EEP TRD Office @eeptrdinstitute Channel on Telegram

EEP TRD Office

@eeptrdinstitute


የውጭና የሃገር ውስጥ የስልጠናና የትምህርት ዕድሎች እንዲሁም ሌሎች ተቋማዊ የትምህርትና የስልጠና ጉዳዮች ለሰራተኞች የሚገለጽበት ገጽ!!
___
We strive to create a learning organization!!

EEP Training & Development Office

[email protected]

EEP TRD Office (Amharic)

የሰ.ኃ.ስ.ል. ቢሮ የውጭና የሃገር ውስጥ የስልጠናና የትምህርት ዕድል ማስታወቂያዎች መድረክ!!
ከታች እንሆናለን የመረጃና ትምህርት ሰነድ የሆነውን የስልጠናና ማህበረሰብ ማመቻቹን ከተለያዩ ተጨማሪ ለውጦቹ ፈቃድ በማድረግ የሰኞ ከሆነ ገንዘብ አንበሳ ይከላከላሉ!!
ኢኢፒ ትምህርት እና መረጃ ለመቆረጥ የበለጠ ወንጀል እና ኢ-ሜይል ያሉቡ አቅራቢያቶችን ሁኔታን ተመራጭና ድረገጽን ውስጥ እንገናኝ። ለማሳየት የሚዘረጋበት በስኩት እንዲለክሱ መሰረት አንድ ወንጀል መቆረጥ ይችላሉ።nnየሰ.ኃ.ስ.ል. ቢሮ ውስጥ የስልጠናና የትምህርት ዕድል ማስታወቂያን ተመልከቱ።

EEP TRD Office

19 Feb, 11:25


ማስታወሻ
___

የረጲ ኃ/ማ/ጣቢያ የውጭ ሃገር የአሰልጣኞች ስልጠና /ToT/ ተሳታፊዎችን ለመመዘን የተቋቋመው ቡድን የመጀመሪያ ደረጃ የጽሑፍ ፈተና በጣቢያው ተገኝቶ በተሳካ ሁኔታ ማከናወኑ ይታወቃል።


ቀሪ የ Interview፣ Presentation እና Writing skill (Language proficiency) ምዘናዎች ደግሞ ሐሙስና አርብ ይቀጥላሉ።


በመሆኑም በቅጹ ላይ ተዘረዘረው መርሃግብር መሰረት በስልጠና ማዕከሉ አዳራሽ በመገኘት ምዘናውን እንድታከናውኑ እናሳስባለን።


ቦታ - ማሰልጠኛ ማዕከል አዳራሽ
ሰዓት - ጠዋት ከ 2:30 - 6:00
           ከሰዓት ከ 7:00 - 10:30
ቀን - ሐሙስ እና አርብ (13-14/06/17)

___

የሰው ኃይል ስልጠናና ልማት ቢሮ

We strive to create a Learning Organization!

EEP TRD Office

13 Feb, 10:35


ማስታወሻ
___

በረጲ የደ/ቆ/ኃ/ማመንጫ ጣቢያ ለሚሰጠው ፈተና የቦታ ለውጥ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል።

በመሆኑም:

ቀን - ማክሰኞ - 11/06/17
ቦታ - በረጲ የደ/ቆ/ኃ/ማ/ጣቢያ
ሰዓት - ጠዋት 4:00

ሆኖ የተስተካከለ በመሆኑ በዚሁ አግባብ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናስታውቃለን።

___

የሰው ኃይል ስልጠናና ልማት ቢሮ

We strive to create a learning Organization!!

EEP TRD Office

09 Feb, 15:05


ማስታወቂያ
___

፩) በረጲ የደ/ቆ/ኃ/ማመንጫ ጣቢያ ለሚሰሩ የስራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች በውጭ ሃገር የሚሰጠውን የአሰልጣኞች ስልጠና (TOT) መርሃግብር የሚሳተፉ 12 ሰራተኞችን ለመምረጥ እንዲቻል የምዘና ስራውን የሚያከናውን ቡድን ተመርጦ ወደ ስራ የገባ ሲሆን ፈተና የሚሰጥበትንና ቃለ-መጠይቅ የሚከናወንበትን ቀን ወስኖ አሳውቆናል።

በዚሁ መሰረት:

ሀ) ማክሰኞ - የካቲት 11 አጠቃላይ ፈተና እና የ paragraph writing ምዘና ይሰጣል፤

ለ) ሐሙስ - የካቲት 13 እና አርብ የካቲት 14 ጠዋትና ከሰዓት ቃለ-መጠይቅና የ 7 ደቂቃ presentation ስለሚቀርብ በሙያችሁ (field of study) ዙሪያ ከወዲሁ PowerPoint እንድታዘጋጁ እናሳስባለን።

[በተለያዩ ምክንያቶች የመርሃ-ግብር ለውጥ ካለ አስቀድመን እናሳውቃለን፤ የቃለ-መጠይቅ ተሳታፊዎችን ቅደም ተከተል በቅርቡ እናሳውቃለን።]

_


፪) የውስጥ አቅም ስልጠና (In-house training) አከናዋኝ አሰልጣኞችን የመመዘን ስራ በተያዘለት ፕሮግራም መሰረት የቀጠለ ሲሆን የምዘና ቡድኑ የአዳማ ቆይታውን አጠናቆ ወደ ሐዋሳ አቅንቷል።

በዚህ መሰረት ነገ ሰኞ እና ማክሰኞ በሐዋሳ የደቡብ ፩ ሪጅን ቢሮ (ሲዳማ ቡና ሕንፃ ላይ) ምዘና ይከናወናል።

__

የሰው ኃይል ስልጠናና ልማት ቢሮ

We strive to create a learning Organization!!

EEP TRD Office

31 Jan, 16:10


ሰላም ለእናንተ ይሁን!!

__

በ In-house training program ተሳታፊ የሚሆኑ አሰልጣኞችን ለመለየት በተያዘው መርሃ-ግብር መሰረት በኮርፖሬት ሴንተር (አ.አ.) የነበረው ምዘና ዛሬ ተጠናቋል።


ሆኖም አንዳንድ አመልካቾች በስራ ምክንያት ለምዘናው በተያዘላቸው መርሃ-ግብር መሰረት መገኘት አለመቻላቸውን ጠቅሰው ተጨማሪ ቀን እንዲሰጣቸው መጠየቃቸውን ተከትሎ የምዘና ቡድኑ ግማሽ ቀን ብቻ እንዲሰጣቸው ውሳኔ አሳልፏል።


በዚሁ መሰረት፣ ለመጨረሻ ጊዜ በአ.አ. የምዘና ማዕከል ከ 40% ለመመዘን ሳትችሉ የቀራችሁ አመልካቾች ብቻ የፊታችን ሰኞ፣ በ 26/05/2017፣ ከጠዋቱ 2:30 እስከ 6:00 ባለው ጊዜ ብቻ የምዘና ስራ ስለሚከናወን በዕለቱ እንድትገኙ እናሳስባለን።


[ለአዳማ እና ሐዋሳ ማዕከል የተያዘው መርሃ-ግብር እንደተጠበቀ ነው]


በዚህ አጋጣሚ ተቋማችንን እንደ መርሃችን Learning Organization ለማድረግ እየደከማችሁ ለምትገኙ የኦፕሬሽን ዘርፍ የስራ ኃላፊዎች፣ የሰው ኃይል ዘርፍ የስራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች በስራ ክፍላችን ስም ከፍ ያለ ምስጋና እናቀርብላችኋለን።


__

የሰው ኃይል ስልጠናና ልማት ማዕከል

We strive to create a Learning Organization!!

EEP TRD Office

30 Jan, 12:06


በአዋሳ የደቡብ ፩ ሪጅን ቢሮ ውስጥ የሚመዘኑ አመልካቾች መርሃግብር!!

___

የሰው ኃይል ስልጠናና ልማት ቢሮ

We strive to create a learning Organization!!

EEP TRD Office

30 Jan, 12:00


Dear Readers,

Apologies for the oversight. We unintentionally missed including Worku Mulu’s name in the above list.

Thank you for your understanding.

EEP TRD Office

30 Jan, 12:00


በአዳማ ፩ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ውስጥ የሚመዘኑ አመልካቾች መርሃግብር!!

___

የሰው ኃይል ስልጠናና ልማት ቢሮ

We strive to create a learning Organization!!

EEP TRD Office

30 Jan, 06:36


ሰላም ለእናንተ ይሁን!

___

የውስጥ አቅም ስልጠና መርሃ-ግብር አካል የሚሆኑ አሰልጣኞችን ለመለየት የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ ሲሆን በአዲስ አበባ የማጠቃለያ ምዘና ፕሮግራም መሰረት ከሰኞ ጀምሮ አመልካቾች ያዘጋጁትን Presentation እያስገመገሙ ምዘናው በተያዘለት ሰዓትና ቦታ ላይ እየተከናወነ ይገኛል።


በዚህ አጋጣሚ ተቋሙን እጅግ የሚያኮሩ አሰልጣኞች እየታዩ ሲሆን ይህም በውስጥ አቅም ስልጠና መርሃ-ግብር በተለያየ መልኩ ተሳትፎ እያደረጉ ለሚገኙ የኦፕሬሽን ዘርፍ የስራ ኃላፊዎችና ሂደቱን ለሚመራው የሰው ኃይል ዘርፍ ትልቅ ብርታት መሆኑን መገንዘብ ችለናል።


ቀጣዩ የምዘና ስራ የሚሰራው በአዳማ ቁ-፩ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሲሆን ለሦስት ቀን የሚቆይ መርሃግብር ተዘጋጅቷል፤ እርሱ እንዳለቀ የምዘና ቡድኑ በዚያው ወደ አዋሳ አቅንቶ ደቡብ ፩ ሪጅን ላይ በሁለት ቀናት ምዘና ያከናውናል።


አዲስ አበባ ያላችሁ አመልካቾች ከወዲሁ ቀሪ ጊዜያችሁን እንድትጠቀሙበት አደራ ለማለት እንወዳለን።

___

የሰው ኃይል ስልጠናና ልማት ማዕከል

We strive to create a learning Organization!!

EEP TRD Office

26 Jan, 15:22


ሰላም ለእናንተ ይሁን!!

___

እነሆ አንድ ቀን ብቻ ቀረው!!

___

አስቀድመን በያዝነው መርሃ-ግብር መሰረት የውስጥ አሰልጣኞችን የምዘና ሂደት ነገ እንጀምራለን።

___

Are you ready?...
___

ቦታ - የማሰልጠኛ አዳራሽ (ከስልጠና ክፍሉ ቢሮ ጀርባ፣ ከዳታ ሴንተር ጎን)

ሰዓት - ጠዋት 2:30

___

ማሳሰቢያ
--

+ የመመዘኛ ነጥቦችን በሙሉ በድጋሚ ያስተውሉዋቸው!
+ እያንዳንዱ መመዘኛ የሚይዘው የራሱ ነጥብ አለው!
+ ማሰልጠኛው ላፕቶፕ እና ፕሮጀክተር ስለሚያቀርብ የእርስዎን Presentation file (PowerPoint) በፍላሽ ማምጣት ብቻ በቂ ነው!
+ በተሰጠዎት ደቂቃ ውስጥ ለማጠናቀቅ መቻል ወሳኝ ነው!
+ Be yourself!! Be smart!!
+ ውጤት የሚገለጸው የአዲስ አበባ ምዘና ሙሉ ለሙሉ ሲጠናቀቅ ነው!

__

መልካም ዕድል!!
___

የሰው ኃይል ስልጠናና ልማት ቢሮ

We strive to create a learning Organization!!

EEP TRD Office

17 Jan, 13:38


ማስታወቂያ
___

በውስጥ አቅም የስልጠና መርሃግብር (In-house training program) መሰረት በኦፕሬሽን ዘርፍ የሚያሰለጥኑ ባለሙያዎችን ለመምረጥ በተደረገ ጥረት የምዝገባ፣ የመጀመሪያ ዙር ምዘና እና ቅሬታ ተቀብሎ የማስተካከል ስራ ተሰርቶ መጠናቀቁ ይታወቃል...


በዚህም መሰረት ወደ ሁለተኛው ዙር ያለፉ አመልካቾችን በቀሪ 40% የማወዳደሪያ ነጥቦች መዝኖ ለመለየት እንዲቻል ከአዲስ አበባ (Corporate evaluation center) እንደሚጀመር በገለጽነው መሰረት ከዚህ በታች በተገለጸው መልኩ ዝርዝር መርሃግብር ተዘጋጅቷል።


በመሆኑም በወጣላችሁ መርሃግብር መሰረት በስልጠና ክፍሉ አዳራሽ (ተለዋጭ ቦታ ካለ አስቀድመን እንገልፃለን) ከጠዋቱ 2:30 እና ከሰዓት 7:30 ጀምሮ ተገኝታችሁ ምዘናውን እንድታከናውኑ እናሳስባለን።


የሰው ኃይል ስልጠናና ልማት ቢሮ

We strive to create a learning Organization!!

EEP TRD Office

17 Jan, 12:08


ማስታወሻ
___

በረጲ የደ/ቆ/የኃ/ማመንጫ ጣቢያ የውጭ ስልጠና ማስታወቂያ መሰረት አመልካቾችን መዝግበን እንደነበር ይታወሳል፤ ከዚሁ ጋር ተያይዞ ሰራተኞች ቅሬታ እንዲያቀርቡ ባወጣነው ማስታወቂያ መሰረት የ 6 (ስድስት) ሰራተኞችን ቅሬታ ተቀብለናል።

ይህም ለተቋሙ የትምህርትና ስልጠና ኮሚቴ ቀርቦ ጉዳዩን በዝርዝር ከተመለከተ በኋላ ውሳኔ አሳልፏል።

በዚህም መሰረት በስራ ክፍሉ ውስጥ 2 ዓመት ከ 9 ወርና ከዚያ በላይ የሰሩ 4 ሰራተኞች ወደ ምዘና ስርዓቱ እንዲካተቱ ውሳኔ አሳልፏል።

በመሆኑም በዚሁ አግባብ ለፈተና ዝግጅት እንድታደርጉ እያሳሰብን የምዘና ቡድን እንደተቋቋመ የፈተና ቀን የምናሳውቃችሁ መሆኑን እንገልፃለን።

___

የሰው ኃይል ስልጠናና ልማት ቢሮ

We strive to create a learning Organization!!

EEP TRD Office

15 Jan, 15:51


ማስታወሻ

___

ከረጲ የደ/ቆ/ኃ/ማመንጫ ጣቢያ የውጭ ሃገር ስልጠና ጋር በተያያዘ ባወጣነው ማስታወቂያ መሰረት ለስራ ክፍላችን የቀረቡ ቅሬታዎችን ተቀብለናል።


ከዚሁ ጋር ተያይዞ የቅሬታ ማቅረቢያ ጊዜ መጠናቀቁን ተከትሎ ሁሉንም ቅሬታዎች ለተቋሙ የትምህርትና ስልጠና ኮሚቴ ልከናል።


ስለሆነም ኮሚቴው በስራ ላይ ያሉ መመሪያዎችንና የሦስትዮሽ ስምምነቱን TOR  መነሻ አድርጎ ውሳኔ እስኪሰጥበት ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን እናሳስባለን።

___

የሰ/ኃ/ስልጠናና ልማት ቢሮ

We strive to create a learning Organization!!

EEP TRD Office

15 Jan, 14:57


ማስታወሻ
___

በውስጥ አሰልጣኞች የምልመላ ሂደት ከ 60% የተጠናቀቀውን የምዘና ውጤት ማስታወቃችንን ተከትሎ ቅሬታዎችን ስንቀበል መቆየታችን ይታወቃል፤ 


በዚሁ መሰረት፣ የምዘና ቡድኑ ቅሬታዎችን መዝኖ ማስተካከያ ያደረገባቸውን የስምንት ሰራተኞችና የስራ ኃላፊዎችን ዝርዝር አሳውቆናል።


በቀጣይ ለእያንዳንዱ አመልካች ከ 40% የሚመዘንበትን መርሃግብር በዚሁ ገጽ ላይ ስለምናሳውቅ ተገቢውን ዝግጅት እንድታደርጉ ከወዲሁ ለማስታወስ እንወዳለን።


የሰ/ኃ/ስልጠናና ልማት ቢሮ

We strive to create a learning Organization!!

EEP TRD Office

15 Jan, 14:48


እዴት ናችሁ?
___

ትናንት በተዘጋጀው Anonymous Poll ላይ በመሳተፍ ለተቋማችን የሚጠቅም ግብዓት እንዲገኝ በማድረጋችሁ እጅግ አድርገን እናመሰግናለን።


ሃሳቡን የወደዱት ባልደረቦች ባጋሩን በርከት ያሉ positive መልዕክቶች መነሻነት ይህን ዓይነቱን Anonymous Poll (የግለሰቡ ማንነት ሳይታወቅ የሚከናወን የድምጽ አሰጣጥ ስርዓት) በተለያዩና ለተቋም ፋይዳ ባላቸው ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የምንቀጥል መሆኑን ለመጠቆም እንወዳለን።


እስካሁን ምርጫ ያላደረጋችሁ ብትመርጡልን ተፈላጊውን Sample size ለማሟላት ይረዳልና ብታስቡበት ደስ ይለናል።


ብዙ ምስጋና!!

የሰ/ኃ/ስልጠናና ልማት ቢሮ

We strive to create a learning Organization!!

EEP TRD Office

10 Jan, 17:28


ማስታወቂያ

___

የድህረምረቃ ፕሮግራሞች (NGAT) የመግቢያ ፈተና ለመውሰድ የተመዘጋባችሁ በሙሉ ይህንን ሊንክ

( https://ngat.ethernet.edu.et)

በመጫን መረጃ ማግኘት ትችላላችሁ።

EEP TRD Office

09 Jan, 17:09


ለመረጃ... [እንድታውቁት]

EEP TRD Office

08 Jan, 09:25


ማስታወቂያ
___

ቀደም ሲል ለረጲ የደረቅ ቆሻሻ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በተዘጋጀ [የአሰልጣኞች ስልጠና] የውጭ ሃገር የስልጠና ዕድል ዙሪያ ማስታወቂያ አውጥተን እንደነበር የሚታወስ ነው።


በዚህ መሰረትም የኃይል ማመንጫው የአመልካቾችን ዝርዝር በውስጣዊ ማስታወሻ ልኮልናል።


በመሆኑም በዝርዝሩ ላይ ቅሬታ ያላችሁና በማስታወቂያችን ላይ ያወጣነውን መስፈርት ሙሉ ለሙሉ የምታሟሉ የማመንጫ ጣቢያው ሰራተኞች ጉዳዩ በተቋሙ የትምህርትና ስልጠና ኮሚቴ ውሳኔ ከማግኘቱ በፊት እስከ ጥር 6/2017 ድረስ ቢሮአችን በመቅረብ ቅሬታችሁን በጽሑፍ እንድታቀርቡ እንጠይቃለን።


ከዚሁ ጋር ተያይዞ 50% በሚይዘው የቃለ-መጠይቅና ተያያዥ መመዘኛዎች መሰረት የዕጩዎች መለያ ፈተና ለመስጠት ዕቅድ ስላለን [በዝርዝሩ ላይ ስማችሁ የተመለከተውና ከቅሬታ በኋላ እንደ ተገቢነቱ ስማችሁ የሚካተት ሰራተኞች] ስልጠናውን የሚሰጠው ዩኒቨርሲቲ የሚልከውን ፈተና ሰኞ ጥር 12/2017 ለመስጠት ዝግጅት ስላደረግን ከወዲሁ እንድታውቁት እናሳስባለን።

___

የሰው ኃይል ስልጠናና ልማት ቢሮ

We strive to create a learning Organization!!

EEP TRD Office

06 Jan, 12:00


Update on In-House Training Instructor Application Process
---
Dear Applicants,

Following our previous announcement, we have published the list of applicants who have successfully secured 45% or more of the 60% points in the evaluation. The remaining 40% will be determined through interviews and related competition assessments.

We kindly request those shortlisted to prepare accordingly for the interviews, which will be held at the designated centers listed in the announcement.

For those not included in the list:
• If you have any complaints or inquiries, please submit them via our office email address.
• Corporate staff members are encouraged to visit our office in person for any questions.

Thank you for your attention, and we wish you all a joyful holiday!

HR Training & Development Office

We Strive to Create a Learning Organization!!

EEP TRD Office

03 Jan, 15:16


ማስታወሻ
___

የመጀመሪያው ዙር የውስጥ አሰልጣኞች የምዘና ሂደት ተጠናቆ ወደ ሁለተኛ ዙር ያለፉ አመልካቾች ዝርዝር ተለይቷል።


የሁለተኛ ዙር ማጣሪያ የቃለ-መጠይቅ ክፍል ሲሆን በውስጡ ልዩ ልዩ መመዘኛዎችን አካቷል።

ሰኞ ዕለት: [28/04/17]

@ በመጀመሪያው ማጣራት ያለፉ አመልካቾች ዝርዝር
@ የሁለተኛው ዙር ምዘና የሚከናወንባቸውን ነጥቦችና ተያያዥ መረጃዎችን በማስታወቂያ እናወጣለን።

ለአሁኑ የቃለ-መጠይቅ ምዘና ማዕከላትን ከዚህ በታች በተቀመጠው Excel sheet ላይ እንድትመለከቱ እንጠይቃለን።

___

የሰው ኃይል ስልጠናና ልማት ቢሮ

We strive to create a learning Organization!!

EEP TRD Office

01 Jan, 13:17


For your information👆

EEP TRD Office

25 Dec, 09:04


ማስታወቂያ
---
ከአንዳንድ የመመሪያ ማሻሻያ ስራዎች ጋር በተያያዘ የሳፕ-1 ማስታወቂያ በያዝነው መርሃግብር መሰረት ስላላወጣን ይቅርታ እንጠይቃለን፤ ማሻሻያዎቹ እንደተከናወኑ የሚወጣ ይሆናል፡፡

ከዚህ በታች የተመረጡ አሰልጣኞችን በውጭ ሃገር ለማሰልጠን የሚያስችል ማስታወቂያ አውጥተናል፡፡

የሰው ኃይል ስልጠናና ልማት ማዕከል

We strive to create a learning Organization!!

EEP TRD Office

06 Dec, 14:30


ማስታወሻ
____

የሰው ኃይል ስልጠናና ልማት ቢሮ Learning Organization ለመፍጠር የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት እንዲቻል በ In-house Program የውስጥ አሰልጣኞችን በመጠቀም የተለያዩ ስልጠናዎችን ለመስጠት እንዲቻል ተቋማዊ የስልጠና ፍላጎቶችን ለይቶ መጨረሱ ይታወቃል።


በዚሁ መሰረት በ GO እና TSO ዘርፍ አሰልጣኝ መሆን ለሚፈልጉ አመልካቾች ማስታወቂያ አውጥቶ ምዝገባ ያከናወነ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት የዘርፉ የስራ ኃላፊዎችና የሚመለከታቸው ባለሙያዎች ያሉበት ቡድን ተቋቁሞ የምዘና ስራ እያከናወነ ይገኛል። 


ውጤቱንም በአጭር ጊዜ ለመግለጽ እንሞክራለን።


ከዚሁ ጋር በተያያዘ በ SAP phase 1 modules ላይ በሚቀጥለው ሳምንት ማስታወቂያ የምናወጣ ስለሆነ በ phase 1 modules ላይ ብቻ ስልጠና በመስጠት ልምድ ያላችሁም ሆነ ዕውቀቱ ኖሯችሁ ማሰልጠን የምትፈልጉ ሰራተኞችና የስራ ኃላፊዎች ከወዲሁ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እንጠይቃለን።


የሰው ኃይል ስልጠናና ልማት ቢሮ
We strive to create a learning Organization!!

EEP TRD Office

06 Nov, 15:27


ማስታወሻ
___
የውስጥ አሰልጣኞችን ለመመልመል ያወጣነው የማራዘሚያ ማስታወቂያ ሰኞ መጠናቀቁ ይታወሳል።


ይሁንና ማመልከቻዎቹን በኢሜይል እንደመቀበላችንና ቁጥሩም እጅግ ከፍ ያለ እንደመሆኑ በእኛ ስህተት አልያም በእናንተ ትክክለኛ የኢሜይል አድራሻ እና የማመልከቻ ቅጽ አለመጠቀም ምክንያት ያልተመዘገቡ ሊኖሩ እንደሚችሉ እንገነዘባለን።


ስለሆነም፣ ከታች በተያያዘው ቅጽ ላይ ስማችሁ የሌለ ሆኖም በጊዜ ገደቡ መሰረት ያመለከታችሁ በሙሉ አዲስ ማመልከቻና አዲስ ኢሜይል ስለማንቀበል: 


፩) ቀድሞ የላካችሁትን ኢሜይል በትክክለኛው የማሰልጠኛው ኢሜይል አድራሻ forward ብቻ እንድታደርጉ፣ [ነባሩን ኢሜይል በድጋሚ forward ማድረግ፣ የኢሜይል አድራሻው የግለሰብ ሳይሆን የቢሮው ብቻ መሆኑን ማረጋገጥ]


፪) ለማመልከት ከተቀመጠላችሁ ቅጽ ውጭ እንዳትጠቀሙ አልያም ፎርማቱን በ scan copy እንዳትልኩ፣ [የሚላከው excell format ብቻ ነው፣ ወደ pdf እንዳይቀየር]


፫) ኢሜይሎችን forward የማድረግ ተግባር የሚቆየው እስከ እሁድ ብቻ ነው፣

__
HR Training and Development Office

We strive to create a learning organization.

EEP TRD Office

25 Oct, 14:31


ማስታወቂያ
--
የሰው ኃይል ስልጠናና ልማት ቢሮ የውስጥ አሰልጣኞችን ለመመልመል በወጣው ማስታወቂያ መሰረት በስራ ክፍሉ የኢሜይል አድራሻ አማካይነት አመልካቾችን ስንቀበል መቆየታችን ይታወሳል፡፡


ይሁንና በርከት ያሉ አመልካቾች ማስታወቂያውን አላገኘንም የሚሉ ቅሬታዎችን ስላቀረቡልንና በ GO ዘርፍ የአዳማ 1 የን/ኃ/ማ/ጣቢያ እና በ TSO ዘርፍ የ Converter station የስልጠና ፍላጎቶች አለመካተታቸው ስለተገለጸልን ምዝገባው እነርሱን ያማከለ እንዲሆን ለማድረግ የምዝገባ ቀነ ገደቡን ለአንድ ሳምንት ያራዘምን ሲሆን የመጨረሻው ቀን ጥቅምት 24/2017 መሆኑን እናስታውቃለን፡፡

--
ማሳሰቢያ፡-

·        ለምዝገባ የስራ ክፍሉ ከላከው ቅጽ ውጪ አይጠቀሙ፤
·        በአንድ ጊዜ ከአንድ በላይ ኢሜይል አይላኩ፤ ማስተካከያዎች ሲኖሩዎት በቀደመው ኢሜይል ላይ reply በማለት ማስተካከያውን ይላኩልን፤
·        በግል ኢሜይል የሚላኩ ማመልከቻዎች ኮሚቴው ጋ ስለማይደርሱ እባክዎን በስራ ክፍሉ ኢሜይል አድራሻ ብቻ ([email protected]) ይላኩ፤

--

ከውስጥ አሰልጣኝ ምልመላ ጋር በተያያዘ ለተነሱ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች (FAQ) ምላሽ ስለመስጠት፡-

1.      አስቀድሞ በተቋሙ ውስጥ በማሰልጠን ተግባር ላይ ተሰማርተው የነበሩ ሰራተኞችን/ የስራ ኃላፊዎችን ማስታወቂያው ይመለከታልን?

 
·        በትክክል! የራስ አቅም ስልጠና ዓላማ በተቋሙ ውስጥ በእውቀት ሽግግር ላይ የሚሰሩ ባለሙያዎች/ የስራ ኃላፊዎች በአሰልጣኞች ስልጠና /TOT – Andragogy/ ርዕሰ ጉዳይ ላይ ስልጠና የወሰዱ ብቻ እንዲሆኑ ማድረግ ነው፤ በዚህም መሰረት በስልጠና ተግባር ላይ የሚሰማሩ ሰራተኞች በየሦስት ዓመቱ የሚታደስ የሰርተፊኬሽን ስልጠና ወስደው ሰርተፊኬት መያዝ ይጠበቅባቸዋል፤

 
2.      አስቀድሞ ተመሳሳይ ፕሮግራም በሌለበት ሁኔታ የማሰልጠን ልምድ ከመስፈርቶች ውስጥ ለምን ተካተተ?

 
·        ይህ አሰራር ጅምር እንደመሆኑና ቀደም ሲል በተቋሙ ውስጥ በቂ አሰልጣኞች ሰርተፊኬት እንዲኖራቸው ስላልተደረገ መስፈርቱ የዚህ ዙር የማወዳደሪያ ነጥብ አይሆንም፤ ሆኖም ተቋሙ በሁሉም የስራ ዘርፎች በቂ አሰልጣኞችን ፈጥሬያለሁ ብሎ ሲያምን ከዚህ በኋላ በሚኖሩ የኦፕሬሽን ዘርፍ ውድድሮች ላይ ማወዳደሪያው በ 100% ተግባራዊ ይደረጋል፤

 
3.      በሌሎች ዘርፎች ላይ ማስታወቂያ መች ይወጣል?

 
·        ቀደም ሲል እንደገለጽነው በሁሉም የስራ ዘርፎች ማስታወቂያዎች ይወጣሉ፤ በቅርቡ በ SAP Phase I ርዕሰ ጉዳዮች (HCM, FICO, PS, Material mgt… ወዘተ) ላይ አሰልጣኞችን እንመለምላለን፤ በቀጣይም በ HR, Safety, QMS, Legal, Finance, Cyber security, ICT, Gender… በመሳሰሉት ዘርፎች ላይ አሰልጣኞችን እንለያለን፤ በሦስተኛ ደረጃ የፕሮጀክትና የዲዛይን ይዘት ባላቸው የ Engineering, GC, TSC, Planning እና መሰል ዘርፎች ላይ አሰልጣኞችን እንለያለን፡፡

 
4.      ከከፍተኛ በታች የስራ አፈፃጸም ምዘና ውጤት ያለው የሚለው ሃሳብ ቢብራራ፤

 
·        “ከከፍተኛ በታች የስራ አፈፃጸም ምዘና ውጤት ያለውና በሕ/ስምምነቱ መሰረት በዲሲፕሊን ቅጣት የጊዜ ገደብ ውስጥ የሌለ መሆን አለበት” የሚለው አገላለጽ መጠነኛ ስህተት ያለው ስለሆነ “ከፍተኛ እና ከከፍተኛ በላይ የስራ አፈፃጸም ምዘና ውጤት ያለውና በሕ/ስምምነቱ መሰረት በዲሲፕሊን ቅጣት የጊዜ ገደብ ውስጥ የሌለ መሆን አለበት” በሚል ይታረም፡፡

 
·        ከፍተኛ የስራ አፈፃጸም ውጤት ማለት ከ 90 እስከ 94.99 ድረስ ያለ ነጥብ ነው፤

 
5.      የስራ ልምድ ውጤት እንዴት ነው የሚሰላው?

 
·        የስራ ልምድ የሚሰላው እስከ 14 ዓመት ላለው የስራ ልምድ ለእያንዳንዱ ዓመት አንድ ነጥብ በመስጠት ሲሆን፣ 15 ዓመት እና ከዚያ በላይ ያገለገሉ ባለሙያዎች/ የሥራ ኃላፊዎች ሙሉ 15 ነጥብ የሚያገኙ ይሆናል፡፡

____

የሰው ኃይል ስልጠናና ልማት ቢሮ

We strive to create a learning Organization!

EEP TRD Office

20 Oct, 17:50


edX
https://www.edx.org

EEP TRD Office

20 Oct, 17:50


ጥቆማ - ፪
___
Electric ን ጨምሮ በየትኛውም የሙያ መስክ ባለህበት ሆነህ የምትበቃበት፣ ውጤታማነትህን ተከትሎም Online certificate የምታገኝበት በርከት ያሉ ዌብሳይቶች አሉ፤

ለዛሬ ሁለት ዝነኛ ሳይቶችን እናስታውስህ... Coursera እና edX

ከስራ ፋታ ስታገኝ፣ የእረፍት ጊዜ እንዳይባክን ስትሻ እኒህ ሳይቶች ውስጥ ቆይ... 
___
Coursera
https://www.coursera.org

EEP TRD Office

20 Oct, 17:31


ጥቆማ - ፩
___
የ Electric ርዕሰ-ጉዳይ ይመስጥሃል? ስለምን ማወቅ ትፈልጋለህ? የምትሰራው የት ነው? ኃይል ማመንጫ፣ ኃይል ማከፋፈያ፣ ኃይል መቆጣጠሪያ...

የትም ሁን፣ የትኛውም ስራ ላይ ተሳተፍ፤ ስለ ኤሌክትሪክ ልታውቅ የምትፈልገውን ሁሉ የምታውቅበት ስፍራ ይህ ነው... EEP Portal...

Subscribe አድርገው፤ ማንኛውንም Article በ email አድራሻህ ማግኘት ትችላለህ።

የትም ሆነህ ብቁ የምትሆንበት Portal ይኸው... 
____

https://electrical-engineering-portal.com/

EEP TRD Office

20 Oct, 17:18


Knowledge is like an ocean!

EEP TRD Office

19 Oct, 10:05


Final!! - Education Cost Refund Policy Beneficiaries Announcement
___

Dear Women Employees and Work Unit Heads,

Greetings. 


As you may recall, we previously shared the list of this year’s beneficiaries for the Education Cost Refund Policy, requesting your feedback and any concerns you might have. We have since collected and reviewed all issues raised, both via email and physical submissions.


After a thorough review of the complaints, the Education and Training Committee has reached a decision and finalized the list of approved applicants for the refund process.


Please find attached the official memo and the final list of beneficiaries for your reference and further action.


Thank you for your cooperation.


HR Training and Development Office

We strive to create a learning organization.

EEP TRD Office

17 Oct, 14:17


In-House Training Instructors Registration
-------
Dear all,
Greetings!

We are excited to announce that our office is now accepting registrations for in-house training instructors for the operations departments. Attached, you will find a memo outlining the announcement criteria along with the necessary registration formats.

We encourage all interested individuals to submit their registrations. For updates regarding this announcement, please follow us on our office Telegram channel.

Thank you and best of luck!

HR Training and Development Office
We strive to create a learning Organization!

EEP TRD Office

16 Oct, 15:12


Profile of Mr. Wondimu Negash

For those of you who may not be familiar with Mr. Wondimu, here is a brief profile of his accomplishments.

Mr. Wondimu first joined our training center 41 years ago and served for two years. Since then, he has built an impressive career as a senior systems engineer with over 25 years of experience in the defense electronics industry in the UK.

He is also a founding member of KMS Health, where he has contributed to developing technology that facilitates access to qualified healthcare providers. 

Additionally, Mr. Wondimu is a well-known mental health awareness advocate in both Ethiopia and the UK, having authored seven books in Amharic on neuroscience and mental health.

Mr. Wondimu is a founding and active member of organizations such as Ethiopians for Ethiopians (E4E) and United Ethiopians for Peace and Reconciliation (UE4PR). 

He is also deeply engaged in neuroscience coaching and research, with a focus on using neuroscience to promote peace and reconciliation. His public lectures, YouTube blog, and various engagements aim to foster better mental health and societal harmony through scientific understanding.

We are grateful for his dedication to mental health awareness and his valuable contributions to our session today.

Thank you.

TRD team.

EEP TRD Office

16 Oct, 15:11


Gratitude for Today's Mind talk Session

___

Today, our office held an insightful discussion session on the topics of Mind Function and the Chimp Model, based on the work of Prof. Steve Peters, and led by our former colleague, Mr. Wondimu. 

It was an uplifting session that explored how our brain functions and how we can effectively respond to our surroundings. We learned how our brain impacts our daily decisions in both our professional and personal lives.

As this month is dedicated to Mental Health Awareness, we were fortunate to have Mr. Wondimu with us to share his extensive experience on the subject. 

We want to extend my sincere gratitude to everyone who joined the session on such short notice, and a special thank you to Mr. Wondimu for his dedication to raising awareness about mental health.

We look forward to organizing similar sessions in the future by inviting other guest speakers from various backgrounds.

Thank you once again!

Best regards,

HR Training and Development Office

We strive to create a learning Organization!!

EEP TRD Office

10 Oct, 14:40


A Heartfelt Thank You!!
______

Thank you to everyone who contributed to making this graduation day more memorable and special. We deeply appreciate the support we’ve received from the management, work units, and individuals.

A special thanks to the TRD team for your dedication and commitment to making this day a reality.

To our graduates, congratulations! Please remember the valuable advice shared by your managers as you embark on your career journey.

We would also like to extend our gratitude to our esteemed guest, Ato Bogale Feyisa, whose deep knowledge and historical connection to our training center have enriched today’s celebration.

This event is particularly meaningful as it marks the first time in 30 years we have been able to hold a graduation in this hall, a space previously unavailable to us. 

Our graduates this year are fortunate to be part of this significant moment, and we thank the management team for their efforts in making it possible.

Thank you all once again.

Sincerely,

HR Training and Development Office