ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

@zerihungemechu


ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

23 Oct, 06:21


ይታያል...ከሳይክሉ ሁለት ሜትር ርቀት አንድ ሄሌሜት ያደረገ ባለመካከለኛ ቁመት ሰው እጥፍጥፍ ብሎ ወድቆ ይታያል....ሁሉም በቃል ሰይነጋገሩ እየሮጡ ሰውዬውን ከበቡት…
‹‹አባዬ…ይሄ ነገር በእኛ እንዳይሳበብ…ከመነካካታችን በፊት ለፖሊስ ደውለን እናሳውቅ፡፡››ወንዱ ልጅ ስጋቱን ለአባቱ ተናገረ፡፡
‹‹ልጄ ገና ለገና እንጠየቃለን ብለን በሰው ህይወት ላይ እንፈርዳለን….?አይ እንደዛ ማድረግ አልችልም›› በማለት…ሰውዬው ተጠጋና ቀስ ብሎ ሄልሜቱን ፈቶ አወለቀው….ረጅምና ዞማ ፀጉሯ ዝንፍል ብሎ መሬቱን ሞላው፡፡ፊቷ በደም ተሸፍኗል፡፡
‹‹በጌታ ሴት ነች››እናትዬው ተናገሩ፡፡
አባትዬው እጁን ወደ ልጅቷ አንገት ላከና በህይወት መኖሯን አለመኖሯን ለማረጋገጥ ሞከረ፡፡‹‹ተመስገን አለች፣ትተነፋሳለች….ቀስ ብለን ወደቤት እናስገባት…››
‹‹እንዴ አባዬ ለፖሊስ እንደውልና እነሱ ሀኪም ቤት ይውሰዷት››ወንዱ ልጅ ስጋቱን መለሶ አስተጋባ፡፡
‹‹አይ…አይሆንም ፡፡በዚህን ሰዓት እንደዚህ አይነት አለባበስ ለብሳ እንዲህ አይነት ሞተር የምትነዳ ሴት የሆነ ችግር ላይ እንደሆነች እርግጠኛ ነኝ፣…ምን ላይ እንዳለች ሳናውቅ ለፖሊስ በመደወል አሳልፈን አንሰጣትም…አይሆንም..ይልቅ ና ከታች ቀስ ብለህ ያዛት
…ወደቤት እናሳገባት….››አባትዬው ጠንከር ባለ ንግግር ውሳኔያቸውን አሳወቁ፡፡
ወጣቱ ሳይመስለው አባትዬው እንዳለው አደረገ ….ወስደው ጠባቧ ሳሎን ከተዘረጋው ልጆቹ ተኝተውበት ከነበረ ባለሜትር ከ20 ፍራሽ ላይ አስተኟት፡፡እናትዬው ቦርሳውን አንጠልጥላ በማስጋበት ወደ ጓዲያ ወስደው አስቀመጡት፡፡ ….ከላይ የለበሰችው ልብስ አወለቁላትና የቆሰለ ወይም የደማ ቦታ እንዳለ መፈለግ ጀመሩ ግንባሯ ላይ ከጀርባ በኩል የሚፈስ ደም አለ ግማሽ ፊቷ ቆዳዋ ተገሽልጦ በደም ተሸፍኗል፡፡ ሌላ ቦታ ሰላም ትመስላለች፣ቢያንስ ለጊዜ የሚታይ ቦታ የለም፡፡
‹‹ምን እናርግ..ፊቷ እኮ በጣም ተጎድቷል…ደሟም እየፈሰሰ ነው..የግድ ህክምና ማግኘት አለባት፡፡››

ሴቷ ልጅ ለመጀመሪያ ጊዜ ተናገረች‹‹እዚህ ከጀርባችን ያለው ኪሊኒክ ለምን አንወስዳትም?››
‹‹በሊሊት ይሰራሉ እንዴ?››
‹‹አዎ ተረኞች አሉ…፡፡››
ወደኪሊኒክ በመውሰዱ ሁሉም ተስማሙ…ወጣቱ ልጅ እና አባትዬው ተራ በተራ እያዘሉ ከቤታቸው ግማሽ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ወደሚገኘው ኪሊኒክ ወሰዷት…ሀኪሞቹ ቁስሏን አፅድተው ግንባሯ ላይ የለውን ስንጥቅ ሰፍተውና ግማሽ ፊቷን በፋሻ ሸፍነው ህክምናቸውን ጨረሱ…ለማንኛውም ሆስፒታል ወስደው ሙሉ ምርመራ እንድታደርግ እንዲያደርጉ አዛው… ሸኞቸው፡፡
እነሱ ግን ቀጥታ ወደቤት ነበር የመለሶት፡፡….እሷ ያ ሁሉ ሲሆን ከገባችበት ከፊል ሰመመን አልነቃችም ነበር፡፡….ከዛ አቶ ለሜቻ ከልጃቸው ከፊራኦል ጋር እየተረዳዱ በማዘል ወደበት ከመለሷት እና መልሰው ካስተኞት በኃላ በዛ ውድቅት ለሊት በሞተሩ የተጣሰውን የውጭ አጥር ወደነበረበት መለሱና ሞተሩን ተጋግዘው ወደውስጥ በማስገባት ጎዲያ ውስጥ አስገብት፡፡
ፊራኦል‹‹አባዬ ምን እያደረክ እንዳለ ምንም አልገባኝም?››ሲል አባትዬውን የጠየቀው
‹‹ልጄ እንደምታያት ልጅቷ ሴት ነች..ወጣት ሴት…..እንዴትም አድርጌ ባስበው በዚህ እድሜ ያለች ሴት ልጅ በሰላም ሆና በዚህ ውድቅት ለሊት ሞተር አትነዳም…ልጅቷ የሆነ ችግር ላይ ነች….››
‹‹እኮ እኔም እኮ ምለው እንደዛ ነው..ችግር ላይ ነች..እኛንም አብራ ችግር ውስጥ ትከተናለች እያልኩህ ነው፡፡››
‹‹ልጄ ስጋትህ ይገባኛል …ትክክልም ነህ፡፡እኔ ግን አባት ነኝ…እንደእሷ ልጆች አሉኝ..ነገ እንሱም የሆነ ችግር ውስጥ ሊገቡ እና እንዲህ የማያውቁት ቦታ በማያውቁት ሰው እጅ ሊወድቁ ይችላሉ ..ለልጆቼ ጡር አላቆይም…ይህቺ ልጅ ከገባችበት ሰመመን ነቅታና ከህመሟ አገግማ የሆነችውን ከነገረችን በኃላ ምን ማድረግ እንዳለብን እንወስናለን..እስከዛ ግን አይሆንም››
‹‹ከረፈደብንስ?›››

‹‹ከረፈደብን ስትል….?››
‹‹ምን አልባት ባትነቃስ?››
‹‹ተው ልጄ ..እንደዛ አይሆንም….አምላክማ እንዳዛ አሳልፎ አይሰጠኝም፣በል አሁን ተነስ ከብርድ ላይ እንግባ፡፡››
አካባቢው ትኩረት የሚስብ ነገር አለመኖሩን ካረጋገጡ በኃላ ከለሊቱ 10 አካባቢ ለመተኛት ወደውስጥ ተያይዘው ገቡ…እናትዬው እና ለሊሴ የለሌት እንግዳዋን በግራና በየቀኝ አጅበው በድንጋጤ እንዳፈጠጡ ቁጭ ብለዋል….፡፡
እናትዬው ወ.ሮ እልፍነሽ አንዴ ጓዳ ፤ሌላ ጊዜ ሳሎን ይመላለሳሉ…መልሰው ደግሞ ከጎኗ ቁጭ ይላሉ… በፍራቻና ግራ በመጋባት እህህ እያሉ ያጉረመርማሉ‹‹ይሄኔ እናቷ አላየቻት፣ወይ የሰው ልጅ፣አሁን እሺ ባትነቃስ?››ብቻቸውን ይለፈልፋሉ፡፡
ይቀጥላል
youtube-https://www.youtube.com/@ethio2023
ቴሌግራም -https://t.me/zerihunGemechu
TikTok-https://www.tiktok.com/@zerihungemechu67
ፌስቡክ- https://www.facebook.com/zerihun.gemechu.5

ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

23 Oct, 06:21


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-ሶስት
(ያለፈው ምዕራፍ ያመለጣችሁ ወደሚከተለው የቴልግራም ቻናል ጎራ በማለት ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ቴሌግራም -https://t.me/zerihunGemechu)
//
በፀሎት የልብ ንቅለ ተከላ ካደረገች በኃላ ልክ እንደዛሬው አይነት በህይወቷ ወሳኝ የሆኑ ትላልቅ ውሳኔዎችን አሳልፋለች….አንዳንዴ‹‹ በእውነት እንዲህ እያሰብኩና እያደረኩ ያለሁት እኔው ነኝ?››ብላ በራሷ እስክትደመም ድረስ ነበር ለውጦ፡፡

‹‹አሁን የሌላ ሰው ለዛውም የሞች ንፅህ ልብን በሰውነቴ ተሸክሜ ርካሽ የሆነ ስራ ፈፅሞ አልሰራም››የሚል አቋም ላይ ደርሳ በዛ መሰረት ነው የምትንቀሳቀሰው…ትንሽ ለስሜቷ የማይመችና የሚቆረቁር ነገር ሲያጋጥማት እንደድሮው ‹‹ቆይ እስኪ ልሞክረው›› ብላ ዘላ አትገባበትም….ጊዜ ወስዳና ተረጋግታ ታስብበታለች..ነገሩን ትመዝንና እሷንም ሆነ ሌላውን ሰው የሚያሳዝንና የሚያስከፋ መስሎ ከተሰማት ወዲያው መንገዷን ታስተካክላለች….ይሄ በብዙ ነገሮች ጠቅሟታል…ግን ደግሞ ቤተሰቦቾን በተመለከተ እንደበፊቱ ነገሮችን አይታ እንዳላየች እንድታልፍ አላደረጋትም…እያንዳንዱ በመሀከላቸው ያለው ጥላቻና ጥል በጣም ያስጨንቃትና እረፍት ይነሳት ጀመር…ለምን ብላ እንድትጠይቅ..ጥፋቱ የማንኛቸው ይሆን እያለች እንድትመረምርና ፣እንዴት ሊስማሙና ትክክለኛ ባልና ሚስት ሆነው ለእሷም መቼ እንደ ትክክለኛ ወላጅ የምትፈልገውን ፍቅር ሊለግሶት እንደሚችሉ ማለምና መተከዝ የጀመረችው ከበርካታ ወራቶች በፊት ነው፡፡
በፀሎት ጨረቃ በነገሰችበትና ከዋክብቷች ሰማዩ ላይ ተበትነው በሚንሸራሸሩበት በዛ ውድቅት ለሊት እቤቷን ጥላ ..ከእናትና አባቷ ርቃ …ከጋደርዶቾ አምልጣ መሄዷን እንጂ ወዴት እንደምትሄድ ለምን ያህል ሰዓት መንዳት እንዳለባትና የመንገዷ ማዳረሻ የት እንደሆነ ምንም የምታውቀው ነገር የለም፡፡ዝም ብላ ብቻ በዛ ውድቅት ለሊት የአስፓልቱን መሀከል ይዛ በመድሀንያለም ቤተክርስቲያንን አጠር ተኮ በሚገኘው መንገድ ወደፊት በመውጣት ዋናውን አስፓልት ገባችና ቀጥታ ወደ ስቴዲዬም ሚወስደውን መንገድ ያዘች….መስቀል አደባባዩን እንደጨረሰች ወደግራ ታጠፈችና ወደላንቻ የሚወስደውን የአስፓልት መንገድ ያዘች..
ከትራፊክ መጨናነቅ ነፃ የሆነውን መንገድ በፍጥነት መጋለብን ተያያዘችው…ምንም ሳታውቀው ለአንድ ሰዓት ያህል ከነዳች በኃላ አቃቂ ድልድይ ጋር ስትደርስ ወደቀኝ ተጠማዘዘችና ወደአቃቂ የሚወስደውን መንገድ ገባች ፣…መንዳቷን ቀጠለች…ድንገት ተረጋጋችና ሞተሩን አቀዝቅዛ አቆመችና አካባቢውን ስታስተውል የምታውቀው ሰፈር ሆኖ በማግኘቷ ደነገጠችም.. ተገረመችም….እዚህ ሰፈርና እዚህ ቦታ ለመምጣት ባለፈው ሁለት አመት ስትመኝ ነበር….ቢያንስ በሳምንት አንድ ቀን በህልሟ እዚህ አካባቢ መጥታ ስትዳክር ነው የምታየው..ግን መጥታ የምትፈልገውን ነገር ለማድረግ አባቷ ሊፈቅድላት አልቻለም..ለጠባቂዎችም በጥብቅ ስለተነገራቸው እንኳን አሁን ያለችበት ሰፈር ይቅርና ክፍለከተማው ውስጥም ዝር እንድትል እንዳይፈቅዱላትም ፤ከዚህ ቀደም ምንአልባትም ከአመት በፊት ሰፈሩንና እቤቱን ለአንድ ጊዜ በስንት ጭቅጭቅ ያሳያት እራሱ አባቷ ነበር፡፡

በጊዜው መኪናዋን አሁን ሞተሯን ያቆመችበትን ቦታ አቁሞ…የቤቱን በራፍ በጥቁሩ የመኪና መስታወት ወደውጭ እየጠቆመ…‹‹አየሽ የልጅቷ ቤተሰቦች የሚኖሩት እዚህ ነው..እኛ አሁን የሚገቡት አባቷ ናቸው…አብሯቸው ያለው ደግሞ ልጃቸው ነው….እናትና እህቷም አሉ››እያለ ነበር ያብራራላት፡፡
‹‹አባዬ እንዲት እንዲህ ጭንቁርቁስ ያለ ቤት እንዲኖሩ ትፈቅዳለህ..?እየው እስኪ አጥሩን..እቤታቸውን ተመልከተው››በምሬት አባቷን መጠየቋን ታስታውሳለች፡፡
‹‹ልጄ ምን ላድርግ ?በግድ በወታደር አስገድጄ ሌላ ቤት ውስጥ እንዲገቡ ማድረግ አልችል››
‹‹ማለት…?››
‹‹ነግሬሻለሁ እኮ …ቤተሰቡ ከእኛ አምስት ሳንቲምእንደማይቀበሉ ምለው ነው የነገሩን››
‹‹አባዬ ይሄ ምንም ሊገባኝ አልቻለም…የተሸከምኩት እኮ የልጃቸውን ልብ ነው….በልጃቸው ሞት እኮ ነው አሁን እኔ በህይወት መኖር የቻልኩት…አልገባህም አባዬ …ለምን እሷ ሞታ እኔ ኖርኩ..?እግዚያብሄር ይሄን እንዴት ፈቀደ…?.አባዬ በየቀኑ የጥፋተኝነት ስሜት እየተሰማኝ ነው…እየተሰቃየሁልህ ነው…››
‹‹አውቃለው ልጄ…እነሱ ፍቃደኛ ቢሆኑ እኔ የሀብቴን ግማሽ እንኳን ብሰጣቸውና
..ላደረጉልኝ ነገር ምስጋና ባቀርብ ደስ ይለኝ ነበር…ግን ተቀባይ ከሌላ መስጠት ስለፈለግሽ ብቻ አይሳካልሽም፡፡››
‹‹ቢሆንም አባ ..እኔ ልቧን ሰጥታኝ ህይወቴን እንዲራዘም ያደረገቺኝን ልጅ ቤተሰቦች እንዲህ በጉስቁልና እንዲኖሩ አልፈልግም…..ልጃቸው በህይወት ኖራ ቢሆን ትጦራቸው ነበር…የሆነ የሆነ ነገር ታደርግላቸው ነበር….ብቻ አላውቅም የሆነ ዘዴ ፍጠርና እርዳቸው፡፡››
‹‹አይ ልጄ አልገባሽም እንዴ…ልጃቸው ላንቺ ልብ ከመስጠቷ ከአመታት በፊት በእኛ ፋብሪካ የሚሰራውን ወንድ ልጃቸውን እራሱ ስራ እንዲለቅ አድርገውታል…..ለማንኛውም የተቻለኝን እሞክራለው..አሁን ይሄን ያህል ካየሻቸው ይበቃሻል… አንሂዱ ››ብሎ ነበር ከአካባቢው ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ የለቀቁት፡፡

ከዛ ወዲህ ግን ፍፅም ወደአካባቢው እንድትጠጋና ከቤተሰቡ ጋርም በምንም አይነት መንገድ ተገኛኝታ እንዳትተዋወቅ ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ተሳክቶላቸዋል…አሁን ግን ይሄው በደመ ነፍሷ ከቤቱ ፊት ለፊት አስፓልቱ ጠርዝ ላይ ሞተሯን አቁማ ቁልቁል አዘቅዝቃ እያየችው ነው፡፡
‹‹ወደእዚህ መምጣት በአእምሮዬ ስሌት ውስጥ አልነበረም….ሳስበው ግን የልጃችሁ ልብ ነው እየመራ እዚህ ድረስ ያመጣኝ››ስትል አጉረመረመች፡፡ድንገት ስሜታዊ ሆነችና ነዳጁን ረገጠችና ጨምቃ የያዘዘችውን ፍሬን ለቀቀች…አስፓልቱ ን ለቃ ቀጥታ ወደቤቱ አቅጣጫ መንዳት ጀመረች …የሞተሩ ፍሬን ድንገት እምቢ አላት… ያ ደግሞ ጠቅላላ ሰውነቷ በፍራቻ እንዲቀዘቅዝ ነው ያደረጋት…ሞተሩ ከቁጥጥሯ ውጭ እየወጣ ነው.. መንገድን ሰታ ወደቀኝ እየተጓዘች ነው…›የተውሸለሸለ የእንጨት አጥር ቤት ጥሳ ገባች…. የቆርቆሮ በር ካለው ሰርቢስ ቤት በራፍ ጋር ተላትማ በአየር ላይ ተንሳፈፈችና መሬት ላይ ጧ…ጧጧ ብላ ወደቀች....ሞተሩ አጥሩን ጥሶ ሲገባና ከቆርቆሮ በራፉ ሲጋጭ የፈጠረው ድምፅ የፍንዳታ አይነት ነው….እሷ ወዲያው ነው ጭልም እያለባት የሄደው…እንዲህ ባለ ሁኔታ እራሷን አደጋ ላይ የመጣል እቅድ አልነበራትም…….ከቤት ውስጥ ግን ቡዙ ጫጫታና ትርምስ ተሰማ…
‹‹አማዬ ምንድነው……?››
‹‹.ልጆቼን ..››
‹‹ልጆቼን ››
‹‹አባዬ ሰላም ነህ?››
የሶስት ወይም የአምስት ሰዎች ድምጽ እየተሰማት ነው….እያንዳንዱ ድምፃ ልቧ ላይ እየተንጠባጠ እያቀለጣት ያለ ነው የመሰላት፡፡‹‹ምን ሆኜ ነው …?ምን ተፈጠረ…?ይሄን እያሰበች ሳለ ጭልም እያለባት ሄደ ፣እንደምንም ላለመጥፋት ብትሞክርም አልቻለችም
…እራሷን ሙሉ በሙሉ ሳተች….፡፡እቤቱ ውስጥ ያለ አንድ ጎረምሳ እና አንድ ወጣት ሴት… እናት አባት በዛ ውድቅት ለሊት ፈጣሪ ምን አይነት መብረቅ እንደላከባቸው ለማወቅ በሀይለኛ ድንጋጤ እንደተመቱ የተተራማመሱ የቤታቸውን በራፍ እንደምንም ተራ በተራ እየተጋፉ ወደውጭ ወጡ….የውጭ መብራት አብርተው ሲመለከቱ ..ከበራፉ በሶስት ሜትር ርቀት መሬት ላይ የተዘረጋ ጥቁር እና ነጭ ቀለም የተቀባ ዘመናዊ ሞተር ሳይክል

ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

22 Oct, 08:14


የልደት ዝግጅቱ ከምሽቱ 2 ሰዓት ላይ የጀመረ ሲሆን እሰከአራት ሰዓት ያለው ዝግጅት ለሁሉም የሚሆን ሰከን ያለ ሙዚቃ ያለበት የምግብና የመጠት መስተንግዶ ጨምሮ… የተረጋጋ የእርስ በርስ ጫወታ… የኬክ ቆረሳና.. የሻማ ማጥፋት ስርአት …የስጦታ ዝግጅት የተደረገበትና የተለመደ አይነት ነበር…ከአራት ሰዓት በኃላ ግን ጠና ጠና ያሉት ሰዎች አባትና እናቷንም ጨምሮ ግዙፍንና የተንጣለለውን ሳሎን ለወጣቶቹ ለቀው በመሰናበት ሄዱ፡፡የዝግጅቱ አጠቃላይ ሁኔታ ተቀየረ..ሙዚቃዎቹ የፈጠኑና የሚያስጨፍሩ ሆኑ፤ መጠጡ የጠነከረና አስካሪ እየሆነ ሄደ….ይሄም ሆኖ ግን በፀሎትን የሚጠብቁ ሁለት ጋርዶች የሳሎንን የግራና ቀኝ በራፍ ይዘው በተጠንቀቅ እንደቆሙ ነው፡፡እሷም በአይነ ቁራኛ እያየቻቸው ነው…በየሆነ ደቂቃ ልዩነት መጠጥ እንዲወስዱላቸው ለአስተናጋጆቹ መልዕክት ማስተላፏን ፈፅሞ አትረሳም…..መጀመሪያ ስራ ላይ ስለሆኑ መጠጥ እንደማይጠጡ በመናገር መልሰው ነበር..በኃላ ግን እራሷ ሄዳ ‹‹በልደቴ ቀንማ ቢያንስ አንድ ጠርሙስ መጠጣት አለባችሁ ››ብላ እንዲቀበል አስገደደቻቸውና ተቀበሏት…በአንድ ብቻ ግን አላቆሙም፤ አራትና አምስት መደጋገም ቻሉ..፡፡ሰዓቱ እኩለ ለሊት አልፎ ሰባት ሰዓት አካባቢ ሲሆን ሰክሮ ሚለፋደደው በዛ….በፀሎት ግን ከመጀመሪያም ጀምሮ እየጠጣች አልነበረም ….ዛሬ የምትጠጣበት ቀን እንዳልሆነ ከመጀመሪያውኑ ነው የወሰነችው…እንደምንም ጋርዶቹን በጥንቃቄ እያየች…እየተሹለከለከች የፎቁን ደረጃ ተያያዘችውና ወደላይ ወደመኝታ ቤቷ አመራች…ከፍታ ገባች እና መልሳ ከውስጥ ቆለፈችው፡፡

የለበሰችውን ቀሚስ በፍጥነት አወለቀችና ቅድም አዘጋጅታ የነበረውን ጅንስ ሱሪ ለበሰች…፡፡ወርቃማ አርቴፊሻል ፀጉሯን አወለቀችና ጥቁር ሆኖ ከኃላ ረጅም ከፊት አጭር ሆኖ ከፊል ግንባሯን ሚሸፍን ሌላ ፀጉር አጠለቀችና ከላይ ኮፍያ ያለው ጥቁር ጃኬት ደረበችበት፡፡ አይኗ ላይ ጥቁር መነፅር ሰካችና መስኮቱን ከፈተች…፡፡
…መለስተኛ የቆዳ ሻንጣዋን ከአልጋዋ ላይ አነሳችና በጀርባዋ አንጠለጠለችው… አዎ በጀርባ የሚገኘውን የአደጋ ጊዜ መውጫ ተጠቅማ ወደ ምድር መውረድ ጀመረች፡፡ይሄንን መወጣጫ ልጅ እያለች ጀምሮ በጣም ትፈራዋለች፡፡ መጀመሪያ ቀኝ እግሯን አስቀደመች
…….ሰውነቷ ተንቀጠቀጠባት..የሆነ ስህተት ፈጥራ እግሯ አዳልጦት ከመወጣጫው ላይ ተንሸራታ ብትፈጠፈጥ ሁሉ ነገር እንደሚያበቃለትና የአሰበችውን አንዱንም ሳታሳካ እግረ ሰባራና አካለ ጎዶሎ ሆና ለሌላ ስቃይ እደምትዳረግ አሰበችና ዝግንን አላት…በአእምሮዋ የተፈጠረው ክፉ ሀሳብ እዳይፈጠር እየጸለየች..በጥንቃቄ ወደታች መውረዷን ተያያዘችው…ምንም እንኳን ያን የአደጋ ጊዜ ጠባብ መወጣጫ ተጠቅሞ ወደታች መውረድ ሊወስድ ከሚገባው የጊዜ ስሌት በላይ የወሰደባት ቢሆንም ግን ደግሞ ምንም ክፉ ነገር ሳይከሰትባት ሻንጣዋን እንዳዘለች መውረድ ቻለች…ከዛ በግቢው ውስጥ ባሉ የጽድ ዛፎች እየተከለለች፣ከጀርባ ወደሚገኘው ገራዥ አመራች..የአባቷ ታናሽ ወንድም አልፎ አልፎ የሚጠቀምባት ሞተር ሳይክል ወደ ቆመበት ስፍራ አመራችና ቀድማ ሄልሜቱን አንስታ ጭንቅላቷ ላይ ከሰካች በኃላ መተሩን አስነስታ ቀጥታ ወደመውጫው በራፍ አስፈነጠረች፡፡…ወጪ ገቢ ስላለ የውጪ በራፍ አንደኛው ተካፋች ወለል ብሎ እንደተከፈተ ነው፡፡
ዘበኛው ሞተሩን ቢያውቃትም ማን እየነዳት እንደሆነ መለየት አቅቶት ላስቁም ወይስ ልፍቀድ…? በሚል ግራ መጋባት ውስጥ ሳለ ምንም እንዲል እድል ሳትሰጠው አስፈንጥራ የግቢውን ድንበር ጥሳ ዋናው አስፓልት ላይ ወጣች፡፡ ዘበኛው የፈለገ ቢገምት የቤቱ ቅምጥል ልጅ ትሆናለች ብሎ ሊገምት እንደማይችል እርግጠኛ ነች…ዘበኛው ሞተርም እንደምትነዳ እንኳን አያውቅም…
ይቀጥላል
youtube-https://www.youtube.com/@ethio2023
ቴሌግራም -https://t.me/zerihunGemechu
TikTok-https://www.tiktok.com/@zerihungemechu67
ፌስቡክ- https://www.facebook.com/zerihun.gemechu.5

ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

22 Oct, 08:14


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-ሁለት
(ያለፈው ምዕራፍ ያመለጣችሁ ወደሚከተለው የቴልግራም ቻናል ጎራ በማለት ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ቴሌግራም -https://t.me/zerihunGemechu)
//
በፀሎት በእንባዋ እና ሜካፕ ቅልቅል የተበላሸውን ፊቷን በሳሙና ታጠበችና አፀዳችው….መልሶ ሜካፕ መጠቀም ሳያስፈልጋት ቀጥታ ወደሳሎን ሄደች፡፡ከላይ ከአንደኛ ፎቅ እስቴሩን ተጠቅማ ወደታች ስትወርድ በመጀመሪያ አይኗ የገቡት እናትና አባቷ ነበሩ… ጎን ለጎን ተጣብቀውና እጅ ለእጅ ተቆላልፈው…በየመቀመጫው እየተዞዞሩ እንግዶቹን ያዋራሉ፡፡‹‹እንኳን ሰላም መጣችሁ›› እያሉ የውሸት የተጠና ሳቅ ይስቃሉ፡፡ከአስር ደቂቃ በፊት እንደዛ በፀያፍ ቃላት ሲጠዛጠዙ ላያቸው ሰው አሁን በእንደዚህ አይነት ቅርበት መጣበቅ ይችላል ብሎ ማንም ሊያስብ አይችልም፡፡
‹‹ሰላም ተስፋዬ እና ሰላሞን ቦጋለ እንኳን የእናንተን ገፀ ባህሪ ቢሰጣቸው በዚህ ልክ አስመስለው መጫወት መቻላቸውን በጣም እጠራጠራለሁ፡፡››እያለች ወደታች ወርዳ መድረኩ ላይ ወደተዘጋጀላት የክብር ቦታ ሄዳ ተቀመጠች፡፡ወዲያው እሷን ብለው የመጡ የሰፈርና የዩኒቨርሲቲ ጓደኞቾ ዙሪያዋን ከበቧት..እሷም ወላጆቾን እንደአርአያ ወስዳ የውስጧን ብስጭትና ንዴት በሆዷ ቀብራ አንድ ልደቷ እየተከበራላት እንዳለ ደስተኛ ቀበጥ የሞጃ ልጅ በፈንጠዝያና በፌሽታ ልደቷን ማክበሩ ላይ ትኩረቷን አደረገች….፡፡
ከመቀመጫዋ ተነሳችና ከእናቷ ጋር ደነሰች…ከዛ ከአባቷም ጋር ደነሰች…እናም በሁለቱ መሀከል ሆና ለሶስት ሆነው እንዲደነስ አደረገች….ይሄ እንቅስቃሴያቸው እያንዳንዱ ዳንሳቸውና የእርስ በርስ መተቃቀፋቸው በፕሮፌሽናል ቪዲዬ ማን እየተቀረፀና ፎቶም እየተነሳ መሆኑን ታውቃለች….ለዛም ነው እንደዛ እያደረገች ያለችው‹‹ልጄ እስከዛሬ ከነበረው ልደትሽ ሁሉ ይሄ ልዩ ነው…ይሄው ሀያ አንድ አመት ሙሉ ያንቺን ልደት ሳከብር አንድ ቀን አብሬሽ እንድደንስ ጋብዘሺን አታውቂም ነበር….ዛሬ ግን…››ለሶስት ሆነው እጅ ለእጅ ተያይዘው በመደነስ ላይ ሳሉ ነበር አባቷ ስሜታዊ ሆኖ የተናገረው፡፡
እናትዬውም ወዲያው ነበር የራሷን ሀሳብ ያስቀመጠችው‹‹አባትሽ እውነቱን ነው….እኔም ብሆን ከልጄ ጋር የመደነሱን እድል ሳገኝ ይሄ የመጀመሪያ ቀኔ ነው…በጣም ደስ ብሎኛል፡፡››
‹‹እርስ በርሳችሁስ?››ስትል ሁለቱንም ያስደነገጠ ጥያቄ ጠየቀቻችው፡፡
‹‹ማለ…ት?››እናትዬው በተለጠጠ ንግግር ጠየቀቻት፡፡
‹‹አንቺና አባዬ እንዲህ እጅ ለእጅ ተያይዛችሁ ከደነሳችሁ ምን ያህል አመት ሆናችሁ?››ጥያቄውን አፍታታ ደገመችው፡፡

‹‹እኔ እንጃ ልጄ እኔ አላስታውሰውም…..ምን አልባት አንቺ ከመወለድሽ በፊት ይመስለኛል››አባትዬው መለሰ፡፡
‹‹አያችሁ..ልጅ ወላጆቹ የሚያወሩትን ሳይሆን የሚያደርጉትን ነው ኮርጆ ደግሞ የሚያደርገው..እናንተ በዚህ መልክ ስትደንሱ አይቼ ስለማላውቅ ነው እኔም ላደርገው ያልቻልኩት…ፍቅርን በተመለከተ ጥሩ አርአያዎቼ አልነበራችሁም ማለት ነው..አዎ እውነቱ እንደዛ መሰለኝ፡፡››
‹‹አይ ያ እውነት አይደለም፡፡ልጄ እኛ በጣም እኮ ነው የምንወድሽ፡፡››
‹‹እሱ አይደለም ጥያቄው..እናንተስ እርስ በርስ እንዴት ናችሁ…..?ከመሀከላችሁ ማንኛችሁ ናችሁ የታመማችሁት….?ምናችሁን ነው የሚያማችሁ….?እንዴት ነው ይሄን ሁሉ አመታት እርስ በርስ መጠላላት የማይደክማችሁ…..?እንዴት አንዳችሁ እንኳን አትሸነፉም….?ለማንኛውም እኔ ማውራቱ ደከመኝ …ይብቃን…..ከአሁን ወዲህ ልደት ብዬ ስለማልደግስ የዛሬው የመጨረሻችን ነው፡፡››
‹‹የመጨረሻ ማለት?››አሁንም ልጃቸሁን እንደአምስት አመት ህጻን የሚያዩት አባቷ ኮስተር ብለው ጠየቁ፡፡
‹‹አባዬ አትኮሳተር ፡፡አሁን ሀያ አንድ አመት ሞላኝ…እራሴን ችዬ ከቤት መውጪያ ጊዜዬ ከመድረሱም በላይ እያለፈብኝ ነው…በእናነተ ላይ መንጠልጠልና መደገፍ ይበቃኛል…ከነገ ጀምሮ ጋርዶችህ እንዲከተሉኝ አልፈልግም….በሹፌርም አልንቀሳቀስም…..በአጠቃላይ እንደምርኮኛ ወፍ ለዘመናት ካስቀመጥከኝ ጎጆ በሩን ሰብሬ ወጣላሁ ..ክንፌን በሰፊው ዘርግቼ በሰፊው ሰማይ ላይ ባሻኝ አቅጣጫ በራለሁ..አንተም ልታስቆመኝ ያለህ ኃይል በሙሉ በቂ አይሆንም፡፡››
ይሄ ንግግር በሁለቱም ወላጆች ላይ መብረቃዊ ድንጋጤ ነው ያስከተለው‹‹ልጄ እንዲህ አይነት ቀልድ ከመቼ ወዲህ ነው መቃላለድ የጀመርነው..?ይሄ እቤት ዘመንሽን ሁሉ የምትኖሪበት ያንቺ የእድሜ ልክ ቤተመንግስት ነው…እዚሁ አግብተሸ እዚሁ ወልደሽ እዚሁ ነው የምታረጂው..ይሄን ምን ጊዜም ከአእምሮሽ እንዳታወጪው፡፡››
‹‹አባዬ… እናንተም መቼም ቢሆን ይህቺን ቀን ከአእምሮችሁ አታውጧት….››

‹‹እሺ ልጄ አሁን ለእንዲህ አይነት ጭቅጭቅ ጊዜው አይደለም… በድጋሚ መልካም ልደት..››
‹‹አመሰግናለው ..››ብላ ሁለቱንም በየተራ ጉንጫቸውን ሳመችና ልርገፍ እያለ የሚታናነቃትን እንባዋን እንደምንም ከትራ ወደመቀመጫዋ ተመሰችና ከጓደኞቾ ጋር ተቀላቀለች፡፡፡

ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

21 Oct, 06:34


‹‹እኔ እኮ ነኝ ..ምን ያህል ጨካኝና ነፍሰ ገዳይ እንደሆንክ በደንብ አውቃለሁ….እርግጥ ቀጥታ ቃታ ስበህ ሰውን አትገድልም…ውሾችህ ግን የጠላሀውን ሰው ሁሉ ሄደው ቦጫጭቀው እንዲገድሉት በአንድ ቃል ታዛቸዋለህ..እነሱም በየጊዜው ለምትጥልላቸው አጥንት ሲሉ አድርጉ ያልካቸውን ያለማቅማማት ይደርጉታል…››
‹‹እሺ አሁን ቢበቃሽ አይሻልም..?ሳሎን ሙሉ እንግዶችን ሞልተን እኔና አንቺ እዚህ በማይረባ ነገር አንጨቃጨቅ..ግድ የለም..ስድብና ዘለፋሽን ነገ ካቆምሺበት ትቀጥይዋለሽ…የት እሄድብሻለው?››
‹‹አሹፍብኝ…..አንድ ቀን ትክክለኛው ቀን መጥቶ እኔም በተራዬ አሾፍብህ ይሆናል!››
በፀሎት ከዚህ በላይ የወላጆቾን ጆሮ የሚበጥስ ሰቅጣጭ ጭቅጭቅ ማዳመጥ አልፈለገችም…እንባዋን እያንጠባጠበች በሩጫ ወደክፍሏ ተመለሰች፡፡
‹‹በቃኝ…..ለእነዚህ ሰዎች እኔ አልገባቸውም….በቃኝ…..››ቀኝ እጆን አነሳችና ልቧ ላይ አስቀመጠች…የሆነ ሸክም ነገር ልቧ ላይ እንደተጫነባት እየተሰማት ነው፡፡‹‹አልችልም…በእናንተ ምክንያት ባደራ የተቀበልኩትን የሰው ልብ ማበላሸት አልፈልግም…..››ከቁም ሳጥኗ በላይ የተሰቀለውን ሻንጣ ወንበር ላይ ቆማ አወረደች..ኮመዲኖዋን ከፈተችና በተለያየ ጊዜ ለተለያዩ ወጪዎች ከወላጆቾ የሚሰጣትን ስፍር ቁጥር ከሌለው ገንዘብ ውስጥ እየተረፋት እንደቀልድ ወርወር እያደረገች ያከማቸችውን ብር እየዛቀች ሙሉ በሙሉ ወደሻንጣው ከተተች…ከዛ ሁለት ሱሪ ፤ ሁለት ቲሸርት የተወሰኑ ፓንቶችን ጨመረችና ፣ዚፑን ዘጋች..፡፡ከዛ ሌላ ጅንስ ሱሪ ቲሸርትና ባለኮፍያ ጠቆር ያለ ጃኬት መረጠችና አልጋው ላይ ዝግጁ አድርጋ በማስቀመጥ ወደ መታጠቢያ ቤት ገባች…፡፡
ነገ ይቀጥላል……

ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

21 Oct, 06:34


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-አንድ
22 አመቷ ነው፡፡እንዲሁ ከውጭ ለሚመለከታት ሰው ሁሉ የተሟላላት እንከን አልባ ውበት ይዛ እንከን አልባ ኑሮ እየኖረች በእንከን አልባ ደስታ የምትሰቃይ ቅምጥልጥል እድለኛ ነው የምትመስለው፡፡ ግን ቀርቦ ህይወቷን በጥልቀት ላጠና እህ ብሎ የውስጧን ላደማጠ ምን ያህል የማይደረስበት ሽንቁር በህይወቷ እንዳለ በቀላሉ ይረዳል…ግን ያንን እሷን የመቅረብን እድል የሚያገኝ ሰው ጥቂት ነው ..ወይም ጭሩሱኑ የለም……እንዴት ተደርጎ..፡፡
አባቷ በሀገሪቱ ከሚገኙ ጥቂት ቢሊዬነሮች አንድ ናቸው፡፡ቢሊዬን ብር ያላቸው ሰውዬ የወለድት አንድ ልጅ ብቻ ነው…አንድ ብቸኛ ሴት ልጅ፡፡በዛ የተነሳ የበዛ እንክብካቤ፤ ለከቱን ያለፈ ክትትልና ቁጥጥር እየተደረገባት ያለች ልጅ ነች፡፡እርግጥ ቁጥጥሩ ከጊዜ በኃላ የመጣ ነው፡፡እስከ15 ዓመቷ ድረስ በነፃነት ነፃ ሆና ያደገች ልጅ ነበረች…ከ15 ዓመቷ በኃላ ግን ከጤንነቷ ጋር በተያያዘ ነገሮች የተለየ መልክ ያዙ….፡፡
በፀሎት የልብ ህመምተኛ መሆኗ የታወቀው ከ15 ዓመቷ በኃላ ነበር ፡፡ አ17 ዓመት ከሞላት በኃላ ግን ነገሮቸ ፈር ለቀቁና ህመሟ ከፍተኛ ደረጃ ደረሰ…በየሄደችበት ቦታ የተለየ ነገር ገጥሟት ትንሽ ስትጨናነቅ መውደቅና እራሷን መሳት ስትጀምር…24 ሰዓት በክትትል ስር እንድትሆንና ጠባቂዎች ከአጠገቧ እንዳይለዩና በመንገዷ ሆነ በማንኛውም እንቅስቃሴዋ ምንም አይነት እንከን እንዳያጋጥማትና ካጋጠማትም በፍጥነት አፋፍሰው ሆስፒታል እንዲወስዷት የታቀደ የጥንቃቄ እርምጃ በአባቷ ተወሰደ ..በዚህ ውሳኔ መሰረት ሳትወድ በግዷ ነፃነቷም ተነጠቀ፡፡
በፀሎት በአስተዳደጓ ምክንያት ገና የታዳጊነት ህይወቷን ሳታገባድድ ነው ህይወት ስልችት ያለቻት፡፡ አቶ ኃይለ መለኮት ስጦታው ሀብታቸውን ተከትሎ ባለዝና እና ታዋቂ ከመሆናቸውም በላይ የተናገሩት የሚደመጥላቸው፤ ያዘዙት የሚፈፀምላቸው ተፈሪ ሰው ናቸው፡ወይዘሮ ስንዱ መሸሻ የአቶ ኃይለ መለኮት የትዳር አጋር ናቸው..አብረው በጋብቻ 28

ዓመት አሳልፈዋል፡፡ከዚህ ውስጥ በዚህ ትዳር ውስጥ ፍቅር አብሯቸው የነበረው ለስምንት ዓመት ያህል ብቻ ነበር፡፡ከዛ በኃላ አንድ ቤት በጋራ ተጋርተው ከሚኖሩ ዳባሎች የተለየ ትርጉም ያለው ትዳር አልነበረም..አንደውም እርስ በርስ በእየእለቱ እያደገ የሚሄድ ጥላቻ…አንዱ ሌለኛውን ለማበሳጨትና ደስታ ለመንጠቅ የሚደረግ ተንኳልና አሻጥር እናም ደግሞ ከዛም አልፎ አንዱ ሌለኛውን ለማስወገድ እስከመመኘት የሚደረስ የበቀል ስሜት …..በቃ በጋብቻቸው ውስጥ ያለው ነገር ይሄ ነው፡፡አዎ ሁለቱም ወላጆቾ በመረረ የእርስ በርስ ጥላቻ ነፍሳቸው የበከተ..አንደኛው የሌለኛውን ጉዳት ብቻ ሳይሆን ሞትም ጭምር አምርሮ የሚመኝ.. አንድ ህንፃ ውስጥ በሚገኝ ሁለት ክፍል ውስጥ ተነጣጥለው የሚተኙ….የጋራ ጣሪያና የጋራ ሳሎን ስለሚጠቀሙ የሚቀፋቸው…..የሁለት አለም ሰዎች ናቸው..ወላጆቾ፡፡ግን ይህ ሁሉ ሆኖ ሁለቱም በእኩል ደረጃ ከልባቸው የሚያፈቅሩት አንድ ነገር አለ..ልጃቸውን፡፡ብቸኛ ልጃቸው በፀሎት…፡፡ ከተጋቡ ከስድስት አመት በኃላ በስንት ስለትና የህክምና እርዳታ ነው የወለዷት..ስሟንም በፀሎት ያሏት በፀሎት አገኘንሽ ለማለት ፈልገው ነው፡፡ከእሷ በፊትም ሆነ ከእሷ በኃላ ሁለቱም ሌላ ልጅ አልወለዱም….ሳይፈልጉ ቀርቶ አይደለም…እንዴትስ ላይፈልጉ ይችላሉ?፡፡ የዚህን ሁሉ ሀብት ወራሽ ሚሆን ስድስት ሰባት ልጆች ቢኖራቸው ምን አልባት በመሀከላቸው ያለው መራራቅና ጥላቻ የዚህን ያህል ሊንቦረቀቅ አይችልም ነበር ብላው ብዛዎች ያወራሉ….…ያም ሆነ ይህ አሁን በዚህ ወቅት ከ28 ዓመት የጋብቻ ቀይታ በኃላ ሆድ ከጀርባ በሆነ ግንኙነት የ22 ዓመት ልጃቸው የልደት በዓል በጋራ በአማረ እና በሸበረቀ ሁኔታ ለመክበር ሽርጉድ እያሉ ነው፡፡
አዎ በፀሎት ዛሬ የልደቷ ቀኗ ነው ፡፡ የ22 ዓመት የልደት በዓሏ፡፡በዚህም ምክንያት ቦሌ ከመድኃንያለም ቤተክርስቴያን ጀርባ ሁለተኛ መንገድ ላይ በሚገኘው ቤታቸው ድል ያለ የልደት ዝግጅት አዘጋጅተው ከ100 በላይ ሰዎች ተጠርተዋል፡፡እርግጥ ይሄን የልደት ዝግጅት ቀደም ብላ አልፈለገችውም ነበር፡፡አቧቷ ነው ችክ ብሎ ካልተደገሰ ያለው፡፡በኃላ እሷም በዝግጅቱ ደስተኛ ሆነች፡፡በዝግጅቱ ላይ ከታደሙት መካከል ግማሽ ያህሉ የእሷ የዩኒቨርሲት ጎደኞቾ እና መሰል እኩዬቾ ናቸው፡፡ቀሪዎቹ ደግሞ የሁለት ተፃራሪ ፓርቲ የጋራ ስብሰባ ላይ የታደሙ የሚመስለው የእናቷ እና የአባቷ የቅርብ ሰዎችና የስራ ባለደረቦች ናቸው፡፡
የድግሱን መስተንግዶ ሆነ የመጠጥና የምግብን ዝግጅት በሀላፊነት ወስዶ እያዘጋጀ ያለው በከማው አሉ ከተባሉት ሆቴሎች ውስጥ አንዱ ነው፡፡ዲጄ ከመቀጠሩም በላይ የራሱ ባንድ ያለው አንድ ታዋቂ ድምፃዊ በዝግጅቱ ላይ ተገኝቶ ዘፈኑን እንዲያቀርብ ተደርጎል፡፡ለአንድ

የ21 አመት ቀንበጥ ወጣት ልደት 3 ሚሊዬን ብር ወጪ ሆኗል ቢባል ማን ያምናል…?ግን የሆነው እንደዛ ነው፡፡
በጸሎት ለልደት በዓሏ በልዩ ትዕዛዝ በሀገሪቱ አለች በተባለች ዲዛይነር የተዘጋጀላትን ውብ ቀሚስ ለብሳ ብዙም ያልደመቀ የተወሰነ ሚካፕ ነካ ነካ አድርጋ የምትወደውን ከፈረንሳይ የተላከለላትን ሽቶ ነስነስ አድርጋ አጠር በለፀጉሯ ላይ 50 ሺ ብር የተገዛ ዘንፋላ ባለ ወርቃማ ቀለም የኢጣልያን ፀጉር ደርባበት በከፊል የተለወጠና የተቀየረ መልኳን ይዛ ከክፍሏ ወጣች..አንደኛ ፎቅ ላይ ካለ መኝታ ቤቷ ቀጥታ የልደት ዝግጅቱ ወደሚካሄድበት ምድር ቤት ወደሚገኘው ግዙፉ ሳሎን ከመሄዷ በፊት ወላጆቾ ወደታች መውረድ አለመውረዳቸውን ለማረጋገጥ ከእሷ መኝታ ቤት በተቃራኒው ኮርነር ጎን ለጎን ወደሚገኘው የወላጆቾ መኝታ ቤት አመራች፡፡መጀመሪያ የሚገኘው የእናቷ መኝታ ቤት ስለሆነ በቀስታ ቆረቆረች..ከውስጥ መልስ እየጠበቀች ሳለች ቀጥሎ ካለው የአባቷ መኝታ ቤት የእናቷን ድምፅ ሰማች…፡፡…ግራ ገባት››
‹‹ወይ..ዛሬ ሰላም ሰፍኗል ማለት ነው… እንደዛ ባይሆን እማዬ አባዬ መኝታ ቤት አትገባም ነበር››ብላ አሰበችና በደስታ ፈገግ ብላ ወላጆቾን ላለመረበሽ ፊቷን አዙራ ልትመለስ ስታስብ በጆሮዋ ሾልኮ የገባው ጠንከር ያለ የእናትዬው ንግግር ከእርምጃዋ ገታት፡፡
ቆም አለች ….ጥርት ብሎ እየተሰማት አይደለም..ፊቷን መለሰችና ወደአባቷ መኝታ ቤት ቀረበች..ጆሮዋን በራፉ ላይ ለጠፈች….ሰቅጣጭ ንግግር እየተመላለሱ ነው፡፡
‹‹እስኪ ከውሽሞችህ መካከል አንዷን እንኳን መርጠህ ብትጠራ ምን አለበት…? ሶስት ውሽሞችህን በአንድ ቤት፣እኔን እሺ ግድ የለም ለእነሱ ስሜት አትጨነቅም…ነው እርስ በርስ አይተዋወቁም..?››
‹‹አሁን ለምንድነው የምትነዘንዢኝ…….?ከፈለግሽ አንቺም ውሽሞችሽን መጥራት ትቺያለሽ››
‹‹በእውነት እንዴት ደግ ነህ እባክህ…..እንኳን ውሽማዬን ወንድ ጓደኞቼን መጥራት እንደማልችል አንተም እኔም እናውቀዋለን››
‹‹ለምን ?ምን ችግር አለው..?ድግሱ እንደሆነ የተትረፈረፈ ነው!!››በሹፈት ቃና የታሸውን የአባትዬውን መልስ ሰማች፡፡

‹‹አዎ የተትረፈረፈ ነው…ግን ውሽማ የለኝም እንጂ ቢኖረኝም ላንተ ስለማስብ አልጠራውም››
‹‹ለምን ?››
‹‹ሌላ የሰው ነፍስ በእጅ እንዲጠፋ አልፈልግም....ምን አይነት ቀናተኛና በሽተኛ እንደሆንክ እኔም አንተም እናውቃለን…እስከዛሬ ገና ለገና ከአንቺ ጋር አወሩ ብለህ ስንት ወዳጆቼን አስገደልክ?፡፡››
‹‹ወዳጆችሽን ወይስ ውሽሞችሽን…?ለማንኛውም..ያለመረጃ ሰውን አትወንጅይ››

ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

17 Oct, 14:41


🐯ርዕስ-ጉዞ በፀሎት
🐯ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
👍ረጅም ልብ ወለድ
የሚቀርበው- ከመጪው ስኞ ጀምሮ በየቀኑ ከእሁድ በስተቀር
🤝በፍቅር እና በጋብቻ ስነ-ልቦና ላይ ያተኳረ ስራ ስለሆነ በግንኙነት ውስጥ ያሉ ጥንዶች ቢያነብት በህይወታቸው የሚመነዝሩት የሆነ ጠቃሚ ሀሳብ እንደሚያገኙበት እርግጠኛ ነኝ።
👍አመሰግናለሁ...የስኞ ስው ይበለን

ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

16 Oct, 10:37


🤙በፍፁም እናንተ ሰዎች የሚሏችውን አይደላችሁም!!!

በአምፖል የፈጠራ ውጤቱ የምናውቀው ቶማስ አልቫ ኤድሰን አንድ ቀን ከትምህርት ቤቱ ወደ ቤት የተመለሰው መምህሩ የሰጠውን ወረቀት ይዞ ነበር፡፡ እናም ኤድሰን
ለእናቱ እንዲህ አላት “መምህሬ ይሄን ወረቀት ለእናትህ ብቻ ስጣት ብሎ ሰጠኝ” በማለት ወረቀቱን አቀበላት፡፡
እናት እንባ በአይኖቿ ሞልቶ በወረቀቱ ላይ የሰፈረውን ሀሳብ ለልጇ አነበበችለት፡፡ ያነበበችለት ሀሳብም ይህ ነበር “ልጅሽ በአስተሳሰቡ ምጡቅ (ጀኒየስ) ነው፡፡ ይሄ ትምህርት ቤት ለእሱ አይመጥነውም ፡፡ ለእሱ ብቁ የሆኑ መምህራኖችም ትምህርት ቤቱ የሌለው በመሆኑ እባክሽ አንቸው አስተምሪው ይላል” በማለት እንባዋን እየጠራረገች ወረቀቱን አጣጥፋ መሳቢያ ውስጥ
ከተተችው፡፡
-
እናቱ ካረፈች ከብዙ ዓመታት በኋላ ኤድሰን በክፈለ ዘመኑ ካሉ የፈጠራ ውጤት ባለቤቶች አንዱና ቀዳሚው ከሆነ በኋላ አንድ ቀን እናቱ እቃዎቿን የምታስቀምጥበትን መሳቢያ ማገላበጥ ጀመረ፡፡ ባጋጣሚ የተጣጠፈች ወረቀት ከመሳቢያው ጠርዝ አካባቢ ተሰክታ ይመለከትና
አንስቶ ከፈታት፡፡ ወረቁ ልጅ እያለ ከመምህሩ ለእናቱ ብቻ እንዲሰጥ ታዞ የተሰጠው ወረቀት እንደነበር አውቋል፡፡ ከፍቶ ሲያነበውም ወረቀቱ ላይ የሰፈረው ሀሳብ እንዲህ ይላል “ልጅሽ የአእምሮ ችግር ያለበትና ዘገምተኛ ነው፡፡ ከዚህ በኋላም ወደ ትምህርት ቤቱ እንዲመጣ አንፈቅድለትም” ይላል፡፡
-
ኤድሰን ለሰዓታት ካለቀሰ በኋላ ደያሪውን ከፍቶ እዲህ ሲል ጻፈ “ቶማስ አልቫ ኤድሰን አእምሮው ዘገምተኛ የተባለ ልጅ ነበር፡፡ ነገር ግን በጀግናዋና በልዩዋ እናቴ የምእተ ዓመቱ ጂኔስ ሁኛለሁ፡፡” እናትን መግለጽ እጅግ አዳጋች ነው፡፡በፊደል ገልጸው ሊያስቀምጡት የሚያዳግት ተፈጥሯዊ ጸጋ እናትነት ይመስለኛል፡፡ እጅ አትስጡ፤ በፍጹም ተስፋ አትቁረጡ በራሳችሁ ተማመኑ፣ ማንኛውንም ትግል ሁለት ጊዜ ነው። የምናሸንፈው ቀዳሚውም በአእምሮ ውስጥ የሚያልቀው ነው ይለናል ቶማስ ኤድሰን፡፡ እኔ በሙከራዬ አልወደኩም፤ የማይሰሩ አስር ሽህ መንገዶችን ለይቻለሁ እንጅ ይላል ተስፋ ላለመቁረጥ በአይነተኛ ተምሳሌትነት ቀድሞ ሊጠቀስ የሚችለው ቶማስ አልቫ ኤድሰን፡፡

via-#ራስን መለወጥ

ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

12 Oct, 04:54


📌📌ትርምስ እና ስርአት (Chaos and order)

📍ትርምስ(chaos) በራሱ ያለማወቅ ጎራ ነው ። ያልተገለጠ ግዛት እንግዳ ነገር ነው። ትርምስ ማለት የት እንዳለን በማናወቅበት ጊዜ ያለንበት ቦታ ነው።

📍ስርአት(order) ደግሞ የተገለጠው ግዛት ነው። ስርአት የማህበረሰብ መዋቅር፣ የረገጥነው መሬት እና ለቀናችን ያለን እቅድ ነው። ስርአት ይሞቃል! ብርሃን የሞላበት ህጻናት በደስታ የሚጫወቱበት ደህነነቱ የተጠበቀ ሳሎን ነው። ስርአት የሃገር ባንዲራ ፣ሃይማኖት፣ ቤት እና ሃገር ነው።

📍 ስርአት የአለም ባህሪ ከምንጠብቀው እና ከመኞታችን ጋር የሚገጥሙበት ቦታ ነው።

የምንትንሸራተቱበት በረዶ ጠጣር ሁኖ ሲያንሽራትታችሁ የምትወዱት ጓደኛችሁ ሲታመናችሁ ስርአት ወስጥ ናችሁ። በረዶው ተሰብሮ ሲያሰምጣችሁ ያው ጓደኛችሁ ሲክዳችሁ ትርምሱ ይጀመራል።

🧷 ስርአት በቂ አይደለም።ዝም ብላችሁ ባላችሁበት ሳትቀየሩ መቆየት አትችሉም ምክነያቱም አሁንም ከህይወት የምትማሯቸው ብዙ ጠቃሚ ነገሮች አሉ።

🧷 ትርምስም ደግሞ ሊበዛ ይችላል። ጫናውን መቋቋም መታገስ አትችሉም። መማር ያለባችሁን እየተማራችሁ ቢሆንም ከአቅማችሁ በላይ መጨነቅ አትችሉም።

ስለዚህ አንድ እግራችሁን በተካናችሁበት በምትረዱት ቦታ ሌላኛውን ደግሞ አሁን ለማወቅ እና ለመቻል በምትፈልጉበት ቦታ መትከል አለባችሁ። ከዛ እራሳችሁን የመኖር ሽብር በቁጥጥራችሁ ወስጥ በሆነበት እና ደህነነታችሁ በተጠበቀበት ነገር ግን ለነገሮች ንቁ እና ተሳታፊ በምትሆኑበት ቦታ አስተካከላችሁ ማለት ነው። እዚህ ቦታ ነው ትርጉም የሚገኘው።

Jordan peterson 12 rules of life, Chaos and order(ከዚሁ መንደር የተገኘ)

ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

23 Sep, 19:56


✍️ የአስተሳሰብ ለውጥ ልክ እንደ አውሮፕላን ሁለት ክንፍ አለው!

የአስተሳሰብ ለውጥ ልክ እንደ አውሮፕላን ሁለት ክንፍ አለው ፡፡ አንዱ ክንፍ እውቀት ነው፡፡ ሌላኛው ተግባር ነው፡፡ሰዎች ለመለወጥ የሚቸገሩበት አንደኛው ምክንያት ከእውቀት እጦት የተነሳ ነው፡፡ ምክንያቱም በማታውቀው ነገር ዙሪያ እንዴት ትለወጣለህ? ይሄ ቦታ አልተመቸንም ብንል የት ነው የምንሄደው? እንዴት ነው የምንሄደው? ሄደን ምን ያጋጥመናል? ካላልን አስቸጋሪ ነው፡፡

ሁሉ እውቀት ኖሮን ደግሞ ባለንበት ቁጭ ብንል ተለወጥን ማለት አይደለም። አሁን እንደውም ትልቁ ሽወዳ ያለው አንዳንዴ ብዙ ስለለውጥ ስናውቅ የተለወጥን ይመስለናል፡፡ ከእሱ ደግሞ አለማወቅ ሁሉ ይሻላል፡፡

እውቀት ብርሀን ነው፡፡ ካወክ በራልህ ማለት ነው ፡፡ ቤት ውስጥ መብራት ባይኖር ምንም ማድረግ አትችል ይሆናል፡፡ ግን ቤት ውስጥ መብራት ቢኖር ስቶቩን ለኩሶ፣ እቃውን አውጥቶ፣ ድስቱን ጥዶ ምግብ አብስሎ አያበላህም፡፡ ነገር ግን አንተ እንድትሰራ በር ይከፍትልሀል፡፡

ስለዚህ እውቀትን እና ተግባርን ማቀናጀት ነው ለውጥ የሚፈጥረው! ምንድን ነው መለወጥ የምንፈልገው? እሱን መለየት ያስፈልጋል፡፡ ምንድን ነው ማድረግ ያለብን? እሱንም መለየት እና ማድረግ ነው፡፡ ጓሮህን ከሆነ መለወጥ የምትፈልገው እንዴት መለወጥ እንደምትችል ማወቅ አለብህ፡፡ ከዛ እጅህን ሰብስበህ መነሳት አለብህ፡፡ ጓሮህ ተቀየረ ማለት ነው፡፡

ዶ/ር ምህረት ደበበ
ጥበብ እና ፍልስፍና

ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

21 Sep, 11:33


ችግሮችን ከመፍታት ይልቅ ችግሮችን ማስወገድ ተማር!!

ጥበብ ሕይወትን የምንቀዝፍባቸው ክህሎቶች መለኪያ ነው። ችግሮችን አስቀድሞ መከላከል ከተፈጠሩ በኋላ ከመፍታት የተሻለ ጥበብን ይጠይቃል፡፡እውነታው ሕይወት ከባድ መሆኗ ነው፡፡ ችግሮች በሁሉም አቅጣጫ በየጊዜው ይተኮሱብሃል፡፡ እጣ ፈንታ መርገጫህ ስር ጉድጓዶችን ልትቆፍርብህ ወይም መሿለኪያዎችህን ልትዘጋብህ ትችላለች። ይህንን መቀየር አትችልም፡፡ አስቀድሞ አደጋ ያለው የት ጋር እንደሆነ ከተረዳህ ግን ወዳንተ እንዳይመጣ ለማጠር እድል ይኖርሃል፡፡ በዚህ መንገድ መሰናክሎችን ሁሉ ማስወገድ ትችላለህ፡፡ ይህንን ሀሳብ አልበርት አንስታይን እንዲህ ያስቀምጠዋል፡፡ “ጎበዝ ሰው ችግሮችን ይፈታል፤ ጥበበኛ ሰው ግን ችግሮችን ያስወግዳል፡፡”

ችግሩ ችግሮችን ማስወገድም የሚወደስ ነገር አለመሆኑ ነው፡፡ ሁለት ፊልሞችን አስብ፡፡
1.በመጀመሪያው ፊልም ውስጥ አንድ መርከብ ከበረዶ ክምር ጋር መጠነኛ ግጭት ይገጥመዋል፡፡ መርከቡም ይሰምጣል። በዚህ ጊዜ የመርከቧ ካፒቴን ራስ ወዳድነት በሌለበት መልኩ ራሱን አበርትቶ ተሳፋሪዎቹን ሁሉ ከመስመጥ ይታደጋቸዋል፡፡ መርከቧ ለዘለዓለሙ ከመሰወሯ ከደቂቃዎች በፊት ሁሉንም ተጓዦች በማዳን ከጀልባው ላይ ዘሎ ወደ ሕይወት አድኑ ቦቴ ውስጥ በመግባት የመጨረሻው ሰው ነበር።

2.በሁለተኛው ፊልም ውስጥ ደግሞ እንዲህ ሆነ፡፡ መርከበኛው መርከቧ ከበረዶ ክምሩ ጋር ከመጋጨቷ በፊት አስተውሎ በቂ ርቀት ላይ እንድትቆም አደረጋት፡፡

የትኛውን ፊልም ለማየት የበለጠ ትከፍላለህ?በእርግጠኝነት የመጀመሪያውን ፊልም፡፡ ሌላ ጥያቄ ደግሞ ላንሳልህ፡፡ አንተ በመርከቧ ውስጥ ተጓዥ ብትሆን ኖሮ በየትኛው ፊልም ሁኔታ ውስጥ መሆንን ትመርጣለህ? ያለ ምንም ጥርጥር ሁለተኛው ፊልምን።

እነዚህ ምሳሌዎች እውነተኛ ገጠመኞች ናቸው ብለን እናስብ፡፡ ቀጥሎ ምን ይፈጠራል? የመጀመሪያው ፊልም ውስጥ ያለው ካፒቴን የቴሌቭዥን ፕሮግራም ላይ ይጋበዛል። ምናልባት መርከበኛነቱን ትቶ አነቃቂ ንግግሮችን እያደረገ ሕይወቱን መምራት ሊጀምር ይችላል። መንገድም በስሙ ሊሰየምለት ይችላል፡፡ ልጆቹም (ምናልባት ለመጀመሪያ ጊዜ) በአባታቸው ይኮራሉ፡፡ የሁለተኛው ፊልም ውስጥ የሳልነው ካፒቴንስ? ከስራው በጡረታ እስኪገለል ድረስ ችግሮች እንዳይከሰቱ በቅድመ ጥንቃቄ የመርከበኝነት ስራውን ይሰራል። መርሁም “ከ20 ጫማ እርቀት ላይ ልታልፈው የምትፈራውን ነገር በ500 ጫማ እርቀህ እለፈው” የሚለው የቻርሊ ሙገር የሕይወት መርህ ይሆናል፡፡

እንግዲህ ተመልከት፡- የሁለተኛው ፊልም ካፒቴን ከመጀመሪያው ፊልም ካፒቴን በሚታይ መልኩ የሚሻል ቢሆንም እኛ የምናከብረውና የምናደንቀው ግን የመጀመሪያውን ፊልም ካፒቴን ነው፡፡ ለምን? በቅድመ ጥንቃቄ የሚመጣ ስኬት ለውጪው ዓለም እይታ የሚጋለጥ አይሆንም፡፡

ጋዜጠኞች አስቸጋሪ ሁኔታዎች እንዳይመጡ ካረጉ በሳል ሰዎች ይልቅ ችገሮችን የቀለበሱ የሥራ መሪዎችን ነው የሚያሞካሹት ።የቅድመ ጥንቃቄ ስኬቶች ለውጪው ዓለም የማይታዩ ባለመሆናቸው ምክንያት ሳይታዩና ሳይወደሱ ይኖራሉ፡፡ የእንደዚህ አይነት ስኬቶት ባለቤቶችን ጥበብ የሚያውቁት በእሱ ዙሪያ ያሉ የቡድኑ አባላት ብቻ ናቸው። እነሱም ቢሆን በተወሰኑ መልኩ ቢያውቁት ነው፡፡

የአንተስ ሕይወት? አመንክም አላመንክም ከስኬቶችህ ሁሉ 50% የሚሆኑት የቅድመ መከላከል ጥንቃቄህ ውጤቶች ናቸው፡፡ ሁላችንም እንደምናደርገው ሁሉ አንተም አንዳንድ ነገሮችን በንዝህላልነት ልታደርግ ትችላለህ፡፡ ይህ እንዳለ ሆኖም ግን ስህተቶችን ላለመስራት ሁልጊዜም ትጠነቀቃለህ፡፡ በአርቆ · አሳቢነት ያስወገድካቸውን በስራህ፣ በትዳርህ፣ በትምህርትህ ወይም በሌላ የሕይወትህ ዘርፍ ሊገጥሙህ የነበሩ ችግሮችን አስብ፡፡

ጥንቃቄ (prevention) ቀላል ነገር አይደለም፡፡ ቅድመ ጥንቃቄ በባህሪው ቀድሞ ማየት (imagination) ይጠይቃል ቀድሞ መረዳትና የሚመጣውን መገመት ደግሞ ብዙውን ጊዜ አዛብተን የምንረዳቸው ነገሮች ናቸው፡፡ ይህ አዲስ ሀሳብ አያመጣልንም፡፡ በዓይነ ህሊና ማየት (imagination) ማለት የመጨረሻው ፍትሃዊ ነገር ሆኖ እስክናይ ድረስ ሊሆኑ የሚችሉት ነገሮች ውጤቶችና የመፈጠር እድላቸውን ሁሉ እንዲያስብ አዕምሯችንን ማሰራት ማለት ነው፡፡ ስለሆነም አስቀድሞ ማየትና መገመት ከባድ ስራ ነው።

በተለይ ጉዳዩ ስለአደገኛ ችግሮች ሲሆን ደግሞ ቀድሞ የመገመት ሥራ የበለጠ ፈታኝ ይሆናል፡፡ ሊመጡ እድል ባላቸው ችግሮች ላይ ሁሉ እየተጠነቀቅክ መኖር ይጠበቅብሃል? ይህስ ሁልጊዜ የተጨናነቀ ሰው ሆነህ እንድትኖር አያደርግህም? ተሞክሮዎች የሚያሳዩት እንደዚያ እንዳልሆነ ነው፡፡ ቻርሊ ሙገር እንዲህ ይላል “በሕይወት ዘመኔ ሁሉ የሚመጠብኝን አደጋዎች ስገምት ኖሬያለሁ፡፡ ሁልጊዜ ይሄንን እያሰብኩ፣ አደጋዎች ከመጡም እንዴት መመከት እንዳለብኝ እያሰላሰልኩ መኖሬ ደስተኛ እንዳልሆን አላደረገኝም፡፡”

ሮልፍ ዶልቢ
The art of good life
via-እስማኤል ኢብራሂም

ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

10 Sep, 10:05


https://youtu.be/aT0O9uKJ1WI

ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

10 Sep, 10:04


https://youtu.be/1VKvFHVDagA

ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

08 Sep, 14:49


-❤️ በስውር ላደረጉልኝ በአደባባይ ማመስገን እፈልጋለሁ ፡፡
****
🥦አዲሱን አመት ልንቀበል ሁለት ቀን ነው የቀረን፡፡ሁሌ አዲስ አመት ሲመጣ አሮጌ የተባለውን አመት እንዴት እንዳሳለፍን ኦዲት ማድረግና በመጪው አዲስ አመት የምንከውናቸውን ነገሮች እቅድ ማውጣት ለምዶብናል፡፡እኔም በዚህ ስሌት አመቱን ከህይወት ውጣ ውረዴ አንፃር መዝኜ በምስጋና መዝጋት ፈለኩ፡፡እናም ደግሞ በዚህ ሰዓት በፍፅም ተስፋ መቁረጥ ውስጥ ሆኖ ይህን ለሚያነብ ሰው የሆነች የተስፋ ብርሀን ይረጭለት ይሆናል በሚል እምነት ነው፡፡
////
🤡-ልክ አምና በዚህ ጊዜ የህይወቴ በጣም አስቀያሚው ወቅት ላይ ነበርኩ፡፡ህመሜ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሶ አልጋ ላይ የወደቅኩበት ፤ህመሙን ተከትሎ የተፈጠረብኝ ስቃይ ፤ድባቴና እራስንም ሆነ ዓለምን እንድጠላ እና እንድፀየፍ የተገደድኩበት ሁኔታ ላይ ነበርኩ፡፡እና በዛ ሁኔታ ላይ ሆኜ ስለአዲስ አመት ሲወራ እኔ እንዴት በሰላም እንደማርፍ ነበር ማስበው…መኖር ፍፁም ደክሞኝ ነበር….ፈጽሞ አመት ሙሉ ቆይቼ ይሄኛውን አዲስ አመት ለመቀበል የሚያስችል ትግስቱም ሆነ ፍላጎቱ አልነበረኝም፡፡
🤡ግን ድንገት የድሮ ወዳጆቼ በህይወቴ ተመልሰው መጡ …ከአልጋዬ አንስተው ወደህክምና ወሰዱኝ ..ገንዘባቸውን ያለስስት ከስክሰው እያመላለሱ አሳከሙኝ…እንሆ አሁን ከበሽታዬ ባልድንም ስቃይም ሆነ ድባቴ የለብኝም…በሽታዬ የሚያስከትልብኝን ህመም በመድሀኒት እገዛ እንዴት መቋቋም እንደምችል ተለማምጄ የህይወቴ አንዱ ክፍል እንደሆነ ተቀብዬዋለው….እንደዛም በማድረጌ በፈገግታና በምስጋና እየኖርኩ ነው፡፡ይሄ ሁሉ የሆነው በሚወዱኝ ቤተሰቦቼና በወዳጆቼ እገዛ ነው፡፡
🤡እና የቤተሰቦቼን ላቆየውና ለዚህ ዋና ባለድርሻ የሆኑትን
1/የጀስቲስ ህንፃ ተቋራጭ ባለቤት…ኢንጂነር ዩሱፍ መሀመድ….(ከነቤተሰቡ)
2/ደረጄ ታምራት………….(ከነቤተሰቡ)…..
እንሆ ላለፉት 9 ወራት ለህክምና ለመድሀኒት …እና ተያያዝዥ ወጪዎች እነሱ ሳይሰስቱ በሰጡኝ ብር ነው ያለሀሳብ ስጠቀም የቆየሁት….ለዚህ ደግሞ ቢያንስ በስውር ሰጥተውኛልና በአደባባይ መመስገን ይገባቸዋል ብዬ አስባለው፡፡…እናም ከልቤ አመስግናለው፡፡
ሌላው
🤡እኔን ለማዳን ለበርካታ ወራት የተቻላችሁን ሁሉ በማድረግ ከልባችሁ ለጣራችሁ ገላዬ ሸዋንግዛው እና ባለቤቱ ህይወት መኮንን(የእናንተን ምስጋና በአጭሩ ያደረኩት የአንድ ቤተሰብ አባል ስለሆን ብዬ ነው..ቢሆንም ያደረጋችሁልኝን መቼም አረሳውም)
👌-ሌላው….
በፍላጎታቸውና በፍቅራቸው በየአጋጣሚው ቀዳዳዬን ለመድፈን ለሞከሩት እና ዘወትር አይዞህ እያሉ ብርታት ለሆኑኝ ጓደኞቼ
1/የሲፍለን ኢንጂነሪን ባለቤት..ኢንጂነር ሞሲሳ ታከለ
2/ ተስፋዬ አሰፋ (ከነቤተሰቡ)
3/ኢንጂነር..ግሩም ተፈራ
4/ ›› …ሽመልስ መኮንን
5/››………..ዬሴፍ …..ሌሎችም
6/- የጀስቲስ ህንፃ ተቋራጭ የስራ ባለደረቦቼ የነበራችሁ በአጠቃላይ…..ሁላችሁንም በጣም አመሰግናለሁ፡፡
👉በድጋሚ
ደረጄ ታምራት…ጓደኛዬ ብቻ አይደለም ..ከወንድምም በላይ ነው…..ከላይ ያመስገንኩት ለእኔ ህክምና ላወጣው ብር ነው፡፡ግን በገንዘብ ብቻ አላቆመም….በየሶስት ቀኑ ያለማቆረጥ ይደውልልኛል…ትንሽ ሲያመኝ መኪናውን አስነስቶ ቢሾፍቱ ይመጣና ይዞኝ አዲስ አበባ ይሄዳል….ስራውን ጥሎ ያሳክመኝና ወደቤቱ ይወስደኛል…ከዛ መላአክ የሆነች ባለቤቱ እመቤት ጉልማ በቃኝ ወደቤቴ መልሱኝ እስክል እንደንጉስ ታስተናግደኛለች..ይሄ አንዴ ሁለቴ የሆነ አይደለም..አመቱን ሙሉ ያልተለየኝ እንክብካቤያቸው ለእኔ የህልም ያህል አስደናቂ ነው ….እነዚህን ባልና ሚስቶች ታዲያ ምን ብዬ ማመስገን እችላለሁ….ፅድቅና ኩነኔ የሚኖር ከሆነ … በእኔ ምክንያት ብቻ ይፀድቃሉ፡፡ ወንድሜ በጣም አመሰግናለው፡፡
👌ሌላው
ያለሁበት ሁኔታ ከባድ እንዳይሆንብኝ እቤት ሆኜ ስራ እንድሰራ እና ገንዘብ እንዳገኝ ሁኔታውን ያመቻቸህልኝ ወዳጄ ጋዜጠኛ ፀጋዬ አብራር…..አንተንም ከልብ አመሰግናለሁ፡፡
👉ሌላው
የዚሁ የፌስ ቡክ ወዳጆቼ…መታመሜን በሰማችሁ ጊዜ ያቅማችሁን ላደረጋችሁልኝና ከጎኔ ሆናችሁ ብርታት ለሆናችሁኝ ..አቤት ድረስ መጥታሁ ለጠየቃችሁኝ
1/መሀመድ እንድሪስ ካሳ…..ሙስታጅብ….ሀመር ውቢት….ታደለች ግብሩ…እሌኒ አሮን… ቴድሮስ ሲሳየ…መሲ ነፍጠኛዋ…ያለምዘርፍ ወሌ ..መስፍን ተሰማ….መቅደስ ኃይሌ..ሌሎችም ስማችሁን ለጊዜው ማስታወስ ለተሳነኝ በአጠቃላይ …አመሰግናለው፡፡
መጪው አዲስ አመት ለሁላችሁም …ሰላም የሰፈነበት…በረከት የሚታጨድበት…ፍቅር የሚዘመርበት…የምቾትና የተድላ ይሆንላችሁ ዘንድ ከልብ እመኛለሁ፡፡በድጋሜ አመሰግናለሁ፡፡

1,583

subscribers

281

photos

3

videos