ወሪሳ
ወሪሳ የዓለማየሁ ገላጋይ ልብ ወለድ ድርሰት ነው፡፡ መቼቱን ወሪሳ እና እሪበከንቱ በሚባሉ ተጎራባች መንደሮች ላይ ያደረገው ይህ ልብወለድ ማህብረሰባዊ ማንነታችንን የሚፈትሽ ግሩም ስራ ነው፡፡ በወሪሳ ያልተፈተሸ ማህብራዊ ቅጥ የለም፡፡ ፖለቲካቸን፣ ነጣቂነታችን፣ ታሪካችን፣ የትምህርት ስርዓታችን ከፍ ሲልም ሰው የመሆን ትርክምክማችን ተፈክሮበታል፡፡ ቀልድን በሚፈጥሩ ተናዳፊ ምጸቶች፣ ፈገግና ቀጨም እያልን የደራሲውንም የቋንቋና የትረካ ብቃት እያደነቅን የምናነበው ስራ ነው፡፡
ዓለማየሁ ገላጋይ “አጥቢያ”፣ “ስብሐት ገብረ እግዚአብሔር፡ ሕይወትና ክህሎት”፣ “ቅበላ”፣ “የፍልስፍና አፅናፍ”፣ “ኢህአዲግን እከሳለሁ”፣ “ኩርቢት”፣ “የብርሃን ፈለጎች”፣ “መልክአ ስብሐት”፣ “ወሪሳ”፣ “በፍቅር ስም”፣ “ታለ፤ በእውነት ስም”፣ “መለያየት ሞት ነው”፣ “ውልብታ”፣ እና “ሐሰተኛው፤ በእምነት ስም” ፣ “የተጠላው እንዳልተጠላ”፣ “ቤባንያ”፣ ማዕበል ጠሪ ወፍ፣ የተሰኙ መጻሕፍት ደራሲ እና ሐያሲ ነው።
ከደራሲው ብዙ ስራዎች ውስጥ በዚህ እትማችን ወሪሳን ታነብቡ ዘንድ ስንጋብዛችሁ ደስ እያለን ነው፡፡
ግብዣችን ይቀጥላል፡፡
ከባይራ ዲጂታል መጽሔት ቅጽ 1 ቁጥር 9 የተወሰደ
በእነዚህ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ቤተሰባችን ይሁኑ!
ቴሌግራም- https://t.me/Bayradigital
ድረገጽ (Website)- https://bayradigital.com/
ፌስቡክ (Facebook) - ባይራ ዲጂታል መጽሔት
ትዊተር (Twitter) - https://x.com/BayraDigital
ለማንኛውም አስተያየት ብሎም ጽሑፍ ለመላክ
ኢ-ሜይል- [email protected]
ኑኒ ባይራክ!
ታላላቆች ነን!