آخرین پست‌های FMC (Fana Media Corporation) (@waltatveth) در تلگرام

پست‌های تلگرام FMC (Fana Media Corporation)

FMC (Fana Media Corporation)
This is Fana Media Corporation’s (FMC) official Telegram channel.

For more updates please visit https://shorturl.at/ehosX https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured
49,147 مشترک
44,692 عکس
231 ویدیو
آخرین به‌روزرسانی 08.03.2025 20:32

آخرین محتوای به اشتراک گذاشته شده توسط FMC (Fana Media Corporation) در تلگرام

AddisWalta - AW

26 Nov, 17:21

267

ሩሲያ 5 ከፍተኛ የእንግሊዝ ባለስልጣናት ወደ አገሯ እንዳይገቡ እገዳ ጣለች

ኅዳር 17/2017 (አዲስ ዋልታ) ሩሲያ 5 ከፍተኛ የእንግሊዝ ባለስልጣናትና በርካታ የፓርላማ አባላት ወደ አገሯ እንዳይገቡ ማገዷን አስታወቀች።

እግድ የተጣለባቸው ባለስጣናት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሯ አንጌላ ሬይነር፣ የአገር ውስጥ ሚኒስትሯ ይቬት ኩፐር፣ የኢነርጂ ሚኒስትሩ ኤድ ሚልባንድ፣ የጤና ሚኒስትሩ ዌስ ስቲሪንግ፣ ቻንስለሯ ሬቸል ሪቭስ እና በርካታ የፓርላማ አባላት ናቸው።

ሩሲያ ይህን ውሳኔ ያስተላለፈችው ባለስልጣናቱ ጸረ-ሩሲያ አቋም ያንጸባርቃሉ በሚል መሆኑ ስካይ ኒውስ ዘግቧል።

የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ የእንግሊዝ መንግስት ለዓለም መረጋጋት ሲል የያዘውን ስልታዊ ፍጥጫ እንዲተው ተደጋጋሚ ጥሪ አቅርበን ነበር ብሏል።

ይህ ባለመሆኑ ሩሲያ በጸፋዋ ግለሰቦች፣ የእንግሊዝ ፖለቲካዊ ተቋማት፣ ወታደራዊ ክፍሎች፣ የተራቀቁ ቴክኖሎጂ ኢንዱስትሪዎች እና ጸረ-ሩሲያ አቋም ሲያንጸባርቁ የነበሩ ሚዲያዎች ሁሉ ወደ አገሬ እንዳይገቡ ስትል ውሳኔ አስተላልፋለች ተብሏል።

ሩሲያና ዩክሬን ጦርነት ውስጥ መግባታቸውን ተከትሎ አንግሊዝ በሩሲያ ላይ ማዕቀብ ጥላ ነበረ ሲሆን ሩሲያ በምላሹ የአሁኑን የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ኪዬር ስታርመርን ጨምሮ በዴቪድ ላሚ እና በርካታ የወግ አጥባቂ የፖለቲካ አመራሮች ላይ እገዳ ማስተላለፏ ይታወሳል።

ሩሲያና እንግሊዝ ከሰሞኑ ከፍተኛ ፍጥጫ ውስጥ የገቡ ሲሆን ሩሲያ በሰላይነት የጠረጠረችውን እንግሊዛዊ ዲፕሎማት ከአገሯ አባርራለች።

ከዚህ በተጨማሪ እንግሊዝ ለዩክሬን ሚሳኤል በመስጠትና ሩሲያ ላይ ጥቃት እንደትሰነዝር መፍቀዷ ሞስኮን ያስቆጣ እንደነበርና ፕሬዝዳንት ቭላስሚር ፑቲን ለዚህ ድርጊቷ አንግሊዝን በሚሳኤል ልንመታ እንችላለን ሲሊ ማስጠንቀቃቸው ይታወሳል።
AddisWalta - AW

26 Nov, 15:17

1,672

አየር መንገዱ ከአዲስ አበባ ሮም በሳምንት ሶስት ቀናት ተጨማሪ በረራ ሊጀምር ነው

ኅዳር 17/2017 (አዲስ ዋልታ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአዲስ አበባ ሮም በሳምንት ሶስት ቀናት ተጨማሪ የቀን በረራ ሊጀምር መሆኑን አስታወቀ።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ጣሊያኗ ከተማ የሚየደርገው ተጨማሪ የቀን በረራ ሕዳር 22 ቀን 2017 ጀምሮ መሆኑን የአየር መንገዱ መረጃ አመላክቷል።

አየር መንገዱ ተጨማሪ የቀን በረራዎቹ መጀመር ለደንበኞቹ የበረራ አማራጭ ሰዓት ለማቅረብ እንደሚያስችለው በመረጃው ተጠቅሷል።
AddisWalta - AW

26 Nov, 13:03

2,737

ሩሲያ የእንግሊዝን ዲፕሎማት ልታባርር ነው

ኅዳር 17/2017 (አዲስ ዋልታ) ሩሲያ በአገሯ የሚገኝን አንድ የእንግሊዝ ዲፕሎማት ልታባርር መሆኗን አስታወቀች።

ሞስኮ ዲፕሎማቱን ለማባረር እንደምክንያትነት ያቀረበችው ሰውየው ወደ ሩሲያ ለመግባት ባቀረበው የዲፕሎማትነት ማረጋገጫ ፎርም ላይ ሃሰተኛ መረጃ በመስጠቱ ነው ብላለች።

የሩሲያ ደህንነት ተቋም ዲፕሎማቱ ያቀረበው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን እንደደረሰበትና ይህም የስለላ እና የማሳሳት ተግባር ነው ብሏል።

ተቋሙ ባወጣው መግለጫ በኤምባሲው የፖለቲካ ክፍል ምክትል ጸኃፊ የሆነው ግለሰብ ወደ ሩሲያ ለመግባት ሆን ብሎ የተሳሳተ መረጃ በመስጠቱ ፈቃዱን መሰረዙን አስታውቋል።

አሁን የዲፕሎማቲክ ፈቃዱ የተሰረዘበት እንግሊዛዊ ባለፈው ነሐሴ ሩሲያ ባባረረችው ሌላው የእንግሊዝ ዲፕሎማት ምትክ ወደ ሞስኮ የተላከ እንደነበር ፋይናንሺያል ታይምስ ዘግቧል።
AddisWalta - AW

26 Nov, 12:23

2,683

#ማስታወቂያ

#InfinixEthiopia

የኢንፊኒክስን Note, Hot, Zero ስማርት ስልኮችን እና የኢንፊኒክስ TVን ሲገበያዩ አብሮት ካለ ወዳጅ ዘመድ ወይም ጓደኛ ጋር በመረጡት ስፍራ ፎቶ በመነሳት #InfinixEthiopia የሚለውን ሃሽ ታግ በመጠቀም የማህበራዊ ገጾት ላይ በመለጠፍ የዛንዚባር የቢዝነስ ክላስ ደርሶ መልስ የአውሮፕላን ቲኬት ፣ የኢንፊኒክስ ስማርት ቲቪ ፣ የኢንፊኒክስ ላፕቶፕ እንዲሁም ሌሎች አጓጊ ሽልማቶችን ያሸንፉ፡፡

መመሪያ

1. የኢንፊኒክስ ኢትዮጵያን ፌስ ቡክ ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገጾችን ፎሎው ያድርጉ፡፡
2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማህበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የኢንፊኒክስ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስቶት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡
3. #InfinixEthiopia የሚለውን ሃሽታግ መጠቀሞን አይርሱ፡፡

Tag ሲያደርጉ ለ Facebook @InfinixMobileEthiopia (https://web.facebook.com/@InfinixMobileEthiopia) ፣ ለ Instagram @infinixethiopia (https://www.instagram.com/infinixethiopia/) ለ TikTok @Infinixet (https://www.tiktok.com/@infinixet) እና ለ Telegram @Infinixeth (https://t.me/InfinixEth) ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።
AddisWalta - AW

26 Nov, 10:01

2,904

ለውጡና የለውጡ ፍሬዎች
AddisWalta - AW

26 Nov, 07:06

3,469

በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ 9 ጨዋታዎች ይካሄዳሉ

ኅዳር 17/2017 (አዲስ ዋልታ) ዛሬ ምሽት በ5ኛ ዙር የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ መርሃ ግብር 9 ጨዋታዎች ይካሄዳሉ።

በተለያዩ የአውሮፓ ከተሞች ከሚካሄዱት ጨዋታዎች መካከል ባየርሙኒክ ከፒኤስጂ፣ ኢንተር ሚላን ከአርቢ ላይፕዚንግ እና ስፖርቲንግ ከአርሰናል የሚያደርጓቸው ጨዋታዎች በጉጉት ይጠበቃሉ።

ስሎቫን ባራትስላቫ ከ ኤሲ ሚላን እና ስፓርታ ፕራግ ከ አትሌቲኮ ማድሪድ የሚያደርጉት ጨዋታ ምሽት 2:45 ሲደረግ ሌሎቹ ሁሉም ቀሪ 7 ጨዋታዎች ምሽት 5:00 ሲል ይጀምራሉ።
AddisWalta - AW

25 Nov, 16:32

4,453

የፖርቹጋልና የሮማንያ አምባሳደሮች ብርሃን የዓይነ ስውራን 2ኛ ደረጃ አዳሪ ትምህርት ቤትን ጎበኙ

ኅዳር 16/2017(አዲስ ዋልታ)  የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ በኢትዮጵያ የፖርቹጋል አምባሳደር ልዊሳ ፍራጎሶ እና የሮማንያ አምባሳደር ጂሊያ ፓታቺ ብርሃን የአይነስውራን 2ኛ ደረጃ አዳሪ ትምህርት ቤትን አስጎብኝተዋል።

በቀዳማዊት እመቤት ጽህፈት ቤት ዘላቂ ለውጥን ለማምጣት መሰረት በማድረግ እየተተገበሩ ካሉ ፕሮጀክቶች ውስጥ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በመገንባት ጥራት ያለው ትምህርትን ተደራሽ ማድረግ አንዱ ነው፡፡

በዚህ መሰረት ከተገነቡ ትምህርት ቤቶች ውስጥ በኢትዮጵያ በዘመናዊነቱ ብቸኛ የሆነውን ብርሃን የአይነስውራን 2ኛ ደረጃ አዳሪ ትምህርት ቤትን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ በኢትዮጵያ ለፖርቹጋል አምባሳደር  ልዊሳ ፍራጎሶ እና በኢትዮጵያ የሮማንያ አምባሳደር ጂሊያ ፓታቺን  ማስጎብኘታቸውን የቀዳማዊት እመቤት ጽህፈት ቤት መረጃ አመላክቷል፡፡
AddisWalta - AW

25 Nov, 14:35

4,240

ከተሜነት ከተፈጥሮ የተዋደደበት የመስህብ ሥፍራ ጉለሌ
#ሀገሬ

ገጠር አይደለም፤ መሃል ከተማ ነው። በአንፃሩ የዱር አራዊትን ያቀፈ ጥቅጥቅ ደን መገኛም ነው። ሰማይ ጠቀስ ህንፃዎች በሚታነጹበት በዚህ ሥፍራ በአቅራቢያው በብዝሃ ሕይወት ስብጥር የተሰናሰለ የዕፅዋት፣ የዛፎች እና የዱር እንስሳት ዝሪያዎች ይመለከታሉ።

የመኪኖች ድምፅ ሳያቋርጥ በሚያጓራበት በቅርብ ርቀት በወፎች ዝማሬ እና በነፋሻማ አየር አዕምሮዎን ያድሳሉ። ይህ የመስህብ ሥፍራ በመድናዋ የተቋቋመው በ2002 ዓ.ም ሲሆን 705 ሄክታር ስፋት ያለው ነው። ይህ ውብ የዕጽዋት ማዕከል በስፋቱ ትልቅ፤ በብዝሃ ሕይወት ስብጥሩ ደግሞ አስደናቂ ተፈጥሮ የታደለ ነው።

በመድናዋ አዲስ አበባ ሰሜናዊ ዳርቻ ጉለሌ ክፍለ ከተማ የሚገኘው እና በጥቅጥቅ ደን የተሸፈነው ማዕከሉ ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶችንም ይሰጣል። ለአገር በቀል ዕፅዋት ጥበቃ እና ምርምር ሥራ እንዲሁም የአካባቢ ሥነ ምህዳር እንዲጠበቅ የማድረግ ድርሻውን እየተወጣም ይገኛል፡፡

በዚህም በሀገር በቀል ዕፅዋት እና ለአደጋ ተጋላጭ በሆኑ የዕፅዋት ዝርያዎች ላይ ትኩረት አድርጎ እየሠራ ነው። የምጣኔ ሀብታዊ ጠቀሜታ ያላቸው እና ለሕክምና የሚውሉ የዕፅዋት ዝርያዎችም ከማዕከሉ የትኩረት አቅጣጫዎቹ መካከል የሚጠቀሱ ናቸው፡፡
👇👇
https://web.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/posts/pfbid0ihAFDxHRsQTvYckVaim16FDLjTUTnVTzf1bJszdYPHraAPN9BcppTEu4YFH1ETTxl
AddisWalta - AW

25 Nov, 12:56

4,434

ፒያሳ የተከሰተውን የእሳት አደጋ በቁጥጥር ስር ለማዋል ርብርብ እየተደረገ ነው

ኅዳር 16/2017(አዲስ ዋልታ) አራዳ ክፍለ ከተማ ደጃች ውቤ ሰፈር በቻይና ጃንጉዜ የኮንስትራክሽን ስራ ድርጅት ላይ ያጋጠመውን የእሳት አደጋ በቁጥጥር ስር ለማዋል የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ርብርብ እያደረጉ ነው።
AddisWalta - AW

25 Nov, 09:01

4,678

ኢትዮጵያ የአፍሪካን ችግር በአፍሪካ መፍታት ይገባል የሚል ጽኑ አቋም አላት - ፕሬዝዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ

ኅዳር 16/2017 (አዲስ ዋልታ) የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ኢትዮጵያ የአፍሪካን ችግር በአፍሪካ መፍታት ይገባል የሚለውን ጽኑ አቋሟን በተግባር የገለጠ መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ ገለጹ።

የአፍሪካ አህጉራዊ የሰላም ኮንፈረንስ "የበለፀገችና ሰላማዊ አፍሪካን እንገንባ" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።

የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ በዚሁ ወቅት እንዳሉት ኢትዮጵያ የአፍሪካን ችግር በአፍሪካ መፍታት ይገባል የሚል ጽኑ አቋም አላት።

በአፍሪካ ሰላምና ደህንነትን ለማረጋገጥ ምቹ ሁኔታን እየፈጠረች መሆኑን የገለጹት ፕሬዝዳንቱ ኢትዮጵያ ከሰላም ስምምነቱ ባለፈ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ በማድረግ በቀጣናው ንግድና ኢንቨስትመንት እንዲስፋፋ ገንቢ ሚና ተወጥታለች ብለዋል።
👇👇
https://web.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/posts/pfbid09P1oD7sdK7Kc1EWVivqnAvRkgqiaZC5RqQp3aHLaGfta1acB2TEmAg3FKWQh94ZTl