ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ Telegram Posts

This channel is not operated by Deacon Yaregal Abegaz- ይህ ገጽ የሚንቀሳቀሰው በዲ/ን ያረጋል አበጋዝ አይደለም
https://youtube.com/@yaregalabegaz?si=1f5NHTaQ2l2LbxWQ
“ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ አሳብ ነው።”
— 2ኛ ቆሮ 11፥28
https://youtube.com/@yaregalabegaz?si=1f5NHTaQ2l2LbxWQ
“ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ አሳብ ነው።”
— 2ኛ ቆሮ 11፥28
30,806 Subscribers
426 Photos
107 Videos
Last Updated 01.03.2025 00:50
Similar Channels

14,615 Subscribers

12,861 Subscribers
The latest content shared by ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ on Telegram
The Hexaemeron is the title of nine homilies delivered by Saint Basil the Great on the creation of the universe as revealed in the opening chapters of Genesis. These sermons, delivered at both the morning and evening services of Great Lent, were the most celebrated and admired of the saint’s works. Saint Basil’s brother, Saint Gregory of Nyssa, lauded the Hexaemeron as a superlative work inspired by the Holy Spirit, even to be admired on the same level as the words of Moses. One of the greatest patristic commentaries on Holy Scripture, the Hexaemeron allows us to see the creation through the eyes of one who beheld the Creator Himself.
📖ኰኲሐ ሃይማኖት
【ወጣት ተመልከት እንዳትሳሳት】
✍️...በል ደኅና ኹን! አንተ፤ ዕውሩን ዐይናማ ነህ ቢሉት ዐይናማ ላይሆን፣ የተሰበረውንም ደኅና ነህ ቢሉት ደኅና ላይሆን፣ የንብላውን ሕግ እውነተኛ ለማስመሰል በጻፍከው ስሕተት የምእመናንን ልቡና ይሆንን? አይሆንን? ከሚል ጥርጥር ላይ ስለጣልከው እኔም “ይነግረው ያጣ ያሙኝ አይመስለውም” እንደሚባለው ተረት ዝም ብንልህ ጥፋትህ እየቀጠልክ ስለሔድክ ለምእመናን ነገርህ እውነት ይመስላቸዋል በማለት “ገሥጽ ወተዛለፍ” ያለው ቃል እያጽናናኝ (፪ጢሞ. ፬÷፪) መልሱን ስጽፍልህ ያመላለሱ ዘዴ እያስገደደኝ በማደርገው ንግግር አንዳንድ ላይ “ባርክዎሙ ለእለ ይረግሙክሙ” የተባለው ትእዛዝ ሳይፈርስብኝ የቀረ አይመስለኝምና የሰውን መዳኑን እንጂ መጎዳቱን የማይወድ ቸሩ አምላክ ኹላችንንም ይቅር ብሎ በኢየሩሳሌም ሰማያዊት ያገናኝን፡፡ አሜን፡፡
[ከመጽሐፉ የውስጥ ገጾች የተወሰደ]
🫧መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬ ሊቅ ረቂቅ የሃይማኖት አርበኛ መኾናቸው ዛሬም በመጻሕፍቶቻቸው፤ ሲወሳ፤ ሲመሰከር ፤ትውልድ ሲሻገር ይኖራል። በእቅበተ እምነት ዙሪያም ይኽ ነው የማይባል አሻራ አኑረውልናል ።ከድንቅና ዘመን ተሻጋሪ ስራዎቻቸው መካከል ለኘሮቴስታንቱ ዘመንፈስ ቅዱስ አብርሃ ምላሽ የሰጡበት ኰኲሐ ሃይማኖት የተሰኘው መጽሐፋቸው በትህትና የተለበጠ በእውቀት የተጠረዘ መጽሐፍ መኾኑ መስካሪ የማያሻው እንዲኹም በዚኽ ዘመን ላለው የኑፋቄ ትምህርት እና ግርታ ውስጥ እየወደቀ ላለው ወጣት አይነተኛ መፍትሔ ይኽ መጽሐፍ እንደኾነ መገንዘብ አይከብድም።
©መጽሐፉን በግዮን መጻሕፍት በልዩ ቅናሽ ያገኙታል።
#📚 ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623
【ወጣት ተመልከት እንዳትሳሳት】
✍️...በል ደኅና ኹን! አንተ፤ ዕውሩን ዐይናማ ነህ ቢሉት ዐይናማ ላይሆን፣ የተሰበረውንም ደኅና ነህ ቢሉት ደኅና ላይሆን፣ የንብላውን ሕግ እውነተኛ ለማስመሰል በጻፍከው ስሕተት የምእመናንን ልቡና ይሆንን? አይሆንን? ከሚል ጥርጥር ላይ ስለጣልከው እኔም “ይነግረው ያጣ ያሙኝ አይመስለውም” እንደሚባለው ተረት ዝም ብንልህ ጥፋትህ እየቀጠልክ ስለሔድክ ለምእመናን ነገርህ እውነት ይመስላቸዋል በማለት “ገሥጽ ወተዛለፍ” ያለው ቃል እያጽናናኝ (፪ጢሞ. ፬÷፪) መልሱን ስጽፍልህ ያመላለሱ ዘዴ እያስገደደኝ በማደርገው ንግግር አንዳንድ ላይ “ባርክዎሙ ለእለ ይረግሙክሙ” የተባለው ትእዛዝ ሳይፈርስብኝ የቀረ አይመስለኝምና የሰውን መዳኑን እንጂ መጎዳቱን የማይወድ ቸሩ አምላክ ኹላችንንም ይቅር ብሎ በኢየሩሳሌም ሰማያዊት ያገናኝን፡፡ አሜን፡፡
[ከመጽሐፉ የውስጥ ገጾች የተወሰደ]
🫧መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬ ሊቅ ረቂቅ የሃይማኖት አርበኛ መኾናቸው ዛሬም በመጻሕፍቶቻቸው፤ ሲወሳ፤ ሲመሰከር ፤ትውልድ ሲሻገር ይኖራል። በእቅበተ እምነት ዙሪያም ይኽ ነው የማይባል አሻራ አኑረውልናል ።ከድንቅና ዘመን ተሻጋሪ ስራዎቻቸው መካከል ለኘሮቴስታንቱ ዘመንፈስ ቅዱስ አብርሃ ምላሽ የሰጡበት ኰኲሐ ሃይማኖት የተሰኘው መጽሐፋቸው በትህትና የተለበጠ በእውቀት የተጠረዘ መጽሐፍ መኾኑ መስካሪ የማያሻው እንዲኹም በዚኽ ዘመን ላለው የኑፋቄ ትምህርት እና ግርታ ውስጥ እየወደቀ ላለው ወጣት አይነተኛ መፍትሔ ይኽ መጽሐፍ እንደኾነ መገንዘብ አይከብድም።
©መጽሐፉን በግዮን መጻሕፍት በልዩ ቅናሽ ያገኙታል።
#📚 ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623
በጾማችን የነፍሳችንን ክፉ ልማዶች ካላስወገድን ከሥጋ መከልከላችን ብቻውን ምን ይጠቅመናል? ስንጾም ውለን ጾም ከመግባቱ በፊት እንመገበው የነበረውን ምግብ ለውጠን መናኛ የሆነ የጾም ምግብ በማዕዳችን አቀረብን፡ ሆኖም ግን በጸሙ የምንመገበውን ምግብ እንደ ለወጥን ክፉ ግብራችንን እና ሕይወታችንንስ አብረን ለውጠናል ይሆን? በእውነት እኔ ግን እንዲህ ያደረጋችሁ አልመሰለኝም፡፡ እንዲህ ከሆነ መጾማችሁ ጥቅሙ ምንድን ነው? ስለዚህ ከጾማችሁ ጋር ልማዳችሁንና ሕይወታችሁን ወደ መልካምነት ትቀይሩ ዘንድ በተከታታይ እንድታስቡበት አደርጋችሁ ዘንድ ስለዚህ ነገር እናንተን ማስተማርንና መገሠጽን አላቋርጥም፡፡ (ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ፣ ትምህርት በእንተ ምክንያተ ሐውልታት 4 ቁ 12)
https://youtube.com/playlist?list=OLAK5uy_mkP8VAJuuIigxymiKB_F0V4l6iyFIZMlQ&si=nJSkJNxzrs2mDTjB
ራሳችንን ፍሬ በሌለው መንገድ በከንቱ እንዳናደክም ጥቂት ነገሮችን እንበል፡፡ በርግጥ አሁን የምታደርጉት ነገር - ጾማችሁና መሬት ላይ መተኛታችሁ - በጣም የተመሰገነ ተግባር ነው፡፡ ሆኖም ከእነዚህ ጋር ሌሎች በጾም ጊዜ ሊፈጸሙ የሚገባቸው ተግባራት ካልተጨመሩ በስተቀር ከጾም የምናገኘውን ዋጋ ያሳጡናል፡፡ እግዚአብሔር ኃጢአትን እንዴት ይቅር እንደሚል አሳይቶናል፡፡ በጥንት ዘመን የነነዌ ሰዎች ኃጢአትን ባደረጉ ጊዜ በኃጢአት ቁስላቸው ላይ ጽኑ የሆነ የጾምን መድኃኒት አደረጉ፡፡ መሬት ላይ በመተኛት ማቅና ዓመድ ለበሱ፣ ለቅሶንና ሐዘንን በኃጢአት ቁስላቸው ላይ መድኃኒት አድርገው አፈሰሱ፡፡ ይህም ብቻ ሳይሆን ከዚህ ሁሉ ጋር ደግሞ ሕይወታቸውን ከክፉ ወደ መልካም ለወጡ፡፡ ከዚህ ሁሉ ጋር እግዚአብሔር በምን ምክንያት እንደ ማራቸው ሲናገር እግዚአብሔርም ከክፉ መንገዳቸው እንደ ተመለሱ ሥራቸውን አየ እግዚአብሔርም ያደርግባቸው ዘንድ በተናገረው ክፉ ነገር ተጸጽቶ አላደረገውም' ይላል። ዮና 3፡10 ስለዚህ ከመጾም ጋር ከክፉ መመለስንና ከክፉ ነገር መጾምንም እንፈጽም ዘንድ መዘንጋት የለብንም፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ፣ ትርጓሜ ቆሮንቶስ ቀዳማዊ፣ ክፍለ ትምህርት 4፣ ቁ. 6
ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ፣ ትርጓሜ ቆሮንቶስ ቀዳማዊ፣ ክፍለ ትምህርት 4፣ ቁ. 6
ርቱዐ ሃይማኖት ስለ ጾም በተናገረበት ክፍል የሚጾም ሰው ኹለንተናውን ማስጾም የሚገባው መሆኑን ፣ ማለትም ኃጥያትን እንለያት ዘንድ እንዲህ ሲል ያስተምረናል።
"አፍህ ክፉ ከመናገርን ፣ አንደበትህም ሰውን ከማማት ከመሳደብ ይጹም ፣ ዐይንህም ሴትን ከመመልከት ይጹም ፣ ዦሮህም ዘፈንን ጨዋታን ከመስማት ይጹም ፣ እጅህም የሌላውን ገንዘብ ወስዶ ከመሸጥ ከመማታት ፣ ከመቀማት ይጹም ፣ እግርህም ደምን ለማፍሰስ ከመመላለስ ከመሮጥም ይፁም ፣ ሆድህም ከስስት ጥሉላትንም ከመብላት ይጹም። ጥረስህም ከመሳቅ ይጹም። ልቡናህም ከሽንገላ ፣ ከቂም ከቁጣ ፣ ከመታበይ ፣ከክፉ ነገር ሁሉ ይጹም። ልቡና እንቢ ካላቸው ሌሎቹ አካላት ክፉ ማድረግ አይቻላቸውምና ፣ የብልቶች ( የሕዋሳት) ሁሉ ንጉሣቸው እርሱ ነውና። ሕሊናም ተላላኪው ፣ልብሱ ነው ፣ ናላም የአዕምሮ ፣የጥበብ ፣ የመለኮት ማደሪያቸው ነው። በዚህም አካላትን ሁሉ ይገዛቸዋል። ሁሉንም ወደ መልካምም ይሁን ወደ ክፉ ይመልሳቸዋል። አይሆንም ይሉት ዘንድ አይቻላቸውም ። ከፈለገም በሰማይም በምድርም ሁሉንም ያድናቸዋል። ከፈለገ በሰማይም በምድርም ያጠፋቸዋል። ህሊናህም ከመታወክ ይጹም። ሥጋህም ከዝሙት ይጹም። ሰውነትህም ከስንፍና ፣ ከመቦዘን (ሥራን ከመፍታት) ፣ከዚህና ከመሳሰለው ሀሉ ይጹም። ቅዱስ ጳውሎስ ' እንዲህ ሁነህ በጾምህ ጊዜ ሰውነትህ በሰዎች ሁሉ ዘንድ የመንፈስ ቅዱስ ማደርያ ይሆናል። ' አለህ።
"አፍህ ክፉ ከመናገርን ፣ አንደበትህም ሰውን ከማማት ከመሳደብ ይጹም ፣ ዐይንህም ሴትን ከመመልከት ይጹም ፣ ዦሮህም ዘፈንን ጨዋታን ከመስማት ይጹም ፣ እጅህም የሌላውን ገንዘብ ወስዶ ከመሸጥ ከመማታት ፣ ከመቀማት ይጹም ፣ እግርህም ደምን ለማፍሰስ ከመመላለስ ከመሮጥም ይፁም ፣ ሆድህም ከስስት ጥሉላትንም ከመብላት ይጹም። ጥረስህም ከመሳቅ ይጹም። ልቡናህም ከሽንገላ ፣ ከቂም ከቁጣ ፣ ከመታበይ ፣ከክፉ ነገር ሁሉ ይጹም። ልቡና እንቢ ካላቸው ሌሎቹ አካላት ክፉ ማድረግ አይቻላቸውምና ፣ የብልቶች ( የሕዋሳት) ሁሉ ንጉሣቸው እርሱ ነውና። ሕሊናም ተላላኪው ፣ልብሱ ነው ፣ ናላም የአዕምሮ ፣የጥበብ ፣ የመለኮት ማደሪያቸው ነው። በዚህም አካላትን ሁሉ ይገዛቸዋል። ሁሉንም ወደ መልካምም ይሁን ወደ ክፉ ይመልሳቸዋል። አይሆንም ይሉት ዘንድ አይቻላቸውም ። ከፈለገም በሰማይም በምድርም ሁሉንም ያድናቸዋል። ከፈለገ በሰማይም በምድርም ያጠፋቸዋል። ህሊናህም ከመታወክ ይጹም። ሥጋህም ከዝሙት ይጹም። ሰውነትህም ከስንፍና ፣ ከመቦዘን (ሥራን ከመፍታት) ፣ከዚህና ከመሳሰለው ሀሉ ይጹም። ቅዱስ ጳውሎስ ' እንዲህ ሁነህ በጾምህ ጊዜ ሰውነትህ በሰዎች ሁሉ ዘንድ የመንፈስ ቅዱስ ማደርያ ይሆናል። ' አለህ።
When a man leaves on a journey, he must know where he is going. Thus with Lent. Above all, Lent is a spiritual journey and its destination is Easter, "the Feast of Feasts." It is the preparation for the "fulfillment of Pascha, the true Revelation." We must begin, therefore, by trying to understand this connection between Lent and Easter, for it reveals it something very essential, very crucial about our Christian faith and life.
By Alexander Schmemann
By Alexander Schmemann
የዐቢይ ጾም የመጀመሪያ ሳምንት
ዘወረደ
በዚህ ሳምንት የቃል ርደት፣ የወልድ ልደት፣ የአዳም ድኅነት ቢነገርም እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ግን ከሰማይ የወረደ ሰማያዊ፣ በክብር ያረገ በኩረ ትንሣኤ መሆኑ አይዘነጋም፡። ለዚህም ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ “እውነት እውነት እልሃለሁ፥ የምናውቀውን እንናገራለን፤ ያየነውንም እንመሰክራለን፥ ነገር ግን ምስክርነታችንንም አትቀበሉትም። በምድር ያለውን ስንነግራችሁ ካላመናችሁኝ፥ በሰማይ ያለውን ብነግራችሁ እንዴት ታምኑኛላችሁ? ከሰማይ ከወረደው የሰው ልጅ በቀር ወደ ሰማይ የወጣ የለም፥ እርሱም በሰማይ የሚኖረው ነው። ሙሴ በምድረ በዳ እባቡን እንደ ሰቀለው የሰው ልጅ እንዲሁ ይሰቀል ዘንድ አለው፡፡ያመነበት ሁሉ ለዘለዓለም ሕያው ሆኖ እንዲኖር እንጂ እንዳይጠፋ፣ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘለዓለም ሕይወትን እንዲያገኝ እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን ቤዛ አድርጎ እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶታልና” እንዳለ እርሱ ምድራዊ ያይደለ ሰማያዊ ነው። (ዮሐ.፫፥፲፩-፲፮) “ተጠምቀ ሰማያዊ በእደ መሬታዊ” ስለ ፍቅሩ በፈጠረው የተጠመቀ ሰማያዊ ነው።
ጾመ ድጓው የሚጀምረውም እንዲህ በማለት ነው፤ “ዘወረደ እምላዕሉ፣ አይሁድ ሰቀሉ…. እግዚአ ኩሉ ዘየሐዩ በቃሉ፤ ….በቃሉ የሚያድነውን ከላይ የወረደውን የሁሉን ጌታ አይሁድ ሰቀሉት…”
ዘወረደ
በዚህ ሳምንት የቃል ርደት፣ የወልድ ልደት፣ የአዳም ድኅነት ቢነገርም እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ግን ከሰማይ የወረደ ሰማያዊ፣ በክብር ያረገ በኩረ ትንሣኤ መሆኑ አይዘነጋም፡። ለዚህም ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ “እውነት እውነት እልሃለሁ፥ የምናውቀውን እንናገራለን፤ ያየነውንም እንመሰክራለን፥ ነገር ግን ምስክርነታችንንም አትቀበሉትም። በምድር ያለውን ስንነግራችሁ ካላመናችሁኝ፥ በሰማይ ያለውን ብነግራችሁ እንዴት ታምኑኛላችሁ? ከሰማይ ከወረደው የሰው ልጅ በቀር ወደ ሰማይ የወጣ የለም፥ እርሱም በሰማይ የሚኖረው ነው። ሙሴ በምድረ በዳ እባቡን እንደ ሰቀለው የሰው ልጅ እንዲሁ ይሰቀል ዘንድ አለው፡፡ያመነበት ሁሉ ለዘለዓለም ሕያው ሆኖ እንዲኖር እንጂ እንዳይጠፋ፣ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘለዓለም ሕይወትን እንዲያገኝ እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን ቤዛ አድርጎ እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶታልና” እንዳለ እርሱ ምድራዊ ያይደለ ሰማያዊ ነው። (ዮሐ.፫፥፲፩-፲፮) “ተጠምቀ ሰማያዊ በእደ መሬታዊ” ስለ ፍቅሩ በፈጠረው የተጠመቀ ሰማያዊ ነው።
ጾመ ድጓው የሚጀምረውም እንዲህ በማለት ነው፤ “ዘወረደ እምላዕሉ፣ አይሁድ ሰቀሉ…. እግዚአ ኩሉ ዘየሐዩ በቃሉ፤ ….በቃሉ የሚያድነውን ከላይ የወረደውን የሁሉን ጌታ አይሁድ ሰቀሉት…”
ዘወረደ የዐቢይ ጾም የመጀመሪያ ሳምንት ነው። ስያሜውም የቅዱስ ያሬድ ነው። ትርጉሙም “ከሰማያት የወረደ” ማለት ነው። ቅድመ ዓለም ከአባቱ ከአብ የተወለደ ፣ድኅረ ዓለም ከድንግል ማርያም የተወለደ ነው። ስም አጠራሩ ያለና የነበረ፣ እግዚአብሔር፣ በፈቃዱ ዓለምን ለማዳን የመምጣቱን ምሥጢር የምንረዳበት ሳምንት ነው። ይህ የመጀመሪያው ሳምንት ‹ጾመ ሕርቃል› እየተባለም ይጠራል፡፡ ሕርቃል (ኤራቅሊዮስ) በ፮፻፲፬ ዓ.ም የነበረ የቤዛንታይን ንጉሥ ነው፡፡ለክርስቲያኖች ባደረገው ርዳታ ምክንያት አንድ ሳምንት ጾመውለት ነበር፡፡ ዛሬም ድረስ ጾመ ሕርቃል እየተባለ ይጠራል፡፡ ሙሉ ታሪኩ በፍትሐ ነገሥት ትርጓሜ አንቀጽ ፲፭ ላይ ይገኛል፡፡
በዚህ ሳምንት ቤተ ክርስቲያን ስለ ጾም ጥቅምና እንዴት መጾም እንዳለብን ታስተምረናለች፡፡ቅዱስ ያሬድ በጾመ ድጓው “አከለክሙ መዋዕል ዘኃለፈ ዘተቀነይክሙ ለግዕዘ ሥጋክሙ፤ ለሥጋቸሁ ፈቃድ የተገዛችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃችኋል፤ ከአሁን በኋላ ግን ጹሙ፣ ጸልዩ ለእግዚአብሔር ተገዙ” እያለ የጾም አዋጅ ያውጃል። ጾም ፈቃደ ሥጋን ለፈቃደ ነፍስ፣ ፈቃደ ነፍስን ለፈቃደ እግዚአብሔር የምናስገዛበት መንፈሳዊ መሣሪያ ነው፡፡
ጾሙ በሚጀመርበት ሰንበት በሚሰበከው ምስባክ እንዲህ ብሎ ያሳስበናል፤ “ለእግዚአብሔር በፍርሃት ተገዙ፣ በረዓድም ደስ ይበላችሁ” ጾም ከምግብና ከመጠጥ እንዲሁም ከሌሎች ምቾቶችና ደስታዎች ከመከልከል ያለፈ ጥልቅ ትርጉም ያለው ተግባር ነው። (መዝ.፪፥፲፩-፲፪) “ንጹም ጾመ ወናፍቅር ቢጸነ ከመ ያብርህ ብርሃነ ስብሐቲሁ በላዕሌነ፤ (የእግዚአብሔር) የክብሩ ብርሃን በላያችን ላይ ያበራ ዘንድ ጾምን እንጹም፤ወንድማችንንም እንውደድ” እንዲል። (ጾመ ድጓ)
በዘወረደ እሑድ የሚነበቡት ምንባባትም ይህንን የጾምን ጸጋ የያዙ ናቸው።
“ነገር ግን ፈጣሪያችን የምትበልጠውን ጸጋ ይሰጣል፤ ስለዚህም “እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፤ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል” ይላል፡፡ እንግዲህ እግዚአብሔርን እሺ በሉት፤ ሰይጣንን ግን እንቢ በሉት፤ ከእናንተም ይሸሻል፡፡ እግዚአብሔርን ቅረቡት፤ ይቀርባችሁማል፤ እናንተ ኃጥኣን እጆቻችሁን አንጹ፤ ሁለት አሳብም ያላችሁ እናንተ ልባችሁን አጥሩ፡፡ እዘኑና አልቅሱ፤ ሳቃችሁን ወደ ልቅሶ÷ ደስታችሁንም ወደ ኀዘን መልሱ፡፡ በእግዚአብሔር ፊት ራሳችሁን ዝቅ አድርጉ፤ እርሱም ከፍ ከፍ ያደርጋችኋል፡፡” (ያዕ.፬፥፮-፲)
“በውኑ እንግዲህ በስሙ እናምን ዘንድ የከንፈሮቻችን ፍሬ የሚሆን የምስጋና መሥዋዕትን በየጊዜው ለእግዚአብሔር ልናቀርብ አይገባንምን? ነገር ግን ለድሆች መራራትን፥ ከእነርሱም ጋር መተባበርን አትርሱ፤ እንዲህ ያለው መሥዋዕት እግዚአብሔርን ደስ ያሰኘዋልና፡፡” (ዕብ.፲፫፥፲፭-፲፮)
በጾም የተጠቀሙ ቅዱሳንን እያሰብን ለጾም እንድንተጋም ወደ እነርሱ እንድንመለከት ቤተ ክርስቲያን ታስተምራለች፡፡“ ልባችሁ በመብል ያይደለ በጸጋ ቢጸና ይበልጣልና፤ በዚያ ይሄዱ የነበሩ እነዚያ አልተጠቀሙምና።” (ዕብ.፲፫፥፱) ሳምንቱ በሚጀምርበት ሳምንት የሚነበበው የቅዱስ ጳውሎስ መልእክት እንዲህ ይላል፡፡ ጾመ ድጓው አባቶቻችን ያገኙትን በረከት እንደምናገኝበት ሲገልጽ “የእግዚአብሔር የክብሩ ብርሃን በላያችን ላይ ያበራ ዘንድ ጾምን እንጹም፤ ወንድሞቻችንም እንውደድ፤ ኤልያስ በጾም ወደ ሰማይ አርጓልና፤ዳንኤልም ከአናብስት አፍ ድኗልና፡፡”
ጾም ፈቃደ ነፍስን በፈቃደ ሥጋ ለማሠልጠን የአጋንንት ኃይል ለመቋቋም የሚያስችል የክርስቲያኖች ጋሻ በመሆኑ በሃይማኖት ለሚመሩ ምእመናን እጅግ አስፈላጊና ከምንም በላይ የሕይወታቸው መርሕ መሆን እንደሚገባ ቅዱስ ጳውሎስ በመልእክቱ እንዲህ በማለት ያስተምራል፡፡ ” አሁንም ወንድሞቻችን በዚህ በሥጋችን ሳለን ፈቃደ ሥጋችንን ልንሠራ አይገባም፤ ፈቃደ ሥጋቸውን የሚሠሩ ሰዎች በወዲያኛው ዓለም ምውታን ናቸውና፡፡ የሥጋችሁን ፈቃድ በነፍሳችሁ ፈቃድ ድል ከነሣችሁት ለዘለዓለም ሕያዋን ትሆናላችሁ፡፡ የነፍሳቸውን ፈቃድ የሚሠሩ ሰዎች ሁሉ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸውና፡፡" (ሮሜ ፰፥፲፪-፲፬)
ጾም አበው ቅዱሳን ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በጊዜ ቀምረው፣ በበታ ወስነው፣ በሁኔታ ገድበው... ባስቀመጡልን ወቅት ከእህልና ከውኃ በመከልከልና ሰውነትን በማድከም ብቻ ሳይሆን ለስሕተት ከሚዳርጉ ነገሮችና ቦታዎች ተቆጥቦ በጸሎት መትጋትም እጅጉን አስፈላጊ ነው፡፡ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊትም ይህንን እውነታ በተመለከተ እንዲህ ይላል፡፡ “እኔ ግን እዘንልን፤ ለምንልን ባሉኝ ጊዜ ማቅ ምንጣፍ ለብሼ አዘንኩላቸው፤ ሰውነቴን በጾም አደከምኩዋት፤ ልመናዬም እኔም ወደመጥቀም ተመለሰችልኝ፡፡” (መዝ. ፴፬/፴፭፥፲፫)
ጾም ከሥነ ምግባራት ሕግ አንዱ በመሆኑ እንኳንስ ያልተፈቀደውን የተፈቀደውም ቢሆን የማይጠቅም ከሆነ ፈጽሞ በመተው ለእግዚአብሔር ያለንን ፍጹም ፍቅር የምናስመሰክርበት ምሥጢር ነው፡፡
ጾም ከመብልና ከመጠጥ ጋር የተያያዘም በመሆኑ መብል ጊዜያዊ ስለሆነ ማለትም በዚህ ዓለም እስካለን ብቻ የምንገለገልበት እንጂ ዘለዓለማዊ ስላይደለ ለጊዜያዊ መብልና መጠጥ ምክንያት ከሃይማኖት ሥነ ምግባር እንዳንወጣ ቅዱሳን አባቶቻችን ሐዋርያት ሲመክሩ “መብል በእግዚአብሔር ዘንድ ግዳጅ አይፈጽምልንም ወደ እግዚአብሔር አያቀርበንም፤ ብንበላም አይረባንም፤ አይጠቅመንም፤ ብንተወውም አይጎዳንም” በማለት ሲመክሩን ቅዱስ ጳውሎስም የመብልና የሆድ ጊዜያዊነት አስመልክቶ እንዲህ በማለት አስተምሯል፡፡ (፩ኛቆሮ.፰፥፰)
“ሁሉ ነገር ተፈቅዶልኛል፤ ሁሉ ግን አይጠቅመኝም፡፡ ሁሉ ተፈቅዶልኛል በእኔ ላይ ግን አንድ ነገር እንኳን አይሠለጥንብኝም፡፡ መብል ለሆድ ነው ሆድም ለመብል ነው፡፡ እግዚአብሔር ግን ሁለቱንም ያሳልፋቸዋል”፤ (፩ኛቆሮ.፮፥፲፪-፲፫) “ለሚጠፋ ምግብ አትሥሩ፤ ይልቅስ የሰው ልጅ ለሚሰጣችሁ የዘለዓለም ሕይወት ስለሚሆን ምግብ ሥሩ” እንደ ተባለ (ዮሐ. ፮፥፳፯) ካለን ጊዜ ለመንፈሳዊ ሕይወታችን ጊዜ በመስጠት ቢበሉት የማያስርበውን፣ ቢጠጡት የማያስጠማውን፣ የዘለዓለም ሕይወት የምናገኝበትን ሥጋ እና ደሙን ተቀብለን መንግሥቱን እንድንወርስ ቅዱስ ፈቃዱ ይሁንልን።
በዚህ ሳምንት ቤተ ክርስቲያን ስለ ጾም ጥቅምና እንዴት መጾም እንዳለብን ታስተምረናለች፡፡ቅዱስ ያሬድ በጾመ ድጓው “አከለክሙ መዋዕል ዘኃለፈ ዘተቀነይክሙ ለግዕዘ ሥጋክሙ፤ ለሥጋቸሁ ፈቃድ የተገዛችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃችኋል፤ ከአሁን በኋላ ግን ጹሙ፣ ጸልዩ ለእግዚአብሔር ተገዙ” እያለ የጾም አዋጅ ያውጃል። ጾም ፈቃደ ሥጋን ለፈቃደ ነፍስ፣ ፈቃደ ነፍስን ለፈቃደ እግዚአብሔር የምናስገዛበት መንፈሳዊ መሣሪያ ነው፡፡
ጾሙ በሚጀመርበት ሰንበት በሚሰበከው ምስባክ እንዲህ ብሎ ያሳስበናል፤ “ለእግዚአብሔር በፍርሃት ተገዙ፣ በረዓድም ደስ ይበላችሁ” ጾም ከምግብና ከመጠጥ እንዲሁም ከሌሎች ምቾቶችና ደስታዎች ከመከልከል ያለፈ ጥልቅ ትርጉም ያለው ተግባር ነው። (መዝ.፪፥፲፩-፲፪) “ንጹም ጾመ ወናፍቅር ቢጸነ ከመ ያብርህ ብርሃነ ስብሐቲሁ በላዕሌነ፤ (የእግዚአብሔር) የክብሩ ብርሃን በላያችን ላይ ያበራ ዘንድ ጾምን እንጹም፤ወንድማችንንም እንውደድ” እንዲል። (ጾመ ድጓ)
በዘወረደ እሑድ የሚነበቡት ምንባባትም ይህንን የጾምን ጸጋ የያዙ ናቸው።
“ነገር ግን ፈጣሪያችን የምትበልጠውን ጸጋ ይሰጣል፤ ስለዚህም “እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፤ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል” ይላል፡፡ እንግዲህ እግዚአብሔርን እሺ በሉት፤ ሰይጣንን ግን እንቢ በሉት፤ ከእናንተም ይሸሻል፡፡ እግዚአብሔርን ቅረቡት፤ ይቀርባችሁማል፤ እናንተ ኃጥኣን እጆቻችሁን አንጹ፤ ሁለት አሳብም ያላችሁ እናንተ ልባችሁን አጥሩ፡፡ እዘኑና አልቅሱ፤ ሳቃችሁን ወደ ልቅሶ÷ ደስታችሁንም ወደ ኀዘን መልሱ፡፡ በእግዚአብሔር ፊት ራሳችሁን ዝቅ አድርጉ፤ እርሱም ከፍ ከፍ ያደርጋችኋል፡፡” (ያዕ.፬፥፮-፲)
“በውኑ እንግዲህ በስሙ እናምን ዘንድ የከንፈሮቻችን ፍሬ የሚሆን የምስጋና መሥዋዕትን በየጊዜው ለእግዚአብሔር ልናቀርብ አይገባንምን? ነገር ግን ለድሆች መራራትን፥ ከእነርሱም ጋር መተባበርን አትርሱ፤ እንዲህ ያለው መሥዋዕት እግዚአብሔርን ደስ ያሰኘዋልና፡፡” (ዕብ.፲፫፥፲፭-፲፮)
በጾም የተጠቀሙ ቅዱሳንን እያሰብን ለጾም እንድንተጋም ወደ እነርሱ እንድንመለከት ቤተ ክርስቲያን ታስተምራለች፡፡“ ልባችሁ በመብል ያይደለ በጸጋ ቢጸና ይበልጣልና፤ በዚያ ይሄዱ የነበሩ እነዚያ አልተጠቀሙምና።” (ዕብ.፲፫፥፱) ሳምንቱ በሚጀምርበት ሳምንት የሚነበበው የቅዱስ ጳውሎስ መልእክት እንዲህ ይላል፡፡ ጾመ ድጓው አባቶቻችን ያገኙትን በረከት እንደምናገኝበት ሲገልጽ “የእግዚአብሔር የክብሩ ብርሃን በላያችን ላይ ያበራ ዘንድ ጾምን እንጹም፤ ወንድሞቻችንም እንውደድ፤ ኤልያስ በጾም ወደ ሰማይ አርጓልና፤ዳንኤልም ከአናብስት አፍ ድኗልና፡፡”
ጾም ፈቃደ ነፍስን በፈቃደ ሥጋ ለማሠልጠን የአጋንንት ኃይል ለመቋቋም የሚያስችል የክርስቲያኖች ጋሻ በመሆኑ በሃይማኖት ለሚመሩ ምእመናን እጅግ አስፈላጊና ከምንም በላይ የሕይወታቸው መርሕ መሆን እንደሚገባ ቅዱስ ጳውሎስ በመልእክቱ እንዲህ በማለት ያስተምራል፡፡ ” አሁንም ወንድሞቻችን በዚህ በሥጋችን ሳለን ፈቃደ ሥጋችንን ልንሠራ አይገባም፤ ፈቃደ ሥጋቸውን የሚሠሩ ሰዎች በወዲያኛው ዓለም ምውታን ናቸውና፡፡ የሥጋችሁን ፈቃድ በነፍሳችሁ ፈቃድ ድል ከነሣችሁት ለዘለዓለም ሕያዋን ትሆናላችሁ፡፡ የነፍሳቸውን ፈቃድ የሚሠሩ ሰዎች ሁሉ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸውና፡፡" (ሮሜ ፰፥፲፪-፲፬)
ጾም አበው ቅዱሳን ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በጊዜ ቀምረው፣ በበታ ወስነው፣ በሁኔታ ገድበው... ባስቀመጡልን ወቅት ከእህልና ከውኃ በመከልከልና ሰውነትን በማድከም ብቻ ሳይሆን ለስሕተት ከሚዳርጉ ነገሮችና ቦታዎች ተቆጥቦ በጸሎት መትጋትም እጅጉን አስፈላጊ ነው፡፡ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊትም ይህንን እውነታ በተመለከተ እንዲህ ይላል፡፡ “እኔ ግን እዘንልን፤ ለምንልን ባሉኝ ጊዜ ማቅ ምንጣፍ ለብሼ አዘንኩላቸው፤ ሰውነቴን በጾም አደከምኩዋት፤ ልመናዬም እኔም ወደመጥቀም ተመለሰችልኝ፡፡” (መዝ. ፴፬/፴፭፥፲፫)
ጾም ከሥነ ምግባራት ሕግ አንዱ በመሆኑ እንኳንስ ያልተፈቀደውን የተፈቀደውም ቢሆን የማይጠቅም ከሆነ ፈጽሞ በመተው ለእግዚአብሔር ያለንን ፍጹም ፍቅር የምናስመሰክርበት ምሥጢር ነው፡፡
ጾም ከመብልና ከመጠጥ ጋር የተያያዘም በመሆኑ መብል ጊዜያዊ ስለሆነ ማለትም በዚህ ዓለም እስካለን ብቻ የምንገለገልበት እንጂ ዘለዓለማዊ ስላይደለ ለጊዜያዊ መብልና መጠጥ ምክንያት ከሃይማኖት ሥነ ምግባር እንዳንወጣ ቅዱሳን አባቶቻችን ሐዋርያት ሲመክሩ “መብል በእግዚአብሔር ዘንድ ግዳጅ አይፈጽምልንም ወደ እግዚአብሔር አያቀርበንም፤ ብንበላም አይረባንም፤ አይጠቅመንም፤ ብንተወውም አይጎዳንም” በማለት ሲመክሩን ቅዱስ ጳውሎስም የመብልና የሆድ ጊዜያዊነት አስመልክቶ እንዲህ በማለት አስተምሯል፡፡ (፩ኛቆሮ.፰፥፰)
“ሁሉ ነገር ተፈቅዶልኛል፤ ሁሉ ግን አይጠቅመኝም፡፡ ሁሉ ተፈቅዶልኛል በእኔ ላይ ግን አንድ ነገር እንኳን አይሠለጥንብኝም፡፡ መብል ለሆድ ነው ሆድም ለመብል ነው፡፡ እግዚአብሔር ግን ሁለቱንም ያሳልፋቸዋል”፤ (፩ኛቆሮ.፮፥፲፪-፲፫) “ለሚጠፋ ምግብ አትሥሩ፤ ይልቅስ የሰው ልጅ ለሚሰጣችሁ የዘለዓለም ሕይወት ስለሚሆን ምግብ ሥሩ” እንደ ተባለ (ዮሐ. ፮፥፳፯) ካለን ጊዜ ለመንፈሳዊ ሕይወታችን ጊዜ በመስጠት ቢበሉት የማያስርበውን፣ ቢጠጡት የማያስጠማውን፣ የዘለዓለም ሕይወት የምናገኝበትን ሥጋ እና ደሙን ተቀብለን መንግሥቱን እንድንወርስ ቅዱስ ፈቃዱ ይሁንልን።
"ተወዳጁ ልጅሽ እንዲመግበኝ ትለምኝልኝ ዘንድ እማጸንሻለሁ"
ቅዱስ ባስልዮስ
እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። የመድኃኒት እናት ሆይ በመዓልትም በሌሊትም አማላጅ ትሆኝኝ ዘንድ እሰግድልሻለሁ። እመቤቴ ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ ከእርሱ የሚገኘውን ኃይልን ይሰጠኝ ዘንድ ከአንቺ ወደ ተወለደው ልጂሽ እንድትለምኝልኝ እማጸናለሁ። በመወለዱ ድኅነት የተገባሽ ሆነሻልና። በሔዋን ውድቀት ሆነ። አብ በመላእክት አለቃ በቅዱስ ገብርኤል አማካኝነት ሰላምን የላከልሽ እመቤቴ ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። ሰላምታን ሰጠሽ ሰገደልሽም። ጸጋን የተመላሽ ሆይ እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነውና ሰላምታ ይገባሻል። እነሆ ትጸንሻለሽ ልጅም ትወልጃለሽ፣ ስሙንም አማኑኤል ትይዋለሽ። የልዑል ኃይል ይጸልልሻል፤ ከአንቺ የሚወለደውም ቅዱስ ነው፤ እርሱም የልዑል ልጅ ይባላል አለሽ።
በተቀደሰው ስሙ ኅሊናዬን ልቡናዬን እንዲቀድስ ትለምኝው ዘንድ እማጸንሻለሁ። ንጽሕት ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። የሕይወት ቃል ከአንቺ ሰው ይሆን ዘንድ በሥጋ ከአንቺ ይወለድ ዘንድ የተገባሽ የመድኃኒት እናት እመቤታችን ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። ከአንቺ በመዋሐዱም እኛ ዳንን። እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። በእናታቸው ማሕፀን ሕፃናትን የሚስላቸው ከአባቱ እና ከመንፈስ ቅዱስ ጋርም ሁሉን የፈጠረው በማሕፀንሽ የተቀረጸብሽ የብርሃን እናት ሆይ እሰግድልሻለሁ። ረቂቅ ድንቅ ምሥጢርን ዓለምንም ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣውን እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እለምንሻለሁ። በመንፈሳዊ ልደት ይወልደኝ ዘንድ ወደ እርሱ ዓለምና አዳኝ ወደ ሆነች ዕውቀት ከፍ ያደርገኝ ዘንድ ወደ እርሱ እንድትለምኝልኝ እለምንሻለሁ፣ አማጸንሻለሁ።
የሕይወት መገኛ የነገሥታት ንጉሥ የባለሥልጣናቱ ባለሥልጣን የአምላኮችን አምላክ በበረት ያስተኛሽው እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። አዳኝ ስለሆነው ስለስምሽ እንዲረዳኝ ትለምኝልኝ ዘንድም ወደ አንቺ እለምናለሁ፤ እማልዳለሁም። በማየቱ አዳምንና ከእርሱ ጋር ያሉትን ሁሉ ነጻ ያወጣውን በክንድሽ የታቀፍሽው እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ።
በረቂቅ መመልከቱ እንዲመግበኝ ከሰይጣን መሰናክልም እንዲያድነኝ ትለምኝልኝ ዘንድ እለምንሻለሁ፤ እማጸንሽማለሁ። ዓለማትን ሁሉ ለሚመግበው ጡትሽን ያጠባሽው የመድኃኒት እናት እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ፤ የሰማይ ኃይላት የሚመገቡትም ከእርሱ ነው። ነፍሴን በፈቃዱ ከጸጋው ይመግባት ዘንድ ወደ እርሱ እንድትለምኝልኝ እማጸንሻለሁ።
እመቤቴ ድግል ማርያም ሆይ ተወዳጁ ልጅሽ እንደ ፍጹም ፈቃዱ እንዲመግበኝ በየጊዜው በየሰዐቱ አማላጅ ሁኚኝ። ይህችም ወደ እርሱ የምትለምኝውን ልመና የተመላች መጽሐፍ ናት ። የለመንሁትን ሁሉ እርሱ ያደርግልሻልና። ኃጢአቴን ይቅር ይለኝ ዘንድ ወደ እርሱ እንድትለምኝልኝ እማጸንሻለሁ። ሰላምን ስለሰጠሽ ስለ አብ ከአንቺ ስለተወለደው አንቺንም ስለተዋሐደው ከአንቺም ሰው ስለሆነው ስለወልድ ፣ ስለቀደሰሽ፣ ከሦስቱ ቅዱስ ለአንዱ ማደሪያ ለመሆን እስከሚገባሽ ድረስ ስላነጻሽ ስለመንፈስቅዱስም እለምንሻለሁ። አገልጋይሽን ተወዳጁ ልጅሽ እንዲመግበኝ ትለምኝልኝ ዘንድ እማጸንሻለሁ። ለዘለዓለሙ አሜን።
ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያ
ለበዓለ ኪዳኗ እንኳን አደረሰን።
ዲ/ን ብርሀኑ አድማስ
ቅዱስ ባስልዮስ
እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። የመድኃኒት እናት ሆይ በመዓልትም በሌሊትም አማላጅ ትሆኝኝ ዘንድ እሰግድልሻለሁ። እመቤቴ ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ ከእርሱ የሚገኘውን ኃይልን ይሰጠኝ ዘንድ ከአንቺ ወደ ተወለደው ልጂሽ እንድትለምኝልኝ እማጸናለሁ። በመወለዱ ድኅነት የተገባሽ ሆነሻልና። በሔዋን ውድቀት ሆነ። አብ በመላእክት አለቃ በቅዱስ ገብርኤል አማካኝነት ሰላምን የላከልሽ እመቤቴ ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። ሰላምታን ሰጠሽ ሰገደልሽም። ጸጋን የተመላሽ ሆይ እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነውና ሰላምታ ይገባሻል። እነሆ ትጸንሻለሽ ልጅም ትወልጃለሽ፣ ስሙንም አማኑኤል ትይዋለሽ። የልዑል ኃይል ይጸልልሻል፤ ከአንቺ የሚወለደውም ቅዱስ ነው፤ እርሱም የልዑል ልጅ ይባላል አለሽ።
በተቀደሰው ስሙ ኅሊናዬን ልቡናዬን እንዲቀድስ ትለምኝው ዘንድ እማጸንሻለሁ። ንጽሕት ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። የሕይወት ቃል ከአንቺ ሰው ይሆን ዘንድ በሥጋ ከአንቺ ይወለድ ዘንድ የተገባሽ የመድኃኒት እናት እመቤታችን ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። ከአንቺ በመዋሐዱም እኛ ዳንን። እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። በእናታቸው ማሕፀን ሕፃናትን የሚስላቸው ከአባቱ እና ከመንፈስ ቅዱስ ጋርም ሁሉን የፈጠረው በማሕፀንሽ የተቀረጸብሽ የብርሃን እናት ሆይ እሰግድልሻለሁ። ረቂቅ ድንቅ ምሥጢርን ዓለምንም ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣውን እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እለምንሻለሁ። በመንፈሳዊ ልደት ይወልደኝ ዘንድ ወደ እርሱ ዓለምና አዳኝ ወደ ሆነች ዕውቀት ከፍ ያደርገኝ ዘንድ ወደ እርሱ እንድትለምኝልኝ እለምንሻለሁ፣ አማጸንሻለሁ።
የሕይወት መገኛ የነገሥታት ንጉሥ የባለሥልጣናቱ ባለሥልጣን የአምላኮችን አምላክ በበረት ያስተኛሽው እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። አዳኝ ስለሆነው ስለስምሽ እንዲረዳኝ ትለምኝልኝ ዘንድም ወደ አንቺ እለምናለሁ፤ እማልዳለሁም። በማየቱ አዳምንና ከእርሱ ጋር ያሉትን ሁሉ ነጻ ያወጣውን በክንድሽ የታቀፍሽው እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ።
በረቂቅ መመልከቱ እንዲመግበኝ ከሰይጣን መሰናክልም እንዲያድነኝ ትለምኝልኝ ዘንድ እለምንሻለሁ፤ እማጸንሽማለሁ። ዓለማትን ሁሉ ለሚመግበው ጡትሽን ያጠባሽው የመድኃኒት እናት እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ፤ የሰማይ ኃይላት የሚመገቡትም ከእርሱ ነው። ነፍሴን በፈቃዱ ከጸጋው ይመግባት ዘንድ ወደ እርሱ እንድትለምኝልኝ እማጸንሻለሁ።
እመቤቴ ድግል ማርያም ሆይ ተወዳጁ ልጅሽ እንደ ፍጹም ፈቃዱ እንዲመግበኝ በየጊዜው በየሰዐቱ አማላጅ ሁኚኝ። ይህችም ወደ እርሱ የምትለምኝውን ልመና የተመላች መጽሐፍ ናት ። የለመንሁትን ሁሉ እርሱ ያደርግልሻልና። ኃጢአቴን ይቅር ይለኝ ዘንድ ወደ እርሱ እንድትለምኝልኝ እማጸንሻለሁ። ሰላምን ስለሰጠሽ ስለ አብ ከአንቺ ስለተወለደው አንቺንም ስለተዋሐደው ከአንቺም ሰው ስለሆነው ስለወልድ ፣ ስለቀደሰሽ፣ ከሦስቱ ቅዱስ ለአንዱ ማደሪያ ለመሆን እስከሚገባሽ ድረስ ስላነጻሽ ስለመንፈስቅዱስም እለምንሻለሁ። አገልጋይሽን ተወዳጁ ልጅሽ እንዲመግበኝ ትለምኝልኝ ዘንድ እማጸንሻለሁ። ለዘለዓለሙ አሜን።
ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያ
ለበዓለ ኪዳኗ እንኳን አደረሰን።
ዲ/ን ብርሀኑ አድማስ