40/60 @ባለመብቶች

@balemebtoch


ስለ 40/60 @Balemebtoch ነን።

40/60 @ባለመብቶች

24 Nov, 08:04


በቲክቶክ የሰማነው ውሳኔ
:
የ40/60 የመኖሪያ ቤቶች እጣ አወጣጥ ተገቢነትን በተመለከተ በአ.አ መስተዳድር: በኢት.ንግድ ባንክ እና በፌዴራል ቤቶችና ከተማ ልማት ሚኒስትር ላይ ክስ አቅርበን በሁሉም መዝገቦች(6 መዝገብ) በየደረጃው ባሉ ሁሉም ፍርድ ቤቶች አስፈርደን አፈጻጸም ደርሰን ቤቶቹን ልንቀበል በተቀጠርንበት ሳምንት ጉዳዩ ለህገመንግስት አጣሪ ተመርቶ ከዛም አልፎ ለፌዴሬሽን ምክርቤት ቀርቦ መስከረም 29 ቀን 2016 አ.ም ተከራክረን ያሸንፍንበት ህግ እንደተቀየረ ትላንት በቲክ ቶክ ሰማን!

ለአመታት የተከራከርንበትን ጉዳይ እንደው ውሳኔውን እንኳን አሳውቁን ስንል (ቢያንስ የውሳኔውን ግልባጭ ባትሰጡን እንኳን አንብቡልን እያልን እየለመንን ከርመን ) ለኛ ለዋናዎቹ ባለጉዳዮች እምቢ ብለው ለ11 ክልሎች የውሳኔ ግልባጭ ልከው ለኦሮሚያ ክልል የተላከው የውሳኔ ግልባጭ በቲክ ቶክ ሲዘዋወር አየን ውሳኔያችንን(መርዶአችንን) በቲክቶክ ሰማን!..ያው ሁሉ ነገር አሳፋሪ ነው !

የዛሬ አስር አመት መንግስት ያወጣውን ህግ ተማምነው አነስተኛ ንብረት ያላቸው ሸጠው:የሌላቸው ተበድረው :አንዳንዶቹ በአረብ ሃገር ለአመታት ለፍተው ያጠራቀሙትን ብር ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በዝግ አካውንት ካስቀመጡ ከአስር አመት በኋላ መንግስት 'ተሳስቼ ነው ያንን ህግ ያወጣሁት! ከፈለጋችሁ ብራችሁን ውሰዱ!' ብሏል።

የዛሬ አስር አመት የሰጠኸውን ሁለት መቶ እና ሶስት መቶ ሺ ብር አሁን ሲመልስልህ አባቶች 'ወርቅ ላበደረ ጠጠር መለሰለት የሚሉት አንተ ላይ ደረሰ ማለት ነው!

እኔ ተራው ግለሰብ እንኳን ምናልባት ውሳኔው ቢቀየር(ህጉ ቢሻር) ለደምበኞቼ እንዴት እንደምነግራቸው ተሳቅቄ እንቅልፍ ባጣሁበት መንግስት ውሳኔውን በቲክቶክ ለቆት ሳይ እንዴት አልፈር?!!

የዛሬ አስር አመት የወጣ ያውም በወቅቱ ከነበሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ጀምሮ: የሃገሪቷ ትልቁ ባንክ ፕሬዝዳንት: የዋና ከተማ ከንቲባ:ሚኒስትሮች በየደቂቃው በቴሌቪዥን መስኮት እየቀረቡ ህዝቡን ወስውሰው አንጡራ ሃብቱን ከተቀባበሉት ከአስር አመት በኋላ ከፍትህ ይልቅ ህዝበኝነት በተጫነው አካሄድ እንደነሱ አባባል 'የባለፈው መንግስት ህግ' ህገመንግስታዊ አይደለም በማለት በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን ሃብት ቅጠል የሚያደርግ ውሳኔ ይሰጣሉ!?

በዚህ አጋጣሚ በየደረጃው ያሉ ፍርድ ቤቶች ላሳዩት የህግ የበላይነትን ማረጋገጥ እና ፍትሃዊነት ትልቅ ክብር ያለኝ መሆኑን መግለጽ እፈልጋለሁ ።እኔም የሙያ ባልደረቦቼም በዚህ ጉዳይ በሁሉም ፍርድቤቶች ጥያቄያችን ተቀባይነት አግኝቶ የከሰስናቸውን አካላት ረትተናል።ክርክሩ በፍርድ አደባባይ ተቀባይነት ያላገኘው መንግስት በፖለቲካ ተቋም ለክርክሩ መነሻ የሆነውን ህግ ቀይሬዋለሁ ካለ ግን ምን ማድረግ ይቻላል?!

ቀጣዩ ሂደት ምንድነው?!

ከአመታት በፊት ኢፍትሃዊ የሆነውን አካሄድ አንቀበልም ብለን ስንነሳ በፍርድ ብናሸንፍ እንኳን የሆነ ቦታ ላይ ይህ አይነት የፖለቲካ ውሳኔ እንደሚያጋጥመን እናውቅ ነበር! እናም አሁንም ትግሉን እንቀጥላለን!!

ተቀባይነት ኖረውም አልኖረውም ይህን 'የተሳሳተ ' የተባለውን ህግ ባወጡ እና ባስፈጸሙ እንዲሁም በጊዜ በዜጎች ላይ ጉዳት እንዳይደርስ ህጉን ባላስለወጡ የቀድሞም ሆነ የአሁን ተቋማትና የተቋማት መሪዎች ላይ ክስ እናቀርባለን! ድምጻችን እስኪሰማ በደላችን እስኪሽር ድረስ በቻልነው መንገድ ሁሉ ፍትህ እንጠይቃለን!!

የሚሆነውን አብረን እናያለን!!

(እኔ ይህን አገልግሎት የምሰጠው የዛሬ አራት አመት በተከፈለኝ ክፍያ ብቻ ነው..ለማገዝ የሚፈልግ ማናቸውም ለፍትህ እቆማለሁ የሚል ባለሙያ ጆይን ሊያደርገን ይችላል)

ትግሉ ይቀጥላል!!

40/60 @ባለመብቶች

05 Sep, 15:34


መንግሥታችን ለአንዱ እናት ለአንዱ የእንጀራ እናት መሆኑን እያሳየን ይሆን ?😢☹️😕🤐

40/60 @ባለመብቶች

13 Aug, 13:08


አይ 40/60 እጅ መንሻ ሆኖ ቀረኮ።
ቆጣቢው ቤት አለኝ ብሎ ይጠብቃል፡ በጎን ያከፋፍሉታል።

40/60 @ባለመብቶች

08 Jun, 15:24


https://youtu.be/mm2o0-bK2mU

40/60 @ባለመብቶች

08 Jun, 15:20


Channel photo updated

40/60 @ባለመብቶች

15 Nov, 21:19


አጠቃላይ የ20/80 አዲስ የቤት ፕሮግራም አሸናፊዎች ዝርዝር !

Credit : Mayor Office of AA

@tikvahethiopia

40/60 @ባለመብቶች

14 Oct, 09:03


40/60 @ባለመብቶች pinned «አንድ ሰውና 1ሺ ሰው በህግ ፊት»

40/60 @ባለመብቶች

14 Oct, 05:10


https://youtu.be/mm2o0-bK2mU

40/60 @ባለመብቶች

05 Aug, 13:15


ፍትሕ መጽሄት ቁጥር 96 ነሐሴ 2012
እኔ እና ታከለ ኡማ
በተመስገን ደሳለኝ

......ሳናስበው መገናኛ አካባቢ ያለ ኮንዶሚኒየም ("ገና ያልተሰጠ ነው ") ደርሰን ኑሮ መኪናዋን አቁሞ በጣቱ እንደ ጨፈቃ ወደ ተከመሩ ቤቶች እየጠቆመ:-

እነዚህ ሁሉ የሚቀጥለው ቅዳሜ (ሰኔ 27 መሆኑ ነው) ዕጣ የሚወጣባቸው ናቸው አለና ከኃላ ስትከተለን ለነበረችው የቤቶች ኤጅንሲ ኃላፊ ኢንጅነር ሰናይት ዳምጠው ስልክ ደውሎ ወደ እሱ መኪና እንድትመጣ ነገራት። ወዲያውኑ በሹፌሩ መስኮት በኩል ብቅ ብላ ( እሱ አልወረደም) ማውራት ጀመሩ

" ሰኒ እነዚህ ቤቶችም ሳምንት ዕጣ የሚወጣባቸው ናቸው አይደል?" ሲል ቀለል አድርጎ ላቀረበው ጥያቄ ምላሿ እንደ ቦንብ የፈነዳ ነበር።

"እንዴ ታኬ ቅዳሜ እኮ እጣ የሚወጣው ለፎርማሊቲ እንጅ እኛ እኮ ቆይቷል መስጠት ከጀመርን።"

ሰናይት አለቃዋ እንድትመለስላትና እኔ እንድሰማው የፈለገው ነገር እንዳልገባት አውቄአለው። ለዚህም ነው "ገና ዕጣ ይወጣባቸዋል" ያላቸውን ቤቶች ገና ድሮ እየታደሉ መሆኑን እየነገረችን ያለው (በማግስቱ ድምጻዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ በመገደሉ የይስሙላ ዕጣ ሳይወጣ ቀርቷል።)..............

40/60 @ባለመብቶች

27 Jul, 11:45


Watch "19 ሺህ 40/60 ቤቶች የት ገቡ? | ''መንግስት ሆይ እባክህ ስማን" | "መኪናዬን ሸጬ ፤ ቆሎ እየበላሁ ነው የከፈልኩት" | 40/60 Condominium" on YouTube
https://youtu.be/8omrKvQ-bmg

40/60 @ባለመብቶች

27 Jul, 11:43


https://youtu.be/pdKey94OZ-U

40/60 @ባለመብቶች

17 Jul, 13:12


" ... ከወቅቱ የዋጋ ንረት ጋር ሊሄድ የሚችል አዲስ ታሪፍ ለማውጣት ጥናት እያደረኩ ነው " - የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጠው ቃል ፤ አሁን በሥራ ላይ ያለውን ታሪፍ በማሻሻል ከወቅቱ የዋጋ ንረት ጋር ሊሄድ የሚችል አዲስ ታሪፍ ለማውጣት ጥናት እያካሄደ መሆኑን ገልጿል።

በ2010 ዓ/ም የፀደቀውና አሁንም በሥራ ላይ ያለው የኤሌክትሪክ ታሪፍ መጀመሪያ ላይ ሲወጣ በወቅቱ ከነበረው የዋጋ ግሽበት እና የኑሮ ውድነት ጋር ታሳቢ በማድረግ የተደረገ ጭማሪ ቢሆንም አሁን ገበያ ላይ ያለው የግብዓት የዋጋ ንረት በታሪፍ ላይ ማስተካከያ ለማድረግ እንዳስገደደ ገልጿል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ብዙወርቅ ደምሴ ፤ በ2010 ዓ.ም. የተደረገው የታሪፍ ማሻሻያ በኑሮ ውድነቱ እየተዋጠ በመሆኑ በቀጣይ ለሚታሰቡ የመልሶ ግንባታ ሥራዎች የታሪፍ ማሻሻያው በጣም አስፈላጊ ነው ሲሉ መናገራቸውን ሪፖርተር ፅፏል።

ተቋሙ እየሰጠ ባለው አገልግሎት ዙርያ ላይ የሚነሱ ቅሬታዎችን ለመፍታት ያግዘኛል በማለት በአራት ዙር በአራት ዓመታት እንዲጠናቀቅ ተደርጎ በ2010 ዓ.ም ይፋ ያደረገው የታሪፍ ማስተካከያ በታኅሳስ 2014 ዓ.ም. የመጨረሻ ዙር የሆነውን ጭማሪ ማድረጉ ይታወሳል፡፡

ይሁን እንጂ ካለፉት አራት ዓመታት ወዲህ በተለይም በ2013 ዓ.ም. እየተገባደደ ባለው በ2014 እየታየ ያለው ዋጋ ንረት የሚገመት እንደነበር አለመሆኑን ዋና ስራ አስፈፃሚው ለጋዜጣው ተናግረዋል።

በአገር ውስጥ ሆነ በዓለም አቀፍ ገበያ ከፍተኛ የሆነ የዋጋ ጭማሪ በመኖሩ ምክንያት የኃይል ቆጣቢና መቆጣጠሪያ መሣሪያዎችን ወደ አገር ውስጥ ገዝቶ ለማስገባት ብዙ ሚሊዮን ዶላሮች በማስፈለጉ የታሪፍ ማስተካከያ በከፍተኛ ሁኔታ አስፈላጊ መሆኑን አስረድተዋል።

በመሆኑም በዓለም ካለው የፖለቲካ እንዲሁም የገበያ አለመረጋጋት ጋር ተያይዞ የዋጋ ንረት በመፈጠሩና ከኤሌክትሪክ ከደንበኞች የሚሰበሰበው ወርኃዊ ታሪፍ አገልግሎቱን አሻሽሎ ለማቅረብ በቂ ባለመሆኑ፣ ወቅቱን የጠበቀ የታሪፍ ማሻሻያ በማድረግ የግብዓት ዕቃዎችን በመግዛት ለኅብረተሰቡ መብራት እንዳይቆራረጥ የመልሶ ግንባታና የማስፋፊያ ሥራዎች አሉብን ብለዋል፡፡

ነዳጅ ዋጋ ላይ በየወሩ የታሪፍ ማሻሻያ እንደሚደረገው ሁሉ፣ በኤሌክትሪክ አገልግሎትም ወቅቱን የጠበቀ ማሻሻያ በማድረግ የመልሶ ግንባታና ማስፋፊያ ሥራን ማከናወን እንደሚያስፈልግ አክለዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት በዋጋ ንረቱ ምክንያት ወቅቱን የጠበቀ የታሪፍ ማሻሻያ ለማድረግ አዲስ የታሪፍ ፕሮፖዛል እየተዘጋጀ እንደሆነ የገለጹት አቶ ብዙወርቅ፣ በቀጣይ ፕሮፖዛሉ እንደተጠናቀቀ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቦ ከፀደቀ የታሪፍ ማስተካከያው ወደ ሥራ ይገባል ብለዋል፡፡

#ሪፖርተር

40/60 @ባለመብቶች

15 Jul, 12:00


#SkillMart_International_College

👉 Register to our unique Master's programs
👉 More than 80 merit based scholarships

Address:
👉Addis Ababa, Megenagna, Meseret Defar Building 6th floor, 0928 000 333/111 ።
👉Bahirdar Merkato Market center 0927000222/333
Join us 👉
https://t.me/joinchat/hnbmUYObA5hjNDI0

40/60 @ባለመብቶች

15 Jul, 11:50


በም/ቤቱ እራሳቸውን የተከላከሉት ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ !

" እኔ መጀመሪያ ማንሳት የምፈልገው ፤ መጀመሪያ ከግል ስብእናዬ መነሳት ፈልጋለሁ እኔ እስከማስበው ድረስ ምስኪኑ ህዝብ ቆጥቦ ቤት እንዲያገኝ ነው ፍላጎቴ ፤ ይሄ ከነበረኝ ስብእና እንፃር ሙስና የሚለው የሚገልፀኝ አይደለም።

ነገር ግን ድርጊቱ ተደርጎ ከሆነ እኔም አዝኛለሁ፤ ይሄም ጥልቅ የሆነ ምርመራ ተደርጎ ነገ ሁላችንም የምናየው ይሆናል።

ወደ ዋናው ሀሳቤ ስሄድ የአመራር ሚና ምድነው እኔ የቢሮ ኃላፊነ ነኝ፣ በተለይ የቢሮ ኃላፊ ስሆን አጠቃላይ strategic የሆነ direction ነው የምሰጠው።

እነዚህ የ routine የሆኑ ስራዎች ላይ ስራዎችን አልሰጥም። ነገር ግን በዚህ ሂደት ማየት የሚገባኝን የአመራር ክፍተቶችን እወስዳለሁ። እሱን የምክደው አይደለም።

እኔ በ Presentation ላይ በኢንሳ ተረጋገጠ አላልኩም። የቪድዮ ቅጂ ስላለ እሱን ማየት ይቻላል። ነገር ግን እንዴት ነበር የሚለውን ለዚህ ምክር ቤት ለታሪክ መቅረት ስላለበት ማቅረብ ይገባኛል።

መጀመሪያ ለዕጣው ዝግጁ ስናደርገው ከ9 ወር በፊት ነው ይሄ ስራ ያተጀመረው ይሄ ስራ ከተጀመረ በኃላ መጀመሪያ የተደረገው ለኢኖቬሽን ... እ "

የምክር ቤቱ አፈጉባኤ ወ/ሮ ሱፌና አልከድር ፦

" የተከበሩ ዶ/ር ሙልቀን ... በሂደቱ ላይ ሳይሆን "

ዶ/ር ሙሉቀን ፦

" አይደለም ሀሳቤን ... "

የም/ቤቱ አፈጉባኤ፦

" በቀረበው ላይ ብቻ አስተያየት ይስጡ "

ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ፦

" ገብቶኛል ክብርት አፈጉባኤ ... "

የም/ቤቱ አፈ ጉባኤ ፦

" እሱን ፍርድ ቤት የማያጣራው ጉዳይ ይሆናል "

ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ፦

" አይደለም፤ ይሄ ም/ቤትም... ለመደመጥም እንትን ልሁን ምክንያቱም ይሄ ምክር ቤትም ማወቅ የሚገባውን አካሄዱን ማወቅ ስለሚገባው ስላለበት ነው መናገር ያለብኝ ።

ስለዚህ በሂደቱ አስተያየት መስጠት ያለብኝ በዚህ መልክ ነው።

ሎተሪው ዕጣ ከመውጣቱ በፊት 2 ደብዳቤ በህዳር 17 /2014 በአብርሃም ተፈርሞ ለኢኖቬሽን ሚኒስቴር እና ለኢንሳ የሞያዊ ድጋፍ ኣስፈላጊድን እንድታደርጉ ብለን ፅፈናል።

የኢኖቬሽን ሚኒስቴር በታህሳስ 26/2014 በደብዳቤ ምክረ ሀሳብ ሰጥቶናል። ከዛ በምክረ ሀሳቡ መሰረት የሚስተካከለውን አስተካክለናል። ኢንሳን በተመለከተ ግን ምንም አይነት ነጥብ አልሰጠንም personally እንደውም ዶ/ር ሹመቴን አግኝቼ ለማውራት እባክህን...ክብርት ያስሚንም ስላለች ክብርት ያስሚንም ደውላለት እንደውም ፍቃደኛ ያልሆነበት ሁኔታ ነበር የነበረው። ዕጣው ከመውጣቱ በፊት የነበረው ሂደት ይሄው ነው።

ሰኔ 21 ቀን 2014 በአቶ ሽመልስ የተፃፈ ደብዳቤ ተወካይ ይመደብልን በተባለው ሰዓት ..."

የም/ቤቱ አፈጉባኤ፦

" በጣም ያሳጥሩልን "

ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ፦

" አሳጥራለሁ ግን ካልተሰማሁ at least ይሄ ምክር ቤት ይስማኝ ካዛ በኃላ ችግር የለውም ሌላውን ነገር ..."

የም/ቤቱ አፈጉባኤ፦

" ማለት ይሄ የተከበረው ምክር ቤት ይሄንን ከማጣራት ስልጣን የለውም፤ የማጣራት ስልጣን ያለው ፍትህ ሚኒስቴር ነው "

ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ፦

" ለታሪክ መቀመጥ ስላለበት እኔ ከግል ስብእናዬ ከከፈልኩት የፖለቲካ ዋጋ ካለኝ ነገር ይሄ ምክር ቤት understand አድርጎ ለታሪክ መቀመጥ ስላለበት ነው። ይሄን መናገር የፈለኩት።

ከይቅርታ ጋር ክብርት አፈጉባኤ ባያቋርጡኝ ብቀጥል። አጭር አጭር አድርጌ ልግለፅ።

ስለዚህ ሰኔ 21 ቀን በአቶ ሽመልስ በተፃፈው ደብዳቤ የዘርፉ ምክትል ኃላፊ ለሆኑት ለአቶ አብርሃም ደርሷቸዋል። "

የም/ቤቱ አፈጉባኤ፦

" አሁንም ላስቆሞት ነው። አልፈቅድም። ሁሉንም ዝርዝር እንዳያቀርቡልን አልፈቅድም "

ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ፦

" አጭር ነው ፤ ሀሳቤን ወይም ደቂቃ ይስጡኝና... "

የም/ቤቱ አፈ ጉባኤ፦

" ሀሳቡን አጭር አድርገው፣ የሚቃወሙትን ነገር ላይ ብቻ "

ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍታ፦

" ክብርት አፈ ጉባኤ የምቃወመው ይሄን ሀሳቤን ገለፅኩኝ በኃላ ነው "

የም/ቤቱ አፈ ጉባኤ፦

" ለማስቆም እየተገደድኩ ነው "

ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ፦

" እሺ በምን ልናገር ታዲያ ? "

የም/ቤቱ አፈጉባኤ፦

" በጣም በማሳጠር "

ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ፦

" እሺ፣ ችግር የለውም ! በጣም አሳጥራለሁ። የምክር ቤት አባላትን በጣም ይቅርታ ጠይቃለሁ። ማወቅ ስላለባችሁ ነው።

ሰኔ 21 ቀን በአቶ ሽመልስ የተፃፈው ደብዳቤ እኔ ሰኔ 21 ምናልባት በጊዜው አልነበርኩም በባለቤቴ ወሊድ ምክንያት በዚህ ሰዓት ዳታ ሲቀበሉ፣ እንዲህ ያለውን ደብዳቤ ሲፃፃፉም በጊዜው አልነበርኩም።

የኔ ምክትል የነበረው ግን ይሄንን ዳብዳቤ ተቀብሎ ባለሞያ ወክልሉልን ባለን መሰረት ለሶፍትዌር ዳይሬክተር ባለሞያ እንዲወክል ፅፏል።

ከዛም በድጋሚ አቶ ሽመልስ ሰኔ 21 የቤት መረጃ ለቢሯቹ የላክን መሆኑን ይላል። እዚህ ጋር አቶ ሽመልስ አጠቃላይ የቤት ምዝገባ ያተደረጉበትን፣ ዕጣ የሚወጣባቸውን አቶ ሽመልስ ልኳል።

እኔ በዛ ሰዓት ስላልነበርኩ ምክትሌ አቶ አብርሃም አሁንም ይሄንን ለሶፍትዌር ዳይሬክተሮች መርቶ ወደባለሞያው የገባበት ሁኔታ አለ።

ለምን ይሄን አነሳሁኝ ለሚለው ሁለት ነገር ነው።

አንደኛው ዕጣ ከመውጣቱ በፊት ክብርት ያስሚንም እንደውም እኔ አልነበርኩም ክብርት ያስሚን የእኔ ምክትል ቢሮ ኃላፊዎች ይዛ ቢሯችን መጥታ እዛ ስላልነበርኩኝ ያለውን ነገር ውይይት አድርጋ ሲስተሙ እንዴት ነበር ተብሎ display ተደርጎ ነበር እሱ በማየት ደረጃ እሳቸውም ስላሉ ይገልፁታል።

ሌላው ከ4 በላይ ሙከራ ተደርጓል የተባለው ምናልባት ክብርት ከንቲባ ባሉበት ሙከራ አድርገናል። ከዛም በኃላ ይሄ ኮምፒዩተር እኛ አዲስ ብለን ነው የሰጠነው። እንግዲህ ይሄ too በጣም technical እኔ የተማርኩት በሰላምና ደህንነት more of social science ነው። እኔ strategically በሆነ way ነው እንጂ መሥጠት ያለብኝ ምን አይነት algorithm ተጠቅሟል፣ behind የሰራውን ምን አይነት ሶፍትዌር ይጫን የሚልውን ነገር እኔ አላውቀውም።

ነገር ግን ይሄ ኮምፒዩተር አዲስ ነው። ከግዢ የሰጠነው ነው። ሰጠን ባለሞያው ይጠቀምበት ይሄን ያድርግበት እኔ እንደ አመራርነቴ ወርጄ የማየት role አለኝ ብዬ አላስብም።

ዕጣው ከመውጣቱ ለፊት ማታ ታሸገ፣ ከታሸገ በኃላ ታዛቢ ባለበት ታሸገ፣ ምንም ዳታ እንደሌለው ታይቶ ታሸገ። እኔ ኮምፒዩተሩ ጋርም ቀርቤ አላውቅም። ከዛ በነገታው መጡ ክብርት ያስሚን ባለችበት ሌላም ታዛቢ ባለበት በሩ ተከፍቶ ተገባ ካዛ ኮምፒዩተሩ ታየ ከዛም ክብርት ከንቲባ ባለችበት ያሬድ የሚባል ባለሞያ በቴክኖሎጂ የታወቀ ነው እሱ ይየው ተብሎ መጣ ያሬድ የሚባለው ሰውዬ ክሊክ አድርጎ ያለውን ነገር ጠቅላላ አየ መሄድ ይችላል ብሎ እዛው confirmation ሰጠን ምክንያቱም ክብርት ያስሚንም ስላሉ በዚህ መሰረት ወደ እጣው መጣ።

ወደ ዕጣው ሢመጣ presentation ተዘጋጀ፣ ከዛም ለቢሮው ይመጥናል አንተ ብታቀርበው ተብዬ እንዳቀርብ ተደረገ፤ ከዛ ውጭ Presentation ላይ ያቀረብኩት ደግሞ አንዱ ነገር ጠቅላላ የተሰጠኝን ሀሳብ ነው።

ለምሳሌ ከታች ባለሞያ አለ ከባለሞያው በላይ ዳይሬክተር አለ፣ ከዳይሬክተር በኃላ..."

ዶ/ር ሙሉቀን ይህንን እየተናገሩ እያሉ በቀጥታ በአዲስ ቴሌቪዥን ለህዝብ ሲሰራጭ የነበረው ንግግር ተቋርጧል። በኃላም ያለመከሰስ ማብታቸው ተነስቷል።

@tikvahethiopia