አቡ ሱሀይል @hamidabuhamid Channel on Telegram

አቡ ሱሀይል

@hamidabuhamid


ﺑِﺴْﻢِ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﺍﻟﺮَّﺣْﻤَﻦِ ﺍﻟﺮَّﺣِﻴﻢِ
"ﺍﻗْﺮَﺃْ ﺑِﺎﺳْﻢِ ﺭَﺑِّﻚَ ﺍﻟَّﺬِﻱ ﺧَﻠَﻖَ"
"አንብብ በዚያ(ሁሉን)በፈጠረው ጌታ ስም"
አል ዐለቅ ምእራፍ/1

በዚህ ገፅ ላይ የተለያዩ ኢስላማዊ መልእክቶችና፣በተለያየ ዘርፍ የሚሰጡ ት/ቶችን በድምፅና በቪዲዮ ያገኙበታል።

አቡ ሱሀይል (Amharic)

አቡ ሱሀይል ለሁሉም ኢስላማዊ መልእክቶች እና የሚሰጡ ት/ቶችን ማሰብህን በዚህ አዝምሮ እንዲህ ሲል የገለጸው ኢስላም መደብ የሚለዋዋጭ ለማግኘት ከመጀመሪያ በላይ ያገኙበታል። አንዲሆን በፊታው የቴሌግራም መረጃዎችን እና ቪዲዮዎችን ከድምፅ እና ቪዲዮ በመላክ አቅምን ይፈጠራል። እንደምታሳክ ነው? አቡ ሱሀይል ለሁሉም ኢስላማዊ መልእክቶች እና የሚሰጡ ት/ቶችን ማሰብህን ለማግኘት ችግር እንድሚል ይጠቀሙ።

አቡ ሱሀይል

15 Feb, 11:56


በአል ዒምራን የቁርአን እና ኢስላማዊ ትምህርት ተቋም በማስተማር ላይ ከሚገኙ ኡስታዞች አንዱ ናቸው።

በሀገር ውስጥ እና በተለያዩ ሀገራት ዒልም ቀስመው በመምጣት ሙስሊሙን ኡማ በማገልገል ላይ ይገኛሉ ኡስታዝ ኢልያስ ከማል።

አሁን ደግሞ በአል ዒምራን የቴሌ ግራም ቻናል የተሰናዳውን እና ረመዳንን ከፍ ባለ ራዕይ እንድንቀበለው የሚረዳንን የታላቁ ዓሊም ዒዝ ኢብን ዓብዱሰላም ዝግጅት የሆነውን "መቃሲዱ ሰውም "(የፆም ግቦች) የተሰኘውን ኪታብ በቀጥታ ከምሽቱ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ የሚያቀርቡልን ይሆናል።

አቡ ሱሀይል

15 Feb, 11:38


🕋ጥቂት ቦታ ብቻ ቀረ

የረመዳን ዑምራ ከነብዩ ጋር ሀጅ እንደማድረግ ነዉ
ፈጥነው ይመዝገቡ
ለበለጠ መረጃ:

+251984925484
+251984561484
+251912616170
+251912707039

📍 ቦሌ ድልድይ የሺ ህንፃ  5ኛ ፎቅ
     ቢሮ ቁጥር 506



ሼር ሼር የጉሩፕ

አቡ ሱሀይል

14 Feb, 18:03


https://vm.tiktok.com/ZMknYqfpV/

አቡ ሱሀይል

14 Feb, 06:47


ሼር አድርጉልን🙏

አቡ ሱሀይል

13 Feb, 18:36


# ደዒፉ ኢማንህ ነው።
የተጠናወተህን ስንፍና፣ ሐዲሱ ደዒፍ ነው በማለት ልትሸፍነው አትሞክር!
አንድ ሐዲስ ደዒፍ ነው ማለት፣ ጭራሹኑ አይሰራበትም ማለት አይደለም።
ካለወቁ መጠየቅ እንጂ፣ መቃወም አግባብ አይደለም !

አቡ ሱሀይል

13 Feb, 18:29


በረሱለላህ ﷺ ላይ ሰለዋት በማውረድ ጊዜን ማሳለፍ፣ በኢስቲጝፋር ከማሳለፍ ሙሉ በሙሉ ይበልጣል !
አል ኢማሙል–ከቢር ሺሃቡዲን አል ረምሊይ (ቁ.ሲ)
___
ሰለዋት ታይታ ማይገባበት፣ ፍፁም ቅቡል ዒባዳ ነው።
ሰለዋት ጭንቀትን ይገፋል፤ ወንጀልንም ያስምራል ።
ሰሉ ዐላ ረሱሊላህ ﷺ 😍😍😍

አቡ ሱሀይል

13 Feb, 16:51


ደካማው ባሪያህ… ኃጢአተኛው ባርያህ
እዝነትህን ሽቶ
ጠንቷል ከደጃፍህ 🤲

አቡ ሱሀይል

13 Feb, 16:43


# ያ ረብ
በጭንቅ ውስጥ ሆነው ፈረጃን የሚሹ ባሮች አሉህና ብስራትህን ለግሳቸው! 🤲

አቡ ሱሀይል

13 Feb, 16:35


https://youtu.be/Ng5BcNQtRsg?si=aF3zcj02zaRE21cx

አቡ ሱሀይል

13 Feb, 16:20


« ﺍﻟﻠَّﻬُﻢَّ ﻳَﺎ ﺫَﺍ ﺍﻟْﻤَﻦِّ ﻭَﻟَﺎ ﻳُﻤَﻦُّ ﻋَﻠَﻴْﻪِ، ﻳَﺎ ﺫَﺍ ﺍﻟْﺠَﻠَﺎﻝِ ﻭَﺍﻹِﻛْﺮَﺍﻡِ، ﻳَﺎ ﺫَﺍ ﺍﻟﻄَّﻮْﻝِ ﻭَﺍﻹِﻧْﻌَﺎﻡِ . ﻟَﺎ ﺇِﻟَﻪَ ﺇِﻟَّﺎ ﺃَﻧْﺖَ ﻇَﻬْﺮَ ﺍﻟﻠَّﺎﺟِﺌﻴﻦَ، ﻭَﺟَﺎﺭَ ﺍﻟْﻤُﺴْﺘَﺠِﻴﺮِﻱ
ﻥَ، ﻭَﺃَﻣَﺎﻥَ ﺍﻟْﺨَﺎﺋِﻔِﻴﻦَ . ﺍﻟﻠَّﻬُﻢَّ ﺇِﻥْ ﻛُﻨْﺖَ ﻛَﺘَﺒْﺘَﻨِﻲ ﻋِﻨْﺪَﻙَ ﻓِﻲ ﺃُﻡِّ ﺍﻟْﻜِﺘَﺎﺏِ ﺷَﻘِﻴًّﺎ ﺃَﻭْ ﻣَﺤْﺮُﻭﻣًﺎ ﺃَﻭْ ﻣَﻄْﺮُﻭﺩًﺍ ﺃَﻭْ ﻣُﻘَﺘَّﺮًﺍ ﻋَﻠَﻲَّ ﻓِﻲ ﺍﻟﺮِّﺯْﻕِ، ﻓَﺎﻣْﺢُ ﺍﻟﻠَّﻬُﻢَّ ﺑِﻔَﻀْﻠِﻚَ ﺷَﻘَﺎﻭَﺗِﻲ ﻭَﺣِﺮْﻣَﺎﻧِﻲ ﻭَﻃَﺮْﺩِﻱ ﻭَﺇِﻗْﺘَﺎﺭَ ﺭِﺯْﻗِﻲ، ﻭَﺃَﺛْﺒِﺘْﻨِﻲ ﻋِﻨْﺪَﻙَ ﻓِﻲ ﺃُﻡِّ ﺍﻟْﻜِﺘَﺎﺏِ ﺳَﻌِﻴﺪًﺍ ﻣَﺮْﺯُﻭﻗًﺎ ﻣُﻮَﻓَّﻘًﺎ ﻟِﻠْﺨَﻴْﺮَﺍﺕِ، ﻓَﺈِﻧَّﻚَ ﻗُﻠْﺖَ ﻭَﻗَﻮْﻟُﻚَ ﺍﻟْﺤَﻖُّ ﻓِﻲ ﻛِﺘَﺎﺑِﻚَ ﺍﻟْﻤُﻨَﺰَّﻝِ ﻋَﻠَﻰ ﻟِﺴَﺎﻥِ ﻧَﺒِﻴِّﻚَ ﺍﻟْﻤُﺮْﺳَﻞِ : ﴿ﻳَﻤْﺤُﻮ ﺍﻟﻠﻪُ ﻣَﺎ ﻳَﺸَﺎﺀُ ﻭَﻳُﺜْﺒِﺖُ ﻭَﻋِﻨْﺪَﻩُ ﺃُﻡُّ ﺍﻟْﻜِﺘَﺎﺏِ﴾، ﺇِﻟﻬِﻲ ﺑِﺎﻟﺘَّﺠَﻠِّﻲ ﺍﻟْﺄَﻋْﻈَﻢِ ﻓِﻲ ﻟَﻴْﻠَﺔِ ﺍﻟﻨِّﺼْﻒِ ﻣِﻦْ ﺷَﻬْﺮِ ﺷَﻌْﺒَﺎﻥَ ﺍﻟْﻤُﻜَﺮَّﻡِ، ﺍﻟَّﺘِﻲ ﻳُﻔْﺮَﻕُ ﻓِﻴﻬَﺎ ﻛُﻞُّ ﺃَﻣْﺮٍ ﺣَﻜِﻴﻢٍ ﻭَﻳُﺒْﺮَﻡُ، ﺃَﻥْ ﺗَﻜْﺸِﻒَ ﻋَﻨَّﺎ ﻣِﻦَ ﺍﻟْﺒَﻠَﺎﺀِ ﻣَﺎ ﻧَﻌْﻠَﻢُ ﻭَﻣَﺎ ﻟَﺎ ﻧَﻌْﻠَﻢُ ﻭَﻣَﺎ ﺃَﻧْﺖَ ﺑِﻪِ ﺃَﻋْﻠَﻢُ، ‏»

አላህ ሆይ! የውለታ ባልተቤት፣ ውለታ የሌለብህ፤ የመመፃደቅ ባልተቤት፣ የማይመፃደቁብህ፤ የግርማና የመክበር ባልተቤት፤ የችሮታና የመስጠት ባልተቤት፤ ከአንተ በቀር አምልኮ የተገባው አምላክ የለም፤ የስደተኞች ተገን፣ የጥገኛ ፈላጊዎች ከለላ፤ የፈሪዎች ሰላም ማግኛ የሆንክ
በመጽሐፎቹ እናት ውስጥ እድለ ቢስ፣ (ከእዝነትህ) የተነፈግኩ፣ የተባረርኩ፣ ወይም በሲሳይ የተጠበብኩ ሆኜ የጻፍከኝ ከኾነ፣ በችሮታህ፣ እድለ ቢስነቴን፣ የተነፈግኩ፣ የተባረርኩና፣ በሲሳይ የተጠበብኩ መኾኔን ሰርዝልኝ።
በመጽሐፎች እናት ውስጥ፣ እድለኛ፣ ባለ ሲሳይና፣ ለበጎ ነገር የተገጠምኩ አድርገህ አፅድቀኝ። አንተ በተወረደው መጽሐፍህ፣ በመልእክተኛው ነቢይህ አንደበት እንዲህ ብለሃል፤ ንግግርህም እውነት ነው :–
يَمْحُو اللَّهُ مَا يَشَاءُ وَيُثْبِتُ ۖ وَعِندَهُ أُمُّ الْكِتَابِ
አላህ የሚሻውን ያብሳል፤ ያጸድቃልም፡፡ የመጽሐፉ መሠረትም እርሱ ዘንድ ነው፡፡
[ ሱረቱ አል- ረዕድ፥ - 39 ]
አምላኬ ሆይ! የተወሰነው ሁሉ በሚለይባትና በሚቆረጥባት፣ በተከበረው የሸዕባን ወር አጋማሽ ሌሊት ውስጥ ባለው የላቀ መገለጥ ይኹንብህ፣ የምናውቀውን፣ የማናውቀውንና አንተ የበለጠ የምታውቀውን ፈተና ከኛ ላይ አስወግድ። "

አቡ ሱሀይል

13 Feb, 16:01


Live stream started

አቡ ሱሀይል

13 Feb, 13:58


# ደጋግ የአላህ ባሪያዎች እና የዛሬዋ ሌሊት
___
ኢማም አል ከርማኒይ (ረ.ዐ) እንዲህ ይላሉ
" كان خالد بن معدان، ولقمان بن عامر، وغيرهما يلبسون فيها أحسن ثيابهم، ويتبخرون، ويكتحلون، ويقومون في المسجد ليلتهم تلك. ووافقهم إسحاق بن راهويه على ذلك،
"ኻሊድ ቢን መዕዳን፣ሉቅማን ቢን ዓሚር እና ሌሎችም በዚህች ሌሊት ከልብሶቻቸው ውስጥ ምርጡን ይለብሳሉ፤ ሽቶን ይቀባሉ፤ ኩል ይኳላሉ፤ በዛች ሌሊት በመስጂድ ውስጥ እየሰገዱ ያሳልፋሉ።
ኢስሃቅ ቢን ራሀወይሂም በዚህ ተግባር ላይ ገጥመዋቸዋል"
=======
መሳኢል
_____
ኢማም አል ቁስጠላኒይ (ረ.ዐ) እንዲህ ብለዋል
أن التابعين من أهل الشام كخالد بن معدان ومكحول كانوا يجتهدون ليلة النصف من شعبان في العبادة، وعنهم أخذ الناس تعظيمها
"ኻሊድ ቢን መዕዳንን እና መክሁልን የመሳሰሉ፣ከሻም ሀገር የሆኑ ታቢዒዮች በሻዕባን ወር አጋማሽ ሌሊት ላይ በአምልኮ ላይ ይለፉ ነበር፣ሰዎችም ሌሊቷን ማላቅ ከነሱ ነው የያዙት"
አል መዋሂብ=2/259
_
ኢብኑ ሀጀር አል ሀይሠሚይ(ረ.ዐ)እንዲህ ብለዋል:
" والحاصل أن لهذه الليلة فضلاً وأنه يقع فيها مغفرة مخصوصة واستجابة مخصوصة . "
"ጭማቂው ይህች ሌሊት ደረጃ ያላት፣ልዩ የሆነ መሀርታና፣የዱዓእ ተቀባይነት የሚከሰትባት ሌሊት ነች"
አል ፈታወል ፊቅሂየቱል ኩብራ=3/377
_
እናም ትላልቅ ዑለማኦች የዛሬዋን ሌሊት እዝነትና በረከት ለማግኘት ከመጝሪብ በዃላ፣ በግልም ሆነ በህብረት
3 ግዜ ሱረቱል ያሲንን መቅራት
1ኛው - ረጅም እድሜ ከዓፊያና ለመልካም ተግባር እንዲገጥመን በሚል ኒያ
2ኛው - ከመቅሰፍትና ከአደጋ አላህ እንዲጠብቀን በሚል ኒያ
3ኛው - የልብ ሀብት፤ ከሰው መብቃቃትና ሁስነል ኻቲማ እንዲሰጠን በሚል ኒያ ነይቶ መቅራትና፣
ከእያንዳንዱ ያሲን በዃላ ይህን ዱዓእ ማድረግም አስለምደዋል ።
___
T.me/hamidabuhamid

አቡ ሱሀይል

13 Feb, 13:39


# የዛሬዋ ሌሊት

ኢማሙ ሻፊዒይ (ረህመቱሏሂ ዐለይህ)
وَبَلَغَنَا أَنَّهُ كَانَ يُقَالُ : إنَّ الدُّعَاءَ يُسْتَجَابُ فِي خَمْسِ لَيَالٍ فِي لَيْلَةِ الْجُمُعَةِ, وَلَيْلَةِ الْأَضْحَى, وَلَيْلَةِ الْفِطْرِ, وَأَوَّلِ لَيْلَةٍ مِنْ رَجَبٍ, وَلَيْلَةِ النِّصْفِ مِنْ شَعْبَانَ.
በአምስት ሌሊቶች ዱዐእ ተቀባይነቱ የጎላ ነው ይባል እንደነበረ ደርሶናል፣እነርሱም:–
1:የጁሙዐ ሌሊት
2:የዒደል አድሀ ሌሊት
3:የዒደል ፊጥር ሌሊት
4:የረጀብ ወር የመጀመሪያው ሌሊት
5:የሸዕባን 15 ሌሊት ናቸው
__
አል ኡም=1/265
#t.me/hamidabuhamid

አቡ ሱሀይል

12 Feb, 20:23


🌔 የነገዋ ሌሊት
__
አቡ ሙሰ’ል–አሽዐሪይ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት፣ የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል
*«إِنَّ اللَّهَ لَيَطَّلِعُ فِي لَيْلَةِ النِّصْفِ مِنْ شَعْبَانَ،*
*فَيَغْفِرُ لِجَمِيعِ خَلْقِهِ،*
*إِلَّا لِمُشْرِكٍ أَوْ مُشَاحِنٍ» *.
*رواه ابن ماجه وابن حبان وغيرهما.
قال الإمام الهيثمي في مجمع الزوائد:
"رَوَاهُ الطَّبَرَانِيُّ فِي الْكَبِيرِ وَالْأَوْسَطِ، *وَرِجَالُهُمَا ثِقَاتٌ*"اهـ.
"በሸዕባን አጋማሽ ሌሊት ላይ አላህ (በእዝነቱ) ይመለከታል፤ በሱ ላጋራና ለተጣሉ ሰዎች ሲቀር ለሁሉም ፍጡራኖቹም መሐርታውን ይለግሳል። "

ኢብኑ ማጀህ ኢብኑ ሂባንና ሌሎችም ዘግበውታል።
ኢማም ሀይሰሚይ መጅመዑ ዘዋኢድ በሚለው መፅሀፋቸው ላይ"ይህን ሀዲስ ጦበራኒይ በ"ከቢር" እና በ"አውሰጥ" የሐዲስ ጥራዛቸው ላይ ዘግበውታል። እናም ሁሉም የሀዲሱ አቀባዮች ታማኝ ናቸውም" ብለዋል።

አቡ ሱሀይል

12 Feb, 16:10


# ራሳችሁን አዘጋጁላቸው 🙌

《 በዘመናችሁ ቀናቶች ውስጥ ጌታችሁ (ልዩ) ስጦታዎች አሉት። አዋጅ! ራሳችሁን አዘጋጁላቸው 》 ረሱለላህ ﷺ
___
ከሌሊቶችም ሌሊቶች አሉ! ከነዚህ ውድና ልዩ ሌሊቶች ውስጥ የሸዕባን 15 ኛ ሌሊት አንዷ ናት። የአላህ እዝነት የሚታደልባት፣ መሐርታው የሚለገስባት፣ የየአንዳንዱ ፍጡር አመታዊ በጀት ለአስፈፃሚው አካል የሚተላለፍባት እንቁ ሌሊት ነች።

አማኝ ከአላህ እዝነት ተስፋ አይቆርጥም፤ ራሱንም እንዲህ ካሉ እድያዎች አያብቃቃም፤ አይኩራራም !

#አላህ ሸዕባኑን ይባርክልን፤ ረመዳኑን በአማን በኢማን ያድርሰን 🤲
#t.me/hamidabuhamid

አቡ ሱሀይል

10 Feb, 17:01


# ፊቅሂያዊ ፋይዳ
የረመዷን ቀዷእ እያለበት ሌላ ረመዷን የደረሰበት ሰው ብይን
___
በቅድሚያ ከረመዷን ወር ሳይፆመው ያለፈው ቀን ያለበት ሰው፣ቀጣይ ረመዷን ከመድረሱ በፊት የግድ ቀዷእ ማውጣት(ተክቶ መፆም) እንዳለበት የፊቅህ ሊቃውንቶች ተስማምተዋል፤ለዚህም እንደማስረጃነት ያስቀመጡት በቡኻሪና ሙስሊም ላይ የተዘገበውን ተከታይ ሐዲስ ነው
عَنْ أَبِي سَلَمَةَ ، قَالَ : سَمِعْتُ عَائِشَةَ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهَا تَقُولُ : كَانَ يَكُونُ عَلَيَّ الصَّوْمُ مِنْ رَمَضَانَ، فَمَا أَسْتَطِيعُ أَنْ أَقْضِيَ إِلَّا فِي شَعْبَانَ.
ከአቡ ሰለማህ ተወስዶ እንደተዘገበው,ዓኢሻህ(ረ.ዐ) እንዲህ ትል ነበር:ከረመዷን ወር ውስጥ ፆም ይኖርብኝ ነበር፣ያንንም በሸዕባን ወር እንጂ መተካት(ቀዷእ ማውጣት)አልችልም ነበር።
ይህን አያይዘውም ሓፊዝ ኢብኑ ሐጀር(ረ.ዐ)"በሸዕባን ወር ላይ ለመተካት የነበራት ጉጉት፣ቀዷእን ቀጣይ ረመዷን እስኪገባ ድረስ ማዘግየት እንደማይፈቀድ ያሳያል"ይላሉ።
_
በማስከተል ቀጣይ ረመዷን እስኪደርስበት(እስኪገባበት)ድረስ ያዘገየ ሰው ከሁለት ሁኔታዎች ውጭ አይሆንም!
¶ አንዱ:ማዘግየቱ ተቀባይነት ባለው ምክንያት(ዑዝር)ሲሆን፣ለምሳሌ መፆም የማያስችለው ህመም ዘውትሮበት ማውጣት ያልቻለ ሰው ይሆናል፤ይህ ሰው ምክንያት ስላለው ጥፋተኛ አይሆንም፤ስለዚህ ፆሙን ለፈታባቸው ቀናት ቀዷእ ብቻ ይኖርበታል ማለት ነው።
¶ ሁለተኛ:ቀዷእ ማውጣት እየቻለ ያለ ምክንያት አዘግይይቶ ቀጣይ ረመዷን የደረሰበት ሰው ነው፤ይህ ሰው ያለ ምክንያት በማዘግየቱ ጥፋተኛ ሲሆን፣ቀዷእ እንዳለበት ሊቃውንቶች ይስማማሉ፤ነገር ግን ቀዷእ ከማውጣቱ ጋር ለእያንዳንዱ ቀን ሚስኪን የመመገብ ቤዛ(ፊድያ)አለበት?ወይስ የለበትም?በሚለው ላይ የሀሳብ ልዩነት ፈጥረዋል
★ኢማም ማሊክ፣ሻፊዒይና አሕመድ(ረ.ዐ)መመገብ አለበት ያሉ ሲሆን፣ለዚህም አቋማቸው ከአቡ ሁረይራ፣ከኢብኑ ዐባስ መሰል ሶሓበቶች የተገኘውን ማስረጃ ያስቀምጣሉ።
★ኢማም አቡ ሐኒፋህ(ረ.ዐ)ደግሞ "ከሌሎች ቀኖች መፆም አለበት"በማለት ቀዷእን ብቻ የጠቀሰውን የቁርኣን አንቀፅ በቀጥታ በመውሰድ፣ከቀዷእ ውጪ ምንም እንደሌለበት እይታቸውን አስቀምጠዋል።
___
ወላሁ አዕለም
t.me/hamidabuhamid

አቡ ሱሀይል

31 Jan, 19:11


Bejai nerash naiker ቤት
በተዘጋጀው የግጥም ውድድር የሚሳተፈውን
የወንድማችንን፣ የገጣሚያችንን የ zahid iqbal ግጥም ከስር ያስቀመጥነውን ሊንኩን ተጭናቹ እየገባችሁ ላይክ በማድረግ እናግዝ ያ ጀመዓ!🙏

ሊንኩ ይኸው…

Link :👇👇👇 https://web.facebook.com/vijai.naiker/posts/9169807963096730?comment_id=1143840440691572&cft[0]=AZXyZ_yn3OqnS187vrxUKgj8JO8Y_iFne-d-raRvTKkAQCEKd4EYz2vs3_ClLMLe12R-NZ6xurk-zwvkFOMdCu4_q2kxRgFEl3Pv9WwSXoL8dSZR0LqfBmxQRu0Y0UtBmcLuNPymhIHjkeqm1DqmxGGQsPQSpbrkJ9XxiOMvP6Qtntn__=R]-R

አቡ ሱሀይል

30 Jan, 19:06


🌙 ነገ ሸዕባን 1 ይላል
__
«ያ(የሸዕባን ወር) ሰዎች በረጀብና በረመዷን መሀከል የሚዘናጉበት ወር ነው፣እሱ ስራዎች ወደ አለማቱ ጌታ የሚወጡበት ወር ነው፣ፆመኛ ሆኜ ስራዬ እንዲወጣ እወዳለው»
ሰዪዱና ሙሐመድ ﷺ
ሙስነድ አህመድ
___
የረመዷንን በረከት ለማፈስ፣እድሉን ለመጠቀም ቁርጥ ሀሳብ ያለው አማኝ እራሱን በመልካም ስራዎች ቀድሞ ያለማምዳል፣በረመዷኑ የሚፈልገውን የለውጥ ጉዞ ከአሁኑ ይጀምራል፣ቁርኣን፣ዚክር፣ሶደቃ…መሰል ዒባዳዎች ላይ ይጠናከራል፤ በአጠቃላይ ለረመዷን የሚያወጣውን ፕሮግራምና እቅድ ትግበራውን ዛሬውኑ በመፈፀም ዝግጁነቱን ያሳያል።

ረመዷን መጣልኝ/ደረሰልኝ በሚል ሰውና መጣብኝ/ደረሰብኝ በሚል ሰው መሀከል ያለው ልዩነት ሰፊ ነው………
__
ታላቁ የረመዳን ወር የሚፈልገውን ስንቅ ሰንቀን፣በአማን በኢማን የምንገናኘው ያድርገን።🤲🏻
<<<<>>>
T.me/hamidabuhamid

አቡ ሱሀይል

30 Jan, 11:33


ክፍል ሁለት ዛሬ ከቀኑ 11፡00 አስራ አንድ ሰዓት
በአል ዒምራን ዩቲዩብ ገፅ ይጠብቁን
https://youtube.com/@alimrancmc?si=3FSXVE63VNBk-cjG

አቡ ሱሀይል

27 Jan, 14:11


እነሆ በአል ዒምራን የዩትዩብ ቻናል፣ የዒልም ማዕድ ግብዣ ተሰናድቶልናል!
ትምህርቱ መሠረታዊ የእስልምና ክፍል የኾነውን የዐቂዳ እውቀት፣ በሀገራችንም ኾነ በሌሎች ትላልቅ የአህሉስ ሱንና ወል ጀማዐህ የእውቀት ማዕከላት ውስጥ በሚሰጠው “የዐቂደቱል ዐዋም” ኪታብ፣ ሰፊውን ማህበረሰብ ታሳቢ አድርጎ፣ ቀለል ባለ ገለፃና፣ መጠነኛ በኾነ ትንታኔ የተዘጋጀ ነው።
  የመጀመሪያው ክፍል ተለቋል።  ቻናሉን  subscribe በማድረግ፣ ለሌሎችም በማጋራት ደርሱ ለብዙ ሰው ተደራሽ እናድርግ
https://youtu.be/ESLINOnwWLs?si=c0kCUoqohHumqYY3

አቡ ሱሀይል

27 Jan, 14:05


#ተለቋል ክፍል አንድ👇👇👇👇👇
https://youtu.be/ESLINOnwWLs?si=c0kCUoqohHumqYY3

አቡ ሱሀይል

26 Jan, 19:05


በዛሬዋ ለሊት፣ የሰዪዳችን ﷺ ቀልብ፣ በሰዪዱና ጂብሪል (ዐ.ሰ) አማካኝነት፣ በዘምዘም ውሃ ታጥቦ በንፅሀት ላይ ንፅሀትን እንደጨመረው፣ በጭማሪ ጥበብና፣ ኢማን እንደተዋበው ፣ ሐዘኑን በሚያስረሳ ሀሴት እንደቀየረው… ……

አላህዋ ❤️
ልባችንን ከርሱ ካራቁት ቆሻሻዎችና፣ እኩይ ባህሪያቶች ያንፃልን 🤲
ከምቀኝነት፣ ከኩራት፣ ከጥላቻ ያፅዳልን🤲
በኢማንና በተቅዋ ያበርታልን🤲
በርሱ፣ በውዱ ነቢይና በሷሊሖች ሙሐባ ይሙላልን 🤲
ሀዘናችንን ስብራታችንን በደስታ ይቀይርልን 🤲

አቡ ሱሀይል

26 Jan, 18:11


ለኛ ለሰው ልጆች ውዱ ስጦታ ሂዳያ ( ቀጥተኛውን መንገድ መመራት) ነው። ይህንን ስጦታ ለመሰጠታችን ዋነኛ ምክንያት የኾኑት ደግሞ ሰዪዱና ሙሐመድ ﷺ ናቸው። ለሰዪዱና ሙሐመድ ﷺ ደግሞ ውዷና የተከበረችዋ ሌሊት፣ የኢስራእና የሚዕራጅ ጉዞ የተከናወነባት ሌሊት ነች። ውዱ ተወዳጃችን ﷺ በልቅና ላይ ልቅናን የደረቡባት፣ አላህም እንዲህ ብሎ በቁርኣኑ አግዝፎ ያወሳት ሌሊት ናት።

{ سُبْحَانَ الَّذِي أَسْرَىٰ بِعَبْدِهِ لَيْلًا مِّنَ الْمَسْجِدِ الْحَرَامِ إِلَى الْمَسْجِدِ الْأَقْصَى الَّذِي بَارَكْنَا حَوْلَهُ لِنُرِيَهُ مِنْ آيَاتِنَا ۚ إِنَّهُ هُوَ السَّمِيعُ الْبَصِيرُ }
ያ ባሪያውን ከተከበረው መስጊድ ወደዚያ ዙሪያውን ወደ ባረክነው ወደ ሩቁ መስጊድ በሌሊት ውስጥ ያስኼደው (ጌታ) ጥራት ይገባው፡፡ ከተዓምራቶቻችን ልናሳየው (አስኼድነው)፡፡ እነሆ እርሱ (አላህ) ሰሚው ተመልካቺው ነው፡፡
[ ሱረቱ አል-ኢስራእ - 1 ]

የዛሬዋ ሌሊት የትኛውም ነቢይ ﷺ ያላስተናገደውን ስቃይና መከራ ያስተናገዱት ውዱ ነቢያችን ﷺ፣ ለየትኛውም ነቢይ ያልተሰጠ ክብርን የተቸሩባት፣ የጊዜን እና የቦታን ድንበር ጥሰው፣ አስገራሚ ትዕይንቶችን የተመለከቱባት ሌሊት ነች።

ይህ ታላቅ ሰማያዊ ጉማታ፣ ብዙ ምድራዊ ችግሮች ተቀድመውታል። በየቲምነት ከመወለድ አንስቶ እስከ ሐዘኑ አመት ድረስ ያለውን የአላህ መልእክተኛ ﷺ የህይወት ምዕራፍ የቃኘ ይህን በደንብ ይገነዘባል።

ያሳለፉትን ውጣ ውረድ፣ የከፈሉትን ዲካ የለሽ መስዋዕትነት፣ ያስተናገዱትን መከራና እንግልት ከአሳዛኙ የጧኢፍ መልስ ያደረጉትን ተማፅኖ በማጤን፣ በጥቂቱም ቢኾን መመልከት ይቻላል።

« اللّهُمّ إلَيْك أَشْكُو ضَعْفَ قُوّتِي ، وَقِلّةَ حِيلَتِي ، وَهَوَانِي عَلَى النّاسِ، يَا أَرْحَمَ الرّاحِمِينَ ! أَنْتَ رَبّ الْمُسْتَضْعَفِينَ وَأَنْتَ رَبّي ، إلَى مَنْ تَكِلُنِي ؟ إلَى بَعِيدٍ يَتَجَهّمُنِي ؟ أَمْ إلَى عَدُوّ مَلّكْتَهُ أَمْرِي ؟ إنْ لَمْ يَكُنْ بِك عَلَيّ غَضَبٌ فَلَا أُبَالِي ، وَلَكِنّ عَافِيَتَك هِيَ أَوْسَعُ لِي ، أَعُوذُ بِنُورِ وَجْهِك الّذِي أَشْرَقَتْ لَهُ الظّلُمَاتُ وَصَلُحَ عَلَيْهِ أَمْرُ الدّنْيَا وَالْآخِرَةِ مِنْ أَنْ تُنْزِلَ بِي غَضَبَك ، أَوْ يَحِلّ عَلَيّ سُخْطُكَ، لَك الْعُتْبَى حَتّى تَرْضَى ، وَلَا حَوْلَ وَلَا قُوّةَ إلّا بِك »

“ ጌታዬ ሆይ! የኃይሌን መድከም፤ የመላዬን ማነስ፣ በሰዎች መናቄን ለአንተ አቤት እላለሁ። አንተ የአዛኞች ሁሉ አዛኝ! አንተ የደካሞች ጌታ- አንተ የኔ ጌታ! ለማን ትተወኛለህ? ለሩቅ አጥቂ ትሰጠኝ ወይንም በጠላት እጅ ላይ ትጥለኝ? በኔ ላይ ተቆጥተህብኝ ካልሆነ ስለሚደርስብኝ ሁሉ ግድ የለኝም። ነገር ግን እኔን ደህና ማድረገህ ለኔ የሰፋ ነዉ። ቁጣህ እንዳይወርድብኝ ወይም ጥላቻህ እንዳይሰፍርብኝ፣ ጨለማዎችን በበሩበት ፤ የቅርቢቱም ይሁን የመጭዉ አለም በሰመረበት ብርሃንህ እጠበቃለሁ፤ እስክትደሰት ድረስ፣ ደስታህን እማፀናለው፤ በአንተ እንጂ ዘዴም ሆነ ኃይል የለም።» – ።''
_____
ድኩምነታቸውን፣ ብልሀት ማጣታቸውን፣ በሰዎች መዋረዳቸውን ለአላህ አሳልፈው ሲሰጡ፣ እርሱም በቃቸው።
ሁሉም ቢተውህ እኔ አለሁልህ 💚
ሁሉም ቢንቁህ እኔ ጋር ከሁሉ በላይ ክቡር ነህ ❤️ ብሎ በዛሬዋ ሌሊት አስደሳቸው።
_____
ዝክረ ኢስራእ ወል ሚዕራጅ፣ በተለያየ የህይዎት እንቅፋቶች የተሟጠጠ ተስፋን ያለመልማል፤ የደከመ እምነትን ያበረታል።
……………
*اَللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ وَبَارِكْ وكَرِّمْ بِقَدْرِ عَظَمَةِ ذَاتِكَ الْعَلِيَّةِ، فِيْ كُلِّ وَقْتٍ وَحِيْنٍ أَبَدًا، عَدَدَ مَا عَلِمْتَ، وَزِنَّةَ مَا عَلِمْتَ، وَمِلْأ مَا عَلِمْتَ، عَلَى سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ، وَعَلَى آلِ سَيِّدِنَا وَمَوْلَانَا مُحَمَّدٍ، صَاحِبِ التَّاجِ وَالْمِعْرَاجِ وَالبُرَاقِ وَالْعَلَمِ وَدَافِعِ الْبَلَاءِ وَالْوَبَاءِ وَالْمَرَضِ وَاْلأَلَمِ، جِسْمُهُ مُطَهَّرٌ مُعَطَّرٌ مُنَوَّرٌ، مَنِ اسْمُهُ مَكْتُوْبٌ مَرْفُوْعٌ مَوْضُوْعٌ عَلَى اللَّوْحِ وَالْقَلَمِ، شَمْسِ الضُّحَى بَدْرِ الدُّجَى نُوْرِ الْهُدَى مِصْبَاحِ الظُّلَمِ، أَبِي الْقَاسِمِ سَيِّدِ الْكُوْنَيْنِ وَشَفِيْعِ الثَّقْلَيْنِ، سَيِّدِنَا مُحَمَّدِ بْنِ عَبْدِ اللهِ سَيِّدِ الْعَرَبِ وَالْعَجَمِ، نَبِيِّ الْحَرَمَيْنِ مَحْبُوبٍ عِنْدَ رَبِّ الْمَشْرِقَيْنِ وَالْمَغْرِبَيْنِ، يَا أَيُّهَا الْمُشْتَاقُوْنَ لِنورِ جَمَالِهِ صَلُّوْا عَلَيْهِ وَسَلِمُوْا تَسْلِيْمَا*
# ኢስራእ ወል ሚዕራጅ
# t.me/hamidabuhamid

አቡ ሱሀይል

25 Jan, 19:50


# ኢስራእ ወል ሚዕራጅ
ከሁሉም ቢያገልህ፣ በራሱ ሊያብቃቃህ!
ሰውን ቢያሸሽብህ፣ ለብቻው ሊበቃህ!
#አላህ
T.me/hamidabuhamid

አቡ ሱሀይል

23 Jan, 14:42


# ሰደቀ ረሱሉላህ ﷺ
_____
የአላህ መልእክተኛ ﷺ "በላተኞች ወደ ምግብ ገበታቸው እንደሚጠራሩት፣ ህዝቦች በናንተ ላይ ሊጠራሩባችሁ(ሊተባበሩባችሁ)ይቀርባል" አሉ፤
አንድ ሰው"የዛኔ አናሳ ስለሆንን ነውን ?" አላቸው፤ የአላህ መልእክተኛም ﷺ "እንደውም የዛኔ እናንተ ብዙ ናችሁ፣ ነገር ግን ልክ እንደ ባህር አረፋ ናችሁ፤ ከጠላታችሁ ልብ ላይ የናንተን ፍራቻ ይገፍፋል፤ በልቦቻችሁ ላይ ድክመትን ይጥላል" አሉ።
አንድ ሰው "ድክመት ምንድን ነው? "ሲልም ጠየቃቸው
የአላህ መልእክተኛምﷺ "ቅርቢቷን ዓለም ማፍቀር እና ሞትን መጥላት" በማለት መለሱለት።
__
አቡ ዳውድ ዘግበውታል
T.me/hamidabuhamid

አቡ ሱሀይል

22 Jan, 21:12


🌐ቲክቶክ ያላቹ ቪዲዮ ሰርታቹ ሼር አድርጉ🙏

💻ለመመዝገብ
🔺 https://t.me/Daru_hijra_bot
ወይም
🔻 @Darulhijrateyn1 ያናግሩን።

✈️https://t.me/DARULHIJRATEYNISLAMICCOLLEGE

አቡ ሱሀይል

22 Jan, 09:44


ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ፣ለ abdu book delivery ከታች ያለውን ሊንክ ተጭናችሁ በመግባት፣ መወዳደሪያ ጽሑፉን ላይክ አድርጉለት🤲🙏

Here :

https://web.facebook.com/vijai.naiker/posts/9110697319007795?comment_id=1213788360313849&cft[0]=AZUD0is4QHNxk570uPVohmvFRKBjaEVhRnVkCnY6zfUiqnmRuAmJmfpkmvUQXxdjUVXzNvKVmjI7B8CWzDxk_2wnghkutVKnXyLooxKvZ3Xnhzw-6FnWSInk7Yc64wNBNhsZufKXV7g8r8YIhaLrihFRnPlA7CHV4R8_4PWCdFPg&tn__=R]-R

አቡ ሱሀይል

21 Jan, 19:07


በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ሰቃ ወረዳ የሚገኘው ተውፊቅ የቁርኣን ተሕፊዝ እና ኢስላማዊ ትምህርት ማዕከል፣ ሐፊዘል-ቁርአኖችን እና ኩቱቡ ሲታህ ያጠናቀቁ ተማሪዎችን አስመረቀ
***
"خيركم من تعلم القرآن وعلمه "
"በላጫቹ፣ ቁርአንን ተምሮ ያስተማረ ነው "

  በሚለው የመልእክተኛው ﷺ መርሕ የሚመራው አል-ዒምራን የቁርአን እና ኢስላማዊ ትምህርት ተቋም የቁርአን ትውልድ የማፍራት ጉዞውን ቀጥሏል

  የአል ዒምራን የቁርአን እና ኢስላማዊ ትምህርት ተቋም ቅርንጫፍ የኾነው እና ከአዲስ አበባ 363 ኪ.ሜ፣ ከጅማ 17 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኘው ተውፊቅ የቁርኣን ተሕፊዝ እና ኢስላማዊ ትምህርት ማዕከል በዛሬው እለት 21 ሀፊዘል–ቁርአኖችን እና ኩቱቡ’ሲታህ ያጠናቀቁ 11 ዑለማኦችን አስመርቋል።

በምረቃ መርሀ ግብሩ ላይ ታላላቅ ዑለማኦች ፣ የተማሪ ወላጆች፣ የአካባቢው ሙስሊም ማህበርሰብ እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተገኙ ሲሆን፣ ከአዲስ አበባ ድረስ ተጉዘው የሄዱት የሀገራችን ታላቁ ዓሊም እና የተቋማችን ስራ አስፈፃሚ አባል የሆኑት ሸይኽ ሸሪፍ ሁሴን፣ ለተመራቂ ተማሪዎች ምርቃት እና ዱዓእ አድርገዋል።
በተጨማሪም የተቋማችን ዋና ስራ አስኪያጅ ኡስታዝ አስለም ዩሱፍ ለተማሪ ወላጆች እና ለመድረኩ ታዳሚያን ዳዕዋ እና የእንኳን ደስ አላቹ መልእክት አስተላልፈዋል።

በመርሀ ግብሩ ማብቂያም ላይ ለተመራቂ ተማሪዎች  እና አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት የሽልማት እና የዕውቅና የምስክር ወረቀት ተበርክቷል ።

አቡ ሱሀይል

18 Jan, 15:31


ከታች ያስቀመጥኩላችሁ የፌስ ቡክ ሊንክን ከፍታችሁ በመግባት፣ ኮመንት ቦክሱ ውስጥ Ikram_Ab ያስቀመጠችውን መወዳደሪያ ጽሑፍ፣ ላይክና ኮመንት በማድረግ አበረታቷት። 🙏
ሊንኩ👇
https://www.facebook.com/100002028524680/posts/pfbid0NSdocitN2EpansCM3Lv5vzpC5e7sQmgmDjsMCNeTj5983RLxBjmwu6LWcaJ4M3iml/?app=fbl

አቡ ሱሀይል

18 Jan, 15:17


https://www.tiktok.com/@jemil.electronicse?_t=ZM-8tAiV0bGA9W&_r=1

አቡ ሱሀይል

17 Jan, 10:59


ጁሙዐቱን ሙባረካህ
--------------------
አላህና ነቢን ሙራዳቸው ላደረጉ፣ ከሷሊሖቹ ጎራ ለመቀላቀል ለጓጉ፣ መንገድ አመላካች መጽሐፍ!
# ከደርን አንፅቶ፣ በሰፋእ ለሶፋእ የሚነበብ

–በአል–ተውባህ መጽሐፍት መደብር እና
– Abdu Book Delivery ጋር ያገኙታል።
____
T.me/hamidabuhamid

አቡ ሱሀይል

16 Jan, 18:55


# የተሰውፍ እውቀት አንድ ሰው የነፍሱን ድብቅና እኩይ፣ የሚመሰገኑና የሚወገዝዙ ፀባዮቿን፣ ደካማና ጠንካራ ጎኗን የሚያውቅበት፤ ልቡን ለማነፅ፣ ነፍስን ለማንፃትና፣ መንፈሳዊ አቅምን ለማበልፀግ፣ በተለያዩ የሂደት ደረጃዎችና እርከኖች ላይ እራስን በማለማመድ ወደ ኢህሳን ደረጃ የሚደርስበት የተደራጀ የአስተምህሮ ስነ ዘዴና የሕይዎት ስርዓት ነው።
…………………
#ኣዳብ ሱሉኪል–ሙሪድ

በኡስታዝ አቡ ሱሀይል

መጻሕፍትን ወደመደብራችን ጎራ ብለዉ ይሸምቱ! አለያም ይዘዙን ያሉበት ቦታ እናደርስልዎታለን። ክፋላተ ሀገራት እና ዉጭ ሀገራት ያላችሁ ደግሞ እንደየምርጫችሁ በተለያዩ የትራንስፖርት አማራጮች እንልክላችኋለን።

በመጻሕፍት መደብራችን ፡
የታሪክ መጻሕፍት
የትምህርት አጋዥ እና መማሪያ መጻሕፍት
የተለያዩ ልበ-ወለድ እና ኢ-ልበወለድ መጻሕፍት
የተለያዩ እንግሊዝኛ መጻሕፍት
ቆየት ያሉና አዳዲስ መጻሕፍት እና
ሌሎችም መጽሐፍት ያገኛሉ።

አድራሻችን፦
አዲስ አበባ ፒያሳ ጊዮርጊስ እሳት አደጋዉ ሻገር ብሎ "አባቢያ ራሕመት ታቦር" ሕንፃ ፊትለፊት

ለበለጠ መረጃ በ09-29-57-41-33 ይደዉሉልን።

አቡ ሱሀይል

16 Jan, 11:55


***
በአል ዒምራን የቁርአን እና ኢስላማዊ ትምህርት ተቋም ትምህርታቸውን አጠናቀው በማስተማር እና የተለያዩ መድረኮችን በመምራት የሚታወቁት ኡስታዝ ዓብዱል ሀሚድ አማን

በቅርቡ "አዳቡ ሱሉኪል ሙሪድ" የተሰኘውን ሁለተኛ መፅሀፍቸውን አሳትመው ለአንባቢያን ማድረሳቸው ይታወቃል።

አኹን ደግሞ በተለየ አቀራረብ የዓቂዳ እና የተጅዊድ ትምህርትቶችን በአል ዒምራን የቁርአን እና ኢስላማዊ ትምህርት ተቋም አዘጋጅነት በቪዲዮ ወደ እናንተ ውድ ተመልካቾቻችን ለማድረስ ዝግጅታችንን አጠናቀናል።

ውድ ተመልካቾች ከእነዚህ ትምህርታዊ ቪዲዮዎች አንዱ እና ዋነኛው በዐቂዳ ዘርፍ ላይ በኛ ሀገር ሀሪማዎችም ኾነ በሌሎች ዕውቅ መዳሪሶች ላይ የሚቀራውን፣ የዓቂደቱል ዓዋም (عقيدة العوام ) ኪታብ ደርስ ከ (جلاء الأفهام) የማብራሪያ ኪታብ ጋር፣ በቀጣይ ሳምንት መልቀቅ የምንጀምር ሲኾን፣ በሳምንት ስንት ቪዲዮ (ክፍል) ይለቀቅ? የሚለዉን ምርጫ ለናንተ ውድ ተከታታዮቻችን ሰጥተናል።

በዚህም መሰረት
አንድ ቪዲዮ የምትሉ  👍
ሁለት ቪዲዮ የምትሉ ❤️
ምልክቶች በመስጠት ተሳተፉ

በመጨረሻም ከሁሉም ክፍለ ትምህርቶች በዃላ ጥያቄ፣ የሚለቀቅ ሲሆን ጥይቃዎቹን በመመለስ እንድትሳተፉ አደራ እንላለን።

አቡ ሱሀይል

15 Jan, 19:16


ሸይኽ ዐብዱል ፈታሕ አል ቁደይሽ (ረ.ዐ) ጎረቤት ሀገር የመን ካፈራቻቸው የዘመናችን ዓሊሞች ውስጥ አንዱ ናቸው።
ሸሁ በተለያዩ ኢስላማዊ አመለካከቶች ስር አልፈዋል፤ በየፊርቃው አንጋፋ የሚባሉ ሊቃውንቶችን ተገናኝተዋል።
ይህ የህይዎት ተሞክሮዎቻቸው ለብዙ ድርሳናቶቻቸው መነሻ ኾኗቸዋል፤ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ሙስሊሙን ኡማ እንደ ካንሰር ያጠቁትን በሽታዎች ያማከሉ፣ወሳኝ ጉዳዮችን የዳሰሱ ከ 102 በላይ መጻሕፍትን አበርክተዋል፤ መንሥኤዎችንና ማከሚያ መንገዶችን ጠቁመው ወደ ኢስላማዊ አንድነት የሚያመጡ ሀሳቦችን ዕውቀትንና አደብን መሰረት ባደረገ መልኩ አቅርበዋል።

አብዝኃኛዎቹን መጻሕፍት ማንበብ ችያለው፤ በሰሞኑ የሀበሻ ዚያራቸውም ተቀማምጫቸው፣ አያሌ ፋይዳዎችን ተቋድሻለው። ከመጽሓፎቻቸው ውስጥም ሁለቱን ከእጃቸው ተረክቤያለው። አልሀምዱ ሊላህ
____
መጽሐፎቻቸውን በ pdf ለሚፈልግ፣ ከታች ኮመንት ሳጥኑ ላይ አስቀምጣለው።
# በሊቃውንቶቻችን መሀከል እንዲህ ያሉ ግንኙነቶችና ዚያራዎች ፋይዳቸው የጎላ ነውና ደዋም ብለናል!

አቡ ሱሀይል

14 Jan, 09:18


ከታላቁ የተፍሲር፣ የኡሱልና፣የዐቂዳ ሊቅ ዶ/ዐብዱል ቃዲር አል–ሑሰይን ጋር የነበረኝ ቆይታ ጥቂት ቢኾንም፣ ደርበብ ያሉ ፋይዳዎችን አስጨብጦኛል።
ወሳኝ በሚባሉ ጉዳዮች ዙሪያ የምፈልጋቸውን ምክሮችና አካሄዶች፣ ከዘለቀው ዕውቀታቸውና፣ ካለፉት ተሞክሮዎቻቸው ቆንጥረው ለግሰውኛል።
# በቅርቡ ለንባብ የበቃው አል ወሲጥ የተሰኘ ኪታባቸውን በፊርማቸው አጅበው ጀብተውኛል።
ሸሁ አኹን እየተሸኙ ነው።
ዚያራቸው ይደጋገም ዘንድ ምኞታችን ነው።
_
T.me/hamidabuhamid

አቡ ሱሀይል

12 Jan, 11:54


ዛሬ የአብሬት ሸሆች መውሊድ ነው።
የሸሆች በረካ በኛም ላይ ይደር 🤲

አቡ ሱሀይል

12 Jan, 11:53


https://youtu.be/WncvwyjrK-w?si=aFUOO2w1_l_naNy1

አቡ ሱሀይል

10 Jan, 18:41


ሸህ ሙሀመድ አል ጁሀኒይ (ታላቅ ዓሊምና የዐቀባ ከተማ ሙፍቲ ናቸው)
አሁን ከመጝሪብ እስከ ዒሻእ በመቐለ ከተማ በሚገኘው ሐምዛ መስጂድ ላይ ዳዕዋ እያደረጉ በመሀል ልብን የሚያስደሳ አንድ ንግግር እንዲህ ሲሉ ተናገሩ
በሐዲስ እንደተነገረን ከኡመቶቼ የሚወርደውን ሰለዋት ወደኔ የሚያደርሱ ልዩ መላአክቶች አሉ፤ እኔ እስከዛሬ ካየሁት እነዚህ መላአክቶች ብዙ ሰለዋት ወደ ነቢዩ ﷺ የሚያደርሱት ከዚህ ሀገር ነው! 😍
እንደ ሀበሻ ሰለዋት በብዛት የሚወርድበት ሀገር አልተመለከትኩም
_
ሰሉ ዐለል ሐቢብ ﷺ
_
T.me/hamidabuhamid

አቡ ሱሀይል

05 Jan, 13:25


ዶ/ዐብዱል ቃዲር አል ሑሰይን ታላቅ ሶሪያዊ ዓሊም፤ በተፍሲር በኡሱለል ፊቅህ እና በዓቂዳ ዘርፎች ላይ ተኸሱስ(specialized) ያደረጉ፣ በአኹኑ ሰኣት በቱርክ የሚገኘው የኢሕያእ ዑሉሙዲን መርከዝ ዋና ስራ አስኪያጅ በመኾን ኡማውን እያገለገሉ ካሉ የዘመናችን ሊቃውንቶች ውስጥ አንዱ ናቸው።
  ዛሬ የሐበሻ ኩራት የኾኑት ቀዳማዊ ማዲሓችንን ሸህ ሙሐመድ አወል ሐምዛን እና ታላቁን ዓሊም ሸህ አሕመድ አወሉን አብረን ለመዘየር ተወፍቀናል።
  በዚያራቸው ወቅት ታላቁ ማዲሕ ሸህ ሙሐመድ አወል ሐምዛ በሚስረቀረቀው ድምፃቸው ያስደመጧቸውን መድሕ በቴሌግራም ቻናሌ ላይ ታገኙታላችሁ 👆👆👆
T.me/hamidabuhamid

አቡ ሱሀይል

05 Jan, 11:05


❤️❤️❤️

አቡ ሱሀይል

02 Jan, 18:26


# የ1446 ኛ ዓ.ሂ የረጀብ አል–አሰብ ወር ውዳሴዎች

ታላቁ ዓሊም አል–ሐቢብ ዑመር ቢን ሙሐመድ ቢን ሐፊዝ (አላህ ይጠብቃቸው) በዚህ አመት የረጀብ ወር ላይ ተከታዮቹን ውዳሴዎች እንድናበዛ ምክራቸውን ለግሰዋል ፡-

የአል ፊል ምዕራፍን ሶስት ጊዜ
ከዛም በማስከተል ይህንን ዱዓእ ማድረግ

اللَّهمَّ اجْعَلْ كَيْدَ أَعدَائِكَ أَعْدَائِنَا أَعدَاءِ الدِّينِ في تَضْلِيل واجْعَلْهُم كَعَصْفٍ مَأكُول، يا حَيُّ يا قيُّومُ يَا قَوِيٌّ يَا مَتِين. (ثلاثاً)
አላህ ሆይ ያንተን፣የኛን እና የእስልምናን ጠላቶች ሴራ ከንቱ አድርግ።ቅጠሉ እንደተበላ አዝመራም አድርጋቸው።አንተ ሕያውና ራሱን ቻይ፣ ብርቱና ኃያል የኾንክ ጌታ ( 3 ×)
=====
የቁረይሽ ምዕራፍን ሶስት ጊዜ
ከዛም በማስከተል ይህንን ዱዓእ ማድረግ

اللَّهُمَّ أَطْعِمْنَا مِنَ الجُوعِ ، وَآمِنَّا مِنَ الخَوفِ، يَا رَحْمَنُ يَا رَحِيمُ يَا رَزَّاقُ يا كريم. (ثلاثاً)

አላህ ሆይ! ከረኃብ መግበን፤ ከፍርሃትም ሰላም ስጠን፤ አንተ እጅግ በጣም ሩሕሩሕ፣ እጅግ አዛኝ፣አንተ ሲሳይን ሰጪና አንተ ክቡሩ የኾንክ (3×)
=======
በወሩ ውስጥ የእያንዳንዱ ምዕራፍ እና ዱዓ ቁጥር ሦስት መቶ ጊዜ እስኪደርስ ድረስ

<<<<<<<>>>>>>>>
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلَّمْ عَلى سَيِّدِنا محمَّدٍ وَآلِهِ وَصَحْبِهِ وَعِبَادِكَ الصَّالحين، واعْفُ عَنَّا، واغْفِرْ لَنا ، وارحَمْنَا ، أَنتَ مَولانَا فَانصُرْنَا علَى القَومِ الكَافِرِين.
አሏህ ሆይ በሰዪዱና ሙሐመድ፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በባልደረቦቻቸው፣ እና በደጋግ ባሮችህ ላይ እዝነትና ሰላምህን አውርድ። ይቅር በለን፤ ማረን ፤ እዘንልን፤ አንተ ረዳታችን ነህና በሰዎች ላይ በከሓዲያን ላይ ድልን ስጠን።

ይህንን (ቢያንስ አንድ ሺህ ጊዜ) የጨመረም ሰው አላህ ከችሮታው ይጨምርለታል።
_
T.me/hamidabuhamid

አቡ ሱሀይል

02 Jan, 11:30


Channel photo updated

አቡ ሱሀይል

31 Dec, 13:48


ታላቁ ዓሊምና የአላህ ወዳጅ ሰዪዲ ሸይኽ ዐብዱል ቃድር አል ጀይላኒይ(قدس سره)በመጀመሪያው የረጀብ ወር ሌሊት ይህንን ዱዓ እንድናደርግ በእውቁ "አል ጙንያህ"ኪታባቸው ውስጥ ጠቅሰዋል፤ዱዓውን ከነ ትርጉሙ አስቀምጨዋለው:–
إِلهِي : تَعَرَّضَ لَكَ فِي هذه اللَّيْلِة المُتَعَرِّضُونَ ،وَقَصَدَكَ القاصِدُونَ ،وَأَمَّلَ فَضْلَكَ وَمَعْرُوفَكَ الطَّالِبُونَ ؛وَلَكَ فِي هذه اللَّيْلِة نَفَحاتٌ وَجَوائِزُ ،وَعَطايا وَمَواهِبُ ،تَمُنُّ بِها عَلى مَنْ تَشاءُ مِنْ عِبادِكَ ،وَتَمْنَعُها مِمَّنْ لَمْ تَسْبِقْ لَهُ العِنايَةُ مِنْكَ، وَها أَنا ذا عّبدُكَ الفَقِيرُ إِلَيْكَ، المُؤَمِّلُ فَضْلَكَ وَمَعْرُوفَكَ؛ فَإِنْ كُنْتَ يا مَوْلاي تَفَضَّلْتَ فِي هذِهِ اللَّيْلَةِ عَلى أَحَدٍ مِنْ خَلْقِكَ ،وَجُدْتَ عَلَيْهِ بِعائِدَةٍ مِنْ عَطْفِكَ ،فَصَلِّ عَلى سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ وآلِهِ وَصَحبِهِ، وَجُدْ عَلَيَّ بِطَوْلِكَ وَمَعْرُوفِكَ، يا رَبَّ العالَمينَ .
አላህ ሆይ! በዚህች ሌሊት ቀራቢዎች ወዳንተ ቀረቡ፣አሳቢዎችም አሰቡህ፣ፈላጊዎች ትሩፋትና መልካምህን ተስፋ አረጉ፣በዚህች ሌሊት ውስጥ እድያዎችና ሽልማቶች፣ልገሳዎችና ስጦታዎች አሉህ፤በነሱም ከባሪያዎችህ የፈለግከውን ባሪያ ትመነዳለህ፤ካንተ የሆነች እገዛ ካያልቀደመችለትም ሰው ትከለክላለህ፤ይሄው እኔ ወዳንተ ፈላጊ፣ችሮታህንና መልካምህን ከጃይ ባርያህ!
ረዳቴ ሆይ! በዚህች ሌሊት በአንዳች ፍጡርህ ላይ ችሮታህን ለግሰህ፣በእዝነትህ ውለታን ውለህ ከሆነ፣አንተ የአለማት ጌታ ሆይ በሰዪዳችን በቤተሰቦቻቸውና በባልደረቦቻቸው ላይ እዝነትህን አውርድ፤ከፀጋህና ከመልካምህ ለኔም ለግሰኝ"
_
በድምፅ ለፈለገ 👆👆👆 አስቀምጫለው።
t.me/hamidabuhamid

አቡ ሱሀይል

30 Dec, 19:44


Share_share
https://youtu.be/yiIJwLAOexA?si=xuZAcTkP1eEZYj2V

አቡ ሱሀይል

22 Dec, 03:01


ሰልማን አል–ፋርሲይ (ረ.ዐ) ለአቡ ደርዳእ (ረ.ዐ) እንዲህ ሲሉ ጻፉላቸው: –

ስጋዊ ፍላጎትህን በመተው እንጂ ምኞትህትን አታሳካም ፤ በምትጠላው ነገር በመታገስ እንጂ የምታልመውን ላይ አትደርስም ።
ንግግርህ ውዳሴ፣ዝምታህ አስተንትኖት፣ ምልከታህም ትምህርት ይኹን ።
ከሰዎችም ሁሉ በጣም ደካማ ሰው ፍላጎቱን የተከተለና አላህ ላይ ከንቱ ምኞት የሚመኘው ሲኾን ፤ ከሰዎች ውስጥ በጣም ብልኹ ደግሞ ነፍሱን አድክሞ ከሞት በዃላ ላለው ሕይወት የሰራ ነው።

📚 "በህጀቱል መጃሊስ፣ወኡንሱል መጃሊስ"

አቡ ሱሀይል

21 Dec, 14:51


በአል-ዒምራን የቁርአን እና ኢስላማዊ ትምህርት ተቋም በአዲስ አበባ የሚገኙ የአዳሪ መድረሳ ሙዲሮች የተገኙበት ወርሀዊ መሹራ(ስብሰባ) ተደረገ።

በዛሬው እለት 12/04/14 የተከናወነው ወርሀዊ መሹራ ትኩረቱን የመማር ማስተማር እና የተማሪዎች ኢስላማዊ ተርቢያ ላይ  ያደረገ ነው።

በስብሰባው የየመድረሳዎቹ  የአንድ ወር የስራ ሪፖርት የቀረበ ሲሆን በቀጣይ አካሄድ ዙርያም ሰፋ ያለ ውይይት ተካሂዷል ።

የትምህርት እና ተርቢያ ዘርፍ በቀጣይ በየመድረሳዎቹ ሊሰሩ ይገባቸዋል ያላቸውን ስራዎች በዝርዝር አቅርቧል።

በመጨረሻም ታላቁ የሀገራችን ዓሊም ሸይኽ ሸሪፍ ሁሴን ለኡስታዞች ምክር አዘል መልዕክት እና ዱዓእ በማድረግ ስብሰባው ተጠናቋል።

አቡ ሱሀይል

15 Dec, 19:36


❇️ ከጠቢባኑ አንደበት

1️⃣ ዝምተኛ በዝምታዉ ፈፅሞ አይቆጭም።
2️⃣ አብዝሃኛው ተናጋሪ ግን በንግግሩ ይጸጸታል።

አቡ ሱሀይል

08 Dec, 19:13


ለአንድ ጠቢብ፡- እዚህ የግንዛቤ ደረጃ ላይ እንዴት ደረስክ?
የትኞቹንስ መጻሕፍት አነበብክ? ተብሎ ሲጠየቅ

እርሱም፡- እንዲህ በማለት መለሰ
ሃምሳ ቁስሎችን፣ሰባ ፀቦችን አንብቤያለው፣በብዙ ቀውሶች ውስጥም ኖሬያለሁ።
በቅርብ ሰዎች ዓይን ክህደትን ስላየሁ፣ጥንቃቄ ማድረግን ተማርኩ.
በምወዳቸው ሰዎች ዓይን ጭካኔን ስላየሁ፣ ዝምታን ተማርኩ።
ከቅርብ ጓደኞቼ ክህደትን ስላየሁ፣መራቅን ተማርኩ።
ብዙ የምወዳቸውን ሰዎች ቀበርኩ እና ፍቅር መንኖር እንዳለበት ተማርኩ።
መማር ከፈለጋችሁ አለምን አንብቡ፣መቆሚያ የሌለው ብቸኛው መጽሃፍ ነው
እናም በህይወት ትምህርት ውስጥ፣በነፃ የሚገኝ ምንም ነገር እንደሌለ እወቅ።

አቡ ሱሀይል

08 Dec, 15:10


https://t.me/Semurelectronics

አቡ ሱሀይል

05 Dec, 20:06


“ ለአንድ ሰው ሲባል፣ሺ ሰው ይከበራል ” የሚለውን የዓረቦች አባባል የሚገልፅ መነሻ ሀሳብ በቁርኣን ውስጥ ይገኝ ይኾን? ተብለው ታላቁ ዓሊም ኢብኑል ጀውዚይ (ረ.ዐ)ተጠየቁ …

እርሰዎም : አዎን በማለት ይህን አነበቡ :–

{ وَمَا كَانَ اللَّهُ لِيُعَذِّبَهُمْ وَأَنتَ فِيهِمْ ۚ }
{ አላህም አንተ በውስጣቸው እያለህ የሚቀጣቸው አይደለም፡፡}
[ ሱረቱ አል-አንፋል - 33 ]
<<<<>>>
اللهمَّ صلِّ وسلِّم وبارِك على سيدنا محمَّدٍ الفاتحِ لِما أُغلِقَ والخاتِمِ لِما سَبَق ناصِرِ الحقِّ بالحقِّ والهادِي إلى صراطِك المستقيمِ. صلَّى اللهُ عليه وعلى آلِه وأصحابِه حقَّ قدرِه ومقدارِه العظيم.💚

አቡ ሱሀይል

05 Dec, 19:20


#ለይላችሁን በሰለዋት አድምቁት

قال رسول الله ﷺ :
«أَكْثِرُوا مِنْ الصَّلَاةِ عَلَيّ لَيْلَةٍ الْجُمُعَةِ وَيَوْمَ الْجُمُعَةِ فَإِنَّ صَلَاتَكُمْ مَعْرُوضَةٌ عَلَيَّ»

« በጁሙዓህ ሌሊትና በጁሙዓህ ቀን፣በኔ ላይ ሰለዋት ማውረድን አብዙ,የእናንተ ሰለዋት ለኔ ይቀርብልኛል »
💚 ረሱለላህ ﷺ 🌹

اللهمَّ صلِّ وسلِّم وبارِك على سيدنا محمَّدٍ الفاتحِ لِما أُغلِقَ والخاتِمِ لِما سَبَق ناصِرِ الحقِّ بالحقِّ والهادِي إلى صراطِك المستقيمِ. صلَّى اللهُ عليه وعلى آلِه وأصحابِه حقَّ قدرِه ومقدارِه العظيم.

አቡ ሱሀይል

29 Nov, 13:06


በማ/ኢ/ክ/መ/በጉ/ዞን እኖር ኤነር መገር ወረዳ የሚገኘው የአል–አቅደም የመገር ሸይኽ መስጂድ እና የቁርአን ሂፍዝ ማእከል

አቡ ሱሀይል

28 Nov, 17:40


# ለይለተል–ጁሙዓህ
ሰሞኑን እየተከታተልኩት ከነበረ አንድ ተከታታይ ትምህርት ውስጥ የአንዱን ደርስ ፍሬ ሀሳብ ላጋራችሁ።
ሸይኹ የቂያማ ምልክቶችና፣ተያያዥ ለውጦችን ሸሪዓዊ ማስረጃዎችን መሠረት እያደረጉ ያብራራሉ…
# ሰለዋት በማውረድ፣ወደ ቅንጭብ ፋይዳው እንሸጋገር… ……
ኢስላም ሙላ የሰው ልጆች የሕይወት ዘርፍን የቃኘ መለኮታዊ መመሪያ ነው፤የኢኮኖሚ እንቅስቃሴም በሰው ልጆች ማህበራዊ ግንኙነት ውስጥ ካለው ሰፊ ድርሻ አኳያ ኢስላም የላቀ ትኩረትን ቸሮታል፤በብልሹ የግብይይት ሥርዓት ለተጨማለቁ ማህበረሰቦችም፣ከተውሒድ በማስከተል ይህን ጉዳይ የሚያርማቸውና የሚያስተምራቸው አንድ ነቢይ ልኳል።

እንደ ኢስላም ገንዘብ የአላህ ስጦታም፣አደራም ነው፣ፍቁድም ውጉዝም የሚኾንበትን መንገድ ደንግጎ አስቀምጧል፣መስፈርቱ ሲገኝበትም የዘካን ምፅዋት ለሚገባቸው አካላት መስጠት ግዴታ ይኖርበታል፣እንዴት አመጣኸው በምንስ አወጣኸው ይጠየቅበታል፣በመጨረሻም አላህ ፊት እንዴት አመጣኸው በምንስ አወጣኸው ይጠየቅበታል።

የዚህ ዓለም ማብቂያው ጊዜ ሲቃረብ የሚታዩ ዘርፈ ብዙ ለውጦችና መቀያየሮችን ከሚያስተናግዱት ውስጥ አንዱ የኢኮኖሚው ክንፍ ዋነኛው ነው፤ይህንንም በየእለት እንቅስቃሴያችን እያስተዋልነው እንደኾነ ልብ ይሏል!

ይህን ተከትሎም በዓለም ላይ የኢኮኖሚውን ቂብላ ከቀየሩ መሠረታዊ ለውጦች፣በዋናነት የሚጠቀሰው ተፈጥሮአዊ መገበያያ የኾኑት የወርቅና ብር ማዕድናት ከግብይይቱ መስመር እንዲወጡና፣በተወሰኑ ኃያላን ሀገራት ቁጥጥር ስር ታፍነው እንዲቀመጡ መደረጋቸው ነው።

ይህን በተመለከተ ጥቆማ ከሰጡ ነቢያዊ ትንቢቶች ውስጥ ተከታዩ ሐዲስ አንዱ ነው
عن أبي هريرة - رضي الله عنه - قال: كيف أنتم إذا لم تجتبوا دينارا ولا درهما؟ فقيل له: وكيف ترى ذلك كائنا قال: إي والذي نفس أبي هريرة بيده عن قول الصادق المصدوق. قالوا: عم ذاك؟ قال: تنتهك ذمة الله وذمة رسوله - صلى الله عليه وسلم - ، فيشد الله قلوب أهل الذمة، فيمنعون ما في أيديهم.
رواه البخاري
ሰዪዱና አባ ሁረይራ (ረ.ዐ) እናንተ ወርቅና ብርን ካልሰበሰባችሁ እንዴት ልትኾኑ ነው? ሲሉ
ይህ እንዴት ሚኾን ይመስልሃል ? ተብለው ተጠየቁ
እርሳቸውም: “ የአቡ ሁረይራህ ነፍስ በእጁ በኾነችው እምላለው፣ከእውነት ተናጋሪውና ተነጋሪው ንግግር ይዤ ነው! ” በማለት መለሱ
ምንድን ነው እርሱ? ሲሏቸውም
የአላህና የመልእክተኛው ቃልኪዳን ይጣሳል !
አላህም በሙስሊሞች ስር ይተዳደሩ በነበሩ የሌላ እምነት ባልተቤቶች ልብ ላይ ያትማል !
በእጃቸው ያለውንም ይከለክላሉ! በማለት መለሱላቸው።
____
ይህን ሐዲስ ሊቃውንቱ በተለያየ መልኩ ያጠኑትና የተነተኑት ሲኾን፣ሐዲሱ ከሚያሳያቸውና በተጨባጭም ካረጋገጥናቸው ትርጓሜዎች አንዱ ሙስሊም ያልኾኑ ሀገራት ወርቅና ብር ከሌላው የሚከለክሉበት ጊዜ መምጣቱ ነው።

ይህ ጉዳይ ከብዙ ማህበራዊ ኢስላማዊ ህግጋት ጋር በቀጥታ የሚያያዝ እንደመኾኑ መጠን፣ሊቃውንቶች በስፋትና በጥልቀት በማጥናት ግንዛቤዎችን ማስጨበጥ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል ።
____
የዚህን ለውጥ ታሪካዊ ሂደትና፣በዓለም ሥርዓተ ህይወት ላይ ያሳደረውን ተፅዕኖ በሰፊው ለማወቅ በዘርፉ በተካነው ወንድም Hasen Injamo የተዘጋጁ ሁለት መጽሐፎችን እንድታነቡ አደራ እላለው…
አንዱን መጽሐፍ ከታች በማስቀምጥላችሁ የቴሌግራም ቻናል ውስጥ በ pdf ታገኙታላችሁ ።
https://t.me/Haseniye

አቡ ሱሀይል

28 Nov, 13:53


ዱንያን ተጠንቀቋት 😂
ማን ነህ? ና… ብር አይተህ ቁርኣን ያቋረጥከው

አቡ ሱሀይል

27 Nov, 13:48


https://youtu.be/PC6urhTHt7w?si=7s4efMsEtJaMNEVV
የምርቃት መርሀ ግብር ሙሉ ቪዲዮ

ክፍል አንድ

አቡ ሱሀይል

26 Nov, 19:47


« በዱንያ ላይ ያልጠቀመ ወንድም
በኣኼራ ላይ አይጠቅምም »
#ሰዪዲ አሕመድ አል–ሪፋዒይ(ረ.ዐ)
# አል ቡርሃኑል ሙአየ፟ድ

አቡ ሱሀይል

25 Nov, 18:05


ዱዓቶች ከዑለማኦች ጋር ሊኖራቸው የሚገባ ትስስር
____
መውላና ሸይኽ ሙሐመድ ኢልያስ(ረ.ዐ) እንዲህ ይላሉ
  {የሰው ልጅ በሸይጣን የጥሜት መረብ የተከበበ ነው፤ከዚህም ሊላቀቅ የሚችለው ከመልእክተኛው (ሰ.ዐ.ወ) ወራሾች ጋር ጥብቅ ትስስር ያለው ነው፤እነርሱም ዑለማኦች ናቸው}
_
{ በተብሊጝ ስራ ላይ የቆሙ ሰዎች በዓለማዊ ህይወት ውስጥ በተጠመዱ ሰዎችና፣የሸሪዓህ እውቀትን በማስተማር ውስጥ በተጠመዱ ዑለማኦች መሀከል እንደ አገናኝ መስመር ይኾናሉ፤ያኔ አላህ (ሱ.ዐ) ድልና መደላደልን ቃል የገባበትን፣የሀይማኖተኛነት ጥቅምና ከፍታ ይረጋገጣል።}
__
  { ዑለማኦችን ማክበርና ማላቅ ግዴታ ነው፤እየአንዳንዱ ሙስሊም ዲኑን እንዲያውቅና፣ከዛም ያንን ለሌሎች አድራሽ እንዲኾን መትጋት አለባችሁ፣ይህ የሞተ ሱንና ነው፤ይህንን ሕያው በማድረግ ላይ ከተሳካልን፣ብዙ ግዴታዎችን ሕያው ያደርጋል።
____
ለዲን ሊቃውንቶች እንዲህ በሏቸው
“ እነዚህ በዳዕዋ ላይ የቆሙ ሰዎች ለተብሊጝ መንቀሳቀሳቸው፣የሚችሉትን ያህል ጥረት ማድረጋቸውና፣መምከራቸው ዋነኛ ግቡ ተራው የማህበረሰብ ክፍል የዲን መሠረቶችን እንዲማርና ወደ ዲን እንዲመለስ ተነሳሽነት መፍጠር ነው።
   በትክክለኛው መንገድ ማስተማርና ማነፅማ ልክ የሚኾነው ዑለማኦችና መልካም የአላህ ባሪያዎች በኃላፊነታቸው ላይ ሲቆሙና፣ትኩረታቸውን ወደርሱ ሲያዞሩ ነው፤ይህ ጉዳይ አንገብጋቢ እንደመኾኑ የናንተን ብርቱ ትኩረት ይፈልጋል”።

አቡ ሱሀይል

22 Nov, 20:56


የኡማው ሊቅ ኢብኑ ዐባ፟ስ(ረ.ዐ)

“ ጨው በውሃ ውስጥ እንደሚሟሟው፣
የሙእሚን ልብም የሚሟሟበት ዘመን ይመጣል !
በማለት ተናገሩ
¶ ለምን? ተብለው ሲጠየቁ
«መለወጥ የማይችላቸውን
መጥፎ ተግባራት ሲመለከት » በማለት መለሱለት።
📚 አል–ዑቁوባት/46

አቡ ሱሀይል

21 Nov, 18:10


#ጉዳዮችህን
ጉዳዮች እርሱ ዘንድ ወደማይገዝፉበት
ከፍ አድርጋቸው !
📚ሒልየቱል–አውሊያእ 7/7
✒️ሱፍያን አል–ሰውሪይ(ረ.ዐ)

አቡ ሱሀይል

19 Nov, 18:05


# ያለቦታው አጥባቂዎች ጠፉ !

ሚዛናዊውን ሐይማኖት ከልክ በላይ ስታጠብቀው፣ሐቅን በአንተና በሸይኾችህ አረዳድ ብቻ ወስነህ ስታጠበው፣መንፈሳዊነትን ከአስኳሉ ነጥለህ እላያዊ አምልኮ ብቻ ስታስመስለው …
የሚሰጥህ ውጤት ጥፋትና ብልሹነት ነው!
እየኾነ ያለውም ይህ ነው!
#አዋጅ! ከልክ በላይ አጥባቂዎች ጠፉ፣ከልክ በላይ አጥባቂዎች ጠፉ፣ከልክ በላይ አጥባቂዎች ጠፉ !
… ረሱለላህ (صلىٰ الله عليه وسلم)

# ያ ሙቀሊ፟በል–ቁሉቢ ሰቢ፟ት ቁሉበና ዐላ ዲኒክ
ወነጂ፟ና ሚነል–ፊተን 🤲
T.me/hamidabuhamid

አቡ ሱሀይል

16 Nov, 18:09


# ሰላማዊ ህይወት
አንድ ሰው ወደ ወህብ ቢን ሙነቢህ(ረ.ዐ) ዘንድ በመምጣት
“ነፍሴ ከሰዎች እንድ(ገ)ነጠል አወጋችኝ” ይላቸዋል
እርሰዎም … ተው አታድርገው!
ላንተም ሰው የግድ ያስፈልጉሃል፣ለሰዎችም አንተ የግድ ታስፈልጋቸዋለህ፤እነሱ ካንተ ጉዳይ ይኖራቸዋል፣አንተም ከነርሱ ይኖርሃልና አታድርገው …
ነገር ግን ስትቀላቀላቸው ሰምቶ አልሰሜ፣አይቶ አላዬ፣ዝምተኛ ተናጋሪ ኹን ” በማለት መለሱለት።
____
ሲየር (4/440)
# የጊዜው ዑዝላህ (መነጠል፣መገንጠል)ይህ ነው፤ነገር ግን በየቀኑም ኾነ በየ ሳምንቱ ራስን ከአላህ ጋር ማግለል(ኸልዋ)ፈፅሞ መቅረት የሌለበት የነፍስ መገምገሚያና ማበልፀጊያ፣ወደ ከፍታዋ ማረ፟ጊያ መሰላል ነው።
ጫጫታና ጋጋታ በበዛበት፣ውጥረትና ኹከት በሞላበት፣እውነተኛ ማንነትን ሸፍኖ፣ያልኾኑትን ማስመሰል በበዛበት ተጨባጭ፣የውስጡን ጥሪ እንደሚያዳምጥ፣የነፍሱን ሰላም እንደሚያፍለላግ ሰው ዓቅለኛ የለም! !!
____
T.me/hamidabuhamid

አቡ ሱሀይል

13 Nov, 19:20


“ ሁለቴ በሽንት ማለፊያ የሚያልፍ ፍጡር
ኩራተኛ ሲኾን ይደንቃል !”
#አሕነፍ ቢን ቀይስ (ረ.ዐ)

አቡ ሱሀይል

09 Nov, 18:53


https://t.me/DARULHIJRATEYNISLAMICCOLLEGE?livestream=d44e4732d4ef883847

አቡ ሱሀይል

09 Nov, 18:53


🔮የዳሩል ሒጅራተይን ኢስላማዊ ኮሌጅ የዒልም መጅሊስ የኪታብ ደርስ እንድትገኙ ይጋብዛቹዋል📘

📗የሸይኽ ዐብዱል ፈታሕ አቡ ጉዳህ ሰፈሐት ሚን ሰብሪል ዑለማእ

             11ኛ መጅሊስ

🟢በኡስታዝ ዐ/ሐሚድ (አቡ ሱሀይል)  ሸርህና ተዕሊቅ

ዛሬ ቅዳሜ ማታ ከምሽቱ 4:00_5:00

ደርሱ በቀጥታ የሚተላለፈው በዳሩል ሒጅራተይን ኢስላማዊ ኮሌጅ የቴሌግራም ቻናል…
https://t.me/DARULHIJRATEYNISLAMICCOLLEGE

📝ዑለማዎች ዒልምን ለመቅሰም የከፈሉትን መሰዋትነት አብረን እንመልከት

አቡ ሱሀይል

09 Nov, 14:21


⛔️<የሰው ዓይን እውነት ነው፥ግመልን በድስት፣ሰውየውን በመቃብር ውስጥ ያስገባዋል> ረሱለላህ ﷺ

  አውቀንም ኾነ ሳናውቅ ለሰዎች ህመምና ስቃይ ምክንያት እንዳንኾን እንጠንቀቅ፤በሌሎች ላይ መልካምና ውብ ነገር ስንመለከት ዝም ብሎ ከመደነቅና ከመደመም ይልቅ ማሻአላህ በማለት እንባርካቸው።

እራሳችንንም እንደው ቢያንስ በጠዋትና በማታ ውዳሴዎች እንጠብቅ፤ያለንን ነገር ኹላ ወደ አደባባይ ይዘን አንውጣ፤እዩኝ እዩኝ ማለት መጨረሻው ደብቁኝ ደብቁኝን ያመጣል።

ይህ ከሰሞኑ በሚዲያ ላይ እየተዘዋወረ ያገኘሁት ወጣት አይመን አል ዐሊይ ይባላል፤ የጆርዳን የውበት ንጉስ በሚለው የሚዲያ መጠሪያው ይታወቃል፥በሚያነሳቸው ማህበራዊ ጉዳይ contentoch ብዙ ተከታዮችንም አፍርቷል፤አኹን ላይ ግን በምታዩት መልኩ በአንድ አመት ልዩነት ውስጥ በሆስፒታል አልጋ ላይ ተኝቶ በጠና ህመም እየተሰቃየ ይገኛል።

# አላህ ሙሉ ዓፊያውን ይመልስለት 🤲

አቡ ሱሀይል

06 Nov, 20:03


«ስንት አለ
ሳያውቀው በፀጋዎች እየተዘገየ
በመሀይማን ሙገሳ እየተፈተነ
አላህ ጉዳዩን ስላሳካለትና፣ነውሩን ስለሸፈነለት እየተሸወደ ያለ!

እነዚህ ሶስቱ ብዙኃኑ ዘንድ የደስታና የስኬት ምልክት ተደረገዋል !
የእውቀታቸው መዳረሻም ይህ ኾኗል»

📚መዳሪጁ–ሣ፟ሊኪን 1/518

አቡ ሱሀይል

05 Nov, 18:23


# በፈተና ወረቀት የታሸገ ፀጋ
لكلّ شيءٍ إذا فارقته عِوضٌ
وليس للهِ إن فارقت من عِوضِ
ኹሉን ነገር ስትለየው ተለዋጭ አለው
ስትለየው ተተኪ የሌለው አላህ ብቻ ነው !
ኢብኑ ዐረቢይ(ረ.ዐ)
____
ፈተናዎች በውስጣቸው ካጨቋቸው እጅግ ብዙ ስጦታዎች ውስጥ አንዱና ትልቁ ፀጋ
ከአላህ በቀር …ማንም ቢርቅህ፣ማንንም ብታጣ፣ዋይ ማትልበትን ብርታት ይስታጥቁሃል !
# አልሐምዱ ሊላህ

አቡ ሱሀይል

03 Nov, 17:54


ኢብኑ ዐሳኪር (ረ.ዐ) ከአንድ የሰዪድ ሺብሊይ (ረ.ዐ) ባልደረቦች አንስተው በ‹‹ታሪኽ›› መጽሐፋቸው ላይ እንደዘገቡት፤ሺብሊይን (ረ.ዐ) ከሕልፈታቸው በኋላ በህልሙ ተመለከታቸውና፣አላህ ባንተ ላይ ምን ፈፀመ? ሲል ይጠይቃቸዋል
ሺብሊም ፡- ከፊቱ አስቆመኝና፡- አቡ በከር ሆይ! ለምን ይቅር እንዳልኩህ ታውቃለህን?አለኝ

እኔም፡- በጽድቅ ተግባራቶቼ፤አልኩ
እርሱም፡- አይደለም አለኝ
መልሼ ፡ በአምልኮዬ ቅን በመኾኔ፤ አልኩ
እርሱም ፡- አይደለም አለኝ
አኹንም ፡- በሐጅ፣በጾምና በሰላቴ ነው፤አልኩ
እርሱም አይ! ለዛም አይደለም ይቅር ያልኩህ አለኝ
ቀጥዬ ፡ ወደ ደጋግ ባሮች በመሰደዴና እና እውቀትን ፍለጋ ጉዞዬን በማዘውተሬ ። አልኩ
እርሱም፡- አይደለም አለኝ!

በመጨረሻም ፡- ጌታዬ ሆይ… በእነሱ አማካኝነት ይቅር እንደምትለኝ እና እንደምትምርልኝ አስቤ አጥብቄ የያዝኳቸው የነበሩት መዳኛዎች እነዚህ ናቸው፤አልኩ

እርሱም፡- ይቅር ያልኩህ በእነዚህ ኹላ ምክንያት አይደለም ። አለኝ

አምላኬ ሆይ ታዲያ በምን ነው ? ስል ጠየቅኩ

እርሱም :– በባጝዳድ ጎዳናዎች ላይ ስትሄድ፣ ብርድ አድክሟት፣ከግድግዳ ጥግ ወደ ሌላ ግድግዳ ጥግ ስትጠጋ የነበረችን ድመት ተመልክተህ፣ከዛም አዝነህላት ለብሰህ በነበረው የቆዳ ልብስ ውስጥ ያስገባሃትን ታስታውሳለህን? አለኝ
እኔም፡- አዎን አልኩ
እሱም “ለዚያች ድመት በማዘንህ ነው፣እኔም ያዘንኩልህ ” አለኝ ።
_
T.me/hamidabuhamid

አቡ ሱሀይል

02 Nov, 18:52


ባል ለስራ ጉዳይ ወጣ ይላል
ሚስትም አመሻሽ ላይ "ያላንተ ቤቱ ጨለማ ነው” ብላ መልእክት ትሰድለታለች ❤️

ከተወሰኑ ደቂቃዎች በዃላ በሯ ተንኳኳ
ሚስት በሩን ስትከፍት
ወንድሟ ፋኖስ ይዞ ቆሟል 😳

ምነው በዚ ምሽት? ሰትለው
ባልሽ ደውሎ መብራት እንደጠፋ ነግሮኝ ነው! 😜🙈
# አላህ ያግባባን ማለት ይሄኔ ነው

አቡ ሱሀይል

02 Nov, 17:39


አቡል–ሑይሰን አል–ኑሪይ (ረ.ዐ) ስለ ሱፊዮች ሥነ ምግባር ተጠይቀው፣እንዲህ በማለት መለሱ
“ሌሎችን ማስደሰት፣አዛቸውን መሸከም ”።

አቡ ሱሀይል

31 Oct, 02:51


በዙሪያህ ያለው ውድመት ኹሉ አይጎዳህም
ዋናው ነገር ውድመቱ ልብህ ጋር አይድረስ !

አቡ ሱሀይል

28 Oct, 03:24


አቡ ሁረይራህ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት፤አንድ ሰው ወደ ረሱለላህ በመምጣት
“ አንቱ የአላህ መልእክተኛ ﷺ ኾይ! እከሊት እኮ … በማለት ስለ ሰላቷ፣ፆሟና ምፅዋቷ ጠቀሰ … ነገር ግን ጎረቤቶቿን በምላሷ ትተናኮላለች ” አላቸው …

ረሱለላህም “እርሷ የእሳት ናት!” በማለት ተናገሩ !
_ አሕመድ ዘግበውታል
___
ሐይማኖተኝነትን በውስን ተግባራት ብቻ ለገደበ፣የአምልኳዊ ተግባራትን ፍሬ ለዘነጋ ጥልቅ መልእክትን ያዘለ ሐዲስ
ስንቱ ነው ሰላቱን፣ፆሙን፣ሐጁን ቀጥ አድርጎ እየፈፀመ…ከጎረቤት በላይ የሚቀርቡትን አካላት አዛእ የሚያደርግ !!
_<<<<>>>_
# ኢላሂ መረዳቱን ስጠን
በድካሞቻችን ብኩን አታድርገን !!!

t.me/hamidabuhamid

አቡ ሱሀይል

25 Oct, 07:35


“ስስት(ቋጣሪነት)እና እኩይ ሥነ ምግባር
በአንድ አማኝ ውስጥ አይሰበሰቡም !!!”
#ረሱለላህ ﷺ

አቡ ሱሀይል

19 Oct, 10:10


# በዳውድ ጥበባዊ ንግግሮች ውስጥ ተከታዩ ይገኝበታል

አንድ ዐቅለኛ(አስተዋይ)ሰው አራት ወቅቶችን ቸል ሊል አይገባውም
እነሱም:–
1- ነፍሱን ከጌታው ጋር የሚያገልበት ወቅት
2- ራሱን የሚገመግምበት ወቅት
3- ነውሩን ከሚነግሩት እውነተኛ ወንድሞቹ ጋር የሚቀማመጥበት ወቅት
4- ነፍሱን የተፈቀደ ኾኖ ከሚያምራት ተድላ የሚያርቅበት ወቅት ናቸው።
ይህ ወቅት ለተቀሩት ወቅቶች የበለጠ የሚያግዘውና፣ልቡንም የሚያሳርፍበት ወቅት ነው።

አቡ ሱሀይል

18 Oct, 07:00


‏﷽
۞ إِنَّ اللَّهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِي  يَاأيُّهَاالَّذِينَ آمَنُواصَلُّواعَلَيْهِ  وَسَلِّمُواتَسْليما ۞

اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ  وَبَارِكْ عَلَى سَيِّدِنا
ونبيّنا םבםב رسول ٱɑɺɺ."ﷺ".

اللهم صل وسلم وبارك على سيدنا ونبينا محمد ﷺ وعلى آله وصحبه وسلم تسليماً كثيراً ﷺ

አቡ ሱሀይል

15 Oct, 17:25


# ሰው እንደ ተራራ ነው …

በጥንካሬው ሳይሆን በማይታየው ድብቅ ማንነቱ
ጂኦሎጂስቶች እንደሚሉን “አንድ ተራራ ከሙሉ መጠኑ አንድ ሦስተኛ ክፍሉ ብቻ ነው ለኛ የሚታየን !!
ሁለት ሦስተኛው ክፍሉ ከመሬት ስር የተቀበረ ነው !!

… እኛም እንዲሁ ነን!
የምንደብቀው ከምናሳየው በላይ ነው።
የህመማችን መንስኤዎች የምንበላቸው ሳይኾኑ የሚበሉን ነገሮች ናቸው !!

ወዳጄ … >
በእያንዳንዱ ሰው ውስጥ ተቀበለውም ካደው፣ደበቀውም ይፋ አወጣው… የተዳፈነ ህመም አለ
ከላይ በምታየው ብቻ አትታለል
ነገሮች ለኛ መስለው እንደሚታዩን አይደሉም !
በሰላማዊ ሕይወቱ የምትቀናበት የተረጋጋ ሚመስልህ ሰው
በልቡ ውስጥ አላህ ብቻ የሚያውቀው እሳት ሊኖር ይችላል።
ጭስ ስላልወጣው፣እየተቃጠለ አይደለም ማለት አይቻልም !!!!

#አድሀም ሸርቃዊ
#t.me/hamidabuhamid

አቡ ሱሀይል

13 Oct, 18:26


# የዐቂዳ ብልሹነት
ከሥነ ምግባር ብልሹነት ጋር ትስስር አለው !
:> አል–ሩኸይሚይ

አቡ ሱሀይል

13 Oct, 16:39


“ ወሕሺይ ሆይ ! እኔን(ፊት ለፊት) አለማግኘት ከቻልክ… አድርግ ”
ውዱ የአላህ መልእክተኛ ﷺ አጎታቸውና፣የጥቢ ወንድማቸው የኾነውን ሰዪዱና ሐምዛን(ረ.ዐ)ለገደለባቸው፣በልባቸው አድማስ ውስጥ ጥልቅ ሐዘን ላሳረፈባቸው ሰው፣ያቀረቡለት የትብብር ጥያቄ ነው !!
ምንም እንኳን ይቅርታ አድርገውለት፣ንሰሃውን ተቀብለውት፣ከባልደረቦቻቸው ጎራ ቢቀላቅሉትም፣ፊትለፊታቸው እንዳይቀመጥ፣እይታቸው ውስጥ እንዳይገባ ግን ጠይቀውታል፤ምክንያቱም እርሱን ባዩ ቁጥር ልባቸው ይሰበራል፣ያለፈው ሐዘናቸው ይቀሰቀሳል !
…………………………
በብዙዎቻችን ህይወት ውስጥም ልክ እንደዚሁ ልባችንን ያቆሰሉ፣በቀላሉ የማይረሳ ሐዘንን የጫሩ ሰዎች አይጠፉምና ……
ረሱለላህ ﷺ እንዳስተማሩን፣ይቅር እንላለን፣ያለፈውን እናልፋለን …ነገር ግን ከአላህ በቀር ማንም የማያውቀው ህመምና ቁስል፣በልባችን ሸለቆ ውስጥ ስላኖሩ፣ከጉያቸው እንርቃለን፣ርቀታችንን እንጠብቃለን !
እነርሱም በተቻላቸው አቅም ከእይታችን እንዲርቁ፣ከመንገዳችን እንዲወጡ የትብብር ጥያቄያችንን በአክብሮት እናቀርባለን !!🙏

#ሰላም ለልባችሁ ❤️
#t.me/hamidabuhamid

አቡ ሱሀይል

13 Oct, 07:58


اللهم صل وسلم على سيدنا و شفيعنا وحبيبنا محمد❤️❤️❤️
****
አል-ዒምራን Cmc የቁርአን እና ኢስላማዊ ትምሕርት ተቋም
ተደራሽነት ይኖረው ዘንድ ለሌሎች በማጋራት የበኩልዎን ይወጡ !
ትክክልኛ ማህበራዊ ገጾቻችን
ⓕ አል-ዒምራን Cmc የቁርአን እና ኢስላማዊ ትምሕርት ተቋም
▶️ www.youtube.com/@alimrancmc
♪ https://www.tiktok.com/@alimrancmc
📧 t.me/alimrancmc
?? www.instagram.com/alimrancmc
አል-ዒምራን Cmc የቁርአን እና ኢስላማዊ ትምሕርት ተቋምmc

አቡ ሱሀይል

10 Oct, 18:56


በ“ቡርደህ” የመወድስ መድብል ውስጥ
ሺርኪያ፟ት ገለፃዎችን ከተመለከትክ …
ተውሒድህን አስተካክል !!!
> ፈውዚይ ኮናቴ (ሐ)
# ሰሉ_ ዐለል–ሐቢብ ﷺ

አቡ ሱሀይል

10 Oct, 13:21


🤔

አቡ ሱሀይል

09 Oct, 21:10


"يا سند من لا سند له يا عون من لا عون له يا قريبًا غير بعيد يا غالبًا غير مغلوب يا سامع النجوى يا كشاف البلوى تسمع كلامنا وترى مكاننا ولا يخف عليك شيء من أمرنا نرجوك ونتوسل إليك وسع علينا رزقنا واغفر لنا ذنوبنا وارحمنا واكتبنا في عبادك الصالحين".

አቡ ሱሀይል

09 Oct, 19:34


ደስ የሚል ዜና 💚

መጨረሻውም ያማረ ይሁን 🤲

ትናንት ለወንድማችን አቡ ሃይደር ሕክምና ድጋፍ ማሰባሰብ ተጀምሮ ነበር። ሆኖም ዛሬ ይቁም ተብሏል። ምስንያት በዚህ ሊንክ አንብቡማ

በረካ ሁኑ 🙏

https://www.facebook.com/share/p/ZFDcfyVxSa5yLnwR/

አቡ ሱሀይል

08 Oct, 19:47


#ምሮን እንጂ
መርምሮን ቢኾን
እስካሁንም ባልቆየን !
🤲 ረሕማከ ያ ረብ

አቡ ሱሀይል

08 Oct, 17:32


አሁን አሁን ከየቦታው የምንሰማው ነገር ወላህ ያሳዝናል።

መሀመድ (አቡ ሃይደርን) እዚሁ ፌስቡክ ላይ ብዙዎቻችን የምናውቀ መልካም ወንድማችን ነው። ብዙ ጊዜ ሳቅ'ና ጨዋታዎች ፣ መልካም ስራዎች ባሉበት የማይጠፋው ይሄ ወንድማችን የአንድ ወንድ ልጅ አባት ነው።

እና ይሄ ብርቱ አባት አሁን ላይ ችግር አጋጥሞታል። ለረዥም ዓመት በተደጋጋሚ በሚነሳበት የኩላሊት ህመም የተነሳ ብዙ ችግሮችን ፣ ብዙ ውጣ ውረዶችን አይቷል። ብዙ ከፍ ዝቆችን አስተናግዷል።

አሁንም የባሰ የጤናው ነገር አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል። ከሚኖርበት ጎንደር እዚሁ አዲስ አበባ ድረስ እየተመላለሰ ህክምናውን ሲከታተል ቢቆይም ያለውን ንብረት ከመጨረስ ውጪ ያገኘው ለውጥ የለም።

መሀመድ (አቡ ሃይደር) ከዚህ ህመሙ ጋር እየታገለ የሰው እርዳታ ላለመጠየቅ በብዙ ታግሏል። እዚሁም ሆኖ የተለያዩ ስራዎችን ለመጀመር ሞክሯል። ግን ህመሙ በድጋሜ ሲበረታም የሚሰራባቸውን እቃዎች ሽጦ ገንዘቡን መልሶ ለህክምናው አውሎታል።

አሁን ግን አልቻለም። የእኛን እርዳታ የሚፈልግበት አስገዳጅ ሁኔታ ላይ ደርሷል። ህመሙ በዚህ ጋር በሌላ በኩል ስራ መፍታቱ ተደማምሮ እንኳን ለህክምናው አይደለም ለቤት ኪራይ'ና ለሌሎች መሰረታዊ ነገሮችም የሚያውለው ገንዘብ እስከማጣት ደርሷል።

ድንገት ባልጠበቀው ሁኔታ ሁሉም ነገር ካቅሙ በላይ በመሆኑ'ና ህመሙም ከቀን ወደቀን ስራ ሊያሰራው ስላልቻለ እኛ እንድናግዘው ይፈልጋል ። ፌስቡክ ላይ መሰባሰባችን'ና ቤተሰብ መሆናችን ከሳቅ'ና ጨዋታው ባለፈ ለዚህ አይነት መደጋገፍ ፣ 'አይዞህ...' ለመባባልም እንደመሆኑ ይሄን ወንድማችንን በቻልነው አቅም እናግዘው !

'አለንልህ....' እንበለው !

ሌሎችን ስለሚያነሳሳ ያስገባችሁበትን የገንዘብ ሪሲት ኮመንት ላይ መለጠፉ ይበረታታል....

የባንክ አካውንት

1000653250383 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
143155358 አቢሲኒያ
(መሐመድ ሳሊህ )

አቡ ሱሀይል

08 Oct, 15:56


# የመኗኗር ጥበብ
አውቆ እንዳላወቀ፣አይቶ እንዳላየ
ሞኝ መስሎ መታየት
ወሳኝ የህይወት ክህሎት ነው !!!
___
የምናውቃቸውን ነገሮች እንዳላወቅን ባናልፋቸው
ህይወት ባልጣፋጠች፣ወዳጅነትም ባልዘወተረ ! ነበር

ዐረቦች ይህን የህይወት ክህሎት :የጥበብ ግማሽ፣የልህቀት መሰላል ይሉታል፤በአባባሎቻቸውም :–

“ሞኝ በመምሰል ደረጃችሁን ከፍ አድርጉ”
“አውቆ ሞኝ መሳይ፣የህዝቡ አለቃ ነው ” ይላሉ።
____
ሪቻርድ ዴድኪንድ የተባለ ምዕራባዊ ጸሐፊም
“ ለመኖር ሙሉ ብልሀትህን
ለመኗኗር ሙሉ ሞኝነትህን መጠቀም ይኖርብሃል” ይለናል።
____
እናም አንዳንዴ ባላየ እለፉ፣ባልሰማ ታጠፉ
በየፌርማታው እንቁም፣በየክስተቱ እንፈላፈል ካላቹ
እመኑኝ ትጨልላላችሁ !!
t.me/hamidabuhamid

አቡ ሱሀይል

07 Oct, 21:09


#የኣደም ልጅ ሆይ !
በወንጀሉ ካንተ ለባሰው
ኃጢያቱም እጅጉን ለከፋው
አላህ ይቅር ብሎት፣ንሰሃውን ተቀብሎታል !
:–እናም
ማረኝ ሲሉት የሚደሰት ጌታ እያለህ
ከእዝነቱ እንዴት ተስፋ ትቆርጣለህ ?!!!
t.me/hamidabuhamid

አቡ ሱሀይል

06 Oct, 02:46


||• የጠዋት ውዳሴ
_
ሱረቱል ኢኽላስ(ቁል ሁወላ፟ሁ አሐድ) 3X
ሱረቱል ፈለቅ (ቁል አዑዙ ቢረቢል ፈለቅ)3X
ሱረቱ ና፟ስ (ቁል አዑዙ ቢረቢና፟ስ)3X

- بِسْمِ اللَّــهِ الَّذِي لَا يَضُرُّ مَعْ اسْمِهِ شَيْءٌ ،
فِي الأَرْضِ وَ لَا فِي السَّمَــاءِ وَ هُوَ السَّمِيـعُ العَلِيــمُ ..
ቢስሚላ፟ሂለ፟ዚይ ላ የዱሩ፟ መዐ’ስሚሂ ሸይኡን ፊል–አርዲ ወላ ፊሰ፟ማእ፤ወሁወ’ሰ፟ሚዑል ዐሊም "3X"

حَسْبِيَ اللهُ لَا إلَهَ إلَّا هُوَ عَلَيْهِ تَوَكَّلْتُ وَهُوَ رَبُّ العَرْشِ العَظِيمِ [سَبْعَ مَرَّاتٍ]

ሐሥቢየልላሁ ላኢላህ ኢላሁ ዐለይሒ ተወክከልቱ ወሁወ ረብቡል ዐርሺል ዐዚም (7X)

አቡ ሱሀይል

05 Oct, 20:19


# እንሞታለን
የሚያስፈራንም የሚያፅናናንም ቃል !!

አቡ ሱሀይል

05 Oct, 19:29


# ሲክቡህና ሲያካቡህ
ማንነትህን እንዳያስረሱህ !
__
ዐረቦች ሰውን ያጠፋው ሰው ነው እንዲሉ፣የሰዎች ጋጋታና ጭብጫቦ ከእውነተኛው ማንነትህ አስወጥቶ በቅዠት ማንነት ውስጥ ይዶልሃል፣የሌለህን እንዳለህ፣ያላወቅከውን እንዳወቅክ፣ያላየኸውን እንደጨበጥክ፣የራቀውን እንደደረስክበት አድርጎ ያስይዝሃል፤ዶሮን ሲያታልሏት በግ ነሽ እንዳሏት ኾነህ፤በሌለህ ነገር መመስገን፣በማያገባህ ጉዳይ ውስጥ መዘባረቅ ትጀምራለህ!

ያኔ ከፈጣሪህም ከሰውም ከራስህም ጋር ተራርቀህ ትገኛለህ!!
በቅዠት ዓለም ውስጥ ሌላ ቅዠት ይሉሃል ይህ ነው !!!

የዕውቀት መጀመሪያም ኾነ መጨረሻው
እራስን አውቆ፣ልክ ላይ መቆም ነው !!!
___
t.me/hamidabuhamid

2,655

subscribers

811

photos

62

videos