ግጥም በኢትዮጵያ

@ethiopia_poem


ግጥም በኢትዮጵያ

17 Oct, 18:48


https://t.me/Yonny_Athan?livestream=ef390589f25098de51

ግጥም በኢትዮጵያ

17 Oct, 18:16


https://t.me/Yonny_Athan?livestream=3ce9a555141cadec4d

ግጥም በኢትዮጵያ

17 Oct, 14:14


https://t.me/yomin1_2

ግጥም በኢትዮጵያ

16 Oct, 19:29


https://t.me/Yonny_Athan?livestream=ecb424e5d99c0019f5

ግጥም በኢትዮጵያ

16 Oct, 17:30


እስቲ ልመርቅሽ
        እስቲ ደሞ ልጣሽ
የልብሽን አይቶ እግዜር ከኔ ያውጣሽ
.


ዮኒ_ኣታን

Share @Yonny_Athan
Share @Yonny_Athan

ግጥም በኢትዮጵያ

14 Oct, 10:51


ሰው ፈለገች የሚያፅናናት
ችግር ውስጧን ሚረዳላት
ሰው ፈለገች የሚያፅናናት
የአይኗን እንባ ሚያብስላት

ለጠየኳት ጥያቄዎች
ምንም ነበር መልሰ ቃሏ
ብዙ እንደሆነች ግን
ይናገራል ፊት አካሏ

ብቻ...ዝም ብላለች

ታስታውቃለች ሆድ ብሷታል
ታስታውቃለች እንደከፋት
ቆንጆ መልኳን ተመልክቶ
ማን ይሆን ሰው ደርሶ የገፋት
ደረቅ ብሏል ውብ ከንፈሯ
አላገኘም አንዳች እህል
ቀዝቀዝ ብሏል የእጇ መዳፍ
ምን ሁናለች እቺ ጉብል

ቀና ብላ እያየችኝ
ዘረገፈች የአይኗን እንባ
ስቅስቅ ብላ አለቀሰች
ነጠላ እጇን ተከናንባ

እንዲህ ነው እያለች መናገር ባትችልም የውስጧን አውጥታ
ብዙ አውርታኛለች ከኔ ጋራ ሳለች ቃሏን በዝምታ
ይገርማል አንዳንዴ
ቃላት ሳይደረደር ምስክር ሳይጠራ ሀቀኛ ሳይለካ
ብዙ ሳንናገር በዝምታ ብቻ ቃል ይወጣል ለካ!


ዮኒ
ኣታን @yonatoz

Share @Yonny_Athan
Share @Yonny_Athan

ግጥም በኢትዮጵያ

11 Oct, 14:48


Share
@yonny_athan
@yonny_athan

Gfx by
@mikias_56

ግጥም በኢትዮጵያ

11 Oct, 05:24


ጭጋጉ ሲያከትም በክረምቱ ማብቂያ፤
ፀሐይ ስትፈነጥቅ በመሬት መድረቂያ፤
የፀደይ አበባ ማበብ ስትጀምር ፤
አደይዋ ለሰዎች ተስፋን ስታበስር፤
በወርሐ ጥቅምት በመጀመሪያው ቀን፤
ዛሬን ነዉ የወጣሁ ከእናቴ ማኅፀን።

ያቺ እናቴ በጭንቋ ቀን ምጧ ደርሶ፤
እያነባች ላብ አጥምቋት ፊቷ ርሶ፤
ማርያም ማርያም እያለች፤
ምጧ ቀለለላት ስሟን እየጠራች።

በልደቷ ቀን መታሰቢያ.........
ሰምታ ጸሎት ስዕለቷን፤
ማርያም ማረቻት እናቴን።
በዚያች ሴኮንድ በዚያች ቅፅበት........
ከልቤ ታትሞ ማርያም የሚለው ስም፤
ለዛሬ ደረስኩኝ በፍቅሯ ስሸለም።

የእቅፏን መዓዛ እየመገበችኝ፤
የትህትናን ዋጋ እያስተማረችኝ፤
የልጇን ጌትነት በልቤ ሰሌዳ፤
የእርሷን ትሁትነት በፍቅር አዋድዳ፤
የንስሐ እድሜን ፈጥና አሰጠችኝ፤
አዲስ ቀንን እንዳይ ድንግል ባረከችኝ።
🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎊🎊🎊🎊
ዔደን_ታደሰ @ediwub
ጥቅምት ፩/፳፻፲፯
መልካም ልደት ለእኔ🎂🎂🎊🎊🎊

ግጥም በኢትዮጵያ

09 Oct, 10:32


እኔ ያንቺ አለም
ደብዘዝ የምል ደማቅ ቀለም
የምተጋ ነገን ማልም
ለኔም ላንቺም የምሆን ህልም
ተዛምደናል ኪዳን መተን
መሃላችን ለቃል ሰተን
ነበርሽ የኔ ብርቱ ወገን
ጥንካሬሽ አንድ ያረገን

ያሳዝናል ጊዜሽ እቱ
ተዛምደሻል ከማዕቱ
የሄድሽበት ከኔ ይርቃል
ረስተሻል መሃላ ቃል
የኔ ገላ ያልታደለ
አንቺን ልኮ ባዶ አደረ
ደህና አድሯል ወይ ያንቺ ገላ
ባሉን ትቶ የተዳራ
ሽሎሽ ነው ወይ ከኔ እሱን
ቃል ማሃላን ማፋረሱን
ያሳዝናል ጊዜሽ እቱ
ተዛምደሻል ከማዕቱ
አንድን ይዞ ሳይራቡ
ምን ይሉታል መደረቡ

ዮኒ
ኣታን @yonatoz

Share @yonny_athan
Share @yonny_athan

ግጥም በኢትዮጵያ

07 Oct, 12:34


ልቤን ይዤው ነበር ስነሳ ከሸገር
ታዲያ ምን ወሰደው
አባይን ስሻገር
ገብር ያለ ላንቺ ከፍቅር መቅደሱ
ምን ሊጠቅመው ጣና
የሰው ልብ ማፍሰሱ
የጣናዋ ቆንጆ ልቤ ላይ ከትማ
ውይ አልሞት አልድንም
ከሷ ሌላ አልሰማ
እንዳላጣሽ አንቺን
አልበል ሰማይ ሰማይ
ገባር ወንዙን ሆኔ ልቀላቀል ከአባይ


@yonny_athan
@yonny_athan

ግጥም በኢትዮጵያ

28 Sep, 16:49


የወራት ዘመኑ ቀኑ ተቆረጠ
የማህፀኗን እቅፍ በጊዜ አሳቦ
ሆዷን ረገጠ

በ 18 ምሽት
ለ 19 አጥቢያ ቀኑ ከረፈደ
ማርያም
ማርያም..... ሲባል ዮኒ ተወለደ
🎂🎂🎂🎂🎂🎂🎂🎂🎂
🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳
🥳Share @Yonny_Athan 🥳
🥳Share @Yonny_Athan 🥳
🥳Share @Yonny_Athan 🥳
🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳

12:35 PM

🎂@yonatoz🎂

ግጥም በኢትዮጵያ

28 Sep, 08:27


.ጎርደድ አለችበት
እጥፍጥፍ አለላት ታዘዛት ጎዳና፣
እንቅፋት ያበቅላል
እሷ ካልሳመችው በ'ግሮቿ ዳና፤

ቀጭ _ቋ ቀጭ _ቋ

ክፍት ጫማ አ'ርጋለች

ቀጭ_ቋ ቀጭ_ቋ



የጥፍሯን ጣቶች ምንም አልነካቸው፤
ቀጭ_ቋ ቀጭ_ቋ
እኔ ምን አውቅና ንፋስና አቧራን ምን እንዳለቻቸው!

በጉልቱ ስታልፍ ...(ለሁሉም እማማ ፈገግታ ለገሰች ) ___(ፍግግ)

ቀጭ_ቋ ቀጭ_ቋ

(ወገቧን ይዛ ቆም)

ሳቅ_ጥርሷን ፍልቅልቅልቅ
ዓይኖቿን ጭፍንፍን

"ሀይ .........ማስቲካ ይዘሃል?"

"ምን ማስቲካ ልስጥሽ"?

(አምስት ብር ሰጠችው_በፈገግታ ሸኛት_ ጀብሎ)

.
ቀጭ _ቋ ቀጭ_ቋ

ወረቀቱን ጣለች ከቆሻሻው ቅርጫት፤
ቀጭ_ቋ ቀጭ_ቋ
ዓይኔ ፈለገ፦የፕላስቲክ ውሃ መያዣ፣ ሶፍት፣ ወ.ዘ.ተረፈ..ጫት፤

(እና አዲስ ጥቅልል ያለች የመስቲካ ልጣጭ)

ቀጭ _ቋ ቀጭ_ቋ

ዋሌቴን ከፍቼ ፎቶዬ አጠገብ አኖርኩት
*ትሪደንት መስቲካ*... / ከኔ ይበልጥ ቆነጀ/::

..

ቀጭ_ ቋ


ቀ ጭ ....._ቋ

ልዝብ_ፍዝዝ_ትክዝ ...አለችና
ቀልቧን አስተዋለች እንደተረጋጋች፤
ቀጭ ...._ቋ
ቦርሳዋን ከፈተች ነጠላ ዘርጋች፤

ሽክርክር ወደ-ላይ ትከሻዋ ላይ ጣል
ነጠላዋን ል-ብስ፤
በጥለቱ ጫፎች የዓይን የከንፈሯን
ቀለማቶች እ_ብስ፤
.
ቀጭ_ ቋ

ቤተስክያን ግ-ብት
በግሮቿ ብርክክ

.
እልቅስ እስኪደክማት
እልቅስቅስ እንባዋን እርግፍግፍ፤
ለግዚሐሯ ን-ግር የሆነባትን ግፍ

@topazionnn
@topazionnn

ግጥም በኢትዮጵያ

22 Sep, 18:50


ስራ አይፈታም የእጄ መዳፍ
የትም የትም ይዳብሳል
ድንበር አጥሬን አለፍክ ብሎ
የትኛው እጅ...እጅ ይከሳል!
ካልጠሩኝ ቤት እገኛለሁ
ካልወለድኩት የሀሳብ ማጥ
ገጣሚ ነው ሌላው ስሜ
ፅሁፍ ብቻ ጎኔ ሲላጥ።
ሰዓሊ ነኝ የፊቷን መልክ
ማድያቷን የማጠፋ
በጢስ ጠቆር ያለ ጉንጯን
በእርሳሴ የምገፋ

እኔ እንዲህ ነኝ!


ዮኒ
ኣታን @yonatoz

Share @Yonny_Athan
share @Yonny_Athan

ግጥም በኢትዮጵያ

22 Sep, 15:36


@yonny_athan
@yonny_athan

ግጥም በኢትዮጵያ

21 Sep, 15:58


በቅንድቧ ባይኗ በኩል
አልተቀባም አንዳችም ኩል
አልደረበች ማዳመቂያ አልፈጠራት በጎደሎ
ያኖረልን በግሩምታ ንፁህ ልቧን አስመስሎ
የሰው ሰራሽ ቅርፀ ብዙ
አሎዞራትም በአካሏ
በክፋት የማትኖር
ትሁት መልሰ ቃሏ

ያቹት......እርሷ!


ዮኒ
ኣታን @yonatoz

Share @Yonny_Athan
Share @Yonny_Athan

ግጥም በኢትዮጵያ

20 Sep, 13:20


Share @Yonny_Athan
Share @Yonny_Athan

ግጥም በኢትዮጵያ

18 Sep, 06:04


የተቀነጨበ

ጨዋታ ከሳቅሽ
ከለዛ አንደበትሽ ተደማምሮ ሳለ
ከተፈጥሮሽ እንጂ ከልብሽ ምን አለ?
.
.
.
እንጃልን እኛማ
ላወጋልን ሁሉ
ለሳቀልን ሁሉ ሞትን ካልንማ።

ዮኒ
ኣታን @yonatoz

Share @Yonny_Athan
Share @Yonny_Athan

ግጥም በኢትዮጵያ

15 Sep, 06:35


ከትልቅ ይቅርታ ጋር

"ተፈላጊ" የተሰኘው ልብወለድ በ ዮኒ ኣታን ቻናል እስከ ቁጥር ሁለት ድረስ ሲተላለፍ የነበረ እንደሆነ ይታወቃል በመሆኑም ከጥቂት ሳምንታት በፊት ቁጥር ሶስትን ይዞ በ ዮኒ ኣታን፣ ግጥም በኢትዮጵያ እና የሀገሬ ወጎች ላይ መለቀቅ ጀምሮ የነበረው "ተፈላጊ" አሁን ላይ ባጋጠመን ትልቅ ችግር ማለትም የነበሩትን ፋይሎች በሌላ ሰው ስም ተቀናጅተው እየተለቀቁ ስለሆነ ላልተወሰነ ጊዜ ልብወለዱን ገታ አድርገን አየተወያየንባቸው እንገኛለን።

ስለዚህም ክቡራት ተከታታዮቻችን ከትልቅ ይቅርታ ጋር ላልተወሰነ ጊዜ አቁመነዋል።


የ ዮኒ_ኣታን ቻነል አድሚኖች

@Yonny_Athan
@Yonny_Athan

ግጥም በኢትዮጵያ

14 Sep, 19:11


@yonatoz



Share @Yonny_Athan
Share @Yonny_Athan