—የጠፋሁ ልጅህ ነኝ —
እጅግ ለምወደው ዘማሪ ዲያቆን Ermiyas Girma የሰጠሁት «የጠፋሁ ልጅህ ነኝ» የሚል ለመጀመሪያ ጊዜ የሞከርኩት የንስሓ የመዝሙር ግጥም ነበር። ከሰሞኑን ትዝ ብሎኝ መለስ ብዬ ሳደምጠው ሰው ጋር ከደረሰ 4 ዓመት እንዳለፈው አየሁ። በጊዜው የግል ንስሓዬን የተናዘዝኩበት ሥራ ነበር —ዛሬም ንስሓዬ ነው። ባደመጥኩት ቁጥር የሚያስገርመኝና የሚያስደንቀኝ ነገር ቢኖር ግጥሙ አይደለም። ከእግዚአብሔር ርዳታ ጋር ዲያቆን ኤርምያስ የግጥሙን መንፈስ ተረድቶ የደረሰለት ልብን የሚያራራ ኦርቶዶክሳዊ ዜማና የዘመረበት መንገድ ነው። እስከ አሁን ድረስ 63 ሺህ ሰዎች አዳምጠውታል። ስለዚህ መዝሙር በዙሪያዬ ካሉ ሰዎች መሃል የሚያውቁ ጥቂት ናቸው። እናም ምናልባት ሌሎችም ሰዎች ጋር እንዲደርስ ከረዳ በሚል ዛሬ በይፋ ላጋራው ወድጄያለሁ። ሊንኩ 👇
🛑 https://youtu.be/mcnS_ULmw9A?si=lYVu7zR4E4yxPa0z