آخرین پست‌های FMC (Fana Media Corporation) (@waltatveth) در تلگرام

پست‌های تلگرام FMC (Fana Media Corporation)

FMC (Fana Media Corporation)
This is Fana Media Corporation’s (FMC) official Telegram channel.

For more updates please visit https://shorturl.at/ehosX https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured
49,147 مشترک
44,692 عکس
231 ویدیو
آخرین به‌روزرسانی 08.03.2025 20:32

کانال‌های مشابه

Addis Standard
20,020 مشترک

آخرین محتوای به اشتراک گذاشته شده توسط FMC (Fana Media Corporation) در تلگرام

AddisWalta - AW

25 Nov, 07:18

4,339

በጋዛ ሰርጥ ባለፈው አንድ ዓመት ከ1 ሺሕ በላይ ዶክተሮችና ነርሶች ተገደሉ

ኅዳር 16/2017 (አዲስ ዋልታ) በእስራኤል ሐማስ ጦርነት ምክንያት ካለፈው ዓመት ጀምሮ በጋዛ ሰርጥ በደረሱት ጥቃቶች ከ1 ሺሕ በላይ ዶክተሮች እና ነርሶች መገደላቸውን የጋዛ ባለስልጣናት ገልጸዋል።

ከ310 በላይ ሌሎች የህክምና ባለሙያዎች መታሰራቸው እና በእስር ቤቶች መገደላቸውንም ተናግረዋል።

የህክምና ቁሳቁሶች፣ የጤና ልዑካን ቡድን እና የቀዶ ህክምና ባለሙያዎች ወደ ጋዛ እንዳይገቡ ሁኔታዎች አመቺ ሳይሆኑ መቀጠላቸውን አስረድተዋል ሲል አናዶሉ ዘግቧል።

በጦርነቱ ምክንያት የሟቾች ቁጥር እስካሁን ከ44 ሺሕ አልፏል።
AddisWalta - AW

24 Nov, 18:33

4,911

ማንችስተር ዩናይትድ በአዲሱ አሰልጣኝ ነጥብ ጣለ

ኅዳር 15/2017 (አዲስ ዋልታ) ሩበን አሞሬዬም በመጀመሪያ የማንችስተር ዩናይትድ አሰልጣኝነት ጨዋታው ነጥብ ጣለ።

ማንችስተር ምሽት 1 ከ30 ላይ ከኤፕስዊች ታውን ጋር ያደረገውን ጨዋታ 1 ለ 1 ተለያይቷል።

ውጤቱን ተከትሎ ቡድኑ በ16 ነጥቦች በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ ላይ 12 ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
AddisWalta - AW

24 Nov, 17:04

4,923

ሌስተር ሲቲ አሰልጣኙን ስቲቭ ኩፐርን አሰናበተ

ኅዳር 15/2017 (አዲስ ዋልታ) ሌስተር ሲቲ እ.ኤ.አ ከሰኔ 2024 ጀምሮ በ3 ዓመት ኮንትራት ቀጥሯቸው የነበሩትን አሰልጣኝ ስቲቭ ኩፐርን ከኃላፊነት አሰናበተ።

የ44 ዓመቱ ስቲቭ ኩፐር ሌስተርን ለ5 ወራት በአሰልጣኝነት መርተው ቡድኑ በደረጃ ሰንጠረዥ በ10 ነጥቦች ከወራጅ ቀጣናው በሁለት ነጥቦች ብቻ ከፍ ብሎ በ16ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።

ትናንት ከቸልሲ ጋር የተጫወተው ቡድናቸው 2 ለ 1 በሆነ ውጤት የተሸነፈ ሲሆን አሰልጣኙ ቡድኑን በ15 ጨዋታዎች ብቻ ከመሩ በኋላ ከኃላፊነታቸው ተሰናብተዋል።

የአሰልጣኙ ስንብት በፕሪሚዬር ሊጉ ከቀድሞው የማንችስተር ዩናይትድ አሰልጣኝ ኤሪክ ቴን ሃግ ስንብት ቀጥሎ ሁለተኛው ነው።
AddisWalta - AW

16 Nov, 08:07

264

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ምርጥ የአፍሪካ ካርጎ አየር መንገድ ሽልማትን አገኘ

ኅዳር 7/2017 (አዲስ ዋልታ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎና ሎጂስቲክስ አገልግሎት በ“አሬቢያን ካርጎ አዋርድስ” ምርጥ የአፍሪካ ካርጎ አየር መንገድ ሽልማትን ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ ተቀዳጅቷል።

የሽልማት አሰጣጥ መርኃ ግብሩ በዱባይ ከተማ የተካሄደ ሲሆን መድረኩ በገልፍ ሀገራት ለሚሰጡ ምርጥ የአየር እቃ ጭነት አገልግሎቶች እውቅና የሚሰጥበት ነው።
AddisWalta - AW

16 Nov, 05:56

1,399

ማይክ ታይሰን በጄክ ፖውል ተሸነፈ

ኅዳር 7/2017 (አዲስ ዋልታ) ዝነኛው አሜሪካዊ የከባድ ሚዛን ቦክሰኛ ማይክ ታይሰን ራሱን ከፕሮፌሽናል ውድድር ካገለለ ከ19 ዓመታት በኋላ ወደ ውድድር ተመልሶ ከ27 ዓመቱ ጄክ ፖውል ጋር ቢጋጠምም ተሸንፏል።

ጄክ ፖውል ጋር በኤቲ ኤንድ ቲ ስታዲየም በተደረገው ፍልሚያ ማይክ ታይሰንን በማሸነፍ በቦክስ ሕይወቱ ትልቁን ድል ማግኘት ችሏል።

የ27 ዓመቱ ፖል ፍልሚያውን ድል በማድረጉ እስካሁን ካደረጋቸው 11 ውድድሮች በአንዱ ብቻ የተሸነፈ ሆኗል።
AddisWalta - AW

15 Nov, 16:48

3,088

ታላቁ ሩጫ ሠላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ጥምር የፀጥታ ኃይል ዝግጅት ማጠናቀቁን አስታወቀ

ኅዳር 6/2017 (አዲስ ዋልታ) በአዲስ አበባ የሚካሄደው የዘንድሮው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ፍፁም ሠላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ጥምር የፀጥታ ኃይል ዝግጅቱን አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን አስታወቀ።

ለ24ኛ ጊዜ ከፊታችን እሁድ በሚካሄደው ታላቁ ሩጫ 50 ሺሕ ተሳታፊዎች ይታደሙበታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ሠላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ሊዲያ ግርማ በልዩ ልዩ የአደባባይ ኩነቶች ላይ ጥምር የፀጥታ ኃይሉ በሚያከናውነው ተግባር ከተማችን ፍፁም የተረጋጋ ሠላም እንዲኖራት እና ፀጥታ የሰፈነባት እንድትሆን ማድረግ እንደተቻለ ገልጸዋል፡፡

ከዚህ በፊት የተከናወኑ የአደባባይ ኩነቶች በሠላም እንዲጠናቀቁ የከተማዋ ነዋሪ ያበረከተው አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑን አንስተው የዘንድሮው የታላቁ ሩጫ ስፖርታዊ ውድድርም በሠላም ተጀምሮ በሠላም እንዲጠናቀቅ ህብረተሰቡ ከፀጥታ አካላት ጎን በመቆም የተለመደ ትብብሩን እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽነር ጌቱ አርጋው በበኩላቸው ስፖርታዊ ውድድሩ የከተማችንን መልካም ገፅታ የሚያጎላ መሆኑን ከአዲስ አበባ ፖሊስ የተገኘው መረጃ አመላክቷል።

ከስፖርታዊ ተልዕኮው ውጭ ማንኛውም ዓይነት የተቃረነ መልዕክትን ማስተላለፍ ፈፅሞ የተከለከለ መሆኑንና የፀጥታ ኃይሉም ጥብቅ ቁጥጥር እንደሚያደርግ አስታውቀው ውድድሩ በጨዋነት መንፈስ መካሄድ ይኖርበታል ብለዋል።
AddisWalta - AW

15 Nov, 12:35

3,884

አመንዝራነት እና ቅጣቱ
#ሕግ_ይዳኘኝ

ባለትዳሮች ከትዳራቸው አጋር ውጭ የአመንዝራነት ተግባር ፈጸሙ የሚሉ ወሬዎች በተለያ ጊዜያት ይሰማሉ፡፡

አንድ ባለትዳር በፀና ጋብቻ ላይ ታስሮ ሳለ ከሌላ ሰው ጋር የግብረ ሥጋ ግንኙነት የፈጸመ እንደሆነ በኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ በአመንዝራነት ወንጀል ይቀጣል፡፡

በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 652 መሠረት በተበደለው ባለትዳር የግል አቤቱታ አቅራቢነት ጥፋተኛው በእስራት ወይም በመቀጮ ይቀጣል፡፡

እያወቀ ሕጋዊ ጋብቻ ካለው ሰው ጋር ባመነዘረው ሰው ላይም ይሄው ቅጣት ተፈጻሚ ይሆናል፡፡

አቤት ባይ የአመንዝራነት ተግባሩ እንዲፈጸም የገፋፋ ወይም የተስማማ ወይም ይቅርታ ያደረገ ወይም ከዚሁ ጋር ጥቅምን ያገኘ እንደሆነ ግን ጥፋተኛው በወንጀል አይጠየቅም፡፡

በብርሃኑ አበራ
AddisWalta - AW

15 Nov, 12:02

3,539

አየር መንገዱ ምርጥ በ2024 የቢዝነስ ተጓዦች ሽልማት ተሸለመ

ኅዳር 6/2017 (አዲስ ዋልታ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ2024 የቢዝነስ ተጓዦች ሽልማት ምርጥ የአፍሪካ አየር መንገድ ተብሎ ተሸለመ።

አየር መንገዱ ምርጥ የአፍሪካ አየር መንገድ በመባል ለአምስት ተከታታይ ዓመት ሽልማት መቀዳጀቱንም የአየር መንገዱ መረጃ አመላክቷል።
AddisWalta - AW

15 Nov, 11:53

3,308

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የባሕር ዳር ከተማ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ

ኅዳር 6/2017 (አዲስ ዋልታ) የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ከርዕሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ እና ከሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን በባሕር ዳር ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።

በጉብኝታቸውም የአባይ ድልድይ፣ ግዙፉን የባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ግንባታ፣ የባሕር ዳር ከተማ የኮሪደር ልማት እና ሌሎችንም የልማት እንቅስቃሴዎች ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ በክልሉ ወቅታዊ የሰላም ሁኔታዎች እና የሕዝቡን ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ በሚከናወኑ ሥራዎች ላይ ከክልሉ ከፍተኛ መሪዎች ጋር ተወያይተዋል።

የውይይቱ ዓላማም የክልሉ ሰላም በዘላቂነት እንዲረጋገጥ፣ ሕዝቡም የተረጋጋ ኑሮን እንዲመራ እና ሙሉ አቅሙን በልማት ሥራዎች ላይ እንዲያውል ለማድረግ ያለመ መሆኑን አሚኮ ዘግቧል።

ሰላም ወዳዱ የአማራ ሕዝብ ከጸጥታ መዋቅሮች ጋር በመቀናጀት ሰላሙን የሚያደፈርሱ አካላትን መከላከል፣ ሰላምንም ማስፈን እንደሚገባ ገልጸዋል።
AddisWalta - AW

15 Nov, 11:02

3,379

ኢትዮጵያ ለሶማሌላንድ የመልካም ምኞት መልዕክት አስተላለፈች

ኅዳር 6/2017 (አዲስ ዋልታ) ኢትዮጵያ ለሶማሌላንድ መንግሥትና ሕዝብ የመልካም ምኞት መልዕክት አስተላለፈች።

በመልዕክቱም ሶማሌላንድ ሠላማዊና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ በማካሄዷ ለሀገሪቱ መንግሥትና ሕዝብ የመልካም ምኞት መልዕክት ማስተላለፏን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል።

የምርጫው ሂደትትም የሶማሌላንድ መንግስት በሳልና ዴሞክራሲያዊ መሆኑን የሚያሳይ እንደሆነ ጠቁሟል።