢቀርብኝ
መልዕክቴን አይቶ ዝምቢል
በድንገት ባገኘዉ እንኳ በፍጥነት ከኔ ገሸሽ ቢል...
እኔ ልሙት ይወደኛል...

ቢፈራኝ ነዉ እንጂ ፍቅሬ ቢያስጨንቀዉ
ምን እላት እያለ ስለሚ'ያሳስበዉ
ስልኩን የማይመልስ ትቶኝ የሚሮጠዉ

ሌላ ጊዜ እድል ቀንቶኝ
በአንዲቷ ቀን ካፌ ቀጥሮኝ
አይኖቹ ከስልኩ
አያየኝም ብዬ ያልኩ
ሌላ ሴት እያየ በድንገት ሲጠቅሳት
አይኔ ካይኑ ተገጫጨ
የያዘዉ ብርጭቆ ከእጆቹ አሟለጨ

ፈገግ አልኩ ደነገጠ
ምንን ያህል ቢወደኝ ልቡ የቀለጠ?
አወይ አጋጣሚ ብዬ ተገረምኩ
ይሄኔ ሲያየኝ ደንግጦ ነዉ አልኩ

እኔን ይንሳኝ ይወደኛል ስላችሁ
ደግሞ የዛሬዉን ጉዱን ልንገራችሁ

መጥሪያ አምጥቶ እጆቼ ላይ አስቀመጠ
ላገባ ነዉ ብሎ ልክ እንደ ልማዱ ደሞ ፈረጠጠ

ገለጥኩት...
የልቤ ከምላት ከኔዉ ጓደኛ ጋር
የሚሆናት አጋር

ምን ያክል ቢወደኝ
እንዴት ቢሳሳልኝ
አወይ የሱ ፍቅር

የልቤ ምላትን እንደ ልቡ አድርጐ
እኔን ለማስደሰት ሚያገባት ሰርጐ
ይወደኝ አይደለ
?
ትዝታ ወልዴ

#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመዶ ያጋሩ #share @Qdist
Join and share👇👇
@qdist
@qdist
@qdist
For any question& comment ለማንኛውን
ጥያቄ&አስተያየት @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

18 Jan, 18:27


#እናቴ

ልንገርሽ እናቴ የሆዴን አውጥቼ
ሳርቅ ካጠገብሽ መቼም የሁን መቼ
ሁሌም በልቤ ዉስጥ ዙፋንሽን  ይዘሽ
ትኖሪያለሽ በልቤ ዉስጥ ለኔ ነግሰሽ።

የናትነት ፍቅርሽ መቼም ሳይለየኝ
አለ በልቤ ውስጥ ሁሌም ትዝ እንዳለኝ
ልጄ ብለሽ ስትጠሪኝ በጣፋጭ አንደበትሽ
ማረገውን ሳጣ ከደስታ ብዛትሽ
አያልቅም ተነግሮ እማ ያንች ውለታ
ቢዘከር ቢዘከር ሁሌ ጠዋት ማታ

ብትጨነቂ ለኔ ብትቆጭ  ለኔ
ምን ማርግ ....
ችላለው አያሳያኝ ያንችን ክፉ ለኔ

የአባቴ ምትኬ ነሽ የአምላኬ ስጦታ
ከሰማይ በታች ያለሽኝ መከታ

ለኔ ህይወት ስትኖሪ የአንችን  እረስተሽ ለኔ በፍቅር ብርሃን ብርሃኔን አብርተሽ
በይ እረፊ እንግዲ ልርዳሽ በተራዬ
ለሁሉም ቀን አለ አሁን ነው ፋንታዬ

ለውለታሽ ምላሽ የንሰኝል ቃል
ድንገት ዞር ስትይ እንካን ሳቅሽ ቁጣሽ ይናፍቃል
ክፉ አይንካብኝ እስከ ዘላለሜ
ካንች በፊት ያርገው ያንችን ክፉ ለኔ
ያላንች ባዶነው ሳስበው ህይወቴ
ክፉም ሆንክ ጥሩ ኑሪልኝሬናቴ።
    ጥሩ እና ለእናንተ ምንም መስዋትነት መክፈል ለሚችሉ እናቶች ይሁንላችሁ
መልካም ምሽት

#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመዶ ያጋሩ #share @Qdist
Join and share👇👇
@qdist
@qdist
@qdist
For any question& comment ለማንኛውን
ጥያቄ&አስተያየት @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

16 Jan, 15:33


ከእኔጋ ኦንላይን ስራ መስራት ምትፈልጉ ሊንኩን ነክታቹ ኑ ምንም አይነት ቅድሚያ ክፍያ የለውም ሰዎች like እንደ ቲክቶክ ነው appun አውርዳችሁ አናግሩኝ በቀን እስከ 50$ እነየሰሩ ነው trust me ሰዎች

ሴቶች ስትገቡ 3$ ይሰጣችዃል live መቀመጥ task መስራት ነው ስራው ዎንዶች agent ለመሆን ነው ዋና አላማችን ሴቶች የፈጠነ ስራውን ጀምሩት በዉነት ይለውጣችኋል


Appun አውርዱት👇👇

https://aaaonline.info/pF3NPw

ስለ ስራው ለማዎቅ @esttiff

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

08 Jan, 18:18


ከእኔጋ ኦንላይን ስራ መስራት ምትፈልጉ ሊንኩን ነክታቹ ኑ ምንም አይነት ቅድሚያ ክፍያ የለውም ሰዎች like እንደ ቲክቶክ ነው appun አውርዳችሁ አናግሩኝ በቀን እስከ 50$ እነሰሩ ነው trust me ሰዎች

Appun አውርዱት👇👇
https://aaaonline.info/pF3NPw

በዚህ አናግሩኝ @esttiff

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

01 Jan, 17:32


#ሁላችን_ከንቱ_ነን

የልብ አማኝ ጠፍቶ የአፍ አማኝ ከበዛ
በእውነት አመንጭቶ ፍቅርን ካልገዛ
መማር ከየት ይምጣ ልብ ተቆልፎ
የሰው ልጅ ካልጣለ ማስመሰልን ገፎ

ባንደበቱ ጌታን በልቡ ገንዘብን
አፉ አሜን እያለ በውስጡ ተንኮልን
ምላስ አምላክ ጠርቶ
ልብን ገንዘብ ሞልቶ
የስም ፃድቅ ሰፍቶ
በነብይ ተሞልቶ
ምህረት ከየት ይምጣ
እንዴት ይብረድ ቁጣ!
ጠዋት ክርስቶስን
ከሰአት ሰይጣንን
በግፍ ተሸፍኖ ልባችን በቀልን
የተንኮል አሽክላ አስልተን እየጣልን
ማረን እንላለን እንዴትስ ይማረን
በሁለት ቢለዋ አስብተን እያረድን
ዳዊት ከደገመ ጠዋት ምላሳችን
ማታ ላይ ስድብን ለምዶ አንደበታችን

ሊምረን ቢመጣ ቁጣውን ሊያበርደው
ምላስ ብቻ ቀርቷል ለካስ ልብ ባዶ ነው
በሐይማኖት ጥላ ተሸሽገን ከርመን
እምነት ግን ሲጠየቅ ሁላችን ከንቱ ነን።
ቼር ምሽት


#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመዶ ያጋሩ #share @Qdist
Join and share👇👇
@qdist
@qdist
@qdist
For any question& comment ለማንኛውን
ጥያቄ&አስተያየት @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

01 Jan, 17:25


https://t.me/+K0NLcevX5qgzMjA1

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

30 Dec, 15:05


#ጉቻለሁ_ፍቅሬ

ጓጉቻለሁ የምር
ሽክ ብለህ እምር
ስትመጣ ወደ'ኔ
ባንተ ድምቀት ምክንያት
ሲፈካልኝ ቀኔ
እንደ ወጣቶቹ እስካይህ ዘንጠህ፣
በሱሪ በሸሚዝ በካፖርት አጊጠህ፣
ወይ እንደ አባቶችህ ጋቢና ከዘራ፣
ሰው ሰው እስክትሸተኝ ነብስ እስክትዘራ፣

ጓጉቻለሁ በጣም....
ልክ እንደ ክርስቶስ....
ባይኖርህ ትንሳኤ በሶስተኛዋ ቀን፣
ትመጣለህ በሚል እየዎዘዎዘኝ
የናፍቆት ሰቀቀን፣
መቃብር ፈንቅለህ
እስካገኝህ ባካል፣
ስንት አመት ይፈጃል መቼላይ ይሳካል፣
እላለሁ...
ሁልጊዜ እብሰለሰላለሁ...

ግን እባክህ ፍቅሬ...
ባቆሰልኩት ፊቴ በደራረብኩት ማቅ፣
ንገረኝ መምጫህን ትንሳኤህን እንዳቅ፣

በቅርቡ ከመጣህ ሳይደክም ጉልበቴ ፣
እቀበልሀለሁ ደግሼ ከበቴ፣
ምናልባት ከሆነ ...
ለመምጣት ያሰብከው...
አመታት ተቆጥሮ ዘመንን ሲገፋ፣
እንዳንጠፋፋ...
እኔው እመጣለሁ ጠብቀኝ አትልፋ


#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመዶ ያጋሩ #share @Qdist
Join and share👇👇
@qdist
@qdist
@qdist
For any question& comment ለማንኛውን
ጥያቄ&አስተያየት @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

29 Dec, 19:22


#አንድ_ቀን

#አፍቅሪኝ አልልሽም
እኔ እንዳፈቀርኩሽ
ተጎጂ አልልሽም
እኔ እንደተጎዳሁት
አንቺን በኔ ቦታ ማየት አልፈልግም
ከቶ አያረካኝም…
ግን ብቻ አደራ…
ከልብሽ ውደጂኝ ከውስጥሽ አኑሪኝ
ከህሊናሽ ካልራኩ ቢቆጠሩ አመታት
ታፈቅሪኝ ይሆናል አንድ ቀን ምናልባት


#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመዶ ያጋሩ #share @Qdist
Join and share👇👇
@qdist
@qdist
@qdist
For any question& comment ለማንኛውን
ጥያቄ&አስተያየት @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

28 Dec, 06:21


19😘😍

እንኳን ለቅዱስ ገብርኤል አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ
የአመት ሰው ይበለን😍😘

@qdist

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

23 Dec, 16:55


​​​​​#የመገፋት ህመም የማጣትን ፍቺ
ልንገርሽ እንጂ እኔ የት አውቀሽው አንቺ

ብዙ ነገ እየሳልኩ አብሬ ካንቺ'ጋ
ሳስብሽ አመሸሁ እያለምኩሽ ነጋ
ሀሳቤን ሰርቀሽው ቀኔ አላማረበት
ቀልቤን ሰውረሽው አዋዋል ጠፋበት
ከእኔ'ጋ ነሽ እያልኩ አብረሽኝ ከጎኔ
አንቺ ሩቅ ሄደሻል እዛው ቀረሁ እኔ

የቀረበሽ ልቤ አንቺን በወደደ
የማያውቀው ነፍሴ በእሳትሽ ነደደ
መላ አካሌ አፍቅሮሽ እኔን ጥሎ አበደ
የኔ ያልኩት ሁሉ ትቶኝ ተሰደደ
እፋረድሻለሁ በይ ካሽኝ እያልኩኝ
ለብቻየ ስቀር ብዙ እንዳልነበርኩኝ

ለማን ዳኛ ልክሰስ ማንስ ይሰማኛል
ጉዳቴን ያሰበስ ምንድን ይክሰኛል
ጉዳዬን የሰማ ያ ሁሉ ዳኛ ሰው
ክሴን አቃለለ ብሶቴን መለሰው
እንግዲህ ምን ላድርግ...
ፍትህ ንብረት አይደል አልገዛ አልዋሰው

የሰማኝ በሙሉ የነገርኩት ዳኛ
እሷን ነፃ አረጋት እኔን ጥፋተኛ
ከእንግዲህ ለማንም አልከስም በቅቶኛል
እስካሁን የሰማኝ አይሆንም ብሎኛል
አንቺ ጉልበተኛ አንቺ ባለጊዜ
እኔ ሟች ደካማ የዋጠኝ ትካዜ
አንቺን ማን ተሟግቶ ችሎ ያሸንፍሻል
የቀረበሽ ሁሉ ላንቺ ያዳላልሻል
ቁመናሽ እሳት ነው አይን ጥርስሽ ገመድ
ውበትሽ አሳሳች አሳሳቅሽ ወጥመድ
ማለፍ ቢሳናቸው ይሄንን ፈተና
እኔን 'በዳይ' ማለት ቀለላቸውና
እሷን ተበዳይ ሰው እኔን ወንጀለኛ
ብለው ፈረዱብኝ ከአንድም ሶስት ዳኛ

አምርሮ ቢያነባ እንባዬ ቢፈስም
በያገኘው ችሎት እልፍ ጊዜ ቢከስም
የፍርድን ጥም ሽቶ ከጫፍ ጫፍ ቢያስስም
ገሳጭ ሰው ነው እንጂ አይዞህ ባይ አይደርስም

በቃኝ አልካሰስ ይቅርብኝ ልጎዳ ልተወው ግዴለም
ብቻ አውቄዋለሁ በሰዎች ደጅ እንጂ ፍትህ በአገር የለም
አትፍሰስ ይበቃል ከእንግዲህ እንባዬ
ጩኸቴ አላዋጣም ይርታት ዝምታዬ

እንግዲህ ገብቶኛል...
ላገኘሁት ሰሚ አልከስ አልዘልፍሽም
በየአደባባዩ ስምሽን አልጠራሽም
በየችሎቱ በር ነይ ግቢ አልልሽም...
ስምሽን ባጠፋ ብሰድብሽም እንኳን አትደናገሪ
ጩኸቴ ምንም ነው ዝም ስል ግን ፍሪ

    
#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመዶ ያጋሩ #share @Qdist
Join and share👇👇
@qdist
@qdist
@qdist
For any question& comment ለማንኛውን
ጥያቄ&አስተያየት @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

20 Dec, 16:43


ሲከፋህ አልወድም

አለሜዋ......
የልቤ እንጉርጉሮ
     የልሳኔ ዜማ
ጆሮ ዳባ አትበል
        ቃሌን ስማኝማ
ይቺ ወረተኛ
       ሽሙጠኛ አለም
ቢሮጡ ቢደክሙ
        መውደቅን ምታልም
ለዚች ተንጎራዳጅ
         ልብን ለማትሞላ
ጭፍራ አዘል ከጀርባ
       ለአምሳዮች ተድላ
ዛሬ ሙልት ስትል
        ጎደለዋ ነገ
የንጋት ፀሀይዋ
      ጭራሽ ላልፈገገ
ከዚች ካልሞላላት
          ሙላትን አጠብቅ
የተስፋህን እጅ
         "አላማ አትልቀቅ"

ልቤን ክፍት አለው እምም አለኝ እኔ
ሲከፋህ አልወድም የምወድህ እኔ(ሳቅልኝ).

🥀
@saktawocu🥀

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

18 Dec, 16:28


#ቀን_ሲጥል

ሰምሃል ሊዲያና ራኬብ እየተሳሳቁ ልክ ወደ ዶርም ሲገቡ ኤቤጊያ ወደውጪ ለመውጣት እየተኳኳለች ነበር ሰምሃል ሳቋን በአንዴ አቆመችና ቦርሳዋን አልጋዋ ላይ አስቀመጠችና ወደ ሎከሯ ሄደች ራኬብና ሊድያ ደክሟቸው ስለነበር ሃደው አልጋቸው ላይ ተዘረገፉ ኤቤጊያ መኳኳሏን አቁማ ወደ ሰምሃል እየተጠጋች አረ... ሰሙዬ አሁንም እንዳኮረፍሽኝ ነው ወር ሞላኝ እኮ ካኮረፍሽኝ ያጨዋታሽና ሳቅሽ ናፈቀኝ እባክሽ ይቅር በይኝ በቃ አለቻት ሰምሃል ምንም መልስ ሳትሰጣት አድርጋቸው የነበሩትን ጉትቻ የጆሮ ጌጦች እያወለቀች ሎከሯ ውስጥ ስርአት ባለው መልኩ ታስቀምጣለች።

ኤቤጊያ የሰምሃል ዝምታ ሲበዛባት ጮክ እያለች እሺ ቆይ ምን እንድልሽ ነው ምትፈልጊው ከዚ በላይ መቶ ግዜ እኮነው ይቅርታ ያልኩሽ የምር ሰሙዬ ሁለተኛ አይለመደኝም የእውነት አንቺ የፈለግሺውን ነገር ቅጪኝ እና ልገላገል እኔ ዝምታሽ ሊበላኝ ነው አለቻት ሰምሃል እንደመበሳጨት እያለች የሎከሩን በር አጋጭታ ዘግታው ወደኤቤጊያ ዞረች እኔ አንቺን የመቅጣት ፍላጎት የለኝም የዛን ቀን ርክክለኛ ማንነትሽን ነው ያሳየሽኝ በጣም ነው ያዘንኩብሽ እንደዛ አይመት የቀሸመ ስብእና ይኖርሻል ብዬ አላስብም ነበር እኔ ባንቺ አዘንኩብሽ እንጂ አልተቀከምኩሽም ያስቀየምሽው እኔን ሳይሆን ናኦድን ነው አሁን ውጪ ሊያገኝሽ እየጠበቀሽ ነው ጥሪልኝ ብሎኛል ሄደሽ አናግሪው የእውነት ያደረግሽው ነገር ከፀፀተሽ ይቅርታ በይው ይቅርታ ሳትጠይቂው ብትመለሽ እኔን አያድርገኝ ብላ ጮኀችባት።

ሊዲያ እና ራኬብ የሁለቱን ጭቅጭቅ ድምፃቸውን አጥፍተው ከመስማት ውጪ ምንም ትንፍሽ አይሉም። ኤቤጊያ እያቅማማች እህህህ አሁን እኮ ከራስታው ጋር ልንወጣ ተቀጣጥረናል እንዴት ብዬ ነው ሞሮ ጋር እምሄደው አለቻት ተሳስታ ሞሮ እንዳለችው ስራውቅ በጣም ደነገጠች ሰምሃል ይበልጥ ፊቷ ሲቀላ ታወቃት እዛው በቆመችበት ደነፋች የምርሽን ነው!!! አንቺ እሚያስጨንቅሽ ከእንድ ሰው ጋር ስለመውጣት ነው ያስቀየምሽው ሰው ያስለቀስሺው ሰው አይታይሽም አለቻት ኤቤጊያ በአፍረት አንገቷን አቀረቀረች መልሽልኛ ብላ ጮኀችባት መሄድ ትችያለሽ አልከለክልሽም ግን ዳግም ጓደኛዬ ብለሽ አጠገቤ እንዳትደርሽ አለቻት ኤቤጊያ ደነገጠች እሺ በቃ እሄዳለው የቱ ጋር ነው ያለው አለቻት ሰምሃል ተናዳ ስለነበር እነሱን ጠይቂያቸው ብላ ወደነራኬብ ጠቁማት አልጋዋ ውስጥ ተጠቅላላ ገባች ራኬብ በመስኮት ናኦድ የቆመበትን ቦታ አሳየቻት እሺ ያው እየሄድኩ ነው ሰሙ በድጋሚ ይቅርታ ሁሉንም ነገር አስተካክለዋለው ብላት በፍጥነት ከዶርሙ ወጣች።


ይቀጥላል.....
#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመዶ ያጋሩ #share @Qdist
Join and share👇👇
@qdist
@qdist
@qdist
For any question& comment ለማንኛውን
ጥያቄ&አስተያየት @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

14 Dec, 04:34


#ቀን_ሲጥል

አባዬ ብዙ ካሰላሰለ በኃላ ወደ ኪያር ዞረና ኪያር መኪና መንዳት ትችላለህ ብሎ ጠየቀው አው እችላለው ጋሼ አለው አባዬ የመኪናውን ቁልፍ አቀበለውና በል በቃ ደርሳችው ነገውኑ ዊዝድሮው እንደጨረሳችው ይዘኀው ተመለስ አደራ በጣም ተጠንቀቁ ብሎን ሄደ ልክ አባዬ የውጪውን በር ከፍቶ እንደወጣ yessss..ብዬ ከመቀመጫዬ ተነስቼ ዘለልኩ ወደ ሰሙ እያየው አይ ሰሙ መለኛ እኮ ነሽ ማነው በናትሽ ውሸት እንዲ ያስተማረሽ በአንዴ እዚው ፈጥረሽ አሳመንሽው እኮ አልኳት ሰሙ ኮስተር ብላ እየቀለድኩ አይደለም ናዲ እኔ የእውነቴን ነው የተናገርኩት ዊዝድሮው ሞልተህ ተመለስ እዛ ስንሄድ ምንም ነገር እንዳታደርግ just ዊዝድሮው ሞልተህ ነገውኑ ትመለሳለህ ተናግሪያለው አባትህ ለኛ ነው አደራ ብለውን የሄዱት ምንም ነገር እንዲፈጠር አልፈልግም አለችኝ እሺ ችግር የለውም ግን አንድ ነገር.ላስቸግርሽ እዛ ስንሄድ ኤቤጊያን እንድታገናኚኝ ብቻ ነው እምፈልገው ሌላ ምንም አልፈልግም አልኳት እእህህህህ ለካ ለሷ ብለህ ነው ናዝሬት እምትመጣው አለችኝ ልዋሻት ስላልፈለግኩ አዎ አልኳት እየተናደደች እሺ አለችኝ።

ከሰአቱን ከቤት ወጥተን እዛው ቦሌ አከባቢ ዞር ዞር ብለን ስንዝናና ዋልን ያው እኔ ከቤት ወጥቼ ስለማላውቅ እኔን ለማዝናናት ታስቦ ነው ታናሽ እህቴም አብራን ነበረች እኔና ሰሙ ከኃላ ቀስእያልን ወክ እናረጋለን መሃል ላይ ራኬብ እና ሊዲያ አንድ ላይ እያወሩ ናቸው ኪያር እና እህቴ ደሞ ከፊት ሆነው ይሄዳሉ። እዛው ከሰፈራችን ብዙም የማይርቅ ካፌ ገብተን ስንጨዋወት 11፡00 ሰአት ሆነ ሁላችንም ወደቤት ተመለስን እህቴ ስትቀር ሁላችን ናዝሬት ልንሄድ ተነሳን እናቴ ያዘጋጀችልኝን ትንሽዬ ሻንጣ መኪናው ውስጥ አስገባው እነሰሙም ቦርሳቸውን ምናምን ይዘው ከኃላ ገቡ  ኪያር ቁልፉን ተጭኖ መኪናዋን አስነሳ  እኔ እናቴን ቻው ብያት ወደመኪና ስሄድ ጠንቀቅ በል እሺ የትም እንዳታመሽ ደሞ አለችኝ ሃሳብ የገባት ይመስላል።

እሺ እማ የትም አልሄድም ቻው ብያት ጋቢና ገባው እህቴ ዋናውን በር  እየሮጠች ሄዳ ከፈተችልን ዛሬ የእህቴ ቅልጥፍና እያሳቀኝ ነው ዘበኛው እያለ ምን እሷ ያጣድፋታል እየወጣን እያለ ኪያርን ቻው አለችውና ስንሄድ ቆማ አየችን ገዞ ወደናዝሬት! መንገድ ላይ ሁላችንም  እየተንጫጫን እየቀወጥነው እያወራን ሄድን ሲመሻሽ ናዝሬት ገባን ኪያር መኪናዋን ቀጥታ ወደ ግቢ ይዟት ገባ እነሱሙን ወደ ዶርማቸው አከባቢ አደረሳቸውሊጠይቁኝ ስለመጡ በጣም አመስግኛቸው መሰነባበት ጀመርን ሰሙ ኤቤጊያን ጠራልሃለው መልካም እድል ብላኝ ከራኬብ ጋር ቶሎ ሄደች የሆነ የደበራት ነገር እንዳለ ቀልቤ ይነግረኛል ሊዲያን ምን ሁና ነው አልኳት አይ መንገዱ ነው ትንሽ አሟት ነበር ቅድምም አለችኝና እኔና ኪያርን ቻው ብላን ሄደች።

ኪያር በቃ በርታ በል እኔ እዛ ጋር ሆኜ እጠብቅሃለው እንዳትፈራ ሴቶች እሚፈራ ወንድ አይመቻቸውም እሺ መልካም እድል ብሎኝ ፊትለፊት ጨለማ ውስጥ ጥንዶች የሚቀመጡበት ወንደር ላይ ሄዶ ተቀመጠ። የመጨረሻዋ ሰአት ደረሰች!! ኤቤጊያ ከደቂቃዎች በኃላ ትመጣለች ልቤ በፍጥነት መምታት ጀመረ ሰውነቴ ከበደኝ እንደምንም ራሴን ለማረጋጋት ሞከርኩና ቀና ብዬ መኪናዋን ተደግፌ ቆምኩ ከትንሽ ቆይታ በኃላ አንዲት ሸንቀጥ ረዘም ያለች ውብ ከሴቶች ዶርም ወጥታ ስትመጣ አየው።


ይቀጥላል.....
#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመዶ ያጋሩ #share @Qdist
Join and share👇👇
@qdist
@qdist
@qdist
For any question& comment ለማንኛውን
ጥያቄ&አስተያየት @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

10 Dec, 15:59


#ቀን_ሲጥል

ሰምሃል ለእኔ ብላ ኤቤጊያን አንድ ወር ሙሉ ማኩረፏ አስገረመኝ ተገረምኩባት ስብእናዋ ያስደንቃል አንድ ወር እንኲን በቅጡ ለማታውቀው ሰው ብላ ለአመታት የምታውቃትን ጓደኛዋን አኮረፈች ይገርማል። ብዙ ከጨቀጨቅኳት በኃላ እንዲታረቁ አስማማኃት ሲቀጥል እኔ ኤቤጊያን አልተቀየምኳትም የተናገረችው ነገር ደባሪ ሊሆን ይችላል ግን አሁንም ድረስ ወዳታለው የዛኔ የኔም ጥፋት ነበረበት መታመሜን ልትጠይቅ የመጣችን ሴት ዘልዬ አፈቅርሻለው ምናምን ማለት አልነበረብኝም እንደውም ጥፋተኛው እኔ ነኝ አልኳት።

እያወራን እያለ አባዬ ከቤተክርስቲያን ተመልሶ ነጠላውን አጣፍቶ ወደቤት ገባ አራቱም ደንገጥ ብለው አባዬን ሰላም ሊሉት ከመቀመጫቸው ብድግ አሉ እኔ ደሞ ሁኔታቸውን አይቼ ፈገግ አልኩ እነሰሙ በደምብ ስለማያውቁት ነው ከሁሉም ያሳቀኝ የኪያር ነበር ቤቴ ሁሌ ሲመጣ ኖሮ ዛሬ እንዳዲስ መደንገት ሃ..ሃ..ሃ... አይ ኪያር።

አባዬ ገና ሰምሃልም ሲያያት ነበር ደስ ያለው እንዴ መጣችው እንዴ ጠፍታችው ቆያችው ምነው አላቸው ወደ ሰምሃል እያየ እሷም አፈር እያለች አይ የፈተና ሰሞን ስለነበረ ትንሽ ተጨናንቀን ስለነበር ነው ጋሼ አለችው። አይ ደግ ይሁን በቃ በደምብ  ተጫወቱ እንደቤታችው ቁጠሩትቁጠሩት ብሏቸው ወደላይ ሄደ ቤተሰቦቼ ሰምሃልን በጣም ነው የሚወዷት ስለሷ ብዙም ባያውቁም እኔ ያደረገችልኝን ሁሉ ነግሪያቸው በጣም ወደዋታል በተለይ አባዬ። እኛም ጨዋታችንን ቀጠልን በመሃል እያወራን ዛሬ ከናንተ ጋር ወደ ግቢ ለምመጣት አስቢያለው አልኳቸው ደስ አላቸው ግን ችግሩ አባዬ እሚፈቅድልኝ አይመስለኝም እሱን ለማሳመን የተቻለኝን አደርጋለው እናንተም ታግዙኛላችው እሺ አልኳቸው ተስማሙ ግን ኪያር ቅር ያለው ይመስላል ምክንያቱም ለምን ለማን ብዬ ናዝሬት እንደምመለስ ያውቃል ድጋሚ ኤቤጊያን ለማግኘት እንደሆነ ያውቃል እየደበረው እሺ አለኝ።

ሁላችንም ምሳ ከበላ በኃላ ሁሉም ባሉበት ስፈራ ስቸር አባቴን ግቢ ደርሼ መምጣት እንደምፈልግ ነገርኩት  ወዲያውኑ የቲቪውን ሪሞት ከጠረጵዛው ላይ አንስቶ ድምፁን እየቀነሰ ኮስተር ብሎ ምን? አለኝ ድምፁ ይበልጥ አስፈራኝ። አይ አባዬ አሁን ተሽሎኝ የለ ደህና ነኝ እኮ ግቢ ዛሬ ደርሼ መምጣት ፈል.... አባዬ እስክጨርስ አልጠበቀኝም ቆጣ ብሎ አይቻልም! ብሎ ቀጭን ትእዛዝ አስተላለፈ። ኪያር ጋሽ ምሽጉ እኛ ስላለን እኮ ችግር የለውም እንጠብቀዋለን ምንም አይሆንም አለ አባዬ ግን በሃሳቡ ፀና አይሆንም የሆነ ነገር ቢሆን ፀፀቱን አልችለውም ብቸኛ ወንድ ልጄ ነው አለው።

ዝምታ ሰፈነ ሁሉም ከተረጋጋ በኃላ ሰምሃል ወደ አባቴ እያየች ጋሼ እኔም በእርሶ ሃሳብ እስማማለው ናኦድ ህመም ላይ ነው ነገር ግን ደግሞ ብዙ አመት የለፋበት ትምህርት አለ ያንን ትምህርት እንዲው እንደቀልድ መተው ለእርሶም ለናኦድም የህሊና እረፍት አይሰጥም ናኦድ በጣም ጎበዝ ተማሪ እንደሆነ አውቃለው በዚ አመት ዊዝድሮው ፎርም ካልሞላ  ቀጣይ አመት መመለስ አይችልም ይባረረል ዩኒቨርስቲው የሚያውቀው አሁንም በትምህርት ላይ እንደሆነ እንጂ በህመም ምክንያት አቋርጦ እንደሄደ አያውቅም ስለዚህ ድጋሚ ተመልሶ ያለውን ሁኔታ ገልፃ ዊዝድሮው ሞልቶ መመለስ አለበት እኔም ባይሄድ ደስ ይለኝ ነበር ግን ፋይናል ፈተና ሳይጀመር ዊዝድሮው መሙላት አለበት አለችው። አባዬ በትምህርት ምንም አይነት ድርድር ስለማያውቅ ሊቃወምበት የሚችለው ምክንያት አልነበረውም።

ይቀጥላል.....

#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመዶ ያጋሩ #share @Qdist
Join and share👇👇
@qdist
@qdist
@qdist
For any question& comment ለማንኛውን
ጥያቄ&አስተያየት @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

10 Dec, 15:26


ከማፍቀር የሚገኝ ደስታ የራስ ነዉ። ማፍቀር ምላሽ አይጠይቅም የግድ መፈቀርም አይሻም ማፍቀር በራሡ ደስስ ይላል
        
"እውነተኛ ፍቅር መራራ ነገርን በሚያስከትል እንደስኳር በሚጣፍጥ ቃላት ወይም ጨለማን በሚያስከትል ብርሃን የታጀበ አይደለም የእውነተኛ ፍቅር ብርሃን አንዴ ከበራ የማይጠፋ፣ካመነ የማይክድ፣ከወደደ የማይጠላ የራስን ሕይወት አሳልፎ ለሌላው እስከመስጠት የሚያደርስ መለኮታዊ ስጦታ ነው።

ይሕንን ውድ ስጦታ ከፈጣሪ የሆኑ ፈጣሪ የፈቀደላቸው ብቻ ይታደሉታል በመሆኑም ፍቅር የጨዋዎች አብይ መልእክት እንጂ የባለጌዎች ዲስኩር አይደለም አዎን  እውነተኛ ፍቅር ካምላክ በትጋት የሚሰጥ ነው


Join👇👇👇
@saktawocu
@saktawocu

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

09 Dec, 12:17


Join & share
@etl_1
@etl_1

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

09 Dec, 06:25


#ቀን_ሲጥል

ወር ሞላኝ ቤት ከተቀመጥኩ ከህመሜ ድኛለው ማለት ይቻላል በየቀኑ ሰምሃል ሳትደውል የዋለችበት ቀን ትዝ አይለኝም ሁሌ ትደውላለች ክላስ ትንሽ ተጨናንቀው ስለነበር መጥታ ለመጠየቅ አልተመቻትም  ዛሬ  ግን ከጓደኞቿና ከኪያር  ጋር መጥተው እንደምትጠይቀኝ ነግራኛለች ያው ኪያር ሁሌ ቅዳሜና እሁድን እየመጣ ይጠይቀኝ ነበር እነሰምሃልም ቤታችንን ስለማያውቁት ይዟቸው ይመጣል።

ቤት ውስጥ መቀመጥ ሲሰለቸኝ ውጪ ወጥቼ ከቧንቧው በጎማ አድርጌ  አትክልቶቹን ውሃ እያጠጣው እያለ ታናሽ እህቴ ከፀጉር ቤት መጣች አምሮባታል እየሳቅኩ ምን ተገኘ እንዴ ዛሬ አልኳት እሷም እየሳቀች በፍጥነት  ኪያር ይመጣል አይደል ዛሬ? አለችኝ እቺን ይወዳል ለኪያር ነው እንዲ ፏ ያልሺ ሃ..ሃ..ሃ...   ኪያር እኮ እኔን ሊጠይቅ ነው የሚመጣው አንቺ ምን ቤት ነሽ እምትኳኳይው ብዬ ሳቅኩባት አኩርፋኝ ለምቦጫን ዘፍዝፋ ገባች እኔም እየሳቅኩ ታናሽ እህቴና ኪያር ምን አይነት ጥንዶች ሊሆኑ እንደሚችሉ እያሰብኩ በሳቅ እየፈረስኩ አትክልቶቹን ማጠጣት ቀጠልኩ በርግጥ ኪያር በጣም ጥሩ ልጅ ነው ከእህቴ ጋር አንድ ላይ ቢሆን ምንም ቅር አይለኝም። እንዲ ብዙ እያወጣው እያወረድኩ እያለ አንድ ላዳ ታክሲ በራችን ጋር አቆመ እያጠጣሁበት የነበረውን ጎማ ሰብስቤ ማን እንደመጣ ለማየት ወደ ላዳዋ ሄድኩ እነ ስምሃል እና ኪያር ናቸው።

ሰምሃል ከመኪናው ወጥታ እየሮች መጥታ አቀፈችኝና አንገቴን ሳመችኝ በየቀኑ በስልክ ስናወራ ስለነበር በጣም ተቀራርበናል ሁሌም ስለኤቤጊያ ሳልጠይቃት አልውልም ምን እንደሰራች ከማንጋር እንደዋለች እየጠየቅኩ አሰለቻታለው ዶርም ውስጥ ሆና ስታወራኝ ደሞ ጓደኞቿ ሊዲያ እና ራኬብ ስልኳን በግድ እየቀሙ ያወሩኛል ሶስቱም ደስ እሚሉ ጓደኛሞች ናቸው ፍቅራቸው ያስቀናል። ኪያር ሊዲያና ራኬብም እየተሳሳቁ መጥተው ሰላም አሉኝና ተያይዘን ወደቤት እየገባን እያለ ኪያር ጮክ ብሎ እንግዲ ይህ የምታዩት ትልቅ የተንጣለለ እልፍኝ የጋሽ ናኦል እልፍኝ ነው ቤተመንግስ አይደለም እንዳትደናገጡ እሺ አላቸው ወደነስምሃል ዞሮ እያየ ሁሉም ሳቁ። ለእናቴ ዛሬ ጓደኞቼ ሊጠይቁኝ እንደሚመጡ ስለነገርኳት ለነሱ እሚሆን አሪፍ ምሳ እያዘጋጀች ነበር በአንድ ወር ውስጥ ከኪያር እና የቅርብ ዘመዶቼ ውጪ ማንም ሊጠይቀኝ የመጣ ሰው አልነበረም ብቸኛ የሆንኩ ያህል ነበር የሚሰማኝ። እናቴ  ልክ ስትወጣ ኪያር ድምፁን ዝግት አድርጎ ዝም አለ እናቴ ሰላም አለቻችው ሰምሃልዬ የኔ ቆንጆ እንዴት ነሽ በደህና መጣችው አይደል አለቻት እናቴ ሰምሃልን በጣም ትወዳታለች ህይወቴን ስላተረፈችልኝ።

አንድ ቀን እንደውም ለምን እሷን አታገባም ቀለበት አድርግላት በጣም ጥሩ ልጅ እኮ ናት ብላኝ በሳቅ ፍርስ ስታረገኝ ነበር እናቴ ጣጣ የለባትም ፈታ ያለች ናት ነገር አታከርም። አይ እማ ጉዴን አላወቀች እንዴት በሌላ ሴት ፍቅር እንደምሰቃይ። ሳሎን ውስጥ ቁጭ ብለን እህቴ ዝንጥ ብላ ከላይ መጣች እኔ ስለገባኝ ከት ብዬ ሳቅኩ መጥታ ሁሉንም ሰላም አለቻቸው እሷ ሰላም ስትላቸው እኔ የኪያርን ሁኔታ እያየው ነበር በመሃል አቅቶኝ ድጋሚ ፍርስ ብዬ ሳቅኩ ሁለትም እንደሚዋደዱ እማውቀው እኔ ብቻ ነኝ ደስ ሲል። እህቴ መጥታ ከኔ አጠገብ ተቀመጠች። ወሬ ለማስጀመር ይመስል ኪያር አንተ በጣም ተስማምቶህ የለ እንዴ ወዝህ መለስ አለ  ዛሬ ደሞ እንዴት ነው በሸበጥ እና ቁምጣ አለኝ እህቴ ስትቅለበለብ ናዲ እኮ እንዲ ነው ቅዳሜና እሁድ ቀለል ያለ ልብስ ነው ሚለብሰው ደሞ እቺን ነጭ ቁምጣ ሲወወወ..ዳት አለችው  ፍጥነቷ አስደንግጧት ዝም ብላ ትንሽ ከቆየች በኃላ እናቴን ላግዛት ለናንተ ዶሮ እየሰራች ነው አለቻቸውና ተነስታ ወጣች።

ልክ እንደወጣች ሊድያ ወደኔ እያየች ደስ እምትል እህት አለችህ አለችኝ እኔም እየሳቅኩ አው ባክሽ እንዲ ናት ብዙ ግዜ ቅልብልብ ናት አሁን 12ኛ ክፍል ናት ያው ስትጨርስ እኛ ጋር ትመጣለች አልኳት ሰአቱ ገና ረፋድ ስለነበር ጨዋታችንን ቀጠልን በጨዋታችን መሃል ወደሰምሃል ዞሬ ኤቤጊያ እንዴት ናት አልኳት ፈገግ እያለች ደና ናት አለችኝ። ርብቃ እንደመቆጣት እያለች የት አናግረሻት እምታውቂውን ነው ደና ናት ምትይው እስካሁን እንደተኮራረፋችው አይደል እንዴ ብላ አፋጠጠቻት። ሁለቱ እየተከራከሩ እያለ በመሃል አቋረጥኳቸውና ሰምሃልን ምን ሆናቹ ነው የተኮራረፋቹት ስላት ዝም አለችኝ ወደ ርብቃ ስዞር እኔ ምን አውቄላት እቺ ዝምብላ ከመሬት ተነስታ ነው የዘጋቻት አለችኝ አይኗን እያጉረጠረጠች። ዝምታው ሲበዛ በቃ የዛኔ አንተን ደባሪ ንግግር ስለተናገረችህ አናዳኝ ነው ያኮረፍኳት አለችኝ።

ይቀጥላል ....

#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመዶ ያጋሩ #share @Qdist
Join and share👇👇
@qdist
@qdist
@qdist
For any question& comment ለማንኛውን
ጥያቄ&አስተያየት @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

08 Dec, 05:47


#ቀን_ሲጥል

ኪያር በእህቴ በኩል መጣና ቆይ ላግዝሽ ሲላት ቦታውን ለሱ ለቀቀችለት እና ወደ እናታችን ጋር ሄደ በስንት ትግል መኪናው ጋር ደረስን ላብ በላብ ሆኛለው አባቴ ቀድሞ በሩን ከፍቶልን ገባን ሰምሃል በጣም ደብሯታል በቃ አትጥፋ እሺ ቤት መጥቼ እጠይቅሃለው እግዜር ይማርህ አለችኝ ምን ማለት እንዳለብኝ አላውቅም በጣም ነው ማመሰግነው ሰሙ አንቺም አትጥፊ እደውልልሻለው ስልክሽን እህቴ ጋር ተዪልኝ እና ሂጂ አልኳት።

ሳቅ እያለች እሺ ብላ ስልኳን ለእህቴ ነግራት ልትሄድ ስትል አባቴ ጠራት ድንግጥ ብላ አቤት ጋሼ አለችው አባቴ እየሳቀ ወደሷ ተጠጋና በጣም ነው እማማሰግንሽ ልጄን ስላዳንሽልኝ ውለታሽን በምን እንደምከፍል ወላውቅም ብቻ... እያለ ወደኪሱ ገብቶ ብር ሊያወጣ ሲል አረ በእግዜር ጋሼ እኔ ምንም አላደረኩም ማንም ሰው እሚያደርገውን ነገር ነው ያደረኩት ምንም ብር አያስፈልግም ጋሼ አልቀበሎትም በእውነት የሰራሁትን ስራ በብር አይቀይሩብኝ አያስፈልግም ብላ እጁን ይዛ አስተወችው በግድ ሊሰጣት ሲል አይሆንም ብላ እየሮጠች ሄደች።

ሁላችን አረ ተቀበይው አልናት እየተሳሳቅን እሷም እየሳቀች አይሆንም እቤት መጥቼ እጠይቅሃለው በቃ ቻው ብላኝ ሄደች አባቴ እየሳቀ ወደመኪናው ገባ እህቴም ከኔና ከኪያር ጋር ከኃላ ተቀመጥን እናቴ ከፊት ገባች ኪያር እቤት አድርሶኝ በዛውም ቤተሰቦቹን አዲስ አበባ ጠይቆ ሊመለስ አስቧል።
መንገዳችንን አቅንተን ከ1፡30 ሰአት ጉዞ በኃላ አዲስ አበባ ቦሌ አከባቢ ደረስን ሰፈራችን ቤት ገባን ይዘውኝ ወጥተው ወደ ሳሎን በኪያር እና በእህቴ እገዛ ገባው ደክሞኝ ስለነበር ሶፋው ላይ ተኛው።

ኪያር እራት ከበላ በኃላ ስለመሸ በግድ ካላደርክ አልኩት እሱም ያው እየደበረው እሺ አለኝ። እንደለመድኩት በእህቴና በእሱ እገዛ ሁለተኛው ፎቅ መኝታ ክፍሌ ላይ በመከራ ይዘውኝ ወጡ እናቴ ከኃላ ተከትላን ገባች አልጋው ላይ ከተኛው በኃላ ምን ላምጣላችው አለችን ምንም እምንፈልገው ነገር አልነበረም እህቴና እናቴ ወጡ። ልክ እነሱ እንደወጡ ኪያር ወደኔ እያፈጠጠ እሺ... የቅባት ልጅ እንደዚ ሲያዩሽ የሸራ ቤት ውስጥ እምትኖር ቦርኮ ነበር ምትመስለው ለማያውቅች እእእ ለካ እንዲ የተጃር ልጅ ነሽ አለኝ እየሳቀ ክፍሉን በአይኖቹ እየቃኝ ሆዴን ቢያመኝም ከት ብዬ ሳቅኩ ባክህ ሃብት ምን ያረጋል ጥቅም የለውም እፕልኩት እሱም እየሳቅ ስላለህ ነዋ ምንም እማይነስልህ አለኝ።

ይልቁንስ እሱን ተወውና ኤቤጊያን አናግርልኝ በናትህ ያው እኔ ሲሻለኝ እመጣለው አልኩት ወሬ ለማስቀየስ ይመስል ኪያር በግርምት እያየኝ ትንሽ አታፍርም እንዴ ቆይ አንተ ሌላው ቢቀር እንኳን ለራስህ ክብር ይኑርህ እንጂ እንደዛ ውሻ አድርጋህ ሄዳ አሁንም ወዳታለው ልትለኝ ባልሆነ እፈር ጌታ...ትን እፈር አንተ የምር አመት ከምናምን ከሰውነት ተራ ወጥተ መርፌ እስክታክል ድረስ ወደሃት ምን ፈየደልህ እእእ ሰድባህ አይደል እንዴ የሄደችው ያውም እንደዚ ሆነህ እያየችህ ለመሆኑ የሰደበችህን ስድብ ራሱ ልብ ብለኀዋል እኔ ላንተ በጣም እየረሰናኝ ነበር  የምር ናኦድ እርሳት በቃ አትበጅህም ተዋት አለኝ ተበሳጨው እንዴት ነው ምረሳር እንዴት ነው እምተዋት ይሄን ሁሉ ግዜ ያቃጠልኩት ላላገኛት ነው እንዴ ... አልረሳትም መሄም አልረሳትም መቼም

ደነፋሁበት ወይ ናዲ እምልህን ስማኝ አተን ሌላ ሴት ጥበስ በቃ እሷን እርሳት እኔ አጣብስሃለው ከፈለክ ሌላ ሴት አንተ ብቻ እሺ በል አለኝ እምቢ አልኩት ኪያር ብርድልብሱን ጎትቶት አኩርፎ ተኛ እኔም እያመመኝ ስለነበር ተኛው።
ሲነጋ ኪያር ወደቤተሰቦቹጋ ሊሄድ በጥዋት ተነሳ ቤተሰቦቼም በስም ስለሚያውቁት አመስግነው ላኩት እህቴ ውጪ ድረስ ሸኝታው መጣች ስትመለስ እየሳቀች ነበር ምነው እላታልው እየተሽኮረመመች ምንም ብላኝ ወደክፍሏ ሄደች። እኔም ቀን ከቀን በቤተሰቦቼ እገዛ ራሴን ማስታመም መጠገን ጀመርኩ ቀናት እያለፉ በሳምንት ተተኩ አራት ወንድማማች ሳምንቶችም በአንድነት ተባብረው ወርን አስቆጠሩ

ይቀጥላል ....

#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመዶ ያጋሩ #share @Qdist
Join and share👇👇
@qdist
@qdist
@qdist
For any question& comment ለማንኛውን
ጥያቄ&አስተያየት @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

07 Dec, 09:21


#ቀን ሲጥል

ጓደኛዬ ኪያር ቅር ቢለውም በአባቴ ትእዛዝ መሰረት እንዳለ ጓዜን በሻንጣ ከግቢያችን ይዞት መጣ። ሻንጣውን ይዞት ላብ በላብ ሆኖ ሲገባ እህቴና ሰምሃል ተቀብለው አገዙት ከሰሙ ጋር ብዙም ሳንተዋወቅ ወደ አዲስ አበባ ልመለስ እንደሆነ ሳስብ ደበረኝ ሰሙም የደብራት ይመስለኛል  ግን ምን ችግር አለው ቀጣይ አመት እመለሳለው ይሄ ሴሚስተር እንደሆነ ገና ሊጋመስ ነው::

ገና ወደቤት ሳልሄድ ይሄ አመት አልቆ  ቀጣይ አመት መጥቶ የኤቤጊያን አይን ድጋሚ እስከማይ ድረስ ቸኮልኩ አረ... እኔማ የሷን አይን ሳላይ ለወራት መቆየት እምችል አይመስለኝም ብቻ ትንሽ ይሻለኝ እንጂ ተመልሼ መምጣቴ አይቀርም ናዝሬት እንደሆን የአንድ ሰአት መንገድ ናት አረ... እመጣለው ቀላል እመጣለው።

አባቴ በእኔ በጣም ተናዷል ዶክተሮቹ ሁሉንም ነገር ነግረውታል ሰክሬ ከሰው ጋር ተጣልቼ እንደሆነ አውቋል አሁን ስለታመምኩ ነው እንጂ ቢጮህብኝ ደስታው ነው ንዴቱ ከፊቱ ያስታውቃል አባቴ በጣም ሃይለኛ ሰው ነው እወደዋለው ግን እፈራዋለው ከልጅነቴ ጀምሮ ሳውቀው በትምህርት ቀልድ አያውቅም ለኔም ለእህቴም ከምንም ነገር በፊት ትምህርታችንን እንድናስቀድም ሁሌም ይመክረን ነበር። ኪያር ያመጣውን ጥቁር ተጎታች ሻንጣ አባቴ ከፈተው ልብሶቹ ከታጠቡ ዘመናት ስላለፋቸው  እሚያስጠላ ሽታ አፈነው ወዲያው እየተገረመ አፍንጫውን ይዞ ዞር ብሎ አየኝና ተመልሶ ሻንጣውን መበርበር ጀመረ::

ድንገት የትምህርት ማስረጃዎቼን እማስቀምጥበት ሰማያዊ ባይንደር ከልብሶቹ መሃል ታየው በጣም ደነገጥኩ ያለፈውን ሴሚስተር ግሬድ ሪፖርት ፊት ለፊት እንዳስቀ መጥኩት በደምብ  አስታውሳለው
ሰማያዊውን ባይንደር አነሳውና ቁጢጥ ብሎ ከተቀመጠበት ቀስ ብሎ ተነሳ የልብ ምቴ ሲፈጥን ይታወቀኛል።

ገልጦ ውስጡ ያሉትን ወረቀቶች ማየት ጀመረ ፊቱ ቀስ በቀስ ወደ ቀይነት ሲቀየር አይኖቹ ተጎልጉለው እስኪወጡ ድረስ ሲፈጡ አየኃቸው በጣም ተበሳጭቶ ባይንደሩን ከደነውና ሻንጣው ላይ እንደነገሩ ጣል አድርጎት ከክፍሉ በፍጥነት ወጣ ያለፈውን ሴሚስተር ምንም አልተማርኩም ፋይናል ፈተናም በአግባቡ አልተፈተንኩም ነበር የከዚቀደሙ ውጤቶቼ አሪፍ ቢሆኑም ያሁኑን ግን ከ2 ነጥብ በታች አምጥቼ በማስጠንቀቂያ ነበር ወደዚኛው ሴሚስተር ያለፍኩት አስተማሪዎቹም ቀድመው ስለሚያውቁኝ እንጂ ኤፍ እንደሚሰጡኝ እርግጠኛ ነበርኩ በብዛት ሲ እና ዲ አምጥቼ በማስጠንቀቂያ ነበር ያለፍኩት አባቴ ይህንን ሲያይ ነበር የተናደደው።

ውጪ ከእናቴ ጋር ሆነው ሲጨቃጨቁ ይሰማኛል። ታናሽ እህቴ ወደኔ ጠጋ ብላ አንተ ምን ሆነህ ነው ልብስህ እንዲ እስኪሆን ድረስ  የማታጥበው በጣም ይሸታል ሌላው ቢያቅትህ እንኳን ላውንደሪ ቤት መስጠት ያቅትሃል ብር አልጎደለህ ለምን እንዲ ትዝረከረካለህ አለችኝ ለራሴ ወላጆቼን ይዛብኝ መጥታለች እዚው ራሴን አስታምሜ እነሱ ምንም ሳያውቁ እንድድን እንዳትነግራቸው ብላት ጭራሽ ይዛቸው መጣች ለምን ይዘሻቸው መጣሽ ብቻሽን ነይ አልነበር ያልኩሽ ብዬ ተቆጣኃት እንዴ እና ታዲያ እስክትሞት እንድጠብቅ ነው ምትፈልገው አለችኝ እሷም መልሳ እየተ ቆጣችኝ።

ሰምሃልና ኪያ ይህንን ሁሉ ድራማ ጥግ ላይ ካሉት ወንበሮች ላይ ተቀምጠው ከማየት ውጪ ምንም ቃል አይተነፍሱም እነሱም ለኔ ጨንቋቸዋል። ከታናሽ እህቴ ጋር እየተከራከርን እያለ አባቴ ከአንዲት ነርስ ጋር ወደውስጥ ገባ እና ወደኪያ እያየ  እእእእ ኪያር እስኪ ሻንጣውን ወደመኪናው አስገባልኝ ብሎ አዘዘው ኪያር ምንም ሳያቅማማ ሻንጣውን ይዞት ወጣ አባቴ ብስጭቱ ጋብ ያለለት ይመስላል ነርሷ አጠገቤ መጥታ ጉሉካሱ የተሰካበትን ገመድ ከእጄ ላይ ነቅላ ማስተካከል ጀመረች እኔም ለመነሳት ስዘገጃጅ እህቴና ሰምሃል መጥተው አግዘውኝ ከአልጋዬ ተነስቼ መሬቱን ረገጥኩ።

አባቴ ከኃላ ሆኖ መድሃኒቶቹን በፊስታል ይዞ ተከተለን እናቴ ከጎን ሆና እንባ እንባ እያላት ከማየት ውጪ ምንም አትልም። እኛ በረንዳው ላይ ቀስ ብለን እየሄድን ኪያር ሻንጣውን የአባቴ መኪና ጌር አድርሶት እየሮጠ ሲመለስ ተገጣጠምን።


ይቀጥላል ....
ስለቆየሁባችሁ በጣም ይቅርታ ጠይቃለው ስላልተመቸኝ ነው 🙏
አሁንም አብሮነታችሁ አይለየን

#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመዶ ያጋሩ #share @Qdist
Join and share👇👇
@qdist
@qdist
@qdist
For any question& comment ለማንኛውን
ጥያቄ&አስተያየት @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

03 Dec, 17:36


#ቀን_ሲጥል

መሬት ላይ ስወድቅ ህመሙ ቢበረታም ከህመሙ በላይ ውስጤ ገብቶ ያሳመመኝ ከኤቤጊያ የወጡት አስነዋሪ ቃላት ነበሩ ውጤን በጣም ተሰማኝ።

ሰምሃል እና ኪያር ሊያረጋጉኝ ቢጥሩም ምንም ለውጥ አልነበረኝም ኪያ ሲቸግረው ሮጦ ሄዶ ዶክተሯን ይዟት መጣና ከወደቅኩበት መሬት አንስተውኝ አልጋው ላይ አስተኙኝ ነርሷ ቁስሉን ድጋሚ አፀዳችው እያፀዳችው ፊቴን በእጄ ሸፍኜ አለቅሳለው። እያስለቀሰኝ የነበረው ህመሙ ሳይሆን የኤቤጊያ ንግግሮች ነበሩ ቁርጥ ቁርጥ እያሉ አእምሮዬ ውስጥ ይመላለሱ ጀመር "እኔ ውደደኝ ሙትልኝ አልኩህ፣ ጀዝባ ሁንልኝ ብዬሃለው እኔና አንተ እኮ አንመጣጠንም ፍቅር ምናምን የሚሉት እንቶፈንቶ አይገባኝም፣ ለመሆኑ ረስህን አይተኽዋል...የኤቤጊያ ድምፅ ራሴን እስኪያመኝ ድረስ አእምሮዬ ውስጥ እያቃጨሉ ነበር። 

ነርሷ ከሄደች በኃላ ሰምሃል ወደኔ መጥታ እጄን እያሻሸችኝ ይቅርታ በጣም ናዲ እንዲ ታደርጋለች ብዬ አልጠበቅኩም ነባር በጣም ይቅርታ ይዣት መምጣት አልነበረብኝም አለች የኔ እንባና ሃዘን እየተጋባባት። ራሴን ለማረጋጋት ሞከርኩ በእንባ የራሰው ፊቴን በመዳፌ እየጠረግኩ። በቃ አታልቅስ አይዞህ እሺ ናዲ እኔ አናግታለው አለ ኪያ እልህ ይዞት።

የተፈጠረውን ነገር ለማስረሳት ይመስል ሰምሃል ወይ ረስቼው ቁርስ አምጥቼላቹሃለው ያው ቤት ያፈራውን አለች  ፈገግ እያለች ያው አንተ ጉሉኮስህን ትጠጣለህ ኪያ ይበላል ባይሆን ስትድን ውጪ ጋብዝሃለው አለችኝ የሰምሃል አባባል ፈገግ አስባለኝ ኪያ እየተጣደፈ በፌስታል ያመጣችውን ምሳቃ ከፍቶ ቶሎ ቶለ ይደፍቅ ጀመር ሁለታችንም የኪያርን አበላል አይተን ተሳሳቅን። ኪያ ሁኔታችንን አይቶ ምን ትገለፍጣለህ ለሊቱን ሙሉ አንተን ስጠብቅ ፃሜን ነው ያደርኩት አለኝ ወደኔ እያየ። ለግዜውም ቢሆን ከኤቤጊያ ጋር የተፈጠረውን ነገር ረሳሁት።

ኪያ በልቶ ከጨረሰ በኃላ ትንሽ እንዳወራን ሰምሃልን ወደውጪ ይዟት ወጣ እሚያወሩት አይሰማኝም ቀስ እያሉ ይንሾካሾካሉ እኔም እሚሉትን ለመስመት ጆሮዬን ወድሬ ለመስማት ጣርኩ። ትንሽ ቆይተው ገቡ ኪያር ወደኔ መጣና በቃ ናዲ ዛሬ ከሰሙ ጋር ትሆናለህ እሺ እኔ programming exam ስላለኝ ልሂድና ላጥና ላንተም አስፈቅድልሃለው የተፈጠረውን ነገር ለጋሽ አሴ እነግራቸዋለው ይፈቅዱልሃል አለኝ እሺታዬን ከሰማ በኃላ ተሰናብቶኝ ሄደ።

ከሰምሃል ጋር ብቻችንን ቀረን ምን እንደማወራት ግራ ገባኝ በመሃል ዶክተሯ መጣችና ዝምታውን ሰበረችው ሁሉንም ነገር አይታ ከጨረሰች በኃላ ዛሬስ ተነስተህ ተራመድክ አለችኝ አይ አልተራመድኩም ስላት ተነስተህ ወክ አድርግ ትንሽ አለችኝና ሄደች። ሰምሃል ልታግዘኝ ተነሳች ከአልጋው ላይ ደግፋኝ ከተነሳው በኃላ እንደትናንቱ ኮሪደሩ ላይ ወክ አድርገን ተመልሰን ገባን። አልጋዬ ላይ ተቀምጬ ስልኬን ሳይ ሚስኮል አገኘው ታላቅ እህቴ ነበረች መልሼ ደወልኩላት ሰላም ከተባባልን በኃላ ትንሽ አውርተን የተፈረውን ነገር ለእናትና አባቴ እንዳትናገር አስጠንቅቂያት ነገርኳት በጣም ደነገጠች አሁኑኑ ተነስታ ወደናዝሬት እንደምትመጣ ነገረችኝና ተሰነባበትን።

አሁንም ከሰምሃል ጋር ምን እንደማወራ ግራ ገባኝ ወሬ ለማስጀመር ያክል እስኪ ስለራስሽ ንገሪኝ አልኳት። ሰሙ ፈገግ እያለች ምን እነግርሃለው ማወቅ የምትፈልገውን ጠይቀኝ አለችኝ። ምን እንደምጠይቃት ግራ ገባኝና ዝም አልኩ። ከሰአታት በኃላ እህቴ እየሮጠች እኔ ወዳለሁበት ክፍል ዘው ብላ ገባች በአንዴ ክፍሉን ወከባ በወከባ አደረገችው ግን እሷ ብቻ አልነበረም የመጣችው እኔትና አባቴም አብረዋት ነበሩ ሲገቡ ሳያቸው ደነገጥኩ እህቴን በቁጣ አየኃት።

ጤንነቴን በደምብ ካረጋገጡ በኃላ ጭቅጭቅ ያዝን ሰምሃል ሁሉንም ነገር ዝም ብላ እያየች ነበር ቅር ያላት ትመስላለች። ከብዙ ጭቅጭቅ በኃላ ትምህርቴን አቁሜ ዊዝድሮው ሞልቼ ወደ አዲስ አበባ እንድመለስ ተወሰነ

ይቀጥላል...

#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመዶ ያጋሩ #share @Qdist
Join and share👇👇
@qdist
@qdist
@qdist
For any question& comment ለማንኛውን
ጥያቄ&አስተያየት @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

01 Dec, 17:39


#ቀን_ሲጥል

ድርቅ ብዬ ቀረው አንዲት መልከመልካም ሴት ከፊቴ ቆማለች ሌላ ማንም የሰው ዘር አይታየኝም አቢጊያ ወደ እኔ መጥታ ስላም ነው። ናኦድ አለችኝ ደንዝዤ ቀረው እጄ ይንቀጠቀጥ ጀመር አቢጊያ ህመሙ መስሏት ደነገጠች ወደ ሰመሀል ዞራ ሰሙ እየተንቀጠቀጠ እኮ ነው እያመመው ነው መሰለኝ አለቻት ሰመሃል ፈጠን ብላ ወደ እኔ መጥታ ምነው ናኦድ ደህና አይደለህም እንዴ አለችኝ ቲንሽ ሰመሃልን ሳይ ተረጋጋው ደ..ደና ነኝ አልኩዋት እራሴን ለማረጋጋት ሞከርኩ ቁና ቁና እየተነፈስኩ ስላም ነው አልኩዋት አቢጊያ ፈገግ እያለች ደህና ነኝ እንዴት ነህ አንተ እየተሸለህ ነው አለችኝ።

እኔ ማመን አልቻልኩም በ ህልሜ በ ህልሜ ነው በውኔ? ምንም ይሁን ምን ከእዚ ህልም መንቃት አልፈለኩም ደህና ነኝ አልኩዋት ዝም አለች እሱዋም ዝም አለች ዝምታው ሲበዛ ኪያር ወንበር
ወደእሱዋ አስጠጋላት ተቀመጭ አላት እሱዋም ወንበሩን ስባ ከአጠገቤ ተቀመጠች ኪያር ከሁዋላዋ ሆኖ ፈገግ እያለ ጠቀሰኝና ሰሙ ነይ ዶክተሩዋን እናናግራት እና እንምጣ ብሎዋት ይዙዋት ሄደ።

ክፍሉ ውስጥ እኔ እና አቢጊያ ብቻ ቀረን ልቤ በጣም ይመታል አይደለም አጠገቤ ሆና ከርቀት ሳያት የምበረግገው አሁን በቅርበት ሆና እያየችኝ ነው ህመሙ ሆኖብኝ ነው እንጂ ጥያት ብሮጥ ምነኛ ደስ ባለኝ ዝም ብዬ በ ሃሳብ መብሰልሰል ቀጠልኩ ዝምታውን ለመስበር ይመስል ወደእኔ ቀና ብላ እያየች ሰመሃል ጥሩ የክላሴ ልጅ ናት ትናት ማታ አግኝታኝ ሁሉንም ነገር ስትነግረኝ ምን… በድነጋጤ አውርታ ሳትጨረስ ነገረችሽ ብዬ ጮክ ብዬ ጠየኩዋት ልቤ ከአፌ ልትወጣ ቲነሽ ቀራት አቢጊያ ደንገጥ እያለች አውው…በጣም ያሳዝናል ህግ ባለበት ሃገር እንደዚ ሲደረግ ያሳዝናል አግባብ አይደለም ምን አይነት ሰውስ ቢሆን ነው እነደዚ አይነት ጨካኝ የሚሆነው ዘመኑ ከፍቱዋል አለችኝ። እፎይ…ይ ተመስገን አልነገረቻተም አልኩ በልቤ ዝም ስል ምነው ዝም አልክ አለችኝ አ..አይ ዝም አላልኩም ቲንሽ ሰው ማናገር ስለሚከብደኝ ነው አልኩዋት እየሳቀች ታፍራለህ እንዴ ስትለኝ ተሽኮረመምኩ ይበለጥ ሳቀች ስትስቅ ደስ ትላለች ጥርሶቹዋ የተፈለቀቀ ጥጥ ነው።

የሚመስሉት ፈጣሪ ጥርሶቹዋን ተጠንቅቆ የደረደራቸው ማራኪ ተፈጥሮ ናቸው በእዚ ቅርበት አይቻት ስለማላውቅ ፍቅሯ በውስጤ ሲጨምር እሱዋነቷ ውበቷ እኔነቴን ሙሉ ለሙሉ ሲቆጣጠረኝ ተሰማኝ ሽቶዋ ደስ የሚል መአዛ አለው በግድ አፍንጫዬን ከፍቶ ልግባ ይላል በቃ ሞኝ ሆንኩ እራሴን መቆጣጠር አቃተኝ በደስታ ይሁን በሃዘን ስሜት አላውቅም ማልቀስ ጀመርኩ ውስጤ ባይፈለገውም መቆጣጠር አልቻልኩም ምነው አለችኝ ድንገት ያለፉትን ሁለት አመታት እንዴት እንዴት ሆኝ እንዳሳለፍኩዋቸው አይኔ ላይ ውል አለ ይበልጥ ተከፋው ኤቢ ከእዚ በላይ አፍኜው መቆየት አልችልም ይበቃኛል ልፈነዳ ነው እኔ ባነቺ ምክንያት ብዙ ተሰቃየው እኔ ካየውሽ ቀን ጀምሮ በጣም ነው የወደድኩሽ አምና መስከረም 24 ቀን እናተ ፍሬሽ ሆናችው ወደ ግቢ ስትመጡ ሻንጣሽን እየጎተትሽ ስትገቢ እኔ ደሞ ስወጣ ነበር ያየውሽ እኔ በቃ አልችለም ከእዚ በላይ በፍቅር መቀጣት አልችልም አልችልም አልችልም ባንቺ ምክንያት ትምህርቴን ተውኩ ጎብዝ ተማሪ ነበርኩ ያውም የባቻችን ሰቃይ አሁን ግን ጀዝባ ነኝ ሞሮ…ጉዋደኞቼ ሸሹኝ ሁሉም እራቁኝ አንቺን እንደምውድሽ ግቢው በሙሉ ያውቃል
አንቺ ግን አይደለም እንደምውድሽ ቀርቶ ምን አይነት ስው እንደሆንኩ እራሱ አታውቂም…በቃ በቃ በቃ ብላ ተቆጣች እኔም መነፋረቄን ለጊዜም ቢሆን
ገታውት ደነገጥኩ እኔ ሙትልኝ ውደደኝ ጀዝባ ሁንልኝ ብዬሃለው እንዴ ምን አይነት ወሬ ነው የምታወራው በእራሰህ ስንፍና እኔን ጥፋተኛ ታረጋኛለህ እንዴ እኔ እና አንተ እኮ አንመጣጠንም ለመሆኑ እራስህን አይተውሃል አለችኝ ቅፍፍ እያልኩዋት ፍቅር ምናምን የሚባለው እንቶ ፈንቶ አይገባኝም እሺ ሃ..ሃ ሃ.ሃ…ሃ ይውጣልህ ብላኝ የምጸት ሳቅ እየሳቀች ከተቀመጠችበት እየተገላመጠች ተነሳች።

እያመመኝ እየንተጠራራው እጇን ያዝኳት አቢጊያ እባክሽ አትሂጂ ስላት
እጀዋን መንጭቃ ሄደች ልከተላት ከአልጋው ላይ እየንተጠራራው ስነሳ ከአልጋው ላይ ወደኩ ይበልጥ አመመኝ ወደኋላ ዞር ብላ አየችኝና ወጣች አቢጊያ እንደዚ አይነት መልስ ትሰጠኛለች ብዬ ነበር እሺ ልትል እንደማትችል ገምቼ ነበር ግን እንደዚ ውጪ ከሰመሃል ጋር ተገጣጠሙ መሰለኝ ወዴት ነው ስትላት ሰማሁኝ አቢጊያ በጣም እየበሸቀች ለእዚ ነው የጠራሽኝ ዘመዴ ነው ምናምን ብለሽ ከዚ ጀዝባ ጋር ልታጣብሺኝ ነበር ያመጣሽኝ በጣም ነው የማዝነው ብላ ስትሄድ የጫማዋ ዳና ተሰማኝ ኪያር ወደ ክፍሉ ሲገባ መሬት ላይ ወድቄ ደም እንባ እያለቀስኩ ነበር ደንግጦ ናዲ…ምነው ብሎ ቀና አደረገኝ ሰመሃልም ስትገባ አየችኝ ጩኀቷን አቀለጠችው ወለሉ በደም እየራሰ ነበር  
 ይቀጥላል
...

#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመዶ ያጋሩ #share @Qdist
Join and share👇👇
@qdist
@qdist
@qdist
For any question& comment ለማንኛውን
ጥያቄ&አስተያየት @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

30 Nov, 20:08


#ከልቤ

ለምን አትበለኝ ምክንያት የለኝም
ፍቅር ስሜት እንጂ ሰበብ አይመስለኝም
ብቻ አፈቅርሀለሁ ማፍቀሬ ጥልቅ ነዉ
ፍቅርህ ለኔነቴ የልቤ ዙፍን ነዉ
ህያዉ የሚሆነዉ አንተን በማፍቀር ነዉ

ጅልነት አይደለም ሁሌ አንተን ማለቴ
ሞኝነት አይሆንም በፍቅርክ መክሳቴ
ዉለታ ፈልጌ ዉደደኝ አላልኩም
ፍቅር ሰጠሁ እንጂ ምላሽ አልፈለኩም
በቃ አፈቅርሀለሁ ማለቴን አልተዉኩም

አዎ እወድሀለሁ አዎ አፈቅርሀለሁ
ፍቅርቅር አድርጌህ ሁሌም እኖራለሁ
አንተን በማፍቀሬ እፎይታ አገኛለሁ
አንተን እያፈቀርኩ በደስታ እኖራለሁ
አንተ ካለህልኝ ሙሉ ሰዉ እሆናለሁ
ከኔ እፎይታ ያንተን ደስታ አስበልጣለሁ
ጉዳትክን ከማይ የኔ ልብ
ይጨነቅ ተወዉ ብዬሀለሁ😢

@saktawocu
@saktawocu

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

29 Nov, 16:29


#ቀን_ሲጥል
ክፍል 8

ሰመሃል ለሊቱን ሙሉ ስጠብቀኝ ስላደረች ደክሙዋታል የሷ ጉዋደኞች ለኔ ምን ማደረግ እንደሚገባቸው ሊጠይቁ ወጡ ኪያርም ዶክተሩዋ ጋር ነው እኔ እና በመሃል ብቻ ቀረን ቅድም ያልኩትን አስታውሳ በምን የተነሳ ጸብ ነው ከእሱ ጋር የተጣሀው ብላ ጠየቀችኝ መናገር አልፈለኩም ነበር ግን መልካምነቱዋ ለእኔ ያረገቻቸው ነገሮች እንድናገራት አስገደደኝ። ከመጀመሪያው ሁሉነም ነገንም ነገሮች ስለ አቢጊያ እንዴት እንደማፈቅራት ለእሱዋ ስል ሁሉንም ነገሮች እንደተውኩ እንባዬ መጣ አይገርምሽም በጣም እፈራታለው እስከዛሬ እንደማፈቅራት ቀርቶ ማን እንደሆንኩ እራሱ አታውቅም. ስለሱዋ ያለኝን ነገር ሁሉንም ነገርኩዋት ከ እዛም እነዴት እራስታው ልጅ ከ እሱዋ ጋር እንደሆነ ሺሻ ቤት መጥተው ምን እንደተናገረ ከእዛ እነዴት እንደተጣላን ማታ ላይ ጉዋደኞቹ እነዴት እንደ ደበደቡኝና እንደዚ ጉዳት እንዳደረሱብኝ ነገርኩዋት ሰመሃል ዝም ብላ ከመስማት ውጪ ምንም አትናገርም ነበር ኪያርና የእሱዋ ጉዋደኞች ሲመጡ ድምጻቸውን ሰምታ እያለቀስኩ የነበረውን ማንም እንዳያውቅ እያባበሰችኝ በልብሱዋ እንባዬን አበሰችልኝ።

እነ ኪያር እየተሳሳቁ እየተንጫጩ ገቡ እሺ ምን ተባላችው አለቻቸው ሰመሃል አጠገቤ እንደተቀመጠች ኪያር ከት ብሎ እየሳቀ ፍሳሳሳ…ተብለሃል አለኝ ምን አለችው ሰመሃል እየሳቀች ፈስህ ቢመጣ ሰው አለ የለም ብለህ እንዳታፍነው ፍሳ ተብለሃል ከቅድሙ ይበልጥ እየሳቀ ሴቶቹም አብረው ሳቁ እኔ ቲንሽ ስስቅ ሆዴን አካባቢ አመመኝና ሳቁን ትቼ ፈገግ አልኩኝ። ሰመሃል እየሳቀች ሌላስ አለችው ሌላ ብዙም አይደለም የተወጋው ብዙም
ስላለሆነ መጠነኛ ጉዳት ነው የደረሰበት በቅርቡ ወደ ሙሉ ጤንነትህ ትመለሳለህ አይዞህ አለኝ።

ቲንሽ ጨዋታ ከተጫወትን በሁዋላ እነ ሰመሃል ለመሄድ ተነሱ ሁለት ቀን እንቅለፍ አጥተው እኔን ሲጠብቁኝ ነበር። ድካማቸው በጣም ያስታውቃል ሰመሃል ቀደም አለችና በቃ እኛ እንሂድና እረፍት
እናደርግ ደካክሞናል ነገ እንመለሳለን አይዞህ ናኦድ ትድናለህ አለችኝ እነሱም እሱዋን ተከትለው አውሩ. ሊሄዱ እንደሆን ሳውቅ ቅር አለኝ በጣም አመሰግናለው ምን ማለት እንዳለብኝ አላውቅም ማነም ሰው እንዲህ አድረጎልኝ አያውቅም ሲሻለኝ በሰፊው እክሳቸዋለው አልኩዋቸው እሺ ብለወኝ እየተሰናበቱኝ ወጡ በር ላይ ሰመሃል ኪያርን ጠራችወና አንዳድ ነገሮች አውርታው ሄደች ኪያር ፈገግ እያለ ተመለሰ ምን ብላህ ነው አልኩት አይ ምንም አላለችኝም ስልኩዋን
ተቀብዬልሃለው ደግሞ ከፈለክ አለኝ እሺ አልኩኝ።

#ሰአቱ እየመሸ ሲሄድ ኪያር ወደ
ዶርም ደውሎ የተፈጠረው ነገራቸው በዛውም ሲመጡ ለመደበሪያ ላፕቶፑን
ይዘውለት እንዲመጡ ጠየቃቸው. ከአንድ ሰአት በሁዋላ የዶርሜ ልጆች ከማእላፍና መልካሙ ውጪ ሁሉም ዝንጥ ብለዋል ላፕቶፑን ሰጡኝና እእ ሞሮ ሰላም ነው ምን ሆንክ አሉኝ። በጣም ተናደድኩ እኔን ለመጠየቅ እንዳልመጡ ያስታውቅባቸዋል ዝንጥ ብለው በእዛው ኦቨር ሊውጡ ነው እየተንጫጩ ከተቀመጡበት አምሰት ደቂቃ እንኩዋን ሳይሞላቸው እንሂድ ምናምን ሲንሸኩዋሸኩ ሰማዋቸው በቃ ናኦዴ እግዜር ይማርህ ብለው ተፈትልከው ወጡ. ኪያር ተናዶ ሁለተኛ እንዳላያችው እናተን ብሎ ጉዋደኛ አስመሳይ ብሎ ተጣላቸው እኔ እንዳውም ምንም አልመሰለኘም እንዲያውም ሲሄዱ ንዴቴ ለቀቀኝ።

እነሱ እንደወጡ ማእላፍና መልኬ ሙዝ ማንጎ ጁስ ይዘው ከተፍ አሉ። በርግጥ ማእላፍ በጣም ተናቋሪ ቢሆንመም ቁምነገረኛነቱም በዛው ልክ ነው።ሁለቱም ደንግጠው ገቡ አሁን ገና ከዶርሜ ልጆች ትክክለኛ ጠያቂ አገኘው አልኩ በልቤ...መልኬ በጣም የምወደው የክላሴ ተማሪ ነው። ፍሬሽ ላይ ከመምህር ጋር ተጋጭቶ አፕላይድ F መጥቶበት ላለፉት 3ት አመታት Add ሲያደርግ ከርሞ ዘንድሮ ወደ 3ኛ አመት ትመለሳለክ ብለውት Force withdrawal አስሞልተውታል። ፅናቱ ሚገርምና ሚደንቅ ልጅ ነው አንድም ቀን አስቀይሞኝ አያውቅም።  ሁለቱም እዚው ካላደርን ቢሉም አይሆንም  ኪያር ብቻ በቂ ነው ብዬ ሸኘሗቸው። ከኪያር ጋር ምሽቱን ቲነሽ ፊልም አይቼ ተኛው.ጠዋት ከ እንቅልፌ ስነሳ ሰመሃል አጠገቤ መጥታ ቆማለች ጉዋደኞቹዋ አልነበሩም ብቻዋን ነበር የመጣችው።

ስላም ነው እንደምን አደርክ አለችኝ ደስ የሚል ፈገግታ እየለገሰችኝ። ደሀና ነኝ አልኩዋት በጣም እየተደሰተች አንድ ሰው እንዲጠይቅህ ይዤልህ መጥቻለው እየጉዋጉዋሁ ማን ሊሆን እንደሚችል እያሰላስለኩ ማን ነው አልኩዋት አቢጊያ ግቢ አለች ጮክ ብላ በውኔ ይሁን በእንቅልፍ ልቤ መለየት አቃተኝ አቢጊያ ስትል ልቤ እንደከበሮ ምት ድም ድም ይል ነበር በፍጥነት ይመታል እውነት ይዛት መታ ነው። አንዲት ሴት ወደ ውስጥ
ገባች አዎ እራሱዋ ናት አቢጊ...
 ይቀጥላል
...


#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመዶ ያጋሩ #share @Qdist
Join and share👇👇
@qdist
@qdist
@qdist
For any question& comment ለማንኛውን
ጥያቄ&አስተያየት @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

28 Nov, 16:13


#ቀን_ሲጥል


ወደ ክፍሉ እየገባን ስለሱዋ እጠይቃት ጀመር እሱዋም በትህትና ያለመሰላችት ትመልስልኛለች ያው እንግዲ ስሜ ሰመሃል ይባላል ተወልጄ ያደኩት እዚው ናዝሬት ነው 3ተኛ አመት የኬሚካል እንጂነሪንግ ተማሪ ነኝ አዳማ ዩንቨርሲቲ ሌላ ምን ልንገርህ እያለች ማሰላሰል ጀመረች እንዲ እያሰብች እያለ ናኦድ ብሎ የሆነ ድምጽ ሃል ቃል ሲጠራኝ ስዞር ኪያር ነው። በጣም ደንግጡዋል ሰመሃል ስትነግረው እንዳይደናገጥ ብላ ቀለል አድርጋ ስለነገረችው ብዙም አልመሰለውም ነበር. አንተ ምንድነወ የሆንከው አለኝ።

እየተቆጣኝ አይ ምንም አልሆንኩም ትላለህ እንዴ ፊትህ የተቀቀለ ባቄላ መስሎ አለኝ ካጠገብ መስታወት ነበር ዞር ብዬ አየውት በጣም አብጡዋል ጠቁሩዋል ብዙ ነገር ሆኑዋል በጣም ደነገጥኩ ለእራሴ ኪያ ስልኩን አውጥቶ መነካካት ጀመረ ምን ሊያደርግ እንደሆነ አልጠፋኝም ማን ጋር የምትደውለው አልኩት ቆጣ ብዬ እሱም ከእኔ ቁጣ የበለጠ እየተቆጣ ጋሼ ጋርነዋ ትቀልዳለህ እነዴ እንዲ ሆነህ ዝም የምል ይመስልሃል አንዴ ይምጡና እዛው ሸገር ወስደውህ እቤት ሆነህ ታከም አለ። ተናደድኩ ስልኩን ዝጋው ኪያ እንጣላለን የምር እምዬን ነው የምለህ ዘጋውና እሺ ምን ልትሆን ነው እዚ አለኝ እኔም አላውቅም አልኩት በመሃል ፋታ ሲያገኝ ሰመሃል ፈጠን ብላ ወደ ክፍሉ እንግባ አለቺኝ አአአ እሺ አልኩዋት መንቀሳቀስ ጀመርን ኪያም መጥቶ በጎን ደግፎኝ እየሄድን እያለ ይቅርታ በጣም እናት ሰላም ሳልልሽ ወደ ቁጣ ዝም ብዬ ገባው አይደል አላት።

ሳቅ እያለ እሱዋም ሳቅ እያለች አይ ችግር የለውም ያው ጉዋደኛህ አይደል ይገባኛል አለችው ቲንሽ ተሳስቀው ዝም አሉ እኔም በሁለት አጋዥ እየተደገፍኩ ወደ ክፍሉ ገባው ሁለቱ ሴቶች እየተሳሳቁ እያወሩ ነበር እኔ ስገባ ወዲያውኑ ዝም አሉ ግራ የሚያጋቡ ልጆች ናቸው እኔን አልጋዬ ላይ ደግፈው እንደነበርኩት ካስተኙኝ በሁዋላ ሰመሃል ምንም ቅር ሳይላት ያላበኝን በልብሱዋ ጠረገችልኝ ይህንን ኪያ በግርምት ያያል ቲነሽ ቆይቶ እሱዋን መጠየቅ ጀመረ እኔ እንደማልነግርው አውቆ ምን ሆኖ ነው አላት እኔጃ ብቻ ትናት ማታ ወድ ግቢ ከቤተክርስቲያን ስመለስ ግቢ አካባቢ አስፓልት ላይ በጩቤ ተወ… ኪያ አላስጨረሳትም በጩቤ ብሎ ቀወጠውና እኔ እና እሱዋን በየተራ እያየ ቀጠለችለት ዐዎ በጩቤ ተወግቶ ተደብድቦ መንገድ ዳር ወድቆ አገኘውት እኔም እየጨህኩ መኪና አስቁሜ ወደዚ አመጣውት ጉዋደኞቼ ጠርቻቸው እዚሁ አብረን እየጠበቅነው አደርን ይመስለኛል ሌቦች ተተናኩለውት ነው። አለችው ሁሉንም ነገር ባውቀውም ከእሱዋ አንደበት ስሰማው ተገረምኩ።

#ኪያር በጣም ተናዶ አንተ ጀዝባ ምን አይተውብህ ነው እንደዚ ያደረጉህ ብሎ ተቆጣ ሁለቱ ልጅ አገረዶች ኪያርን ፈርተውት ሊሞቱ ነው ሰመሃልም ደንግጣለች እኔ ግን የ ኪያርን ባህሪ ስለማውቀው ምንም አልመሰለኝም ሌቦቹ አይደሉም የትናቱ ራስታ ልጅ የሱ ጉዋደኞች ናቸው እነማ ብሎ በድጋሚ ጮሀ እልህ የያዘው ይመስላል እጁን ጭምቅ አድርጎ ይዞታል ወይኔ ላግኘው ብሎ ዛተበት እና ቲንሽ መለስ እያለ እና
አሁን ደሀና ነህ ምን እየተሰማህ ነው አለኝ? ደሀና ነኝ ቲንሽ ህመም አለው እንጂ ምንም አልልም አልኩት ፊቱን ከእኔ አንስቶ ወደ ሰመሃል እያዞረ ዶክተሮቹ የት
ናቸው ላናገራቸው አላት ነገረችውና ፈጠን ብሎ ወጣ. ወከባና ቁጣ የበዛበት
ክፍል ባንዴ ጸጥ ረጭ አለ።

በመሃልም ይሄን ዝምታ ለመስበር ይመስላልጉዋደኛህ በጣም ይቆጣል አለችኝ የ ኪያርን ባህሪ አስታውሼ ቲንሽ ፈገግ አልኩኝ። ባክሽ አፉ ብቻ ነው ልቡ በጣም ሚስኪን ነው እንደምታይው ኮስታራ አይደለም ደስ የሚል ተግባቢ ልጅ ነው አትፍሪው አልኩዋት እሱዋም ፈገግታዬ ተጋብቶባት እየሳቀች እሺ አለችኝ። ጠማኝ አልኩዋት አንጀት በሚበላ ድምጽ ውይ እሺ ላምጣለህ ብላ ልትሄድ ስትል አንደኛዋ ልጅ አረ ኦፕሬሽን ያደረገ ሰው ውሃ አይጠጣም ሌላ ነገር ካልሆነ እንጂ ቁስሉ ይፈታል ካላመንሽኝ ዶክተሩዋን ጠይቂያት ወደ ሆድና ልብ ኦፕሬሽን ካደረጉ ለሳምነት ውሃ አትተጪም አባባ ኦፕሬሽን ያደረገ ጊዜ እንደዛ ነበር ያሉት አለቻት እንደዛ ስትል ይበልጥ ውሃ ጠማኝ 
  ይቀጥላል...

#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመዶ ያጋሩ #share @Qdist
Join and share👇👇
@qdist
@qdist
@qdist
For any question& comment ለማንኛውን
ጥያቄ&አስተያየት @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

27 Nov, 16:38


#ቀን_ሲጥል

ዳግም አይኔ ሲከፈት እዛ አስቀያሚ ሰው አልባ አስፓልት ላይ አልነበርኩም ሙሉ
ሰውነቴን ይጠዘጥዘኛል ይተፈጠረውን ነገር አንድ በ አንድ አስታውሳለው ማን
እንደበደበኝ ማን እንደወጋኝ ማነ ሊረዳኝ እንደመጣ ሰክሬ ቢሆንም አስታውሳለሁ
ናኦድ ነቃህ አለቺኝ አንድ ቀጠን ያለ ድምጽ ባለነጠለዋ ልጅ ነበረች ድምጻን ወደሰማውብት አቅጣጫ ተገላመጥኩ ጥግ ላይ የሚገኝ የ ታማሚዎች አልጋ
ላይ 3 ሴቶች ተቀምጠው በጭንቀት እያዩኝ ነውእኔን ያዳነችኝ ባለነጠለዋ ልጅ በአይኔ ፈለኩ መሃል ላይ ተቀምጣለች ወደ እሳ እያየው የት ነው ያለውት አልኩዋት።

ድምጼ በጣም እንደተዳከመ ይታወቀኛል አፌን በጣም መረረኘኝ አዳማ ጀነራል ሆስፒታል ነህ እንዴት ነህ አሁን ህመም ምናምን እየተሰማህ ወይስ ብላ የጀመረችውን ሳትጨርስ ዝም አለች እኔጃ አላቅም ምን እየተሰማኝ እንደሆነ እራሱ ማወቅ አልቻልኩም ኪያር የታለ ብዬ ጠየኩዋት ኪያር ማነው ብላ ጠየቀችኝ ኪያር የቅርብ ጉደኛዬ ነው ስልኬ ካለ አውጪና ኪዩ ብለሽ ፈልግሽ ደውለሸ ጥሪልኝ እባክሽ አልኩዋት እሺ አለችኝና ከ ቦርሳዋ ውስጥ የኔን ስልክ አወጣችና መነካካት ጀመረች እሱዋ ስልኩን ጆሮዋ ላይ አድርጋ ጥሪ ስትጠባበቅ እኔ ጎኑዋ ያሉ ልጆችን ልብ ብይ ማየት ጀመርኩኝ ከዚ በፊት ግቢያችን ውስጥ በአይን አቃችዋለው በደንብ ባይሆንም በ አይን አቃችዋለው ድንገት ሄሎ ኪያር አለቸው ጥያቄ በሚመስል መልክ አዎ አላት መሰለኘ ስላም እንደምነህ ሰመሃል እባላለው አለችውና የተወሰነ ሰከንድ ልትመጣለት ትችላለህ በተረጋጋ መንፈስ ቀለል አድርጋ ነገርችው ኤይደለም ኪያርን እኔንም ቀልል ያለ ነገር እንደሆነ ገመትኩ ድምጹን ላውድ ላ ይ አደርችውና ኪያ መንጫጫት ጀምረ አይ ናኦድ እንዳው ምንድነው የሚሻልህ ይሄኔ አምፑላህን ስትጋት አድረህ ነው አሁን ጨጉዋራዬ የምትለው አንት ሞሮ ትሰማኛለህ የት ነህ ለመሆኑ ምንህን ነው ያመመህ አንተ ጅዝባ አለ ኪያ እኔ ክፋት እንድሌለበት ባውቅም እሱዋ ግን ድምጹ ላውድ ስለሆነ ደነገጠች።

የተበታተነ ሃሳብዋን ስብስብ አድርጋ ለኔ መሸፋፈን ሞከረች ውይ እንደዛ አይደለም አይደለም ከቻልክ መጥተህ አብረሀው ሁን አዳማ ጀነራል ሆስፒታል ቁጥር 130 አለችው ነገሩን ለመቁዋጨት የፈለገች ይመስል እሺ እመጣለው እስከዛ በደንብ ተንከባከቢልኝአላት ስልኩን ዘጋው ወደኔ እያየች ይመጣል እሺ አይዞህ አለቺኝ. ሁለቱ ሴቶች ጉዋደኞቹዋ አሁንም እንደተለጎሙ ነው ዘምታቸው ቲንሽ ግራ ያጋባል ዝምታ በክፍሉ ሞላ አእኔም ጭጭ እነሱም ጭጭ ቲንሽ ቆይቶ አንዲት በእድሜ ግፋ ያለች ሴት ነጭ ጋውን ለብሳ ወደ ክፍሉ ዘው ብላ ገባች እንዴት ነህ አሁን? አለችኝ። ደህና ነኝ እግዜር ይመስገን አልኩዋት ተዛማች የሆኑ ጥያቄዎች ጠየቀችኝና ተነሳች በረንዳው ላይ መረማመድ እነደጀምር ነገረችኝና ሄደች። ከአልጋዬ መነሳት ስጣጣር ሰመሃል አይታኝ ደግፋኝ ቀና እያደረገችኝ እያመመኝ ተነሳው ቁስሉ ጠባሳ ሲሆን ቀጥ ብዬ መሆን አለበት በግድ እያመመኝ ቀና ቀና አልኩ ልቤ በፍጥነት ይመታል ድክምክም ብሎኛል ሰመሀልን ተደግፌ መራመድ ጀመርኩ።

ሰመሀል ታበረታታኛለች ቀስ እያልን እየተረማመድን ከክፍሉ ወጥተን ኮሊደሩ ላይ መራመድ ቀጠልን። የኮሊደሩ ጥግ የአመት ያህል እራቀብኝ ዶክተሩዋ ያለችህን ሰምተህ የል በል ቀስ አይዞሀ በርታ በል በጣም ደከመኝ ላብ በላብ ሆነኩ ሰመሃል ምንም ቅር ሳይላት በልብሱዋ ትጠርግልኛለች ሰመሃል ብዬ ጠራዋት ደንገጥ ብላ  አቤት አለችኝ. ምን አይተሸብኝ ነው ግን ይህንን ሁሉ ደግነት ለኔ ያሳሽኝ እኔ ኮ ለምንም የማልጠቅም ሞሮ እኮ ነኝ ቆጣ እያለች የሰው ዘር በ ሙሉ አንድ ነው እርዳታዬ ለሚያስፈልገው ሰው ሁሉ እጄን እዘረጋለው መልካም መሆን ለራስ ነው አለችኝ እሺ ብዬ እንደኤሊ እየተጎተትኩ መራመዴን ቀጠልኩ ግን ምን በጣም የምትገርም ልጅ ናት በውሰጤ ስለሱዋ ማሰላሰል ጀመርኩ ምን አይነት ሰው ናት ይህን ያህል ድረስ…የኮሪደሩ ጥግ
ደርስን ወደሁዋላ መመለስ ጀመርን።
ይቀጥላል

#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመዶ ያጋሩ #share @Qdist
Join and share👉
@Qdist
@Qdist
@Qdist
For any question& comment ለማንኛውን
ጥያቄ&አስተያየት @E_T_L_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

25 Nov, 17:14


#ቀን ሲጥል
        ክፍል 4

ልቤ በጣም ይመታ ጀመር ከኤቤጊያ ጋር ያለው ራስታ ፀጉር ወንድ እጁን ቀስ ብሎ ወገቧ ላይ. ጣል አረገው እሷም ወደሱ ተጠግታ እቅፉ ውስጥ ገባች በልቤ የአጎቷ ልጅ እንዲሆን ፀለይኩ እኔና ኪያር እሚሆነውን ነገር በፅሞና እያየን ነው እኛ እናያታለን እሷ ግን አታየንም። ራስታው ልጅ ወደጆሮዋ እየተጠጋ የሆነ ነገር ያንሾካሹካል እሷ በሳቅ ትፈርሳለች ልቤ ይቃጠላል ልጁን ጠላሁት  ቀጥሎ ቀስ እያለ ፀጉሯን በእጁ ይጠቀልለው ጀመር። ወደ ኪያ  ዞሬ እየተበሳጨው ይሄንን ራስታ ታቀዋለህ ምኗ ነው አለኝ ኪያ ራሱን በአሉታ ነቀነቀ። ራስታው ልጅ ጅንን ብሎ እያዋራት እያለ ኤቤጊያ ድንገት ከንፈሩን ስትስመው አየው።

ከዚ በላይ መቀመጥ አልቻልኩም ተነስቼ እየሮጥኩ ስሄድ ኪያ ናዲ ብሎ ሲጠራኝ ልሰማው አልፈቀድኩም እነኤቤጊያም መሳሳማቸውን አቁመው አዩን ወዱያው ከአከባቢው ጠፋው ጨለማ ውስጥ ብቻዬን ቁጭ ብዬ እንደጉድ ተነፋረቅኩ ሁሉም ነገር አስጠላኝ በዚ አለም ላይ ትልቁ ህመም የሚወዱት ሰው ሌላ ሰው ሲወድ ማየት ነው ቅስሜ ተሰበረ እንደዛ ሆኜ ወደ ዶርም መመለስ አልፈለኩም ከግቢ ወጣው።

ከግቢያችን ፊትለፊት የሚገኘው የሓና ባርና ሬስቶራንት ሄጄ ሙሉ ኮኛክ አውርጄ አንጀቴ እየተቃጠለ ገለበጥኩት ሙሉ ሰውነቴ ሲደነዝዝ ቀስበቀስ ይሰማኛል እኩለ ለሊት ላይ ጠርሙሴን ይዤ እየተንገዳገድኩ ወጣው ሁሌም ከራሴ መደበቅ ስፈልግ እምሄድባት ሺሻ ቤት አመራው ቤቷ ባለሁለት ክፍል ሆና በብዙ ጀዝባዎች ታጭቃለች የሺሻው የሲጋራው የጋንጃው የአጠፋሪሱ ጭስ ማንንም ከማንም እንዳይተያይ የጋረደው ይመስላል በዛ ላይ በዛ ለሊት በደብዛዛ  መብራት ጭሱም ተደምሮ ለመተያይተ ከባድ ነው። እየተንገዳገድኩ  ገብቼ ባዶ ፍራሽ ላይ ተቀመጥኩ ቤቷ በዝምታ ተውጣለች ሁሉም በየራሱ አለም ይማትታል ትንሽ እንደተቀመጥኩ ገራቢዋ መጥታ ምን ላምጣልህ አለችኝ የተለመደውን አልኳት የገለምሶ ጫትና ሺሻዬን ይዛልኝ ከተፍ አለች እያፈራረቅኩ እየነፋው እዛው ተኛው።

ጠዋት ላይ ከፍተኛ ሁካታ ሰምቼ ደንግጬ ተነሳው ቤቷ ፀጥ ብላለች ማንም የለም ከውጪ አንድ አራት ወንዶች እየተንጫጩ ወከባ እየፈጠሩ ገቡ ከነሱ ውስጥ ትናንት ማታ ከኤቤጊያ ጋር የነበረው ራስታ ልጅ ነበር ገብተው እየተንጫጩ ፊትለፊት ተቀመጡ ደንዤ ስለነበር የልጆቹን ማንነት መለየት አልቻልኩም ዝም ብዬ ለሊት የጀመርኩትን ጫት መቃም ቀጠልኩ ልጁ እንዲው ለአይኔ ቀፎኛል አስጠልቶኛል ትንሽ እየተንጫጩ በሃላ ሺሻቸውን እየነፉ በመሃል አንደኛው እእእእ እንዴት ነበረች ኤቤጊያ ትናንት ማታ እ ሸራ ስትጓተች አለው ስሟ ሲነሳ ድንግጥ አልኩ ራስታው ልጅ ጅንን ብሎ የሳበውን ጭስ ሽቅብ እየለቀቀ ባክህ ተዋት ምንም አትልም አለው ልጁም ቀበል አድርጎ አረ ... ኤቢን የመሰልች ልጅ አጊንተህማ ሲለው ባክህ ከሌሎቹ አትለይም ተራ ሴት ናት ሲል ደሜ ፈላ ድንገት ከተቀመጥኩበት ብድግ አልኩና ተራ ሴት አይደለችም እሺ...!! ብዬ ጮህኩበት።

ሁሉም ሳያስቡት ስለጮህኩ ደነገጡ ራስታው ልጅ ከደነገጠ በኃላ መሳቅ ጀመረ ድጋሚ ሺሻውን እየማገ ጭሱን  ወደላይ እየተፋ ሃ..ሃ..ሃ..ሃ.. የት ታቃታለህ ምን ያገባሃል ስለሷ አለኝ በንዴት በቆምኩበት የሺሻውን እቃ አነሳሁት ሁሉም ከመቀፅበት ብድግ ብድግ አለና  ምን ልትሆን ነው? እእእ ምን ልትሆነው አሉ ለመደባደብ እየተዘጋጁ ሁሉም ቢያቅቱኝም ራስታውን ልጅ እንደምፈነክተው እርግጠኛ ነበርኩ ንዴቴ ረገብ አለልኝና የሺሻውን እቃ አስቀመጥኩና ወደበሩ አመራው እነሱም እየተሳሳቁ ተቀመጡ የማን ድምፅ እንደሆን ባላቅም "ሞሮ" አለኝ ወደበሩ ከዞርኩበት በመቀፅበት ተመልሼ የሺሻውን ጠርሙስ የራስታው ልጅx አናት ላይ በተቀመጠበት ከሰከሱበት ድብድብ ተጀመረ ቤቷ በአንድ እግሯ ቆመች።


ክፍል 5 ይቀጥላል ..


#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመዶ ያጋሩ #share @Qdist
Join and share👉
@Qdist
@Qdist
@Qdist
For any question& comment ለማንኛውን
ጥያቄ&አስተያየት @E_T_L_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

25 Nov, 10:50


Join & share us 👇👇
@etl_1
@etl_1

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

24 Nov, 15:18


ሶስተኛው የዓለም ጦርነት
ክፍል_ሁለት

ከጠዋቱ ሶስት ሰዓት እንደ ሆነ ሲያውቅ እንደ ስራ አስኪያጅነቱ ስብሰባ ጠራ-የሞሳድ መሪው ፊንሐንስ።
ሁሉንም ከስራቸው ሰብስቦዋቸው የስብሰባውን ርዕስ አስተዋወቀ።
"... እንግዲህ..."አለ ጉሮሮውን እንደ መጠራረግ ብሎ።

"...አሁን አንድ አዲስ ነገር በምድረ ቀደምት ኢትዮጵያ ተፈጥሯል። ተልዕኳችን ወደ ኢትዮጵያ ይሆናል ማለት ነው።..."ንግግሩን ገታ አድርጎ ከአህያ ዓይን የማይለያየውን በበርበሬ የተለወሰ የሚመስለውን ዓይኑን ከቀኝ ወደ ግራ በሁሉም ሰዎች አሽከረከረው።
የሁሉንም ሀሳብ ማግኘቱን ሲያረጋግጥ ፥ የእስራኤልን ሙሉ ህዝብ መመገብ የሚያስችል ማሳ የሚመስለው ሰፊ እስኪርን ላይ አንዲ በኋላት ቁንጅኗዋ ሞናኒዛን የሚያስቀና ያላት ኢትዮጲያዊት ብቅ አለች።"...የኛ ስራ ይህቺን ከዓለም ጋር ግብግብ መፍጠር የምትፈልጓን ይህቺን እርኩስ ፍጡር አንቃቹ ታመጣልኛላቹ። ይህቺ ተንከሲስ ፍጡር የኤድስን መድሃኒት ቀመር አግኝታለች።
አሜሪካ በጣም ትፈልጋታለች። እኛም የአሜሪካ ወዳጆች ስለሆን ልንሰጣት ይገባል። ግን መጀመሪያ እንያዛት።..."
ስብሰባው ዶክተር ብሌንን መያዝ ላይ አተኩረው ፍሬያማ የሆነ ነጥብ አንስተው ቢለያዩም ግን ደግሞ '... ይህቺ ተንከሲስ...'በማለቱ ቤተ አይሁዳዊቷ በኮድ ስሟ "ኮል"የምትባሏ ተናዳለች።
'...ምንም ቢሆን አባቴ ኢትዮጵያዊ ነው።...' ኮል ታጉረመርማለች በሆዷ፤ ቀጥላለች '...ቆይ ለማለት የፈለገው ኢትዮጵያውያን ምንም አይችሉም ለማለት ነው? ይሄ ከሲኦል አምልጦ የመጣ ሰይጣን የመሰለ እርኩስ ሰውዬ...' ብትረግመውም መርካት ግን አቃታት።

በአየር ንብረት ለውጥ ላይ በአውሮፓዊቷ ምድር በቤልጄም በተካሄደው ጉባኤ ላይ አወያይ ሆና በመመረጧ አለመከፋቷን ለአማካሪዋ ለፕሮፌሰር ኤ. ዳቡሽ እየተደሰተች ነገረችው።
"...ኦ! ዶክተር ብሌን መጣሽ? እባክሽ ተቀመጭ!"ከወንበሩ ተነስቶ በሞቀ ሰላምታ የተቀበላት የ70 ዓመት ሽማግሌ እራስ ላይ የአፋር ነጭ ጥጥ ማምረቻ ማሳ የመሰለው ፀጉሩ የተስተካከለ እና ቁመናው የሚማርክ አኳዃን ነበረው።
"10 Q ፕሮፌሰር!..."ጉርድ ለባሿ ቀይ መልከመካሟ የጥቁር ደም ያለባት መላዕክትን በሚጠልፈው ድምጿ_ዶክተር ብሌን።
ከተደረደሩት የዓለሙ ጌታ ለፍርድ ሲመጣ የሚቀመጥባቸው ከመሰሉት በሰልፍ ከተደረደሩት ነጫጭ ሶፋዎች በአንዱ ላይ ለምን እንደ ተፈለገች ለመስማት እየቋመጠች ቀጭን ሰውነቷን ይዛ ተሰየመችበት።
"...አቤት ፕሮፌሰር!..."በሰልካካ ድምፅ፤ የእሱን መቀመጥ ጠብቃ እና እንደ መረጋጋት ብላ።
ትንሽ የመፃህፍቶቹን ገፅ ካገላበጠ በኋላ ያገኛትን በፖስታ የታሸገውን ደብዳቤ ያለምንም ቃለ ምልልስ ሰጣት።
'...ምን እስቦ ነው...?' የብሌን የሆዷ ጥያቄ ነው። ይህንን እንድትልም ያስገደዳት ነገር ቢኖር የፍቅር ጥያቄ ስለመሰላት ነው።
ፊቷን እንዳኮሳተረችው የተሰጣትን ፖስታ ከፍታ አነበበችው።
"Dear Bilen Gobaze(PhD)..."
ብሎ የጀመረው ደብዳቤ እሷን ለአወያይነት መመረጧን ያስረዳል።
በዚያን ሰዓት በጀርመን ምድር ፀሀይ ባትወጣም የፊቷ ደስታ ብቻ የፀሀይን ቦታ መተካት ይችላል ነበር።
ይህንንም ደስታዋን ኢትዮጵያ ለሚገኘው ልቧ እስኪጠፋ ድረስ ለምትወደው ፍቅረኛዋ አካፈለችው።
የጉባዔውም እለት ደረሰ።
"...Ok once silent..."አለች በ20000 ተሰብሳቢዎች ፊት እንደተቀመጠች...
***
የአሜሪካው ፔንታጎን የዓለም ሕዝብ እንዲያውቅ ያልፈለገው በምስጢር የያዘውን ጉዳይ ጫፉን ለመያዝ እየሞከረ ያለው ኢትዮጵያዊው የናሳ ቁልፍ ሰው የሆነው ሳይንቲስት ሆካንካ ከፍቅረኛው ሳይውመን ጋር በተቀጣጠረበት ስፍራ የኤስኤስአይ እና የኬጂቢ ሰላዮች መሉ ቦታውን ተቆጣጥረውታል።
የወንድ የአለባበስ መንገድ በሚመስል መልኩ የለበሰችውን ልብስ ግርማ ሞገስ አጎናፅፏታል።
"...እንዴት እንደ ናፈከኝ አጠይቀኝ!"አለችው በስሱ ከንፈሩ ላይ ስማው በሞቀ ሰላምታ ከተቀበለችው በኋላ እና ወንበር ስቦ ከተቀመጠ በኋላ።
"...ከኔ ባይበልጥም።"አላት በሞቀ ፈገግታ።
"...ብናፍቅህማ ልታገኘኝ ትጥር ነበር።"አይኖቿ በአንዴ በርበሬ የተጨመረባቸው ይመስላሉ ለተመለከታቸው።
ሳይንቲስቱ ስሜቷን ጠንቅቆ ስለሚያውቅ
"...ኧረ ስቀልድሽ ነው"ብሏት ሊያረጋጋት እጆቹን ወደ ትከሻዋ ሲሰነዝራቸው ወደ ሆቴሉ የፔንታጎን ከፍተኛ አመራሮች ተከታትለው ወደ ውስጥ አይኖቻቸውን ሳይንቲስቱ ላይ እንደ ጣሉ ገቡ...
ለማንበብ እና መጨረሻውን ለማወቅ የጓጓ 👍ያድርግ


#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመዶ ያጋሩ #share @Qdist
Join and share👉
@Qdist
@Qdist
@Qdist
For any question& comment ለማንኛውን ጥያቄ&አስተያየት👉@E_T_L_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

22 Nov, 17:24


ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy pinned «. #የGame እና ምርጥ ምርጥ APP ቻናላችንን መቀላቀል የምትትፈልጉ join 👇👇👇 @best_game2 @best_game2 የእንግሊዝኛ pp እምትፈሎጉ👇👇 @etl_1 @etl_1 በቀልድ ዘና ፈታ ማለት የምትፈልጉ👇👇 @ethiokeld3 @ethiokeld3»

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

22 Nov, 16:47


.
#የGame እና ምርጥ ምርጥ APP ቻናላችንን መቀላቀል የምትትፈልጉ
join
👇👇👇
@best_game2
@best_game2

የእንግሊዝኛ pp እምትፈሎጉ👇👇
@etl_1
@etl_1

በቀልድ ዘና ፈታ ማለት የምትፈልጉ👇👇
@ethiokeld3
@ethiokeld3

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

22 Nov, 16:02


ሽልማት አድርሰናል ያልደረሰው ካለ ሪፖርተር ያድርግ አድሚኖች ስላዘገዩ ይቅርታ

ቀጣይ የ5000ብር ውድድር ይዘን እንመጣለን

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

22 Nov, 09:14


#ቀን ሲጥል
           
#ክፍል 3

ጠዋት ከእንቅልፌ ስነ ቃ ያለሁበትን ቦታ በደምብ አላውቀውም ብቻ ግማታም ቱቦ ውስጥ ተኝቼ እንዳደርኩ ገባኝ ሰውነቴ በጣም ይሸታል ለእይታም ደስ አይልም ተነስቼ ታክሲ ወደምንይዝበት ቦታ አመራው ሰዉ እያየ ሲጠየፈኝ በደምብ ይታወቀኛል ታክሲው ጋር ደርሼ ልገባ ስል ወያላው አፍንጫውን ይዞ አይቻልም ብሎ በሩን ዘጋብኝ ምንም አልመሰለኝም እንደለመድኩት በእግር መንገዴን ቀጠልኩ ግቢ አከባቢ ስደርስ ኤቤጊያ ከጓደኞቿ ጋር ከግቢ ሲወጡ ከርቀት አየኃት በጣም ደነገጥኩ እየሮጥኩ ወደኃላ ተመልሼ እየሮጥኩ ጠፋው እሷን ሳያት ለምን ፍርሃት እንደሚከበኝ አላውቅም አይደለም በቅርበት አይቻት ቀርቶ በሌለችበት ስሟ ሲነሳ እደነግጣለው ምን እንደሚሻለኝ አላውቅም።

በራሴ በጣም ተናደድኩ ለአንዲት ሴት እንደዚ እሆናለው? ኤቤጊያ አይነጥላ ሆነችብኝ  ራሴን ወቀስኩት የዛሬ አመት የነበረውን ናኦድ አስታወስኩት የድሮ ማንነቴ ናፈቀኝ ደፋር፣ ከሰውጋ ተግባቢና ተጫዋች በትምህርቱ ጎበዝ ራሱን የሚጠብቅ..... ከአንድ አመት በፊት ኤቤጊያ ይህንን ግቢ ስትቀላቀል ልቤ ከሷ ጋር አብሮ ሄደ

አስታውሳለው እንደሁልጊዜዋ ሰማያዊ ጅንስና ጥቁር ሸርት አድርጋ ሻንጣዋን ይዛ እዛ ረጅም አስፓልት ላይ እየጎጠተች ስትገባ እኔ ከግቢ ስወጣ ነበር ያየኋት ከዛን ግዜ ጀምሮ ልቤን የሰረቀችው ቆንጆ እንስት ሌብነቷን እንኳን ሳታውቅ ልቤን አልመለሰችልኝ እኔም ከግዜ ግዜ ፍቅሯ እየባሰብኝ ሄደ ሁሉም ነገር ቀስበቀስ እየተቀየረ ሄደ  የዛሬ አመት የነበረው ናኦድ አሁን የለም አባይ ጓደኞቼ ከኪያር ውጪ ተዘባበቱብኝ ከኔ ተለዩ ይባስ ብሎ ኤቤጊያን እንደምወዳት እያወቁ በስሟ መጫወቻቸው አደረጉኝ። 

ኤቤጊያ ታክሲ ውስጥ ገብታ ከሄደች በኃላ ራሴን አረጋግቼ ወደግቢያችን በር እያመራው አስፓልት ዳር ከቆሙት መኪናዎች አንዱ በመስታወቱ ራሴን ድንገት አየሁት ደነገጥኩ ራሴን በመስታወት ካየሁት በጣም ቆየው ድሮ የማውቀው ፊት ሳይሆን ሌላ ሰው የቆመ መሰለኝ ይህንን መልክ አላውቀውም  በጣም ገርጥቶ የከሳ ጥቁር ፊት የተንጨባረረ ፀጉርና ፂም ቀጫጫ ሰውነት በዛ ቀጫጫ ሰውነት ላይ ሰፊ የቆሸሸ ልብስ ሰው ሁላ ጀዝባ ወይም ሞሮ ቢለኝ አይገርምም እውነትም ሆኛለው። ወደ ድሮ ማንነቴ መመለስ እንዳለብኝ ገባኝ ኤቤጊያ ለኔ ያላላት የፍቅር መርዝ ናት ከልቤ ቆርጬ ላስወጣት ለመጨረሻ ግዜ ለራሴ ቃል ገባው ወደ ግቢ እየሄድኩ የነበረውን ሃሳብ ቀይሬ ወደኃላ ተመለስኩ አንዱን ባጃጅ ኮንትራት አናግሬ ባያምነኝም ቅድሚያ ከፍዬው ቅር እያለው ወደ መብራት ሃይል ወሰደኝ።

ኤቲኤም ብር አውጥቼ ወደ ቡቲክ አመራው ልብሶች ጫማ ሁሉንም  ገዛዛው ራሴን በአዲስ መልኩ ማየት እፈልጋለው። ልብሶቹን ይዤ አንድ ሆቴል ገብቼ አልጋ ያዝኩ ሻወር ገባው ከላዬ ላይ የተራገፈው የቆሻሻ መአት እኔና ባኞ ቤቱ ነው ምናውቅው ራሴን ታዘብኩት በጣም! ከሻወር ስወጣ ሁሉም ነገር ቅልል አለኝ ነገሮች ጥርት ብለው ይታዩኝ ጀመር አዲሱን ልብስ ለብሼ ፀጉሬን ለመስተካከል ወደፀጉር ቤት ሄድኩ ያ ጅብ የዋለበት እርሻ የሚመስለውን ጨበሬ ፀጉር በአግባቡ ተስተካከልኩት ፂሜንም እንደዛ ትንሽ መለስ ያልኩ መሰለኝ ግን አሁን ድሮ የቀይ ዳማ የመሰለው መልኬ ጠቁሮ እንዳልተመቸኝ በደምብ ያሳብቃል  ፀጉር ቆራጩን አመስኜ ወጣው።

እንደሌላ ግዜ ሰው እየተጠየፈ አያየኝም ትንሽ ደስ አለኝ ወደ ቀድሞ ግብሬ መመለስ ጀመርኩ ሁሌ መብራት ሃይል ስመጣ መፅሃፍ ደርድረው ከሚሸጡት ውስጥ ራስተም ጋር ሄጄ አንድ አሪፍ መፅሃፍ ገዝቼ ወደ በቀለ ሞላ ሆቴል በአንደኛ መንገድ ላይ ወክ እያደረግኩ ሰዉን እየታዘብኩ እሄዳለ ዛሬም እንደዛ ማረግ ፈለግኩ። ራስተም ጋር ስሄድ መፅሃፎቹን እያስተካከለ ሲደረድር አገኘሁት ቀና ብሎ ሲያየኝ ደስ አለው እንዴ ናኦዴ ሰላም ነው ምነው ጠፋህ አለኝ ብዙ ግዜ ሆኖኝ ነበር ራስተም ጋር መፅሃፍ ከገዛው ሰላም ተባብለን ከጨረስን በሃላ አዲስ መፅሃፍ ገዝቼ መንገዴን ወደ በቀለ ሞላ ሆቴል በአንደኛ መንገድ ላይ አድርጌ ሄድኩ ወደ ሆቴሉ ስገባ እንድወትሮው ሰላሙን የጠበቀ ሆኖ አገኘሁት ከራስ ጋር ለማውራት ደስ እሚል ሰላማዊእና ተፈጥሮአዊ ቦታ ነው የዛሮቹ ብዛት የወፎቹ ዝማሬ ሰላም ይሰጣል እኔም ሰላሜን አገኘው አዱስ የገዛሁትን መፅሃፍ ገልጮ ትንሽ እንዳነበብኪ አስተናጋጇ  መጣች ትዝ ሲለኝ ደህና  ምግብ ከበላው በጣም ቆይቻለው የቤቱን አሪፍ ምግብና መጠጥ አዝዤ መፅሃፌን እያነበብኩ ዘመትኩበት ለዚች ቅፅበት ኤቤጊያን ረስቻት ነበረ::

12፡00 ሲል ወደ ግቢ ተመለስኩ ስደርስ እየጨላለመ ነበር ግቢ ውስጥ ስገባ መንገድ ላይ ከኪያር ጋር ተገጣጠምን ሲያየኝ ንፁህ ልብስ ለብሻለው  ፀጉሬ ተስተካክሏል በዕጄ መፅሃፍ ይዣለው ተገረመ እየሳቀ ምን ተገኘ አለኝ ምንም አልኩት እየተቻኮለ ነበር አቅፎኝ ዶርም ጠብቀኝ  እመለሳለው አሁን እያለኝ ፈገግታውን ሳይነፍገኝ እየተጣደፈ ሄደ ዶርም ስገባ ሁሉም መሳሳቅ ጀመሩ እንደ ኪያ የደስታ ሳይሆን የፌዝ እንደነበር በደምብ አውቃለው። አንደኛው በጣም እየሳቀ ሞሮሮሮ.... ምን ተገኘ ኤቢን ጠበሻት እንዴ አለኝ ተናደድኩ ሞሮ እሚለው ስድብ አናደደኝ ከተቀመጥኩበት ተነሳውና ከዚ በኃላ ሞሮ ብትለ ኝ እንጣላለን አልኩት እየሳቀ እሺ አለኝ ተናድጄ ልወጣ ስል ኪያር በሩን ከፍቶ ገባ ያለው ነገር ወዲያው ስለገባው ይዞኝ ወጣና ወደ አም ፊ አከባቢ ያሉት ደረ ጃዎች ጋር እያረጋጋኝ ሄደን ተቀመጥም።

አሁን ባየው መስተካከል እንደተደሰተ ነግሮኝ እንድበረታ እያፅናናኝ ስለ ኤቤጊያ ምን ማድረግ እንዳለብኝና እሱ ለኔ እንደሚያናግራት እየነገረኝ እያለ ኤቤጊያ ከሌላ ወንድ ጋር ሆና ከኛ ፊትለፊት ደረጃዎቹ ላይ ስጥቀመጥ ድንገት አየኃት።
ክፍል አራት እንዲቀጥል
👍👍👍

#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመድዎ #share @Qdist
Join&share 👉
@Qdist
@Qdist
@Qdist
For any comment&question ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት 👉 @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

20 Nov, 16:18


#ሶስተኛው የዓለም ጦርነት

ክፍል_አንድ
ከምኔው እንደ መሸ ስራዋን ገታ አድርጋ ስታስበው ተዓምር እንደሆነባት ለእራሷ መልሳ አጫወተችው- በእነ አቶ መኩሪያ ቤት ተከራይታ የምትቀመጠው ፍቅር።
"አቤቱ ፀሃይን በምስራቅ አውጥተህ በምዕራብ የምታጠልቅ አምላክ በሁሉም ሐይማኖቶች ስምክ ይባረክ..."ቧንቧው አጠገብ ቆማ የሃያ ሶስት ዓመቷ ወጣት በሆዷ አይኖቿን ወደ ሰማይ ልካ ታመሰግነዋለች።

ከሚወዳቸው ተማሪዎቹ ለሁለት ቀናት የተለያቸው የፍቅር ጎሮቤት የሆነው መምህር አየለ ስልክ እየነካካ ወደ ቧንቧው ሲመጣ ያላስተዋለችው መላዕክትን አስቶ የሚጥለውን ጀርባዋን ሰጥታው ስለቆመች እንጂ "..አንዴ መንገድ.."ሲላት በወንዳወንድ ድምፅ አትደነግጥም ነበር።

ሃብትን ከቁንጅና የያዘው ተቀጥራ የምትሰራበት ድርጅት ባለቤት የሆነው ዕዝራ ያላስደነገጣት፤ የቢሻው ሰውነት ያላስደመማት ቁንጅናን ከፈጣሪ የፈጠራ ክፍል ገዝታው የወረደች የምትመስለው ፍቅር እንደ በድን ደርቃ ቀረች።
ሰይጣን ንቀትን ከማን ተማረ ቢባሉ እና ከ አየለ ነው ቢሉ ምንም ስህተት የለውም።
አይኖቹን ከስልኩ ሳይነቅላቸው ሲቀር ሃሳቡን ለመሳብ ብላ "ወይኔ እግሬን"ብትል በአንድ አይኑ አጮልቆ ከገላመጣት በኋላ ምንም ሳይናገራት ቧንቧውን ዘግቶ በአሮንጓዴ ባልዲ የሞላውን ውሃ በቀኝ እጁ እንዳንጠለጠለው ወደ ቤቱ ገባ።
ፍቅር አበደች። አበደች ከምለው ይልቅ ሰይጣን ሆነች ይቀላል። ወደ መምህር አየለ ቤት እየተጣደፈች ሄደች...

አየለ እየተመለከተ የነበረውን የአለቃውን ትዕዛዝ በኢሜል ተቀብሎ እቅድ እያወጣ ሳለ የቤቱ በር ኃይል በተሞላበት ምት ተንኳኳ።
"... እንደሆነ የዚህን ወር የቤት ክራይ ከፍያለው፤ታድያ አቶ መኩሪያ ምን ፈለጉ?..."ጠየቀ እራሱን።

አሁንም ተንኳኳ። በመጀመሪያው ምንም አይነት መልስ ስላልሰጠ "ማነው?"አለ በተረጋጋ መንፈስ።
አሁን በዝግታ ተንኳኳ። እሱን እና እሱን ብቻ በምታስተኛው ትንሿ መሬት ላይ ከተነጠፈችው ፍራሹ ያን ፈርጣማ ሰውነቱን ተሸክሞ ብድግ አለ።
ሰፊ ከብቶች የሚሰማሩበት ከመሰለው ፊቱ እንደ ጥቅጥቅ የአማዞን ደን የበቀለው ፂሙ ላይ የመኮሳተር ስሜት ሲያሳይ፥ የጠዋት ኮከብ የመሰሉት ከዓይኖቹ በላይ ያሉት በፀጉር የተሸለሙት ቅንድቦቹ ግርማ ሞገስ ይሰጡታል።

እግዚአብሔር የእጁን ጣቶች አለስልሶ የፈጠረው እንዲፅፍበት ብቻ እንዳልሆነ ፍቅር የተረዳችው የተከራየበትን የእነ አቶ መኩሪያን ቤት በር በትህትና ሲከፍተው ነው።
ከአናቱ በላይ ያለው ጠቋቁር ፀጉሮች "...ተጨቆን ድረሱልን..."እንደሚሉ ለመረዳት ሰው መሆን በቂ ነው።
ከአናቱ ዝቅ ብሎ የሚገኙት መንቲያ ጆሮቹም ሲቆሙ መመልከት ያስፈራል።
የለበሰው ቁምጣ የእግሮቹን ማማር ቁልጭ አድርጎ ያሳያል።

የለበሰው ሲሊፐር ግን መምህር እንደሆነ አይናገርም።"...አቤት..."አላት በሩን በቀኝ እጁ እንደያዘ ኮስተር ብሎ።
"...እእእ እንትን ፈልጌ ነበር..."ሳታውቀው ተርበተበተች። ፍርሃትን በስም እንጂ በአካል አታውቀውም፤ዛሬ ገና ተዋወቀችው።
በሆዱ "እንትንሽ እንትን ይሁንና..."
"እሺ ምን?"አላት
"...እንትን...ባልዲ ፈልጌ ነበር..."ፊቷ ይንቀጠቀጣል።

በቁም ያለ በድን ማንን ታውቃለክ ተብሎ አየለ በዚያ ጊዜ ቢጠየቅ ፍቅርን ነው ማለቱ እንደ ማይቀር የተረዳችው ልክ እሱ ባልዲው ሊሰጣት ሲግባ ከፊት ለፊቷ በተሰቀለው መስታወት ስትመለከተው ነው


#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመድዎ #share @Qdist
Join&share 👉
@Qdist
@Qdist
@Qdist
For any comment&question ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት 👉 @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

19 Nov, 17:57


ሰላም ቤተሰብ የውድድሩ አሸናፊዎች እንሆ ይዘን መተናል
1,
#code_2 Tigist
2,
#code_1 Helen
3,
#code_3 Sami
ከ1_3 የዎጣችሁ ከላይ ስማቸሰሁ የተጠቀሰው በቃላችን መሰረት ሽልማታችሁን መውሰድ ትችላላችሁ account ቁጥራችሁን ላኩልን በካርድ መልክ እምትፈልጉ ደግሞ ስልክ ቁጥራችሁን ለመላክ
👇👇
@e_t_l_bot

ቀጣይ የ5000ብር ውድድር ይዘን እንመጣለን እስከዛው ቻናል #share ማድረግ አይረሳ👍
ቼር ምሽት

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

17 Nov, 17:18


ኢትዮጵያዊ ነን!

ፈቅደን ሲመሩን ችቦ ተቀባይ
ለሚነዱን ግን አሻፈረን ባይ
ካልነኩን በቀር ቀድመን ማንዘምት
ከጋሻ በፊት ጦር የማንሸምት

ኢትዮጵያዊ ነን!
ህብር ያስጌጠው ህይወት ለማብቀል
ዘር ሳናጣራ የምንዳቀል
ለነዱን ሰይጣን ለመሩን ሰናይ
ጌታን ከገባር ለይተን ምናይ
ኢትዮጵያዊ ነን!
ብዙ ህልሞችን ወዳንድ ዐላማ
የሰበሰበ ገርቶ ያስማማ
በደምና ላብ ያቆምነው ካስማ
አገዳ አይደለም የሚቀነጠስ
የዝምድናችን መተሳሰርያ
ሺ ጊዜ ቢከር የማይበጠስ
ኢትዮጵያዊ ነን!
ምን ሆድ ቢብሰን ምን ብንቸገር
እድር አይፈርስም እንኩዋንስ አገር
ብለን በትግስት የምንሻገር
ሲገፈትረን ግፈኛና አጥቂ
ቁልቁል ሲሰደን ሽቅብ መጣቂ
ለውርደት ሲያጩን የምንጀነን
...
በእውቀቱ ስዩም

Join and share your friends👇👇
@qdist
@qdist

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

17 Nov, 11:00


🚨🚨ትብብር ለቤተሰቦቻችን በሙሉ

ቻናላችን ስልካቹ ላይ #MUTE የሚለው ላይ መሆኑን አረጋግጡ #UNMUTE የሚለው ላይ ከሆነ የምንለቃቸው መረጃዎች በፍጥነት አይደርሳችሁም!

ከላይ በምስሉ ላይ እንዳለው እንድታደርጉልን በትህትና እንጠይቃለን 🙏 ስለትብብራችሁ እናመሰግናለን።

#ቻናሉን SHARE በማድረግ ቤተሰባዊነታችንን እናጠናክር ። 😍🙏

SHARE 
SHARE  SHARE SHARE

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

17 Nov, 06:33


#ቀን ሲጥል
#ክፍል 2


በላይ ኤቤጊያ ብሎ ሲጣራ በድንጋጤ ብዛት ጭልፊት እንዳየች አይጥ ዘልዬ ወደውስጥ ገብቼ አልጋዬ ውስጥ ተደበቅኩ። በላይ ማለት በጣም እሚያናደኝ ልጅ ነው ኤቤግያን እንደምወዳት አውቆ ሁሌም ይፈታተነኛል ሞኝ የሆነ ልጅ ነው ፍቅር የማይገባው ብዙ ግዜ አንስማማም።

ሁሉም የዶርም ልጆች ሁኔታዬን እያዩ ይበልጥ ተሳሳቁብኝ ተናድጄ ተነሳውና በላይን ምን መሆንህ ነው ምትጠራት አልኩት መልስ አልሰጠኝም ዝምብሎ ይገለፍጣል ድሮም እንዲው ነው ከማግጠጥ ሌላ ምንም አያቅም ጅል!!! ወደ አልጋዬ ተመለስኩና በመስታወቱ በኩል ሆኜ ስታልፍ አየኃት አዬ እዳ ምን ቀን ነው ያየኃት ኤቤጊያ ካለፈች በኃላ ሁሉም ወደ ውስጥ ገቡ ኪያር ና ምሳ እንብላ አለኝ ወደ አልጋዬ አጮልቆ እያየ አልበላም አልኩት እሺ ብሎኝ ሄደ ኪያ ደስ እሚለኝ ለዚ ነው መጨቃጨቅ መጋተት ምናምን አይመቸውም እኔም አልወድም አልፈልግም ካልኩ አልኩ ነው ተመልሼ እንቅልፌን ለጠጥኩ።

10፡00 ሰአት አከባቢ ከእንቅልፌ ነቃው ዶርም ማንም የለም ሁሉም ክላስ ሄደዋል ከአልጋዬ ተነሳውና ወደሎከሬ ሄድኩ ልክ ሎከሩን ስከፍተው ሁለት ትንንሽ አይጦች ጫማዬን እያጣጣሙ ሲግጡት አየው ልክ እኔን ሲያዩ ተፈትልከው በእግሬ ስር እየተሽሎከሎኩ ፈረጠጡ እማማዬ .... ብዬ ለጉድ ጮህኩ ሲያስጠሉ ቀፋፊዎች ነብሴ መለስ ስትል ዝርክርክ ካለው ልብሶቼ ውስጥ እምለብሰውን ልብስ መፈለግ ጀመርኩ።

ሁሉም ልብስ ከታጠበ በጣም ቆይቷል በግ በግ ይሸታል ደና ሲታጣ ይመለመላል ጎባጣ አደል ያለችው አያቴ ከበክት ውስጥ ትንሽ የበከተውን ልብስ መፈለግ ጀመርኩ አንድ ድሮ ሳውቀው ነጭ የነበረ አሁን ግን መንችኮ ቡኒ የሆነ ሰፊ ሸርት አገኘው ለበስኩት ከታችም ቆሻሻ የቃመ ሰፊ ሰማያዊ ጅንስ አርጌ ቅድም አይጦቹ የገጠቡትን ጫማ ያለካልሲ አድርጌ ከዶርም ወጣው ወዴት እንደምሄድ አላውቅም እግሬ ወደመራኝ ብቻ ከዚ ግቢ ውጪ ብቻ ይሁን ድንዝዝ ብዬ ከግቢያችን ወጣው ናዝሬት የለመደባትን ፀሃይ በአናት በአናቴ ትለቅብኛለች።

 
#የግቢያችንን በር አልፌ ፊትለፊት ወዳለው ሱቆች ሄድኩ ባለሱቁ ደስታ ሁሌም ያቀኛል ሳልጠይቀው አንድ ፓኮ ሲጋራ እጄ ላይ አስቀመጠልኝ ብሩን ከኪሰ በርብሬ አውጥቼ ከፍዬው መንገዴን ቀጠልኩ የግቢያችን ተማሪዎች ታክሲ አጥተው መደዳውን በር  አከባቢ ተደርድራው ይጠብቃሉ አንድ ኮሳሳ ታክሲ ስትመጣ ተሯሩጠው እየተጋፉ ይገባሉ።

በእግር መንገዴን ወደ መብራት ሃይል አደረኩ ደስታ ከሰጠኝ ፓኮ ሲጋራ ፈልቅቄ አንዷን አውጥቼ አፌ ላይ ሰክቼ ኪሴ ውስጥ ክብሪት ፍለጋ ማሰንኩ የቅድሙ ሱሪ ውስጥ እንደረሳሁት ትዝ አለኝ ተበሳጨው አከባቢዬ ላይ የእሳት ምንጭ የሚገኝበት መንስኤ ማሰስ ጀመርኩ ከርቀት አንድ የጎዳና ተዳዳሪ ልጅ በተሰበረ ምድጃ እሳት ስታቀጣጥል አየው እየሮጥኩ ወደሷ ሄድኩ እሙዬ እሳት ልጫር አልኳት እሺ አለችኝ ሲጋራውን ከአፌ ሳልነቅል አጎንብሼ አፌ ላይ እንዳለ የእንጨቱን ጭስ እየታጠንኩ ለኮስኩት ልጅቷ ገርሟት ታየኛለች እኔ ግን መንገዴን ቀጠልኩ ብቻዬን በሃሳብ አለም እየዋለልኩ እግሬ ወደሚወስደኝ ቀጠልኩ።

ኤቤጊያን እንዴት እንደዚ እስከምሆን ድረስ ላፈቅራት ቻልኩ ሁሌም ስለሷ ሳላስብ አይነጋም አይመሽም እሚገርመው ግን እሷ እኔ አይደለም እንደምወዳት ቀርቶ ማን እንደሆንኩ እንኳን አታውቅም ኤቤግያ የአዲስ አበባ ልጅ ናት እኔም የዛሬን አያድርገውና የፒያሳ ልጅ ነበርኩ ነቄ ሁሉን ያየው ግን ምን ያደርጋል ፍቅር ሲይዝ ሳያስጠነቅቅ ነው ልክፍት ነው የኔማ ሳያት ሁላ እምገባበት ነው ሚጠፋኝ።

#እንዲ በሃሳብ እየተብሰለሰልኩ መብራትሃይል አከባቢ ደረስኩ ግማሹ ፓኮ ሲጋራ አልቋል ሆዴን በምግብ ሳይሆን በጭስ የሞላሁት መሰለኝ  ከነጋ አልበላሁም 11፡30 ሆኗል ሆዴ ያኮረፈ ይመስል ያጉረመርማል አስፓልቱ ዳር ካሉት የተቀቀለ ድንች ሻጮች ጋር ሄድኩና ሁለት እንቁላል በዳባና ሚጥሚጣ እዛው አጠገባቸው አስፓልት ዳር ሆኜ በላውና ተነስቼ መንከራተቴን ቀጠልኩ ድንገት የሞባይል ቤት አየውና አንድ ሃሳብ መጣልኝ

ለአቤጊያ ብቻ እምደውልበት አዲስ ሲም ማውጣት! ወደሱቁ ገብቼ አንድ አዲስ ሲም ገዝቼ ወጣው ከዛ ወደለመድኩት ባር ሄድኩ ድራፍቴን ስጋት ስጋት ስጋት አመሸው ማታ ላይ ወደግቢ ስመለስ አዳልጦኝ አንድ ቱቦ ውስጥ ወደቅኩ በቆሻሻ ውሃ ጨቅይቷል ኤጭ የራሱ ጉዳይ! እዚው አድራለው ቀን የገዛሁትን ሲጋራ በጣም የሚሸተው ውሃ ውስጥ ካለው ኪሴ አውጥቼ ያልበሰበሱትን አውጥቼ  ባር ውስጥ በተቀበልኩት ላይተር ለኩሼ ሁሉንም አፌ ውስጥ ሞጀርኳቸው ....

ክፍል ሶስት እንዲቀጥል
👍👍

#share and join us
@ethiokeld3
@ethiokeld3
@ethiokeld3

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

15 Nov, 05:47


#ቀን_ሲጥል
ክፍል 1

ከደስታ ብዛት ሳይታወቀኝ ያ ቀጭን አለንጋ የመሰለ እጇን ጥብቅ አርጌ ይዣት አብረን እየሄድን ነው እንደሞኝ ያረገኛል ዝም ብዬ እየተገላፈጥኩ ከራስ ፀገሯ እስከ እግር ጥፍሮቿ አተኩሬ አያታለው ፀጉሯን ብኒ ቀለም ተቀብታው ተፈርዟል ከሩቅ ሲታይ የዛገ የእቃ ማጠቢያ ሽቦ ይመስላል ደነገጥኩ እንደዚ ስላት ሰምታኝ ይሆን ሆ..ሆ..ሆ አፌን ብሰበስብ ይሻላል በስንት ስለት ያገኘኃትን ልጅ የዛገ ሃገሬ ሽቦ ብያት ልጣት እንዴ ፊቷ ደሞ እንዴት እንደሚያምር ውውውይ ቀይ ረዘም ያለ ፊት ነው ያላት አይኖቿ ትላልቅ ከንፈሮቿን ደማቅ ቀይ ቻፒስቲክ ተቀብታዋለች።

የለበሰችው ጥቁር ቦዲ እና ሰማያዊ ጅንስ እላይዋ ላይ ጥብቅ ብሎ እሚያምረው ሰውነቷን ጉልት አድርጎ ያሳያል ፍዝዝ ብዬ እያየኃት እያለ አውራ እንጂ አለችኝ እ...እእ እሺ አወራለው አልኳትና ድጋሚ ዝም አልኩ ምን እንደማወራት አላውቅም።

ኤቤጊያ በጣም እምታምር ልጅ ናት አልመጥናትም አውቀዋለው እሷ የቆንጆዎች ቆንጆ እኔ ደግሞ ገጣባ! የጀዝባዎች ጀዝባ ሞሮ አዬዬዬ መከራ አለች አያቴ እንዴት ይሆን እንደምወዳት እማስረዳት ዝም ብዬ ስብሰለሰል ሳመኝ አለችኝ እ.. ም ምን አልኳት አይኗን ጨፍና ከንፈሯን አሹላ ወደኔ ስትጠጋ ደነገጥኩ ፍርሃቴን እየደበቅኩ እኔ አይኔን ጨፍኜ ወደሷ.... ጀርባዬ ቅቤ ይወጣው ይመስል  እንደጉድ ይንጠኛል ናዲ.... ናኦድ አንተ ናኦድ አረ በጌታ ክላስ ረፈደ ተነሳ አንተ ምናባክ ነው ማትነሳው ትከሻዬን ለጉድ ይነቀንቀኛል ከንፈሬን እንዳሾልኩ አይኔን እያጨናበስኩ ነቃው አጠገቤ ኤቢጊያ የለችም ያለው በእጄ ጭምቅ አርጌ የያዝኩት በላብ የሞጨሞጨ ትርሃስ ብቻ ነው ከወገቤ ቀና እያልኩ ወደኃላ ዞርኩ።

እንደቅቤ እሚንጠኝ ልጅ  ጓደኛዬ ኪያር ነው ከጣፋጭ ህልም ውስጥ ስለቀሰቀሰኝ በጣም ተበሳጨው ምናባክ ላርግህ ማን ቀስቅሰኝ አለህ አንተ የኔ አላርም ማናባክ አረገህ ብዬ ቀወጥኩት ባክህ አትጩህብኝ ክላስ እየረፈደብን ነው ተነሳና እንሂድ አለኝ አልሄድም ብዬ ቁርጥ ያለ መልስ ሰጠሁት አንተ ጀዝባ ፈተና አለን እኮ ዛሬ ተነስ ብሎ ብርድልብሴን ገፈፈኝ ውይ ኪያ በናትህ ተወኝ ምን እኔ ፈተና ሲያመልጠኝ መጀመሪያዬ ነውደ

#እንዴ ብርቅ አስመሰልከው እኮ ብዬ ብርድልብሱን በሃይል ነጠቅኩትና ድጋሚ ተጠቅልዬ ተኛው ኪያር ደብተሩን አንስቶ ጥሎኝ ወጣ ኪያር ጥሩ ጓደኛዬ ነው ብዙ ግዜ ስድብና ቁጣ ይቀናዋል ልቡ ግን የዋህ ነው ደስ እሚለኝ የባህርዳር ልጅ ነው ከፍሬሽ ጀምሮ ስከአሁን አራተኛ አመት ድረስ አንድም ቀን እንኳን ሳንቀያየም አለን የዛሬን አያድርገውና በጣም ጎበዝ ተማሪ ነበርኩ ሁሉ እሚቀናብኝ ብዙ ጓደኞች የነበሩኝ ግን ምን ያደርጋል ኤቤግያን ካፈቀርኩ በኃላ ሁሉም ገደል ገባ እኔም ራሴን ጣልኩ ጀዘብኩ ሁሉም ሰው ጀዝባው ሞሮ እያለ ሲጠራኝ ኪያር ብቻ ነው በስሜ ሚጠራኝ እሱም ሲበሳጭብኝ እንደነሱ ጀዝባው ይለኛል ግን ምንም አይመስለኝም።

#እውነትም ጀዝቢያለው ለምንም ነገር ግድ አይሰጠኝም ቀኑን ሙሉ አልጋዬ ላይ ተሰፍቼ ስለ ኤቤግያ ብቻ ሳስብ እውላለው ማታ ደሞ ራሴን በአልኮሆልና በጭስ  ውስጥ ተደብቄ አገኘዋልው ቀንና ለሊት ኤቤግያን ሳስብ እውላለው አድራለው እሷ ግን ማን እንደሆንኩ መፈጠሬን እንኳን አታውቅም ኤቤግያ ኤቤግያ ኤቤግያያያ... እንደው ምን ልሁን ምን ይሻለኛል ኤጭ ብርድልብሴን ሸፈንኩና የቅድሙን ህልም ፍለጋ ተመምኩ ግን ቴዲ ህልም አይደገምም ብሎ የለ አጣሁት ከየት ይምጣ ተበሳጨው እርሜን ኤቢን ከጎኔ ሁና ባያት ልስማት ስል ኪያ ቀሰቀሰኝ ተኛው ምሳ ሰአት ኪያር እየሮጠ መጥቶ ድጋሚ ቀሰቀሰኝ ለጉድ ጮህኩበት አንተ ቃጭል ታወኝ በቃ ልተኛበት አልኩህ አይደል እንዴ ምን ላርግህ አልኩት።

እየሳቀ ናዲ ኤቤግያ በኛ ብሎክ ጋር እያለፈች ነው አለኝ ከምኔው ተስፈንጥሬ ከአልጋዬ ወርጄ የዶርማችን በረንዳ ጋር እንደተሰየምኩ አላውቅም ኪያ ከት ብሎ ሳቀ ሁሉም የዶርሜ ልጆች ነገረ ስራዬ አስቋቸው እየሮጡ መጥተው አብረውኝ ቆመው እኔን ማየት ጀመሩ።ግድ አልሰጠኝም አቢ ቀይ ቅድም በህልሜ ያየኃቸውን ልብሶቿን ለብሳ በኛ ዶርም አከባቢ እያለፈች ነው ልቤ ፍስስ ሲል ተሰማኝ ድንገት አንዱ የዶርሜ ልጅ ጮክ ብሎ ኤቤግያ ብሎ ተጣራ
ይቀጥላል
...

#Share and join us👇
@ethiotibeb3
@ethiotibeb3
@ethiotibeb3

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

14 Nov, 15:53


#Code_5

🎧🎶esttif

Join and share
👇👇
@qdist
@qdist

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

13 Nov, 15:40


#Code_4

---ዳግመኛ ከመልካም ስብዕና ተወለድ!!
--------------------------------------------------
ሰው ሆነህ መኖርህ አንተንና ሌሎችን ካልጠቀመ ገና አልተወለድክም........!!የሰው ልጅ በፍጥረቱ ሰው ሆኖ በዚህ ምድር ላይ ቢፈጠርም(ቢወለድም) ሰው ለመሆን ግን ከመልካም ስብዕና ማህፀን ዳግመኛ መወለድ ይኖርበታል።ብዙዎች ከዚህ ማህፀን ስላልተወለዱ (ስላልወጡ)ዛሬ ለምናያት ሀገራችን ችግር መንስኤ ሆነው እናያቸዋለን ከሀገርም አልፎ ለአለም የችግር ምንጭ ሆነው ይኖራሉ።

ሰው ሲኖር ለግሶ እንጂ ተቀብሎ መኖር የለበትም ከራስ በላይ በዙሪያው ለሚገኙ ሰዎች ኖሮ ማለፍ አለበት ሰው ሆኖ መገኘት ቀላል ሆኖ ሳለ የሰው ልጅ ግን ሰው መሆንን ይፈራል.. ምክንያቱም ሰው በመሆን ውስጥ ስለራስ ጥቅም ማሰብ ስለሌለ,ሰው በመሆን ውስጥ ማግበስበስ ስለሌለ ሰው በመሆን ውስጥ ዬኔ የሚባል ነገር ስለሌለ ሰው በመሆን ውስጥ ራስን ማበልፀግ ስለሌለ...ሰዎች ሰው መሆንን ይፈራሉ ለዚህም ነው ዳግመኛ ከስብዕና ማህፀን ያልተወለዱ ሰዎች በኔነት ስሜትና በራስቸው ደስታ ብቻ መኖር የሚያስደስታቸው።

እነዚህ አይነት ሰዎች ከራሳቸው ዘላቂ ደስታ ውጭ የወንድማቸው ችግር ለነሱ ምንም ነው የሰውን ችግር መስማት ለነሱ ምቾት ይነሳቸዋል ስለዚህ በራሳቸው የተጣመመ የህይወት መንገድ ጉዟቸውን ያደርጋሉ።አንተ ግን ሰው ሁን ዳግመኛ ከስብዕና ማህፀን ተወለድ ከራስህ ደስታ ይልቅ ለሌሎች ደስታ ኑር ከራስህ በላይ ሌሎችን ወደህ ተገኝ ለሌሎች አርአያ ሆነህ የደስታቸው ምንጭ ለመሆን ጥረት አድርግ ለችግሮቻቸው የመፍትሔ ሀሳብ አቅርብ።ያኔ ሰው መባልህ ብቻ ሳይሆን ሰው ሆነህ መፈጠርህ ዘላለማዊ ጥቅሙ ይገባሀል።

በምድር ላይ ካንተ በላይ ደስተኛ አይኖርም በመጨረሻም በምድር ላይ ሰው ተብለህ መጥተህ ዳግመኛም በመልካም ተግባርህ ከስብዕና ማህፀን ተወልደህ ህያው መሆንህን ታረጋግጣለህ።
ገዛኸኝ መስፍን


#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመድዎ #share @Qdist
Join&share 👉
@Qdist
@Qdist
@Qdist
For any comment&question ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት 👉 @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

12 Nov, 14:46


#Code_3

#ሳትስሚኝ በፊት

...አንዴ ስሚኝ
የምነግርሽ አለኝ
የምታዳምጪኝ
 አዎ
ስለኖርኩት የልቤ ሀቅ
ስለሳቅኩት የጥርሴ ሳቅ
...ደሞ
ሳይቀያየሙ ስለመታረቅ
      እየተያዩ ስለመናፈቅ
        ስለመነፋፈቅ
          ፍቅርን ስለመኖር
           ፍቅርን ስለማኖር
...ብቻ በጣም ብዙ ነገር
     ልነግርሽ እያሰብኩኝ ነበር
...ግና
  ከዝርዝሩ በፊት
       ከሁሉም ከሁሉም
  አለኝ ደግ ምርቃት
        ለኔም ሆነ ላንቺም
    በይ ተቀበይ
    የወዳጅ ምርቃት
             ከቶ አይናቅም

  ...እስኪ አሜን በይ
  ...እስኪ ይሁን በይ
      ልመርቅ ተቀበይ
              
  ከጠላቴ ልታረቅ
            ጠላትሽም ይናቅ
              አሜን!
  ክፉዬ ካንቺ ይጥፋ
       ክፉሽ ከኔ ይራቅ
            አሜን!
  ቀኔ ባንቺ ይፍካ
     ቀንሽ በኔ ይድመቅ
              አሜን!
   ከኔ ተደበቂ
     ባንቺ ውስጥ ልደበቅ
              አሜን!
   ከኔ ይሁን እንባሽ
        ካንቺ ይሁን ሳቄ
              አሜን!
   አወጪኝ "ከዚ አለም"
      ላውጣሽ ነጥቄ                    
   አሜን አሜን አሜን!
    ሁሉም ይሁን ያፌን
  ...ታዲያ
     በስሜ የማልኩት
      በስምሽ ያስማለኝ
       ሁሉንም ያስባለ
    "እነግርሻለሁ"
           ልኩት ሁሉ
            ምርቃቴ ውስጥ አለ
    አዎ...አሜን በይ
    አዎ...ይሁን በይ
    አሁን ግን
    ላንድ አፍታ አንዴ
     ...ሁሉንም ተይ
  
 ዕድሜሽን ሳልቀማው
               ዕድሜዬን ሳትቀሚኝ
    ለማንም ሳላማሽ
     ለማንም ሳታሚኝ
    ከበሽታሽ ዕድን ዘንድ
                   እንድታስታምሚኝ
   ሁሉንም ተይና
      አሁን በይ
    ...ጥግ ድረስ ሳሚኝ!
ሳሚ     

#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመድዎ #share @Qdist
Join&share 👉
@Qdist
@Qdist
@Qdist
For any comment&question ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት 👉 @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

11 Nov, 17:13


Code 2

ሚስት ከመሞቷ በፊት ባሏን እንዲህ ብላ ጠየቀችዉ "እኔ ከሞትኩ በኋላ ሌላ ሚስት ታገባለህ"? የቀብርሽ አፈር እስከሚደርቅ ድረስ በፍፁም አላገባም አላት። እሷም ማናችንም ወደማንቀርበትከእለታት በአንዱ ቀን አረፈች።

ከጊዜያት በኋላ ማግባት ፈለገና ቃሉን ለመሙላት የሚስቱ መቃብር አፈር መድረቅ አለመድረቁን ለማወቅ ሲሄድ... አልደረቀም እርጥበት አለዉ በሁለተኛዉም ቀን በሶስተኛዉም ቀን እርጥብ ነው። እዲህ እያለ ለ13 አመታት በሙሉ ሁሌ የቀብሯ አፈር እርጥበት እንደያዘ ነዉ።

እሱም በቃሉ መሰረት አላገባም አንድ ቀን ከወትሮ በተለየ ጎህ ከመቅደዱ በፊት ወደ መቃብሯ ቢሄድ ወንድሟ የመቃብሯን አፈር ዉሀ እያጠጣዉ ተመለከተ በአግራሞት ደርቆዐቀረ "ለምን"? ብሎ ጠየቀ። ወድድሟም እንዲህ ሲል መለሰ እህቴ ከመሞቷ በፊት በህይወት እስካለሁ ድረስ ሁሌ ጎህ ሳይቀድ መቃብሯን ዉሀ እንዳጠጣዉ በኑዛዜ መልኩ ቃል አስገብታኛለች ለዛ ነው ሁሌ ከመንጋቱ በፊት ውሃ እማጠጣው ሲል መለሰለት።

ባልም በሃዘን ውስጥ ሁኖ ከዚህ በኋላ ቃልህን እኔ እፈፅማለው በማለት ከዛ ቀን ጀምሮ የመቃብራን አፈር እራሱ እያጠጣ አመታቶች ነጎዱ በመጨረሻም የሂወት ሰሌዳዉ አበቃና ለፍቅሩ ታማኝ እንደሆነ እሱም ሞተና ተጎራበታት... እናም አፍቃሪዋ ሞታም ፍቅሯን ለማንም ሳታስነካ ዝንተዓለም የራሷ ብቻ አድርጋ ያዘችዉ። ፍቅር እንዲህ ነው
😍😘
Tigist

#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመድዎ #share @Qdist
Join&share 👉
@Qdist
@Qdist
@Qdist
For any comment&question ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት 👉 @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

09 Nov, 17:49


Code 1

የፍቅር አልሜ የሂወት ምዕራፎ
አንተን ያለምኩ ለት መስመሬን አልፎ
ያኔ ይጀምራል መራራው ሂወቴ
ገና ባፍላ እድሜዬ በጨቅላ አንደበቴ
ያኔ በልጅነት በለጋው እድሜዬ
በማላውቀው ስሜት ያነገስኩህ ስዬ
ደሰ የሚል ስቃዬ እልፍ አላፍ ብሶቴ
ገና አይንህን ሳየው ጠፍቶኝ እኔነቴ
አንዳች ስሜት መቶ ውስጤን ተቆጣጥሮ
መናገር ስሞክር ቃሌ ተሰባብሮ
ይሰማኛል ድምፄ ትርጉም አልባ ሁኖ
የውስጥ ስሜቴ ከሀሳቤ በኖ
እንጂማ ባወጋህ ድፍረቱን ታድዬ
ውስጤን አዳምጬ አንደበቴን ሰዬ
እኋው ልማልልህ ልጅነቴን ይንሳኝ ብዬ ተገዝቼ
               አንተን ይንሳኝ ብዬ አለሜን አጥቼ
እኔ እንደምወድህ እራሰህን አቶድም
የኔን ፍቅር ብታይ ማፍቀርን አታውቅም

ድንገት ብታይማ ለማየት አድሎህ
በዕንባ ዘለላዬ ብዕሬን አቅልሜ
በዜማ ተውቦ የውሰጥ ህመሜ
በልቤ ያረፉት ረቂቃ ቃሎቼ
እልፍ አላፍ ግጥሞቼ
ይናገሩ ነበር ካንደበቴ በላይ የውስጤን አጉልተው
ቃል የሌለው ፍቅር መሆኑን ተረድተው

እንጂማ ባወጋህ ድፍረቱን ታድዬ
ውስጤን አዳምጬ አንደበቴን ስዬ
እኋው ልማልልህ ልጅነቴን ይንሳኝ ብዬ ተገዝቼ
                 አንተን ይንሳኝ ብዬ አለሜን አጥቼ
እኔ እንደምወድህ እራስህን አቶድም
የኔን ፍቅር ብታይ ማፍቀርን አታውቅም

አንዳንዴ ሲብሰኝ እምባዬ ሲቀድመኝ😥
አፌ ተቆላልፎ የውስጤን ሸሽጎ
በይመጣል ናፍቆት ነገን ተስፋ አድርጎ
በመጠበቅ ደዌ በማይልቅ ለቅሷ
አንተነትህ ነግሷ ከልቤ ምሷሷ
ፊት ለፊት ላወጋህ ያጣሁትን ድፍረት
ብዕሬን አውግቼው ውስጤ ያለውን እውነት
ልሂድ ወይስ ይምጣ እያልኩ ሳንገራግር
ስሜቴን ሸሽጌ  በይሉንታ አጥር
በመሀል እረፍዶ
ጆሮዬ ቢያሰማኝ የሰረግህን መርዶ
ሊያገባ ነው ቢሉኝ ከኔ ሌላ ወዶ
ዳግም ላይመለስ
ጎጆውን ሊቀልሰ
ሊሄድ ነው ሊያገባ አንቺን ይሉንታ አጥሮሽ
ሸሽገሽ ያኖርሺው እውነተኝ ፍቅርሽ
እንዲያ ብለው ሲሉኝ
ያኔ እንኩዋን ሳያገርመኝ
ከገደበኝ አጥር የይሉንታ መንደር
የዕድሜ እኩሌታዬን የጠበኩት ፍቅር
ከደስታው ታድሜ
ከሰርጉ ሙዚቃው
እሰክሰታና ፌሽታው
የልጅነት ህልሜን ዳርኩት እያለቀስኩ
ያብርሀም የሳራ ትዳር ይሁን እያልኩ

Helen

#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመድዎ #share @Qdist
Join&share 👉
@Qdist
@Qdist
@Qdist
For any comment&question ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት 👉 @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

09 Nov, 17:47


እንሆ ተጀመረ ለአንድ ተወዳዳሪ የሚሰጠው 24ሰዓት ነው #view እሚያዘው በ24ሰዓት ውውጥ ነው መልካም እድል

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

08 Nov, 10:17


ሰላም ቤተሰብ ማንኛውም የምለቀቀው link የማስታወቂያ ስራ ነው እኛን አይወክልም

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

06 Nov, 21:01


#ጥበብ ማለት ምን ማለት ነው?

#ጥበብ ከአልማዝ ከእንቁ ከወርቅ ይልቅ ውድ ናት ጥበብ በባህር ዘንድ የለችም ሞትም አላቃትም ይላል። ጥበብ እንዳለች ሁሉም ያቃል  መኖሪያዋን ግን ማንም አያውቅም፡፡

አሁን በየትኛውም ስፍራ የሚያሰፈልገን ጥበብ ነው። ሰዎች ጥበብ ስለሌላቸው ሣይሆን የሚጎዱት ጥበብ ስላነሳቸው ነው። ብዙ ትዳሮች የፈረሱት በጥበብ ማነስ ምክንያት እንጂ በአጋንንት ምክንያት አይደለም።

#ጥበብ መብራት ናት የመብራት አላማ ማሣየት እንጂ መብራት አይደለም ማሣየት ማለት የሌለህን ነገር ይሰጥሃል ማለት አይደለምደለም ያለህን ነገር ግን ያጎላልሃል። ብዙ ሰዎች ያለቦታቸው የተቀመጡት ውስጣቸው ያለውን ነገር ባለማየት ነው። ጥበብ ስታበራልህ ግን ታያለህ።

ጥበብ በብዙ ላብ የምታገኘውን ነገር ወዲያው እንድታገኘው ትረዳሃለች። ጥበብ ማለት መስራት ሳይሆን አሠራር ነው።ጥበብ ሲመጣ አደረገ ሳይሆን እንዴት አደረገ የሚለውን እንድታቅ ታደርግሃለች። ጥበብ አደራረግን ታሳውቃለች

ቼር ሌሊት

#share & join 👇
@ethiotibeb3
@ethiotibeb3
@ethiotibeb3

#If you have any comment or question 👉 @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

06 Nov, 17:43


ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy pinned «ሰላም ቤተሰብ ማንኛውም ችሎታ ያለው ሰው በዉስጥ መስመር ያናግረኝ ሁለተኛው ከ8000 በላይ ተከታዮች ያለው ቻናላችን በአዲስ መልክ እየተዋቀረ ነው እናም ለእናንተ እድሎችን ይዘን መተናል #ማንኛውም ችሎታ አለኝ የሚል ችሎታውን ሰውን እያዝናና ሃሳብ እየተቀበለ ማዳበር እንዲችል እድሉን ይዘንላችሁ መተናል #ግዴታ በፅሁፍ ይሁን አንልም #በመነባንብ በትረካ መልኩ ወይም በግጥም መልክ #record እያደረጋችሁ…»

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

06 Nov, 17:36


ሰላም ቤተሰብ ማንኛውም ችሎታ ያለው ሰው በዉስጥ መስመር ያናግረኝ ሁለተኛው ከ8000 በላይ ተከታዮች ያለው ቻናላችን በአዲስ መልክ እየተዋቀረ ነው

እናም ለእናንተ እድሎችን ይዘን መተናል
#ማንኛውም ችሎታ አለኝ የሚል ችሎታውን ሰውን እያዝናና ሃሳብ እየተቀበለ ማዳበር እንዲችል እድሉን ይዘንላችሁ መተናል

#ግዴታ በፅሁፍ ይሁን አንልም #በመነባንብ በትረካ መልኩ ወይም በግጥም መልክ #record እያደረጋችሁ መልቀቅ ትችላላችሁ

admin መሆን እሚፈልግ እና ችሎታው ያለው
@betsi_e1 ማናገር ይችላል
ቻናሉ👇👇
@ethiotibeb3
@ethiotibeb3
@ethiotibeb3
ቼር ምሽት ቤተሰብ🙏

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

06 Nov, 07:29


Thank you 4k subscribers family😍

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

05 Nov, 13:02


የት ነሽ ኢትዮጵያ

#እናቴ ሀገሬ
የት ነሸ
የት ነው የቀበሩሽ
የት ነው የደበቁሽ
የነገሩን ሃገር አንቺ እኮ አይደለሽም
እኛ የሰማነው ለኛ የነገሩን

ጥበብ የሞላባት
ፍቅር ያደገባት
እውቀት የተረፋት
ሰይጣን የቀናባት
የጥበብ መፍልቂያ የፍቅር መገኛ
አንዲት አቢሲኒያ
ኢትዮ ኢትዮጵያ
የቅዱሳን ምድር የሃያላን እናት
የነ ያሬድ ምድር የነ ላሊበላ
የነ አክሱም አባት የነ ጎንደር እናት
እድሜ የማይሽረው ጥበብን ያነፁት
እንደ ታሪክ ሁኖ የሰማነው እውት
ከመስማትም በላይ የወረስነው እውት
ምነው ተቻኮልን ታሪክን ለማጥፋት
ሀገር ለመበትን ጎጥን ለማስፋፋት
ቆይ ግን
ማን ነው የናፈቀው የኢትዮጵያ ሰላም የኢትዮጵያ እድገት

ማን ነው የናፈቀው የኢትዮጵያ መዝሙር
ማን ነው የናፈቀው
ተቀላቅሎ ማየት ሰማንያውም ብሄር
አንድ ሁኖ ሲሰራ አንድ ሁኖ ሲዘምር
የናፈቀው ማን ነው የኢትዮጵያ ሰላም?

ያች አንድ ኢትዮጵያ የጥበብ መፍለቂያ
ኧየ የት ነው ያለች እናቴ ኢትዮጵያ
?😭
#share
@esttiff

#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመድዎ #share @Qdist
Join&share 👉
@Qdist
@Qdist
@Qdist
For any comment&question ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት 👉 @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

05 Nov, 06:10


አለመኖር

አርቆ ማሰብ ጠፍቶብናል መኖር ለዛሬ ብቻ መስሎናል መኖር ግን በእውነቱ ዛሬ ብቻ ነው ነገ እና ትላንት ሁለቱም አለመኖር ናቸው። በመወለዳችን ምን ያህል እድለኞች እንደሆንን አናውቅም።

እስኪ ያልተወለዱትን አስቧቸው መኖር እኮ በአለመኖር ጥልቅ ውስጥ የተሰጠን ስጦታ ነው። ከዚህ በፊት አልነበርንም፣ ወደፊትም አንኖርም። ይህን ማስተዋል ለምን ተሳነን?  ምክንያቱም ከሁሉም ህመማችን ስር የተሰወረብን እውነት ይህ ነው።
✍️ ዶ/ር  ዳዊት

#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመድዎ #share @Qdist
Join&share 👉
@Qdist
@Qdist
@Qdist
For any comment&question ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት 👉 @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

04 Nov, 17:34


የሞባይል ካርድ እንድሞላ ቁጥሩን ልኮልኝ "ስሞክረው አይሰራም" እለዋለው

ምን ቢለኝ ጥሩ ነው🙈
"እኔ ጋ ሰርቷል ደጋግመሽ ሞክሪው
😂😂😂
#share @funnytime433

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

04 Nov, 14:00


#ስሚ
አምና እና ካቻምና
    መውደድሽ አስክሮኝ
    ፍቅርሽም  አውሮኝ
    የፃፍኩልሽ ቅኔ
    የጻፍኩልሽ ግጥም
    አሁን ግን ሳስበው
    ምንም አይመስለኝም።

ውዴ አትቀየሚኝ እውነቱን ልንገርሽ
ጨረቃን አይመስልም
             በፍፁም ውበትሽ
የፊትሽ ብርሀን
             ከፀሐይ አይበልጥም ገላሽልስላሴው
             ብዙምአይመስጥም
በፊት ያልኩት ሁሉ ዛሬ ላይ ሳስበው 
ችግሩ የአይኔና የአተያየቴ ነው።

#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመድዎ #share @Qdist
Join&share 👉
@Qdist
@Qdist
@Qdist
For any comment&question ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት 👉 @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

03 Nov, 17:07


#እየጠበኩሽ ነዉ

በሄድሽበት እንደ መንገድ
በቆምሽበት እንደ ጥላ
ንፁህ ነፍሴ ተከትላሽ
አንቺን አምና አንቺን ብላ
ሲመሽ ሲመሽ በህልሜ ላይ
ዘላለሜን እያየሁሽ
ተመልሼ ማልመልሰዉ
ሙሉ እድሜየን ያዉ ሰጠሁሽ
እየጠበኩሽ ነዉ

በቸኮለዉ በዚህ ዘመን
መጣደፉ በበዛበት
አሁን አለ ያልነዉ ነገር
ትንሽ ቆይቶ በሌለበት
አንቺን የሚል የኔ ፍቅር
አንቺን የሚል የኔ አንደበት
ብቻ ፀንቶ ይጠብቃል
ዉብ ፍቅርሽን በቅንነት
እየጠበኩሽ ነዉ

ደማቅ ፀሃይ ይሄዉ ገባች
ጨለማዉን አስከትላ
ብርቱ ክንዴን ሊፈትነዉ
የእድሜየ ጎርፍ ወንዙን ሞላ
በልጅነት ጨዋታችን
በዉሃ የተጫወቱ
ዉሃ አጣጬን ስጠብቅሽ
ትዳር ጎጆ መሠረቱ
እኔ አፍቃሪሽ ግን እየጠበኩሽ ነዉ

በመንገዱ ግራና ቀኝ
የበቀሉት አበባዎች
ቢራቢሮ የሚጠሩ
የልጅነት እምቡጥ መልኮች
ድንገት በፀሃይ ሳይደርቁ
ድንገት በንፋስ ሳይረግፉ
እንደጠበኩሽ ነይና
ከድካማቸዉ ይረፉ

ቼር ምሽት

#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመድዎ #share @Qdist
Join&share 👉
@Qdist
@Qdist
@Qdist
For any comment&question ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት 👉 @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

02 Nov, 18:11


ወርቅ ይቆሽሻል እንጂ ግራሙ አይቀንስም የሰው ልጅም ይፈተናል እንጂ ወድቆ አይቀርም

ወዳጆ በዛሬ ፈተና እጅ አትስጥ ነገ ሌላ ቀን ነው እንደ ወርቅ ቆሻሻን አሸንፈህ አብረቅርቀህ ውጣ እናጨዋጋህን ውድ አድርገው። ዛሬ ያልተረዱህ ሁሉ ነገ ሲፈልጉህ ታገኛቼዋለህ!
የተባረከ ምሽት
#share @qdist

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

02 Nov, 16:39


Let's go 3500subscribers guys #share #share your friends

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

02 Nov, 14:06


#ሱሰኛ_ነኝ

አዎ ሱሰኛ ነኝ ሱሴ እልፍ የበዛ
አንድ ሁለት ካላልኩ ፊቴ የማይወዛ
ቀኔ የማይበራ ሚጨልም ደንጋዛ
አይኔ ማይከፈት እንዲሁ በዋዛ
አጨሳለሁ ገና መቼ ተጨሰና
የፊደል ጭራሮ መች ተለኮሰና
የቃላት ቅርንጫፍ መች ተማገደና

በጭሱ ናውዤ በዜማው ሰክሬ
አልችልም ልላቀቅ ክፉኛ ታስሬ
አዎ ሱሰኛ ነኝ ውስጡ ተነክሬ
ድንገት ያጣው ጊዜ አልችልም ዳክሬ
ምርኩዝ አያነሳኝ ምቀር ተሰብሬ
አዎ ሱሴ በዝቷል ጠልቆ ከደም ስሬ

ቃል ከቃል ሲጋጠም በሚፈጥረው ግለት
ስቃጠል ኖራለሁ ካጣው ስለምሞት
የፊደል ስደራ የወግ አቀማመጥ
የቃሎቹ ጉልበት ሲጮሁ ብለው ፀጥ
ወኔ ቢስ ሲሰማው የሚያረገው ሸነጥ
የሀረግ ሹል ስለት የብዕር ረመጥ
ያቅበዘብዘኛል ብሎኝ አላስቀምጥ

አዎ ሱሰኛ ነኝ የቃላት ግጥምጥም
የቤት መቺዎቹ እኛ ያሉት ፍርጥም
ጊዜ ማይሽራቸው ስንቱን ቢሽሩትም
አዎ ሱሰኛ ነኝ እኔማ የግጥም


#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመድዎ #share @Qdist
Join&share 👉
@Qdist
@Qdist
@Qdist
For any comment&question ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት 👉 @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

01 Nov, 18:40


#ፍቅር ሲደናበር

የመዋሀድ ስሜት
የመዋደድ ነገር
ሳላውቀው ሳታውቂው ውስጤን ዘልቆት ነበር

በኔ እና አንቺ መሀል
ፍቅር ሲወላውል ፍቅር ሲደናገር
ሳላውቀው ሳታውቂው ተሰጥቼሽ ነበር
ግን በፍቅር ጥፋት
ግልፅነት አጉድሎ
ፍቅር አራራቀን ራሱን ከልሎ

ቢገባሽ ቢገባኝ
የሰጠውሽ ቦታ
አላጣሽም ነበር ፍቅር የጠፋን ለታ

ብታውቂው ባላውቀው
ፍቅር እንደሰወረኝ ልቤን እንደሰረቀው
አንቺም ባልወቀሽኝ እኔም ባላዘንኩኝ
ሳጣሽ ከምሆነው
ካንቺ ጋር እያለው ራሴን በሆንኩኝ

ግን ቀን አይመለስ ታሪክም ገስግሷል
በኔም ባንቺም መሀል
ነበር ባይሆን ኖሮ መውደድን ፀንሷል።
ፍቅር ሲወላውል ፍቅር ሲደናበር
ሳለውቀው ሳታውቂው እኔ አፈቅርሽ ነበር።
Ermias

የተባረከ ሌሊት ቤተሰብ🙏

#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመድዎ #share @Qdist
Join&share 👉
@Qdist
@Qdist
@Qdist
For any comment&question ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት 👉 @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

01 Nov, 07:04


ቻለንጅ 1

ሽልማት ያለው ቻለንጅ ለመሳተፍ ዝግጁ ናችሁ?
ግጥም
አስተማሪ የህይወት ታሪክ
ፍልስምና እንዲሁም አስተማሪ እና ቁም ነገር አዘል ነገር ያላችሁ በሙሉ ተሳተፉ
በመነባንብ መልኩም መሳተፍ ይቻላል ግጥምም በተመሳሳይ

ቢቻል የተኮረጀ ባይሆን ይመረጣል
አሸናፊዎች የሚለዩት
1, የህዝብ ቻናል ላይ ሼር የተደረገለት
2, ብዙ ሼር ካለው ያ ማለት ሼር የምታደርጉላቸው ልጆች ለሌሎች ደሞ እንዲያደርጉ ተናግራችሁ የሼር ብዛታችሁን መጨመር ትችላላችሁ
3, ብዙ እይታ ካለው
4, የራስ ፈጠራ ከሆነ

1ኛ ለዎጣ 200 ብር
2ኛ 150ብር
3ኛ 100ብር
አካውንት የሌለው ሰው ካለ በካርድ መልክ መውሰድ ይችላል

መልካም እድል ሰዎች🏅🏅🏅🏆


የናንተ ስራ ቻናል ላይ የሚለቀቀው ከጥቅምት 30ጀምሮ ነው የሰራችሁትን እስከዛ @e_t_l_bot በዚህ መላክ ትችላላችሁ ውጤቱ በቻናሉ ተከታዮች ይወሰናል በድጋሚ መልካም እድል

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

31 Oct, 15:20


#ፍቅር ነው የራበኝ

ደህና ነኝ እንዳልል
  ደህንነቴ ጠፍቷል
እሞኛል እንዳልል
ይሄው ፊቴ ፈክቷል
ሰው ሲያየኝ ጤነኛ
ውስጤ በሽተኛ❤️‍🩹
ቆይ ምን ብየ ላውራ
ሰሚ ሰው አግኝቼ
በልቤ ጠራ ውስጥ
የትኛውን ትቼ

አይቶ በሚፈርድ
ጆሮ ጠቢ ምላስ በሞላበት ሀገር
ለየትኛው ሰሚ
ለየትኛው ሀኪም ህመሜን ልናገር?
ከማንነት በላይ
ከምንነት በላይ
ምን ቃል ሊተነፈስ?
በሽፋን መለኪያ
ምን እውነት ሊታፈስ?

ፍቅር ነው የራበኝ💔
እሱ ነው ያመመኝ💘
የሀገሬ መሬት ሰው እያካሰሰ
ሰው እያናከሰ
የሀገሬ ቋንቋ
ዘር እያስቆጠረ
ክልል እያጠረ

ያዳም የአብራክ ክፋይ
ሰውነት ቀረና
በጎሳ በብሄር
ታጥሮ ህልውና

በሽብር አይምሮ
ሀገር ይታመሳል
ለማይጠቅም አለም
ንጹህ ደም ይፈሳል
ክብር የሰው ስጋ
በግፍ ይቆረሳል
አፍ እየቀደመ
የህሊና ደወል
መሰማት ተስኖት
የአምላክ ቃል ይፈርሳል።

ይሔው ነው ህመሜ
የእድሜያችን ጣሪያ
ሰማኒያ ላይሞላ
በሳር በቅጠሉ
ባፈር ስንባላ
እኔ ነኝ የኔ ነው
ማንነቴ እንትን ነው
የሚል እድር ፈላ
በሉ እስኪ ንገሩኝ
ማንነት ምንድን ነው?
ምንነት የቱ ነው ?

ሰው ከመባል ወዲያ
ምን ትርጉም ተገኝቶ?
ከአምላክ ፍጡር ውጭ
ምን ጠላት መጥቶ?

ምንድን ነው ነገሩ
ዝንትአለም መናከስ
ድምበር እያጠሩ
በመግባቢያ ቋንቋ
በትውልድ ቀየ ዘር እየቆጠሩ
ምንድን ነው ዘር መቁጠር
ዘር ማሳለይ እንጅ
ሰው ላይ ምን ያደርጋል
ማን በሀሩር ደርቆ
ማን በዝናብ ያድጋል?

አመሉ ነው እንጅ
ሞኝነት ነው እንጅ
ጥንትም ተፈጥሮውን
ሰው በአምላክ ካመነ
ማን ሀበሻን መርጦ
ማን ፈረንጅ ሆነ?
ከግዜሩ ሆኖ እንጅ
ፍጥረት የተሰጠ
ይሁንልኝ ብሎ
ማን ፆታ መረጠ።

ከአፈር ተፈጥሮ
አፈር የሚሆን ሰው
ከአፈር ጋር ታግሎ
አፈር የሚቆርሰው
ምነው? ይሄ ትውልድ
ከራስ የዘለለ ማስተዋል አነሰው ።

ይገርማል...
በማለዳ ፀሀይ
በምሽት ከዋክብት ቀን እየተዋጀ
ህዝቤ አንደጎበጠ
ቅን ሆኖ ቀን ሳያይ ሰማኒያውን ፈጀ።
አዎ እኔ ፍቅር ነው የራበኝ💔
ቼር ምሽት
🙏

#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመድዎ #share @Qdist
Join&share 👉
@Qdist
@Qdist
@Qdist
For any comment&question ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት 👉 @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

31 Oct, 06:05


...አለም በራሷ ዋጋ ያላት ነገር አይደለችም። የእኛ ሀሳቦች ናቸው ዋጋ የሚሰጧት። ድንጋይን ከድንጋይ አስበልጠን ይሄኛው ተራ ነው ይሄኛው ውድ ነው እንላለን እንጂ ድንጋዩቹ በራሳቸው ውድ እና ርካሽ አይደሉም።

አልማዝም ባልጩትም ሆነ ጠጠር እኛ ውድ ወይም ርካሽ አልናቸው እንጂ በራሳቸው ዋጋ የላቸውም በአለም ሁሉ ያለ ነገር እኛ በምንሰጠው ምላሽ ብቻ ነው አስደሳች አናዳጅ አሳዛኝ አስቀያሚ የሚሆነው ።...ደስታም ሆነ ሀዘን ካንተ አእምሮ የሚፈልቁ ነገሮች ናቸው...

ሀይል አለህ ሀይልህም ዓለምን የመቀየር ሳይሆን ዓለምን የምታይበት እይታህን የሚቀየር ነው።
ፍልስፍና ከዘርዓያቆብ እስከ ሶቅራጠስ

መልካም ቀን ቤተሰብ

#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመድዎ #share @Qdist
Join&share 👉
@Qdist
@Qdist
@Qdist
For any comment&question ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት 👉 @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

30 Oct, 04:08


ሶስት አይነት ሰዎችን አክብር
#የእውቀት ባለቤቶችን
#ቤተሰብህን
#አዛዉንቶችን
ሶስት ነገሮች ይኑሩህ
#ታማኝነት
#እምነት
#መልካም ስራ
ራስህን ከሶስት ነገሮች አርቅ
#ሰዎችን ከመናቅ
#ከማጭበርበር
#ከብድር
ሶስት ነገሮችን ተቆጣጠር
#ምላስህን
#ቁጣህን
#ስሜትህን
ከሶስት ነገሮች ራስህን ጠብቅ
#ከመጥፎ ስራ
#ሰዎችን ከማማት
#ከምቀኝነት
ሶስት ነገሮችን ፈልግ
#እዉቀትን
#ጥሩ ስነምግባርን
#ታዛዥነትን
ሶስት ነገሮችን ንጹህ አድርግ
#ልብህን/አይምሮህን
#ሰዉነትህን እና ልብስህን
#ንግግርህን
ሶስት ነገሮችን አስታዉስ
#ሞትን
#ሰዎች የዋሉልህን ዉለታ
#ሰዎች የሰጡህን ምክር
መልካም ቀን

#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመድዎ #share @Qdist
Join&share 👉
@Qdist
@Qdist
@Qdist
For any comment&question ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት 👉 @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

29 Oct, 20:19


ውርስ ውበት
ሞትሽን አልመኝም
አንቺ ከሞትሽ ግን..

በፈረሶች ፀጉር
ለሚዋቡ ሴቶች
ውርስ ተይላቸው
አብሮሽ አይቀበር
ውበት ይሁናቸው

ብዙ ኩል ቀላቅለው
አሳር ለሚበሉ
ስራ አቅልይላቸው
አይንሽን ይትከሉ

ለቁንጅና ድጋፍ
አፍንጫ ጆሯቸው
ለጌጥ ለሚበሱ
ያንቺን አውርሻቸው
ውብ ጌጥ ነው በራሱ

ሳቃቸው እንዲያምር
ተነቅሰው በመፋቅ
አሳር ለሚበሉት
ጥርስሽን ስጫቸው
ወስደው ያስተክሉት

ሁሉንም አካልሽን
ከአፈር መበስበስ
መቀበር አድኚ
ቆመሽ ብቻ አይደለም
ሞተሽ ውበት ሁኚ

ፀባይሽ ግን ውዴ...

እኔ ያልቻልኩትን
አፈሩ ከቻለው
አደራ አታውርሺ
ፀባይሽ ቢወረስ
ትርፉ መቃጠል ነው

ሞትሽን አልመኝም
አንቺ ከሞትሽ ግን...

ውበትን ለሚሹ
ሴቶች አውርሻቸው
እኔም ያንቺ አፍቃሪ

እኔም ያንቺ አፍቃሪ
ውርስሽን ልካፈል
እነሱን ላግባቸዉ

ቼር ሌሊት🙏

#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመድዎ #share @Qdist
Join&share 👉
@Qdist
@Qdist
@Qdist
For any comment&question ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት 👉 @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

27 Oct, 13:30


አሁን ሁሉም ነገር ተስተካክሏል መወዳደር እሚፈልግ መላክ ይችላል

እንዲሁም አድሚን ሁኖ መስራት እሚፈልግ በውስጥ መስመር ያናግረኝ ለቻናል እድገት ጎበዝ ነኝ ያለኝን ለሰው ለማቅረብ ችሎታው አለኝ እሚል ሰው አድሚን የመሆን እድል ሰጥቻለው በቦቱ ፃፉልኝ
@e_t_l_bot

ስትመዘገቡ ያላችሁን ችሎታ አብራችሁ አስቀምጡ መልካም እድል

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

27 Oct, 10:51


ዛሬ እምትሳተፉ ልጆች ቦት እየሰራ አይደለም ሲሰራ እነግራችኋለው በዚሁ አጋጣሚ ብዙ ሰው ለመወዳደር እየፃፈ አይደለም እድላችሁን ሞክሩ

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

25 Oct, 07:39


ማሰብ ስታቆም ማመን ትጀምራለህ
"A life without reasoning is unworthy of man"


አንዳንዶች ፍልስፍና በዘመናችን እምብዛም የሚወደድ ሆኖ አለመገኘት ብቻ ሳይሆን እየተጠላም ነው ይላሉ፡፡

ሶቅራጥስ ራሱን አሳልፎ የሰጠላት ፕሌቶም ፍልስፍናን ከማጣት ይልቅ ሞት ይሻላል በማለት ሁለት ጊዜ መስዋዕት ሆኖ የቀረበላት ጳጳሳት ተከታዮችዋን ያሰሩባት ያሰቃዩባት... ይህች «ፍልስፍና» «ለመሆኑ ምን ብታነሳ ነው ይህ ሁሉ የመጣባት?» ብሎ መጠየቅ ተገቢ ነው

ተከታዮቿ የፍልስፍና ትልቁና የመጀመሪያ ጥያቄዋ «እውነት» ስለሆነ ነው ይላሉ «እውነት ምንድ ነው?» የሚለው ጥያቄ ፍልስፍና የተጣለችበት መሠረት ነው "በእርግጥ የምናየውን ነገር የምናየው የምንሰማውን ነገር የምንስማው የምናሸተውን ነገር የምናሸተው የምንነካውን ነገር የምንነካው...እውነት ስለሆነ ነው? ወይስ እውነት ነው ብለን ስለምናስብ?" በማለት ፈላስፎቹ ይጠይቃሉ

ይኸ ዓለም «ለእያንዳንዱ ሰው እምነቱ የእሱ እውነት ነው» ይለናል፡፡ «እምነትህ እውነት ነው›› በሚለው በዚህ ዓለም ውስጥ ፈላስፎቹ ደግሞ «ማስረጃ ማቅረብ የማትችልበት እምነት እውነት ሊሆን አይችልም» ይላሉ።

ታላቁ ፈላስፋ ፍሬዴሪክ ኒቼ «የምታምነው ለመኖሩ ማስረጃ ማቅረብ ካልቻልክ እምነትህ ውሸት ነው አባቴ ለእኔ ያስተላለፈው እምነት አያቴ የነገረውን ነው  አያቴም የቅድም አያቴን ይዞ ለአባቴ አስተላለፈው እንግዲህ እኔ የምኖርበት እምነት አስቀድሞ ሌሎች የኖሩበትን እንጂ እኔ በማስረጃ አረጋግጬ ያገኘሁት አይደለም ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ለእምነትህ ማስረጃ የለህምና ውሸት ነው›› ይላል፡፡ ሌሎችም ፈላስፎች በዚህ ይስማማሉ፡፡

እንግዲህ ወደ «እውነት» ጥያቄ ስንመጣ ኒቼ ሊነሳ የሚገባው ፈላስፋ ይሆናል፡፡ እንደኒቼ እምነት «እውነት በተገቢ ሁኔታ የተነሳችበት የተጠየቀችበት በአንድ ሰውና በእንድ ቦታ ብቻ ነው ይኸውም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እሱም በጲላጦስ ነው» ይላል፡፡ አናቶሊ ፍራንስም በዚህ አባባል «እስማማለሁ ብቻ ሳይሆን አምንበታለሁም» ይላል።

«ጲላጦስም እንግዲህ ንጉሥ ነህን? አለው:: ኢየሱስም መልሶ እኔ ንጉሥ እንደሆንሁ አንተ ትላለህ እኔ ለእውነት ልመሰክር ተወልጃለሁ ስለዚህም ወደ ዓለም መጥቻለሁ ከእውነት የሆነ ሁሉ ድምፄን ይሰማል አለው፡፡ ጲላጦስም እውነት ምንድር ነው? አለው»
                                                ዮሐ 17:38
እንግዲህ ጲላጦስ በጥያቄ የጀመራትን «እውነት» ለመመለስ የመጀመሪያ ሞካሪዎች ነገር ግን በሚገባ ያልመለሱት በመባል የሚነቀፉት ሶፊስቶች (Sophists) ናቸው::

«ስለ እውነት ለማወቅ ከስሜት እንነሳ» ይላሉ (ይኸን አባባላቸውን ሌሎቹ ፈላስፎች ለጆሮ የሻገተ ጩኸት ነው ይሉታል)፡፡ «እውነት የሚመጣው ከስሜት ነው፤ ስለዚህም የእውነት ጥያቄ (በሌላ ኣባባል ለጲላጦስ ጥያቄ መልሱ) ስሜትህ ነው» ይላሉ፡፡ «ስለዚህም እውነት ማለት የምትቀምሰው፣ የምታሽተው ፣ የምትነካው፣ የምትሰማውና የምታየው ነገር ነው» ማለት ነው በዚህ መልስ መጀመሪያ አለመስማማቱን የገለፀው ፕሌቶ ነበር።

«እውነት ማለት ሶፊስቶች እንደሚሉት ስሜትህ ከሆነ እውነት የለም ማለት ነው» ይለናል። «ምነው?» ሲሉት «ምክንያቱም እያንዳንዱ ሰው አንድን ነገር የሚያሸተው፣ የሚነካው፣ የሚቀምሰው...በተለያየ መንገድ ነውና» ባይ ነው።

"አንድን ነገር ሁለት ሰው በሁለት መንገድ ከሰማው ወይም ካየው ነገሩ አንድ መሆኑ አብቅቶዋል፤ ስለዚህም ነገሩ በራሱ እውነት አይደለም» ነው አባባሉ።

"ስለሆነም የእውነት ጥያቄ የሚመለሰው በምክንያታዊ ማሰብ (Reasoning) እንጂ በስሜት አይደለም" ይላል። «አንድን ነገር ለማየት ማሰብ ያስፈጋል። አስቀድመህ የምታስበው ነገር ወደ አይንህ መልዕክት አስተላልፎ የምታየውን ማየት ቻልክ በሌላ አባባል የምታየው እውነት መሆኑን የምታውቀው በማሰብህ ነው ስለዚህ እውነት ማለት "ማሰብ" ነው» ይላል፡፡

ይኸን የፕሌቶን አባባል የተስማማበት አሪስቶትል ነበር፡፡ በዚህም ላይ ተመስርቶ «የማሰብ ሕግ» (Laws of Reasoning) የሚል አወጣ፡፡ «በዚህ ዓለም ላይ ያለ ማንኛውም ነገር እውነት የሚሆነው በመታየት በመነካት ወዘተ ሳይሆን ስለነገሩ በሚኖረን ሐሳብ ነው» ማለት ይሆናል፡፡

እዚህ ላይ እንደ ፊሮ ዓይነቶቹ ታላላቅ ጠርጣሪ ፈላስፎች ተነሱና «አንድን ነገር ሁልጊዜ እውነት የሚያደርገው ስለነገሩ ማሰብ ስለቻልን አይደለም» ይላሉ፡፡ በተለይም ፊሮ የአሪስቶትልን የማሰብ ሕግ» ሲያጣጥል «እንግዲህ አንድን ነገር እውነት የሚያደርገው ማሰብ ስለቻልን ከሆነ ሰው የሚያስብ ፍጡር ነው ሶቅራጥስ ደግሞ ሰው ነው ስለዚህም ሶቅራጥስ ሰው ስለሆነ ማሰብ ይችላል ማለት ነው ይኸ ደግሞ ሁልጊዜ አይሠራም። ምክንያቱም ሰው ሁሉ ማሰብ ይችላል ማለት ሞኝነት ነውና» ይለናል። በአጭሩ የእያንዳንዱ ሰው ሐሳብ ትክክለኛ ነው ማለት እስካልተቻለ ድረስ ስለ አንድ ነገር ማስብ ብቻ አንድን ነገር እውነት አያደርገውም ማለቱ ነው።
ጥበብ ከጲላጦስ


#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመድዎ #share @Qdist
Join&share 👉
@Qdist
@Qdist
@Qdist
For any comment&question ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት 👉 @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

21 Oct, 15:56


SORRY GUYS AND ALSO THANK YOU EVERYTHING
I LOVE YOU EVERYONE

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

21 Oct, 08:19


ቻሌንጅ 2

እኔ private ሊንክ እምሰጠዉ እና ስራ መስራት እሚፈልግ ሰዉ inbox ያናግረኝ ke 8000-10000 ሰብስክራይብ አስደርጋለሁ ብቃቱ አለኝ እሚል ሰው ካለ የ 5000 ብር ሽልማት አዘጋጅተናል

ከፈለጋቹ በምታዉቁት ሰዉ ቻናል ማስታወቂያ ማሰራት ትችላላቹ ከፈለጋቹ ደሞ ይሆናል ብላቹ ያሰባቹትን መንገድ ምርጫዉ የናንተ ነዉ አደርገዋለዉ የሚል ሰዉ inbox

እሚቆየዉ ለ20 ቀን ብቻ ነዉ በ 20 ቀን እችላለሁ እሚል ሰዉ ኢንቦክ
ስ @e_t_l_bot ያናግረኝ

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

20 Oct, 15:16


ቻለንጅ 1

ሽልማት ያለው ቻለንጅ ለመሳተፍ ዝግጁ ናችሁ?
ግጥም
አስተማሪ የህይወት ታሪክ
ፍልስምና እንዲሁም አስተማሪ እና ቁም ነገር አዘል ነገር ያላችሁ በሙሉ ተሳተፉ
በመነባንብ መልኩም መሳተፍ ይቻላል ግጥምም በተመሳሳይ

ቢቻል የተኮረጀ ባይሆን ይመረጣል
አሸናፊዎች የሚለዩት
1, የህዝብ ቻናል ላይ ሼር የተደረገለት
2, ብዙ ሼር ካለው ያ ማለት ሼር የምታደርጉላቸው ልጆች ለሌሎች ደሞ እንዲያደርጉ ተናግራችሁ የሼር ብዛታችሁን መጨመር ትችላላችሁ
3, ብዙ እይታ ካለው
4, የራስ ፈጠራ ከሆነ

1ኛ ለዎጣ 250 ብር
2ኛ 150ብር
3ኛ 100ብር
አካውንት የሌለው ሰው ካለ በካርድ መልክ መውሰድ ይችላል

መልካም እድል ሰዎች🏅🏅🏅🏆


የናንተ ስራ ቻናል ላይ የሚለቀቀው ከጥቅምት 30ጀምሮ ነው የሰራችሁትን እስከዛ @e_t_l_bot በዚህ መላክ ትችላላችሁ ውጤቱ በቻናሉ ተከታዮች ይወሰናል በድጋሚ መልካም እድል

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

20 Oct, 08:35


አድባር ጠራኝ
ጌታ መራኝ
ለግጥም ብዕሬን አተባ
በሬን ከፍቼ ባባርረው በጓሮ በር ዞሮ ገባ።

ቃላትን በቃላት ላይ ደራረበ
መንፈሱ በላዬ ላይ አረበበ
ስሜት ሰጠኝ
ሀሳብ ሰጠኝ...
በጩኸት መሀል ሰማሁት በዝምታ መሀል ዋጠኝ
ረበሸኝ በጠበጠኝ...
ሁለመናዬን የራሱ አረገ
መንፈሴም ከኔ ጋር ሆኖ ጥሎኝ ሰማያት አረገ።

እኔን ለኔ ተወልኝ
ነፍሴን በፍቅሩ አሻፈዳት
አይኔ እያየ ከጉያዬ ከጎኔ ስቦ ወሰዳት
እኔን ግን ለኔ ተወልኝ
ነፍሴን ግን በፍቅሩ ሰዋት።

ከኔ ቀጥሎ
ከሰው ነጥሎ
እንደ ባዕታዊ ባዕት ውስጥ ዘጋባት ብርሃን ከልክሎ
መንፈሷን ላበራች ውብ ነፍስ ሌሊት ነው ሚሻላት ብሎ።

አድባር ጠራኝ
ጌታ መራኝ
ቀረብ ስል ሶስት አረገኝ
( እኔ ~ ነፍሴ ~ የነፍሴ መንፈስ )
ከወንጌሉ አጣቅሼ
ምዕራፍ እንተን ቁጥር እንትን ስል ጠቅሼ
እንዳልችል እንኳ
"እኔና ነፍሴ አንድ ነን
እኔ በነፍሴ እኖራለሁ
ነፍሴም በኔ ዘንድ አለች "
ብሎ ማለት
እኔነቴ ያለ ነፍሴ እድፍ ጉድፍ በዛበት።

ንግድ አረኩት ሁሉን ነገር ያዋጣል አያዋጣም ጥናት
ለወለድኳቸው ግጥሞች አልችል አልኩኝ መሆን እናት።
ስሜት ሰጦኝ
ብዕር ሰጦኝ
ልብ ሰጦኝ....
ከሰዎች መሀል ነጥሎ
ቅፅበታትን ከውብ ቃላት አንድ አድርጎ ሰጦኝ መርጦ
አያያዙን አልችል አልኩኝ አዕምሮዬ ከልቤ በልጦ።

ክፋቴ የሞት እኩያ ምቀኝነት የ 'ለት ግብሬ
ግጥም ብዬ የምፅፈው ስሜት አልባ ተራ ወሬ
ለጥበብ ባደላደለው
ልብ በሚባል እርሻ የበቀልኩኝ ያሳብ አረም
ዙሪያዬን በሾህ አጥሬ ካመት ዓመት ማልታረም።
ከዛ ግን ጌታ መጥቶ
እኔን ጠርቶ
ነፍሴን ነፃ ሊያወጣት ከራሴው ቀራኒዮ ላይ ሰቀለኝ
ያን ጊዜ ነፍሴ አመለጠች አንዳችም ሸክም ቀለለኝ።

ከጌታ ስር ሄጄ ተደፋሁ በፅኑ እንባ ተላመንኩት
" ነፍሴን ከኔ እንደነጠልክ
እኔን ከኔ ነጥልና
እኔን በነፍሴ አኑረኝ'' አልኩት።

#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመድዎ #share @Qdist
Join&share 👉
@Qdist
@Qdist
@Qdist
For any comment&question ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት 👉 @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

19 Oct, 10:05


ምድር ላይ ብዙም ያልሰነበተው ካሙ ከሆነ ስፍራ በባቡር ለመሳፈር ሲጣደፍ ጓደኛዉ በመኪና ካላደረስኩህ ብሎት እያሽከረከር ሲጓዝ በሌላ መኪና ይገጫሉ። ጓደኛዉ ሲተርፍ ካሙ ግን በአደጋው ይሞታል። ልክ እንደ ፅሁፎቹ አሟሟቱም ፍልስፍናዉን የሕይወት ወለፈንድን- ያደምቃል ይላሉ ብዙዎች ከአባባሎቹ ለዛሬ እንቀንጭብ

በዚህ ሁሉ መኃል መረዳት የቻልኩት በተሸፈነ ድቅድቅ ክረምት ውስጥም የተሸሸገ በጋ በውስጤ ተዳፍኖ መኖሩንና ማግኘቴን ነው

እስከ ዕንባህ የመጨረሻ ጠብታ ጥረስ ኑር
ደስተኛ ለመሆን ስለሌሎች ከልክ በላይ መጨነቅ የለብንም።

በሁሉም ውብ ልብ ውስጥ አንዳንዴ ኢ-ሰብአዊ የመሆን ነገር አለ።

ሰዎች ያለቅሳሉ ምክንያቱም ይች ዓለም ፍትሐዊ አይደለችምና

እኔ ያለሁት ስላመጽኩ ነው።

ነጻነት የተሻለ የመሆን ዕድል እንጂ ሌላ አይደለም።

ልቦ-ለድ በምስል የተገለጸ ፍልስፍና እንጂ ሌላ ዐይደለም

በዓለም ላይ ያለው ክፋት ሁል ጊዜ ከድንቁርና የሚመጣ ነው፣ መልካም ህሳቤም ከሌለው የመጥፎ ስሜት ያህል ይጎዳል።

የሕይወት ትርጉም ምን መሰለህ(ለሽ) 'ራስህን ከማጥፋት የሚከለክልህ የምታደርገው ማንኛውም ነገር እሱ የሕይወት ትርጉም ነው።

በየቀኑ የምትወስነው በጣም አስፈላጊው ውሳኔ 'ራስህን ላለመግደል መወሰን ነው።

ሕይወት የሁሉም ምርጫዎችዎ ድምር ውጤት ነው፣ ታዲያ ዛሬ ምን እያደረክ ነው?
✍🏽አልበርት ካሙ


#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመድዎ #share @Qdist
Join&share 👉
@Qdist
@Qdist
@Qdist
For any comment&question ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት 👉 @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

18 Oct, 15:59


#ስሞት ዝም በይኝ

ነፍሴም በፀጥታ
ሁሉን ነገር ትታ
እንዲያው ትረፍበት
አይንሽን ሳላየው
ድምፅሽን ሳልሰማ
ከሰው አፍ እርቄ
ማፍቀሬን ደብቄ
መስኮቴን ዘግቼ
ስምሽን ሳልጠራ
ወሬሽን ሳልሰማ
ዝም ጭጭ እንዳልኩኝ
አራሴው ልሰዋ

እናም አትምጪብኝ
ልቤን አታጓጊው
ከሀጢያት ለመንፃት
ባዶ ተስፋ አትስጪው
መሔጃዬ ሲቀርብ
ሆዴን አታባቢው
የእስከዛሬው ይብቃ ዳግም አትበድይኝ
ብቻ እረፍት እንዳገኝ
እንዲሁ እንዳለሁኝ
ችላ ችላ ብለሽ
ስሞት ዝም በይኝ!!

የኔ ፍቅር
የልቤ ላይ ንግስት
እኔን የገዛሽኝ
የፍቅሬ እመቤት
ሁሌ ምትማርኪኝ
የአይኔ አራብ ስስት
ከዚህ ከደሳሳው
ዘማማው ጎጆዬ
መተሽ ከማታቂው
ገብተሽ ከጓዳዬ
እድል ስጠኝ አትበይ
ጊዜም ስጠኝ አትበይ
ሂጂልኝ ከፊቴ
በሬንም አትግፊ
ከቶም አታንኳኪ
እኔ ብቸኛ ነኝ
እንደድሮው ሆድሽ
እንዳዛኙ ልብሽ
እራስሽ እራቂኝ
ጣል ጣል አድርጊኝ
እፎይታን እንዳገኝ
ስሞት ዝም በይኝ።

ደቂቃም አትቆዪ
ዘግይተሻልና
ወደቤትሽ ሂጂ
ሌላም አላስቸግር
በዚህ ብቻ እርጂኝ
ጊዜው ስለሄደ
ቀኑም ስለመሸ
እረፍትን እንዳገኝ
ለፅድቅ እንዲሆንሽ ስሞት ዝም በይኝ።

#ከወደዱት_ለወዳጅ_ዘመድዎ #share @Qdist
Join&sha
re 👉
@Qdist
@Qdist
@Qdist
For any comment&question ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት 👉 @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

17 Oct, 16:25


*ዝምታዋ ገፋኝ *

ዝምታዋ ገፋኝ አራቀኝ ከጎኗ
ፍቅሯን ለመናገር ቢዘጋ ልሳኗ
ባንኳኳው ደጃፏን ሚከፍትልኝ ባጣ
ከጎረቤት ዞርኩኝ ሚሰማኝ ከመጣ
ቃላትን ቀምሬ አስውቤ አሽቀርቅሬ
ዝምታ መልስ ሆነ ፍቅሬን በማብሰሬ
የውስጤን መከፋት በውስጤ ቋጥሬ
ለመሄድ ተነሳው ወደ መራኝ እግሬ
ወድሻለው ስላት መውደዷን ባትነግረኝ
ከሌላ እንድከጅል ዝምታዋ ገፋኝ

ነግሪያት ነበረ.....
ልክ እንደፏፏቴ ድምፄን ብዙ አድርጌ
በበራቸው ደጃፍ አንገቴን አስግጌ
አባቷም ዘልፈውኝ ብለውኝ ባለጌ
አሳዲጊም የለህ መረን የልጅ ዋልጌ
እያሉኝ ሰምታለች እኔም ሰምቻለው
ፍቅሬን ተናገርኩኝ ግን ከቁብ ሳላየው

እሷ ግን አድምጣኝ አንዳችም አላለች
የኔን ማፍቀር ሰምታ ማፍቀሯን ደበቀች
አስር ጊዜ ሰምታ እንዳልሰማ ሆነች
ዝምታዋ ቢያል ደጋግሞ አስፈራኝ
አታፈቅረኝ ብዬ ልርቃት ወሰንኩኝ
በርሃ አቋርጬ ከደጋው ስገባ
ወዴት ነህ አለችኝ ስለኔ አስባ

የብርዱ ወር አልፎ ስሟሟቅ ስድላላ
ትከተለኝ ጀመር በሄድኩበት ሁላ
እወድህ ነበረ በድንገት ብትለኝ
የመፍራቷን ሚስጢር ደርሳ ብታዋየኝ
ያን ፍቅሬን አስቤ እንባ ተናነቀኝ
ግን ምንላርግ ርቄያለው ዳግም ላትመልሰኝ
ልቧ እየፈለገ ዝምታዋ ገፋኝ፡



#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመድዎ #share @Qdist
Join&share 👉
@Qdist
@Qdist
@Qdist
For any comment&question ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት 👉 @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

14 Oct, 21:02


ማን ነው ከኔ የተሻለው?

እኔ ማለት በፈተና ጊዜ በጭንቀቴ ጊዜ ፈጣሪ እርዳኝ የምል ብኩን ሃዘኔን ጭጭንቀቴን እንዳስወገደልኝ ደግሞ በቅጡ ተረጋግቼ እንኳን ማመስገን የማላቅ ደካማ ደስታን ሳገኝ ደስታን እንዳገኝ ያደረገኝ ፈጣሪ መሆኑን የምረሳ ደካማ መን ነው ግን ከኔ የተሻለ?

ወዳጆቼ በሁሉም ነገር አምላክን እናመስግን መቼም ሁላችንም በአፅንኦት የምናምነው አምላክ አለን በመከራ ብቻ ፈላጊው አንሁን። በሁሉም ነገር ፈጣሪያችንን ከፊት ለፊት እናስቀድም።

በፈተና አማራሪ በፈተና ደካማ መስለን ወደ ቤቱ አንሂድ ይልቁንስ ሳንደክም ቀርበነው እንታረቀው ፈተናን እሚያበዛብን ከቤቱ እንዳንዎጣ ስለሚፈልግ ነው።

ዘዳጄ እያለህ አመስግነው
የበደለህን ይቅር በለው
ጠላትህን እንደ እራስህ ውደደው
ክፉ የሆኑብህን በፍቅር አሸንፋቸው
እሲኪ ነገ እንደነጋ የአኮረፋችሁትን ሰው ይቅርታ በሉት
የበደላችሁን ሰው በደሉን ባትረሱትም ተውት እና አናግሩት
ፍቅር ያሸንፋል የሚለው አባባል በታሪክ ብቻ አይዎራ በተግባርም ፈፅሙት
ወዳጆቼ ቂም በቀል ሰላምን ይነሳል
የሰላም ናፋቂ የፍቅር ሰባኪ መሆን ከፈለጋችሁ ይቅርታን አስቀድሙ በደልን እርሱ ፈጣሪያችሁን አስቀድሙ
ከኔ የተሻለ ሁሉ ይህን ያድርግ ብልጥ ሰው መከራን ከሰው ይማራል ሞኝ ደግሞ ከራሱ ይባላል
እንደ እኔ እስኪደርስባችሁ አጠብቁ ፈጣሪን አመስጋኝ ይቅርታን ሰላም እና ፍቅርን ናፋቂዎች ሁኑ
አለም አንድ ትሆናለች
እውነትን ትሰብካለች
በፍቅር ትወድቃለች
ቼር ሌሊት ወዳጆቼ🙏🙏


#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመድዎ #share @Qdist
Join&share 👉
@Qdist
@Qdist
@Qdist
For any comment&question ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት 👉 @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

12 Oct, 20:52


በአንድ ወቅት አንድ በፈጣሪ የሚያምን የተከበረ ሰው ባልና ሚስት የሆኑ ድሀዎችን በአትክልተኝነት ይቀጥራቸዋል ይህ የተከበረ ሰውዬ አንድ ቀን በረንዳው ላይ ቁጭ ብሎ ሲመለከት የአትክልተኛው ሚስት በጣም ውብ መሆኗን ያይና ያለወትሮው ስሜቱ ይነሳሳበታል። ከእሱና ከእነሱ በቀር በግቢው ውስጥ ማንም እንደሌለ ካረጋገጠ በኃላ ሆን ብሎ ባሏን የሆነ ነገር እንዲያመጣለት ራቅ ወዳለ ቦታ ይልከዋል ባሏ ወደተላከበት ቦታ ሲሄድ እሱና የአትክልተኛው ሚስት ብቻ ይቀራሉ ይህኔ ይህ የተከበረ ሰው የአትክልተኛውን ሚስት ጎትቶ ብዙ በር ወዳለው ዘመናዊ ቤቱ ያስገባታል።

ልጅቱም ሰውየው ኃያልና የተከበረ ስለሆነ እምቢ ብለው ባሌንም ሆነ እኔን ሊጎዳን ይችላል ብላ በመፍራት ዝም ብላ ትገባለታለች ሰውየው ቤቱ ውስጥ ካስገባት በኃላ ልብሶቹን እያወላለቀ፡- "ማንም እንዳያየን ሁሉንም በሮችን ዝጊያቸው ይላታል" ልጅቱም በሮችን ስትዘጋጋ ከቆየች በኃላ "አሁን የፈለጉትን ማድረግ ይችላሉ ጌታዬ! ከአንዱ በር በቀር ሁሉንም ዘግቻቸዋለሁ አንዱን በር ግን መዝጋት አልቻልኩም!'' ትለዋለች።

ሰውየውም ዞር ዞር ብሎ አይቶ ሁሉም የቤቱ በሮች እንደተዘጉ ካረጋገጠ በኃላ ስለየትኛው በር እንደምታወራ ግራ ገብቶት ''የትኛውን በር ነው መዝጋት ያልቻልሽው?'' ሲላት ልጅቱም አንገቷን ደፍታ "አይታይዎትም ጌታዬ በእኛና በእግዚአብሄር መካከል ያለው በር እኮ ክፍት ነው። ልዘጋው ብሞክርም አልቻልኩም። እሱም ከቅድም ጀምሮ እያየን ነው። ከቻሉ እርስዎ ይዝጉትና የፈለጉትን ያድርጉ።" ብላ መለሰችለት

ሰውየውም ምንም እንኳን ስሜት አካልቦት መጥፎ ድርጊት ለመፈፀም ቢነሳሳም ከዚያ በፊት ባለው ህይወቱ በጥሩ እምነት ታንፆ ያደገ ነበርና ይህንን ስትለው ወደ ቀደመ ማንነቱና እምነቱ ተመልሶና የጋለው ስሜቱ ሙሽሽ ብሎ ቀዝቅዞ ይቅርታ ጠይቆ ምንም ሳያደርግ አሰናበታት ይባላል።

አንተስ ከታሪኩ ምን ተማርክ? ፈጣሪህን የሚያህ መሆኑን ረስተህ ወይም ንቀህ ሰውን ግን ፈርተህ ተደብቀህ የፈፀምከው ድርጊት አለ?
ቸር ምሽት 🙏

#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመድዎ #share @Qdist
Join&share 👉
@Qdist
@Qdist
@Qdist
For any comment&question 👉 @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

11 Oct, 15:33


ቻለንጅ 1

ሽልማት ያለው ቻለንጅ ለመሳተፍ ዝግጁ ናችሁ?
ግጥም
አስተማሪ የህይወት ታሪክ
ፍልስምና እንዲሁም አስተማሪ እና ቁም ነገር አዘል ነገር ያላችሁ በሙሉ ተሳተፉ
በመነባንብ መልኩም መሳተፍ ይቻላል ግጥምም በተመሳሳይ

ቢቻል የተኮረጀ ባይሆን ይመረጣል
አሸናፊዎች የሚለዩት
1, የህዝብ ቻናል ላይ ሼር የተደረገለት
2, ብዙ ሼር ካለው ያ ማለት ሼር የምታደርጉላቸው ልጆች ለሌሎች ደሞ እንዲያደርጉ ተናግራችሁ የሼር ብዛታችሁን መጨመር ትችላላችሁ
3, ብዙ እይታ ካለው
4, የራስ ፈጠራ ከሆነ

1ኛ ለዎጣ 200 ብር
2ኛ 150ብር
3ኛ 100ብር
አካውንት የሌለው ሰው ካለ በካርድ መልክ መውሰድ ይችላል

መልካም እድል ሰዎች🏅🏅🏅🏆


የናንተ ስራ ቻናል ላይ የሚለቀቀው ከጥቅምት 30ጀምሮ ነው የሰራችሁትን እስከዛ @e_t_l_bot በዚህ መላክ ትችላላችሁ ውጤቱ በቻናሉ ተከታዮች ይወሰናል በድጋሚ መልካም እድል

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

11 Oct, 15:32


ሰው እንዳንተ ነው

ዛሬ ላይ ቁሞ ትላንትን በትዝታ ነገን በስጋት የሚኖር ሰው ማለት እንዳንተ ነው ዛሬን ለመኖር የማይደፍር በሰንጣቃ ዓለት እንዳለ በትላንትናና በነገ መካከል የሚተክዝ ነው ሰው ማለት እንደ አንተ ነው እውነቴን ነው የቅዱሳን አምላክ ምስክሬ ነው የተሰማህን ያ ሰው ተሰምቶታል ያመመህ ሕመም እዚያ ሰውዬ ጋ እየጀመረ ነው :: ሰው ማለት እንደ አንተ ነውና ኅሊናው ሳይወቀስ አይቀርም ክፋት ሲያበዛ በበደል ላይ በደል ሲጨምር ዝምታህን ሰብሮ ክፉ ሊያናግርህ ሲሻ ውስጡ እየተሰቃየ ነው ባንተ ስህተት ውስጥ ለመደበቅና እፎይታ ለማግኘት እየፈለገ ነው አንተም ብትሆን እየበደልካቸው ዝም ሲሉህ ያምሃልና በጣም ክፉ ስትሆን የሚተፋህ በጣም ደግ ስትሆን ሰስቶ የሚርቅህ ሰው ማለት እንዳንተ ነው እንደ አንተም ስለሆነ መሸነፍን የማይፈልግ ይቅርታ ማለትን እንደ ተራራ የሚያይ ነው ::

#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመድዎ #share @Qdist
Join&share 👉
@Qdist
@Qdist
@Qdist
For any comment&question 👉 @e_t_l_bot

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

10 Oct, 10:09


ቻለንጅ 1

ሽልማት ያለው ቻለንጅ ለመሳተፍ ዝግጁ ናችሁ?
ግጥም
አስተማሪ የህይወት ታሪክ
ፍልስምና እንዲሁም አስተማሪ እና ቁም ነገር አዘል ነገር ያላችሁ በሙሉ ተሳተፉ
በመነባንብ መልኩም መሳተፍ ይቻላል ግጥምም በተመሳሳይ

ቢቻል የተኮረጀ ባይሆን ይመረጣል
አሸናፊዎች የሚለዩት
1, የህዝብ ቻናል ላይ ሼር የተደረገለት
2, ብዙ ሼር ካለው ያ ማለት ሼር የምታደርጉላቸው ልጆች ለሌሎች ደሞ እንዲያደርጉ ተናግራችሁ የሼር ብዛታችሁን መጨመር ትችላላችሁ
3, ብዙ እይታ ካለው
4, የራስ ፈጠራ ከሆነ

1ኛ ለዎጣ 200 ብር
2ኛ 150ብር
3ኛ 100ብር
አካውንት የሌለው ሰው ካለ በካርድ መልክ መውሰድ ይችላል

መልካም እድል ሰዎች🏅🏅🏅🏆


የናንተ ስራ ቻናል ላይ የሚለቀቀው ከጥቅምት 30ጀምሮ ነው የሰራችሁትን እስከዛ @e_t_l_bot በዚህ መላክ ትችላላችሁ ውጤቱ በቻናሉ ተከታዮች ይወሰናል በድጋሚ መልካም እድል

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

08 Oct, 15:16


ቤተሰብ ሼር እየታየኝ አይደለም ምንድን ነው እስኪ የምታነቡት ሁሉ ቢያንስ ለ10 ጓደኞቻችሁ #share አድርጉ☝️☝️☝️ 500ሰው ለ10 ጓደኞቻችሁ🙏 @qdist

ኢትዮ ግጥም እና ፍልስፍና ethio poem&philosophy

08 Oct, 15:16


​​ውሸት ነው

ፍቅሬ እንዳንዴ አመሌን የማጣው
በንፁ ጨዋታሽ የምነጫነጨው
በጥርስሽ ብርሀን ፊቴን የማጠቁረው
ምነው ሆዴ ስትይ ብወድሽ የምለው
እውነት እንዳይመስልሽ አይደለም ውሸት ነው

ደግሞም አንዳንድ ቀን                         
   እኔ አንቺ አብረን ሆነን
የምለይሽ በሰመመን 
ከሰመመን መልሰሽኝ
ምን ነው ሆዴ ስትይኝ                                  
ሀሳብ የከተተኝ
ፍቅርሽ ነው ያልኩትኝ
እውነት ይሁን ውሸት እኔንም አልገባኝ
ሌላም በሌላ ቀን አዱኛ ስተርፈን
አድባር ሲቀርበን ፍቅር በልተን
ፍቅር ሰርተን እንዳበቃን
ታፈቅረኛለህ ስትይኝ ከእኔ በላይ ያልኩትኝ
በእውኔ አይሆንም በህልሜ መሰለኝ
ደግሞም ሌላ ጊዜ
ከሀገር ምድር ተገልለን
እኔ ባንቺ አንቺ በእኔ ተጠልለን
ምሽት ደርሶ ሲለያየን
ጀንበር ዘቀዘቀችች መለየት ሊሆን ነው
ነግቶ እስከማይሽ ናፍቆት ብዙ ነው
ብዬ ያወራሁሽ እኔ ልሙት ብዬሽ
እውነት እውነት ስልሽ
እውነት እንዳይመስልሽ
ውሸት ነው ልንገርሽ
በፈጠረሽ አምላክ ይሄን ሁሉ እውነት
አሁን የነገርኩሽ እራሱ ውሸቱን እውነት
እንዳይመስልሽ እውነት ግን አለሜ
ውሸት ይመስልሻል አንቺን ባላፈቅር
ይሄ ሁሉ ይወራል ውሸቴን ነው ተብሎስ
ከወደዱት ሌላ ለጠላት ይፃፋል
እውነቱን ልንገርሽ ሊፃፍም ይችላል
እውነት ነው ብሎ ማታለል ይቀላል
እኔ ግን ልንገርሽ
እውነት ነው ስልሽ
እውነት እንዳይመስልሽ
ውሸት እንዳይመስልሽ...
ኤፍሬም ስዩም

#ከወደዱት_ለወዳጅ_ዘመድዎ #share
@qdist
@qdist
@qdist
For any comment&question 👉 @e_t_l_bot