THIKVAH-ETHIOPIA @thikvahethiopia Channel on Telegram

THIKVAH-ETHIOPIA

@thikvahethiopia


ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

THIKVAH-ETHIOPIA (Amharic)

ቲክቫህ-ኢትዮጵያ በማኅበረሰብም ሲመሰብም ይህ ቤተሰብ በአባላት በመለጠ፣ መልዕክትን በመጠበቅ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብን እየመሰባሰቢ ነው። በቲክራና በአፋንከሆሞም በመከላከል ከአባሉም አንዳንድ መረጃዎች እንደሚያቀርቡ ካደንሽ አዝማሚነት ያስነሳል። እና በቀጥታ ባለቦቻችሁ ላይ ትክክለኛው መረጃን ለማያገኙ ይረዳል።

THIKVAH-ETHIOPIA

10 Feb, 17:35


#ጥቆማ

ብሩህ እናት !

ሴቶችን እስከ ግማሽ ሚሊዮን ብር የሚያሸልም “ ብሩህ እናት ” የተሰኘ የፈጠራ ውድድር መዘጋጀቱ ተገለጸ።

የሴቶችን ድካም የሚያቀሉ ቴክኖሎጂ ተኮር የፈጠራ ሀሳቦችን በማቅረብ ለሚያሸንፉ ሴቶች ቋሚ ችግር ፈቺ ተቋም የሚሆኑበትና ከ100 ሺሕ እስከ 500 ሺሕ ብር የሚያሸልም ውድድር ለሴቶች ብቻ ማዘጋጀቱን የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ገልጿል።

የፈጠራ ውድድሩ የተዘጋጀው ከኢንተርፕርነሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት፣ ከእናት ባንክ፣ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሴቶች ጉዳይ ጋር በጋራ በመሆን መሆኑን መስሪያ ቤቱ ዛሬ በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።

በዚህም “ ማሰልጠን፣ መሸለም፣ ማብቃት ” በሚል መሪ ሀሳብ በኢትዮጵያ በሁሉም አካባቢ ላሉ ሴቶች እድሉ እንጀተመቻቸ፣ ከተመዘገቡት 5ዐ የተሻለ ሀሳብ ላቀረቡ ተወዳዳሪዎች ስልጠና እንደሚሰጥ አመልክቷል።

“ ፕሮግራሙ ላይ የላቀ የፈጠራ ሀሳብ ያላቸው ሴቶች ተወዳዳሪዎች መከካልም 10 ለሚሆኑት አሸናፊ የቢዝነስ ሀሳብ ፈጣሪዎች እውቅናና የገንዘብ ሽልማት እንዲያገኙ ይደረጋል ” ሲል መስሪያ ቤቱ ጠቁሟል።

ለውድድሩ አሸናፊዎች ሽልማቱ ምንድን ነው ?

ከተመዝጋቢዎቹ የተሻለ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ሀሳብ ያቀረቡ 1ዐ ተወዳዳሪዎች እንደየደረጃቸው ከ100 ሺሕ እስከ 500 ሺሕ ሽልማት መዘጋጀቱ ተገልጿል።

በገለጻው መሠረት፣ ለ1ኛ አሸናፊ 500 ሺሕ፣ ለ2ኛ አሸናፊ 400 ሺሕ፣ ለ3ኛ አሸናፊ 300 ሺሕ፣ ለ4ኛ አሸናፊ 200 ሺሕ፣ ለ5ኛ አሸናፊ 150 ሺሕ እንዲሁም ከ6 እስከ 10ኛ ላሉ አሸናፊዎች 100 ሺሕ ብር ይሸለማሉ።

በመግጫው የተገኘው እናት ባንክ በበኩሉ፣ ለአሸነፉበት ሴቶች ቴክኖሎጂ ተግባራዊነት የሚያስፈልገውን የገንዘብ ብድር እንደሚያመቻች ገልጿል።

ምዝገባው መቼ ተጀምሮ ? መቼ ይጠናቀቃል ?

ምዝገባው ከዛሬ (ሰኞ የካቲት 3 ቀን 2017 ዓ/ም ጅምሮ እስከ የካቲት 24 ቀን 2017 ዓ/ም ደረስ እንደሚከናወን ተነግሯል።

ለተወዳዳሪዎች የቡት ካምፕ ስልጠና ከመጋቢት 8 እስከ መጋቢት 19/2017 ዓ/ም እንደሚሰጥ እና የውድድሩ ማጠቃለያና ሽልማት መጋቢት 20 ቀን 2017 ዓ/ም እንደሚሆን የተመላከተ ሲሆን፣ ለተጨማሪ መረጃ 0948874085፣ 0913154944 መደወል ይቻላል ተብሏል።

#ThikvahEthiopiaFamilyAA

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

10 Feb, 14:34


" የግለሰቧ የአየር መንገድ ግቢ ውስጥ የልደት ምስል ቀረጻ ከተቋሙ አመራሮች እውቅና ውጭ የተደረገ ነው " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሰሞኑ በማህበራዊ ሚዲያ ሲዘዋወር የነበረው የልደት ምስል ቀረጻ ከተቋሙ ማናጅመንት እውቅና ውጭ የተደረገ መሆኑን አስታወቀ፡፡

አየር መንገዱ ባወጣው መግለጫ " አንዲት ግለሰብ በአውሮፕላኑ መወጣጫ ደረጃ ላይ የተለያዩ ዲኮሮችን በማድረግ የተነሳችው ፎቶ ሲዘዋወር ታይቷል ፤ ግለሰቧ የተነሳችው ለጥገና በቆመ አውሮፕላን ላይ ነው " ብሏል።

" ድርጊቱ ከተቋሙ አመራሮች እውቅና ውጭ የተደረገ ነው " ሲልም ገልጿል።

" ይህ ክስተት ስላስከተለው ማንኛውም አይነት ችግር ወይም አሉታዊ ግንዛቤ ከልብ እናዝናለን " ያለው ተቋሙ " በአሁኑ ወቅት ጉዳዩን እየመረመርን ነው የተቋሙም አሰራር ሳይከተሉ ይህንን ዝግጅት ባዘጋጁት ላይ የእርምት እርምጃ ይወሰዳል " ሲል አሳውቋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቪዲዮው ላይ ከምትታየው ግለሰብ ምንም አይነት ክፍያ እንዳልተቀበለ እና ከግለሰቧ ጋር ምንም አይነት የውል ስምምነት እንደሌለው ህዝቡ ይወቅልኝ ብሏል።

አየር መንገዱ ውስጥ ይህ ሁሉ ሲፈፀም እና ሲከናወን የአየር መንገዱ አካላት የት ነበሩ ? ያመቻቸውስ ማነው ? የሚለው ትልቁ ጥያቄ ነው።

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

10 Feb, 14:33


“ በ6 ወራት ለ66 ሺህ 741 የማህበረሰብ ክፍሎች የሥነ አዕምሮ ህክምና አገልግሎት ተሰጥቷል ” - አማኑኤል ሆስፒታል

አማኑኤል የአዕምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በ2017 ዓ/ም፣ “ በ6 ወራት ለ66,741 የማህበረሰብ ክፍሎች የሥነ አዕምሮ ህክምና አገልግሎት ተሰጥቷል ” ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

በዚህም 64,256 የተመላላሽ፣ 257 ህፃናት የአዕምሮ፣ 410 ሰዎች የሱስ ህክምና መሰጠቱን የሆስፒታሉ የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ አቶ አብዩ የኔአለም ገልጸዋል።

እንዲሁም ለ240 የተሃዲሶ፣ ለ921 የአስተኝቶ፣ ለ1,564 ሰዎች ደግሞ የድንገተኛ የህክምና አገልግሎት መሰጠቱን አቶ አብይ አስረድተዋል።

በተመላላሽ፣ በአስተኝቶና በድንገተኛ የህክምና አገልግሎት ከተሰጣቸው ታካሚዎች መካከል 36,300 የጤና መድን ተጠቃሚዎች መሆናቸው ተመልክቷል።

በተመላላሽና በተኝቶ ህክምና በስድስት ወራት የወንጀልና የፍትሃ ብሔር ተመርማሪ ለሆኑ 413 የህብረተሰብ ክፍሎች የህክምና አገልግሎት መስጠቱም ተገልጿል።

“ በሆስፒታሉ አማካኝ አስተኝቶ የቆይታ ጊዜ በ2016 ዓ/ም ከነበረው 36 ቀናት በ2017 ዓ/ም 6 ወራት ወደ 33 ቀናት ማድረስ፣ የአልጋ የመያዝ ምጣኔም በመጀመሪያ 6 ወራት መጨረሻ ላይ 85.2% መፈጸም ተችሏል ” ተብሏል።

ሆስፒታሉ ከ1930 ዓ/ም ጀምሮ በተኝቶ፣ በተመላላሽ፣ በድንገተኛ፣ የጭንቅላት ምርመራ፣ በኤሌክትሪክ ንዝረት፣ በህፃት የአዕምሮ፣ ከህግ ጋር የተያያዙ የአዕምሮ ህክምናና ምርመራ እንዲሁም የነርቭ ህክምናዎችን እየሰጠ የሚገኝ አንጋፋ ሆስፒታል ነው።

#ThikvahEthiopiaFamilyAA

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

10 Feb, 14:33


“ ገዢው ብልጽግና እንደ ፓርቲም አንቆጥረውም ” - አዲሱ  የመኢአድ ተሿሚ ፕሬዜዳንት

መላው ኢትዮጵያ አንድነት ደርጅት (መኢአድ) በቅርቡ ፓርቲውን ለስድስት ዓመታት በመሩት አቶ ማሙሸት አማረ ምትክ አቶ አብርሃም ጌጡን ፕሬዜዳንት አድርጎ ሾሟል።

አንዲሱ የፓርቲው ፕሬዜዳንትም ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገዢውን ፓርቲ በብርቱ ተችተዋል።

" ጠባብ " የሚል ትችት የሚሰነዘርበት የኢትዮጵያ የፓለቲካ ምህዳርን ለመቋቋም ምን ያህል ተዘጋጅተዋል ? ተብሎ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ የቀረበላቸው ተሿሚው ብርቱ ትችት ያነገበ ምላሽ ሰጥተዋል።

አዲሱ የመኢዓድ ተሿሚ ፕሬዚዳንት አቶ አብርሃም ጌጡ ምን አሉ ?

“ እንደ ተመራጭ መሪ በድንገት አይደለም የመጣሁት፡፡ ለ26 አካካቢ ዓመታት ፖልቲካሊ አክቲቭ ሆኘ ረጅም ትግል እያደረኩ ነበር፡፡ ከዚህ አንፃር የመኢአድ አባላትም ከፍተኛውን ድምጽ ሰጥተውኛል፡፡

በኢትዮጵያ ፖለቲካ መጻዒው እጣ ፋንታችን ስናየው እውነት ለመናገር የአሁኑን ገዢ ፓርቲ ፓርቲ ነው ብለን ለመናገርም ይከብዳል፡፡ ገዢ ፓርቲ የሚባለው ሁሉንም እኩል የሚገዛ ነውና፡፡ መልቲ ፓርቲ ሲስተም የተገነባባቸው ዓለማት የሚመሩት በዴሞክራሲ ህግ ነው፡፡

የዴሞክራሲ ስርዓት የሚያድግ የነበረው ደግሞ በዚያች አገር በሚኖረው የፖለቲካ ኃይል ነው፡፡ የኛ አገር የፖለቲካ ሂደትና ባህሪ ምን ነበር ? አሁንስ ምን እየሆንን ነው? ብለን ስናስብ ገዢ ፓርቲ አለ ማለት አይቻልም፡፡ 

ገዢ ፓርቲ የፖለቲካ ስፔሱ ነጻ ሆኖ የፓለቲካ አክተሮች ሜዳው ላይ ወርደው፣ አማራጭ ሃሳባቸውን ለህዝብ ሰጥተው መራጩም ተመራጩም ተሳትፎ ወደ ስልጣን የሚመጣበት መሆን አለበት፡፡

የመረጠውንም ያልመረጠውንም እኩል ማስተዳደር፣ ኃላፊነቱን፣ ግዴታውን ሲወጣ ገዢ ፓርቲ ይባላል፡፡ ከዚህ አንፃር ገዢውን ብልጽግና እንደ ፓርቲም አንቆጥረውም፡፡ ፓርቲ በውስጡ ብዙ ነገሮችን መያዝ አለበት።

የፓለቲካ ፓርቲ ማለት የራሱ ፕሮግራም፣ ርዕዮተዓለም፣ አደረጃጀት ያለው ነው፡፡ አሁን ስልጣን ላይ ያለው የፖለቲካ ኃይል ፋንዳሜንታል የሆኑ ነገሮች በውስጡ የሉትም፡

ዝም ብሎ የተደራጀ፣ የሕዝብ፣ ብሶትና ትግል በአጋጣሚ አስፈንጥሮ ወስዶ ቤተ መንግስት ያስቀመጠው የፖለቲካ ኃይል ነው፡፡ ህዝቡ ከነበረበት የለውጥ ፍላጎት ተነስቶ መርጦታል፡፡ 

ከተመረጠ በኋላ ግን አገሪቱ ወዴት እየሄደች ነው? ምንድን ነው የሆነችው? ሰርቫይዝ ማድረግ የምትችልብት መሰረታዊ አገራዊ ምሰሶዎች አሉ ወይ? ተብሎ ሲታሰብ በጣም አደጋ ነው፡፡ 

ድሮ ኢትዮጵያ መስቀልኛ ጥያቄ ገብታለች እንል ነበር። መስቀልኛ ጥያቄ የሚባለው በመስቀልኛ ቦታ ተቁሞ ግራ ቀኝ ሲታይ ነውና አሁን ግን መቆምም አይቻለም፡፡ መቆሚያ፣ መንቀሳቀሻ መሬት የለም።

የጸጥታና ሰላምን የሚያስከብር ኃይል በሌለበት ቀጣይ የአገሪቱ የፖለቲካ እጣፋንታ ምን ይሆናል? ለሚለው ጥያቄ ፈጣሪ እጁን ዘርግቶ ኢትዮጵያን ካልጠበቃት አሁን ባለው ተጨባጪ ሁኔታ ከባድ አደጋ ላይ ናት።

ይህን ብለን ግን በዝምታ ቁጭ እንልም፡፡ መኢዓድ ፓርቲ ኢትዮጵያዊነትን በማስቀደም በቀጣይ አሸናፊ ሆኖ ሊወጣ ብቻ ሳይሆን ሌሎችንም የአንድንት ኃይሎች የሚባሉትን አሰብስብን የፖለቲካ ትግል ያደርጋል።

መንግስት የህዝብን ድምጽና ሰቆቃ አዳምጦ የፖለቲካ መፍትሄ ሊሰጥ ተቋቋመ ተቋም መሆን አለበትና አብሶሉት ሞናርኪዎች ሲያደርጉት እንደነበረው እንዲያደርግ አንፈቅድለትም፡፡ ለዚህም ብርቱ ትግል እናደርጋለን፡፡
 
ሰው ሚያሳድዱ፣ የሚያግቱ፣ በመሳሪያ የሚጨፈጭፉ አካላት ስልጣንን መከታ ሊያደርጉ ይችላሉ፡፡ ግን በየትኛውም መስኮት ሂደው መደበቅ አይችሉም፡፡ ይህን እንነግራቸዋለን። የፖለቲካ ጥበቡ ለህዝብ መፍትሄ መፈለግ ነውና እሱን እናሳያለን ” ብለዋል።

በቀጣዩ ምርጫ ተመራጭ ሆኖ ለመቅረብ ያላቸውን ዝግጅትና ፓለቲካዊ አስቻይ ሁኔታ በተመለከተ ማብራሪያ ጠይቀናቸው በሰጡን ምላሽ፣ “ የመጀመሪያ ስራችን በምርጫና ሥራ ወደ ስልጣን መምጣት ነው ” ሲሉ መልሰዋል።

“ ይህን ለማድረግ ጠንክረን እንሰራለን። ህዝቡ በቲፎዞ ካርድ መብቱን ሰጥቶ እንደአሁኑ ቤቱ እንዲፈርስ፣ ህልውናውን እንዲያጣ አናደርግም። ኢትዮጵያ በከፍተኛ ችግር እንዳለች የሚጠባ ህጻን የሚያውቀው ጉዳይ ነው፡፡ ይህንን አስተካክለን ጥሩ ተመራጮች ሆነን ለመቅረብ ዝግጅት እያደረግን ነው ” ብለዋል።

#ThikvahEthiopiaFamilyAA

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

10 Feb, 14:33


#MPESASafaricom

⛺️🗺 ሃይኪንግ ላይ ሆናችሁ ዳታ መጠቀም ፈልጋችሁ ታውቃላችሁ? እነሆ አዲስ ቅመም!

💨⚡️ የትም ይዛችሁት መሄድ የሚያስችላችሁ 3000 mah የባትሪ አቅም ያለውና አዳዲስ የቴክኖሎጂ ትሩፋቶችን ይዞ በአንዴ እስከ 8 ሰው ድረስ የሚያስጠቅመውን ልዩ ቅመም MIFIን ገዝተን ፈጣን 4G ኢንተርኔት እንጠቀም! ለ30 ቀን ከሚቆይ ነጻ 30ጊባ ዳታ ጉርሻ ጋር 😋

ከሳፋሪኮም ጋር አንድ ወደፊት⚡️
  
🔗 የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናውርድ፦ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

#SafaricomEthiopia #1Wedefit #Furtheraheadtogether

THIKVAH-ETHIOPIA

10 Feb, 14:32


#ብርሃን_ባንክ
መክፈል አልተመቸኝም የማይሉበት!

ብርሃን ስኩል_ፔይ ባሉበት ቦታ ሆነው ለልጆችዎ ትምህርት ቤት ክፍያ ሳያስቡ; በብርሃን ሞባይል ባንኪንግ ወይም ኢንተርኔት ባንኪንግ ተጠቅመው ክፍያ የሚፈፅሙበት ምቹ አገልግሎት ነው።
እንደ ስማችን ብርሃን ነው ስራችን፡፡
#schpay #berhanschoolpay #schoolfee #payment #berhanbank #bank #stressfreebanking #bankinethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

09 Feb, 19:18


#መቄዶንያ

ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው !

ትላንት የካቲት 1/2017 ዓ/ም በጀመረው የመቄዶንያ የአረጋዊያን እና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል የድጋፍ ማሰባሰብ ዘመቻ እስኩን 120,000,000 ብር ተሰብስቧል።

መቄዶንያ በሚያስገነባው ሆስፒታል ጭምር ያለው ህንፃ ለማጠናቀቅ የገንዘብ እጥረት አጋጥሞታል። ህንፃው ለማጠናቀቅ ገንዘብ ተቸግረናል። ለማጠናቀቅ ወደ 5 ቢሊዮን ብር ያስፈልጋል።

በቀጥታ ይከታተሉ 👇
https://www.youtube.com/live/q0bMjwt9PvM?feature=shared

የምትችሉትን ሁሉ ድጋፍ አድርጉ።

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

09 Feb, 12:41


🔊 #የሠራተኞችድምጽ

" ቋሚ ሠራተኞች ሆነን ሳለ በደሞዝ ማሻሻያው አልተካተትንም " - የሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ መንግስት ሠራተኞች

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ሪፎርሙን ተከትሎ የሚከሰቱ የኑሮ ዉድነትና ተያያዥ ጉዳዮችን ታሳቢ በማድረግ የመንግስት ሠራተኞች ደሞዝ ማሻሻያ ተደርጎ ከጥቅምት ወር 2017 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ የተደረገ መሆኑ ይታወቃል።

በሲዳማ ክልል፤ ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን፤ ሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ በተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች የሚሰሩ የመንግስት ሠራተኞች ግን " ከ2012 ዓ/ም ጀምሮ በቋሚነት ተቀጥረን እየሰራን ያለን ቢሆንም በአዲሱ የመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ማሻሻያ አልተካተትንም " ሲሉ ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስገብተዋል።

ቅሬታቸዉን ካደረሱን መካከል ፦
- በከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን፣
- ማዘጋጃ ቤቶች፣
- በትምህርት ዘርፍ ፣
- በሴቶችና ሕፃናት እንዲሁም በሕብረት ስራ ጽ/ቤቶች የሚሰሩ ሠራተኞች ናቸው።

" በወቅቱ በአግባቡ ማስታወቂያ ወጥቶ ተመዝግበንና ተወዳድረን ማለፋችን ተረጋግጦ የቋሚነት ደብዳቤ ተሰጥቶን ላለፉት አምስትና ስድስት ዓመታት ደሞዝ ሲከፈለን በቆየንባቸው መደቦች ላይ እየሰራን ባለንበት በአዲሱ የደሞዝ ማሻሻያ አለመካተታችን ለዘርፈ ብዙ ችግሮች ዳርጎናል " ብለዋል።

" ለወረዳዉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሃብት ልማት ጽ/ቤት እና ለክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ ቅሬታችንን በአካልና በፅሁፍ ብናቀርብም ተገቢዉ ምላሽ አልተሰጠንም ጉዳዩን ለኢትዮጵያ እምባ ጠባቂ ተቋም ለማቅረብ መረጃ እያደራጀን ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት ፤ የሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰዉ ሃብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሃይሉ አቢኖ ፥ " በወረዳዉ በ2012 ዓ/ም የነበረው አግባብነት በሌለው ቅጥር በአንድ መደብ ሶስትና አራት ሰዎችን በተደራራቢነት የመቅጠር ሁኔታዎች አሁን ለተፈጠረው ችግር ዋነኛ ምክንያት ሆኗል " ሲሉ ገልጸዋል።

ከዞኑና የክልሉ ፐብልክ ሰርቪስ ጋር በመናበብ መፍትሔ እያፈላለጉ ስለመሆኑም ጠቁመዋል።

በወቅቱ ይህን ተግባር የፈፀሙ አመራሮች እና የሰዉ ሃብት ልማት ኃላፊዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን የሚናገሩት ኃላፊዉ በወረዳዉ በዚህ መልክ ተጠቀጥረዉ በአዲሱ የደመወዝ ማሻሻያ ያልካተቱና በቀጣይ መፍትሔ የሚፈለግላቸዉ 470 በተለያዩ መስሪያ ቤቶች ዉስጥ የተለዩ ሰራተኞች ስለመኖራቸዉ አክለዋል።

የሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ፐብልክ ሰርቪስና የሰዉ ሃይል ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ በዛብህ ባርሶ በበኩላቸው በ2011 እና 2012 በአከባቢው ሕገወጥ ቅጥሮች መፈፀማቸውን ገልጸዋል።

በወረዳዉ አጣሪ ቡድን ተቋቁሞ በአዲሱ ደሞዝ ያልተካተቱንና በወረዳው ቅጥር ያልተፈፀመባቸዉ ክፍት መደቦችን የመለየት ስራ መከናወኑን አንስተዉ በሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ ብቻ 407 ክፍት መደቦች መኖራቸዉን ለማወቅ መቻሉን ገልፀዋል።

የክልሉ የበላይ አመራሮች በሚያስቀምጡት አቅጣጫ መሰረት እነዚህን ሠራተኞች በነዚህ ክፍት መደቦች የመደልደልና ሌሎችም ሕጋዊ አመራጮች በመፈለግ በአጭር ጊዜ ዉስጥ እልባት ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጉዳዩን እስከመጨረሻ ተከታትሎ መረጃውን ይልካል።

#ThikvahEthiopiaFamilyHW

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

09 Feb, 12:32


የIMF ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ ምን አሉ ?

የዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋም (IMF) ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ በኢትዮጵያ የስራ ቆይታ አድርገዋል።

በዚህም ወቅት ከጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ጋር ጨምሮ ከፌዴራል ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር መክረዋል።

የነበራቸውን ቆይታ በተመለከተ ከገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ጋር በጋራ መግለጫ ሰጥተው ነበር።

ምን አሉ ?

ዳይሬክተሯ ፤ " የኢትዮጵያ ሪፎርም ከባድ እና ጊዜ የሚወስድ ነው ፤ እባካችሁ ታገሱ " የሚል ጥሪ አቅርበዋል።

ኢትዮጵያውያን ለትዕግስት እንዲያሳዩ እና ከመንግስት የኢኮኖሚ ማሻሻያ ጥረቶች ጎን እንዲቆሙ ጠይቀዋል።

ጆርጂዬቫ ፥ " የሪፎርሙን ግቦች ለማሳካት የአንድነት አስፈላጊ ነው " ሲሉ አፅንኦት ሰጥተዋል።

" ኢትዮጵያ የተቀበለችው ሪፎርም ከባድ እና ጊዜ የሚወስድ ቢሆንም እጅግ ትልቅ ውጤት ያስገኛል " ሲሉ ተናግረዋል።

" ህዝቡ በትዕግስት እንዲጠብቅ ጥሪዬን አቀርባለሁ " ያሉት ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ " ህብረተሰቡ ከሪፎርሙ ጀርባ በመሰባሰብ በአንድነት ድጋፍ ማድረግ አለበት " ብለዋል።

ጆርጂዬቫ ፥ ኢኮኖሚውን የበለጠ አጥጋቢና ብቁ ለማድረግ ብዙ የሚሠራ ሥራ አለ " ብለው " እባካችሁ መንግሥት ሥራውን እንዲያጠናቅቅ ድጋፍ አድርጉ " የሚል ጥሪ አቅርበዋል።

የዋጋ ንረትን ለመፍታት የሚሰራው ስራ ውስብስብ መሆኑን ያልሸሸጉት ዳይሬክተራ " የዋጋ ንረትን ወደ ታች ለማውረድ ጠንካራ የገንዘብና የፊስካል ፖሊሲዎች፣ የኢኮኖሚውን የማምረት አቅም ማስፋት፣ የወጪ ንግድና የውጭ ምንዛሪ ገቢን ማሳደግ እና የግሉ ሴክተርን ማብቃት ይጠይቃል " ብለዋል።

ሌላው ያነሱት ጉዳይ በG20 የጋራ ማዕቀፍ ኢትዮጵያ እያካሄደች ያለችውን የዕዳ መልሶ ማደራጀት ድርድር በተመለከተ ነው።

ጆርጂዬቫ ፤ " የዕዳ መልሶ ማዋቀር ሂደት የመጨረሻ ደረጃ ላይ ይገኛል ፤ ከኢትዮጵያ አበዳሪዎች ጋር ባለኝ ግንኙነት ይህ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

የIMF ፕሮግራም አካል ሆነውን የታክስ እርምጃዎችን በተመለከተም ፤ የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ለብሄራዊ በጀቱ ድጋፍ ለማድረግ ወሳኝ የሆኑ የታክስ አቅሞችን መለየታቸውን ጠቁመዋል።

ጆርጂዬቫ ፥ የኢትዮጵያ አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት ዕድገት ከIMF የመጀመሪያ ትንበያዎች መብለጡን ማብራራታቸውን ዘሪፖርተር አስነብቧል።

የማኔጂንግ ዳይሬክተራ ንግግር ተከትሎ " መሬት ላይ ካለው እውነታ ጋር የሚገናኝ አይደለም " የሚሉ አስተያየቶች ሲሰጡም ተመልክተናል።

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

08 Feb, 20:10


ልታስመርቀዉ ከቤተሰቦቿ ተደብቃ የመጣች እጮኛዉን ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ የገደለዉ ግለሰብ በ20 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጣ።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን አርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ጉርባ በሚባል ቀበሌ የገዛ እጮኛዉን ጭካኔ በተሞላበት መልኩ በአሰቃቂ ሁኔታ በስለት አንገቷን በመቁረጥ ሕይወቷ እንዲያልፍ ያደረገዉ ወጣት በፅኑ እስራት መቀጣቱን የአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ም/ኢንስፔክተር ጋፋሮ ቶማስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመዉ ነሐሴ 16/2016 ዓ/ም በአርባምንጭ ከተማ ጉርባ ቀበሌ ነው።

ተከሳሽ ዮናስ ጫፊቄ የተባለው ግለሰብ የጂንካ ዩኒቨርሲቲ 1ኛ  ዓመት ተማሪ የሆነችዉን ሟች ሊዲያ ዮሐንስ እሱን ለማስመረቅ ወደ አርባ ምንጭ ከተማ በመጣችበት ተከራይቶ በሚኖርበት ቤት አሰቃቂ ድርጊቱን መፈፀሙን የምርመራ መዝገቡ ያስረዳል።

ወጣቷ " እጮኛዬ ይመረቅልኛል " በሚል ደስታ ከቤተሰቦቿ ተደብቃ ተከሳሽ ተከራይቶ ወደ ሚማርበት  ቤት መጥታ በዋዜማዉ ለምረቃዉ የሚሆኑ የዲኮር፣ የዳቦና ለስላሳ መጠጦችና በቡና ዝግጅት ቤቱን አሰማምራ በምሽቱም ግቢ ዉስጥ ያሉ ተከራዮችን ጠርተዉ ከሸኙ በኋላ ሟች ሀገር ሰላም ብላ በተኛችበት ከሌሊቱ 7 ሰዓት ገደማ እራሷን መከላከል በማትችልበት ሁኔታ በቢላዋ አንገቷን አርዶ መግደሉን የምርመራ መዝገቡን ዋቢ አድርገው ፖሊስ አዛዡ ገልፀዋል።

ፖሊስ አዛዡ አክለው እንደገለጹት ፥ በወቅቱ በተደረገዉ ማጣራትም ሆነ በክስ መዝገቡ ላይ እንደሰፈረዉ ወንጀለኛው " ወደ ዩኒቨርሲቲ በሄድሽበት ሌላ የወንድ ጓደኛ ይዘሻል " በሚል ነው በር ዘግቶ አሰቃቂ የወንጀል ድርጊቱን የፈጸመው።

ፖሊስ በዚህ ዘግናኝ ወንጀል ዙሪያ ተገቢዉን ማጣራትና ምርመራ አድርጎ ለዐቃቤ ሕግ ማቅረቡን አስታውቀዋል።

ዐቃቤ ሕግም ክስ በመመስረት ለፍርድ ቤቱ ተከሳሽ የወንጀል ድርጊቱን መፈፀሙን የሰዉ፣ የሰነድና የህክምና ማስረጃዎችን በማቅረብ አስረድቷል።

በቀረቡ ማስረጃዎች እና ምስክሮች ግራ ቀኙን ሲያጣራ የቆየዉ የጋሞ ዞን ከፍተኛዉ ፍርድ ቤት በቀን 29/5/2017 ዓም በዋለዉ ችሎት ተከሳሽ ዮናስ ጨፊቄ በተከሰሰበት በአሰቃቂ ሁኔታ ነብስ የማጥፋት ወንጀል ጥፋተኛ መሆኑን በማረጋገጥ በ20 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ መወሰኑንም ኢንስፔክተር ጋፋሮ ቶማስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

#ThikvahEthiopiaFamilyHW

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

08 Feb, 18:25


#መቄዶንያ

" ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው !! "

መቄዶንያ የአረጋዊያንና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል በሚያስገነባው ሆስፒታል ጭምር ያለው ህንፃ ለማጠናቀቅ የገንዘብ እጥረት ስለገጠመው እግዛ እንዲደረግ ለመላው ኢትዮጵያውያን ጥሪ መቅረቡ ይታወሳል።

ዛሬ “ በሰይፉ ኢቢኤስ የዩቱብ ቻነል ” ድጋፍ ማድረጊያ መርሀ ግብር እየተካሄደ ነው።

ደጋጎች ሁሉ ድጋፍ እንድታደርጉ ጥሪ እናቀርባለን።

የድጋፍ ማድረጊያ አማራጮች ከላይ ተያይዘዋል።

መቄዶንያ “ ህንፃው ለማጠናቀቅ ገንዘብ ተቸግረናል። ለማጠናቀቅ ወደ 5 ቢሊዮን ብር ያስፈልገናል ” ማለቱ አይዘነጋም።

በቀጥታ ይከታተሉ 👇
https://www.youtube.com/live/q0bMjwt9PvM?feature=shared

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

08 Feb, 16:28


#እንድታውቁት

" የመክፈያ ጊዜ እየተጠናቀቀ በመሆኑ ግብራችሁን ያልከፈላችሁ እንድትከፍሉ እናሳስባለን " -የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ

የአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መግለጫ " በተለመዶ የጣራና ግድግዳ ግብር እየተባለ የሚጠራው የቤትና ቦታ ግብር የሚከፍሉ ግብር ከፋዮች ግብሩን ያለቅጣትና ወለድ የሚከፈልበት ጊዜ እየተጠናቀቀ በመሆኑ እንድትከፍሉ እናሳስባለን " ብሏል።

በዚሁ መግለጫው ግብሩ የከተማ ቦታና ቤት ግብር በከተማ ቤት ግብር አዋጅ ቁጥር 80/1968 መሰረት የሚሰበሰብ ግብር መሆኑ መገንዘብ እንደሚገባ ያሳሰበ ሲሆን 429 ሺህ 829 ግብርከፋዮች የቤትና ቦታ ግብር ክፍያ እንዲፈፅሙ ይጠበቃል ብሏል።

የቢሮው የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፥ " ግብር ከፋይ ነዋሪዎች ያለቅጣት መክፈያው ጊዜ ሳይጠናቀቅ ከየካቲት 30 በፊት እንዲከፍሉ እና ያልከፈሉ ነዋሪዎች ግን ቅጣቱን ከነወለዱ ለመክፈል እንደሚገደዱ " ገልጸዋል።

አቶ ሰውነት " እናት ፓርቲ ካስተላለፈው መልእክት ጋር በተያያዘ እኛን የሚመለከተን ነገር የለም " ያሉ ሲሆን ለቢሮው የደረሰው ምንም አይነት የፍርድ ቤት እግድም ሆነ መመሪያ አለመኖሩን በመግለጽ " ሰው ጋር መዘናጋት ይታያል ይህ ደግሞ ለቅጣት ሊዳርጋቸው ይችላል በቀረው ጊዜ ክፍያችሁን ፈጽሙ " ሲሉ አሳስበዋል።

#ThikvahEthiopiaFamilyAA

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

08 Feb, 16:27


" ፋይናንስ ቢሮ ይግባኝ በመጠየቁ አፈጻጸሙ ከትላንትና በስቲያ ጀምሮ ታግዶ ነው ያለው " - እናት ፓርቲ

እናት ፓርቲ የአዲስ አበባ ፋይናንስ ቢሮ ከሚያዝያ 2015 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ ያደረገው የጣሪያ ግድግዳ / ንብረት ግብር መመርያ እንዲቆም የመሠረተው ክስ በፍርድ ቤት ተቀባይነት አግኝቶ መመሪያው "ተፈጻሚ ሊሆን አይገባም " ሲል ፍርድ ቤት ጥር 9 ቀን ብይን መስጠቱን ፓርቲው ማስታወቁ ይታወሳል።

ይህንንም የፍርድ ቤት ውሳኔ በጋዜጣዊ መግለጫው አሳውቆ የነበረው ፓርቲው የፋይናንስ ቢሮ ይግባኝ በመጠየቁ ምክንያት የውሳኔው አፈጻጸም ከትላንትና በስቲያ ጀምሮ መታገዱን የፓርቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሰይፈሥላሴ አያሌው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

የፓርቲው ፕሬዝዳንት በዝርዝር ለቲክቫህ በሰጡት ሃሳብ ምን አሉ ?

" ጥር 9 ቀን 6:30 ላይ ውሳኔውን ከፍተኛ ፍ/ቤት አሳልፎ 7:30 ላይ የፋይናንስ ቢሮ አቃቢ ህግ በቃለ መሃላ ' ለከፍተኛ ፍ/ቤት ፕሬዝዳንት ይግባኝ እስከምል ድረስ አፈጻጸሙ ይታገድልን ለ15 ቀንም ፓርቲው ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳይሰጥ ' አሉ።

የፍርድ ቤቱን ትእዛዝ መጠበቅ ስለነበረብን እኛም ለ15 ቀናት ጠበቅን 15 ቀኑ የሞላው አርብ ነበር ሰኞ መግለጫ ሰጠን።

በ15 ቀን ውስጥ ይግባኝ ባይጠይቁም ከትላንት በስቲያ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት አፈጻጸሙ ታግዶ እንዲቆይ በሚል ይግባኝ መጠየቃቸውን የሚገልጽ ደብዳቤ ቢሮአችን ላይ ተለጥፎ አግኝተናል።

እየተነጋገርን ያለነው ስለ ህግ ጉዳይ ነው ክፍያው ይቀጥል አይቀጥል አይደለም እኛ እያልን ያለነው ከተማ መስተዳደሩ የጣለው ግብር ከህግ አግባብ ውጪ እንደሆነ ነው መሆኑን ደግሞ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አረጋግጦልናል።

እያንዳንዱ ከህዝብ የሚሰበሰብ ሳንቲም የህግ መሰረት ሊኖረው ያስፈልጋል ይህ የጣራና ግድግዳ ግብር እየተሰበሰበ ያለው ከህግ አግባብ ውጪ ነው የሚከፈለው ገንዘብ መቆም አለበት ብለን ነው ክስ የመሰረትነው።

ፍርድ ቤቱም ክፈሉ አትክፈሉ አይደለም እያለ ያለው ነገር ግን ለክፍያ መመሪያ የነበረው በሚያዝያ 2015 የወጣው እና እንዲፈጸም የሚያስገድደው መመሪያ መሻሩን ነው የገለጸው።

በዚህም መሰረት የህግ ውሳኔ አፈጻጸም አካሄድ ቢኖረውም የከተማ መስተዳደሩ ይህንን ግብር ወደ ፊት እንዲሽረው ይጠበቃል።

የፋይናንስ ቢሮ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ቢጠይቅም የከፍተኛ ፍ/ቤትን ውሳኔ ያጸድቀዋል ብለን ነው የምናምነው ቢሽረው እንኳ ሰበር ሰሚ ችሎት በመኖሩ ጉዳዩን እስከመጨረሻው እንገፋበታለን።

የኢትዮጵያ ህዝብ 10 ሺ፣20 ሺ እና ሚሊየን ለጣራ እና ግድግዳ በሚል ከፍሎ አያውቅም እንዲህ መክፈል የተጀመረው ከ2015 ዓ/ም ጀምሮ ነው መቼም ይጀመር መመሪያው ህገ ወጥ ነው " ብለዋል።

#ThikvahEthiopiaFamilyAA

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

08 Feb, 16:23


#MPESASafaricom

ስለ M-PESA ኢትዮጵያ አዳዲስ ዜናዎች እና አገልግሎቶችን ለማወቅ ማህበራዊ ሚዲያ  ገፃችንን እንቀላቀል! 💚📲

Telegram-  https://t.me/+-cP9IxZdfKBkNTQ0
Facebook: https://www.facebook.com/share/14qsy45H7u/?mibextid=wwXIfr
Titkok- https://www.tiktok.com/@mpesa.ethiopia?_t=ZM-8tcz302wLwL&_r=1
LinkedIn- https://www.linkedin.com/company/m-pesaethiopia/about/
Instagram: https://www.instagram.com/mpesa.ethiopia/
Youtube- http://www.youtube.com/@M-PESAEthiopia
Twitter- https://x.com/m_ethiopia58462?s=21

#MPESAEthiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

08 Feb, 10:09


#USA : ከቀናት በፊት በአሜሪካ አላስካ ግዛት 9 መንገደኞችን እና 1 አብራሪን ይዞ ሲጓዝ የነበረ አነስተኛ አውሮፕላን ደብዛው ጠፍቶ ከቆየ በኃላ በአየር እና ምድር በተደረገ አሰሳ ስብርባሪው ተገኝቷል።

በአደጋው በሕይወት የተረፈ ሰው የለም።

የ3 ሰዎች አስክሬን በነፍስ አድን ሰራተኞች ተገኝቷል።

ይህ አደጋ በአሜሪካ ከ1 ሳምንት ባነሰ ጊዜ የደረሰ 3ኛው የአቬዬይሽን አደጋ መሆኑን የቪኦኤ ዘገባ ያሳያል።

በአሜሪካ፣ ፔንሲልቫኒያ ግዛት፣ አንድ አነስተኛ የሕክምና ማጓጓዣ አገልግሎት የሚሰጥ ጄት በርካታ ሕንጻዎች በሚገኙበት ሰፈር ውስጥ ተከስክሶ በህይወት የተገኘ እንደሌለ ይታወቃል።

ከዚህ አደጋ በፊት ደግሞ በዋሽንግቶን ዲሲ 60 መንገደኞች እና 4 የበረራ ሰራተኞችን የያዘ የመንገደኞች አውሮፕላን 3 ሰዎች ከያዘ የጦር ሄሊኮፕተር ጋር ተላትሞ አንድም ሰው በህይወት አለመገኘቱ መገለጹ ይታወሳል።

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

08 Feb, 10:09


" ለቅሬታችን ተገቢዉን ምላሽ ባለማግኘታችን ለርዕሰ መስተዳድሩ አቅርበናል " - የአረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ መምህራን

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ዞን አረካ ከተማ በሚገኘዉ የአረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የሚሰሩ አሰልጣኝ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች አዲሱ የደሞዝ ማሻሻያ ክፍያ " አልተከፈለንም " ሲሉ ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አድርሰዋል።

በቁጥር ከአንድ መቶ በላይ የሆኑ የኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች ለደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በአድራሻ የፃፉትንና የተፈራረሙበትን የቅሬታ ደብዳቤ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስገብተዋል።

ሰራተኞቹ በሰጡት ቃልም " መንግስት ለኑሮ ዉድነት ማካካሻ በማለት በሀገር አቀፍ ደረጃ ከጥቅምት 1/2017ዓ/ም ጀምሮ ክፍያ የፈፀመ ቢሆንም እስካሁን የማሻሻያዉ ልዩነት አልተከገለንም " ሲሉ ገልፀዋል።

" ስራ ሳናቆም ተደጋጋሚ ቅሬታ ስናቀርብ ቆይተናል " የሚሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ " ከዚህ ቀደም ከ2015 ዓ/ም ጀምሮ አብዘኞቻችን የተሰጠንን የደረጃ ዕድገት ክፊያ ተግባራዊ አልተደረገም በዚያ ላይ ይህ ሲጨመርበት ለዘርፈ ብዙ ችግሮች እየዳረገን ነዉ " ብለዋል።

ኮሌጁ ስለ ጉዳዩ ምን ይላል ?

የአረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ዲን አቶ ጻድቁ ሳሙኤል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ የደሞዝ ማሻሻያው አለመከፈሉ ትክክል መሆኑን አረጋግጠዋል።

" የፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ በክልሉ ያሉ የሁሉም ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛዎችን መረጃ በአጭር ጊዜ ዉስጥ በመሰብሰብና በማደረጃት ክፍያዉን እንደሚፈፅም ምላሽ ስለሰጠ እየተጠባበቅን እንገኛለን " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የደቡብ ኢትዮጵያ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮን ምላሽም ጠይቋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮ ኃላፊ አቶ አቢዮት ደምሴ በቢሯቸዉና በክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሃብት ልማት ቢሮ እጅ ያለዉ የሰራተኞች ቁጥር መረጃ ከ5 መቶ በላይ ሰዉ የቁጥር ልዩነት በማሳየቱ የማጣራቱ ስራ እስኪጠናቀቅ ክፍያው አለመፈፀሙን ተናግረዋል።

" አሁን ላይ ሁሉም ኮሌጆች መረጃዎችን አጠናቀዉ ወደ ፐብሊክ ሰርቪስ የመላኩ ስራ ስለተጠናቀቀ በአጭር ቀናት ዉስጥ ችግሩ ይፈታል " ሲቡ ያላቸዉን ሙሉ እምነት ገልፀዋል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቴክንክና ሙያ ስልጠና ቢሮ ስር 35 ኮሌጆች መኖራቸዉን ከነዚህም ዉስጥ በወላይታ ዞን አረካ ከተማ በሚገኘዉ አረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ከ150 በላይ አሰልጣኝ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች ስለመኖራቸዉ ከኮሌጁ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

#ThikvahEthiopiaFamilyHW

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

08 Feb, 10:09


#GlobalBank

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ የዲጅታል ባንኪንግ አገልግሎት መስጫ ማዕከል ለአገልግሎት ዝግጁ አድርጓል።

አገልግሎት መስጠት የጀመረው የዲጂታል ባንኪንግ ማዕከል የባንክ ሂሳብ መክፈት፣ ገንዘብ ገቢ ማድረግና ወጪ ማድረግ፣ ቀሪ ሂሳብና የሂሳብ መግለጫ ማሳየት፣ የውጭ ሀገር ገንዘቦችን መመንዘር፣ የተለያዩ ክፍያዎችን መፈፀም ያስችላል።

በተጨማሪም ያለ ኤቲኤም ካርድ አገልግሎት ማግኘት፣ ቼክ መመንዘርና ገቢ ማድረግን  ጨምሮ ደንበኞች የኢንተርኔት ባንኪንግ አገልግሎት መጠቀም በሚፈልጉበት ወቅት በማዕከሉ በመገኘት ለዚሁ አገልግሎት በተዘጋጁ ታብሌቶች መጠቀም ያስችላቸዋል።

ማዕከሉ የቪዲዮ ኮንፈረንስ ክፍል ያለው መሆኑንና ተቀዳሚ (corporate) ደንበኞች ባሉበት ቦታ ሆነው የቪዲዮ ባንኪንግ አገልግሎት ማገኝት የሚያስችላቸው አገልግሎትም እንደሚሰጥ ጠቅሷል።

የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ተስፋዬ ቦሩ ይህ ማዕከል ሥራ መጀመሩ ባንኩ ተወዳዳሪ እንዲሆን ከማድረጉም ባሻገር የባለአክሲዮኖችን ጥቅም ከፍ ከማድረግ እና የሀገርን ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ጠቅሰዋል።

ባንኩ በዘንድሮው አመትም ከታክስ በፊት ብር 757.6 ሚሊዮን ማትረፉን የገለጸ ሲሆን የቅርንጫፍ ብዛቱንም ወደ 238( ሁለት መቶ ሰላሳ ስምንት ) ከፍ ማድረግ ችሏል። በአሁን ሰዓትም ባንኩ ከ 1.7 ሚሊየን በላይ ደንበኞች እንዳሉት አሳውቋል፡፡

የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ደ/ር ተስፋዬ ቦሩ ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ያስቀመጠውን የባንክ ካፒታል ዕድገት ዝቅተኛ ጣሪያ በቀረው ጊዜ ውስጥ እንደሚያሳካ ገልጸዋል።

ባንኩ የተቀማጭ ሂሳቡን  ከ 20.6 ቢሊዮን ብር በላይ ያደረሰ መሆኑንና የባንኩ ጠቅላላ ሃብት ደግሞ ከ 26.6 ቢሊየን ብር በላይ መድረሱንም አስታውቋል።

ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሜክሲኮ አካባቢ  ለዋና መ/ቤት ግንባታ በተረከበው  5,550 ካ.ሜ ቦታ ላይ የወደፊት የዋና መ/ቤት ህንፃ ለመገንባት በሚያስችሉ ቅድመ ሁኔታዎች ላይ እየሰራ ይገኛል።

#GlobalBankEthiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

27 Jan, 12:49


#እንድታውቁት #አዲስአበባ

ከነገ ጀምሮ ከፊጋ - ወደ ሳፋሪ እንዲሁም ከሳፋሪ -ወደ ፊጋ የሁለቱም አቅጠጫ መንገዶች ላልተወሰኑ ቀናት ዝግ ይሆናሉ።

የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ፤ በአዲስ አበባ ከተማ በ2ኛው ዙር ከሚለሙት የኮሪደር መስመሮች መካከል የሲሚት- ጎሮ መንገድ አንደኛው መሆኑ አስታውሷል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በለሚ ኩራ ክ/ከተማ የሲ ኤም ሲ- ፔፕሲ - ጎሮ - መንገድ  ልዩ ቦታው ሳፋሪ መብራት አካባቢ ብሪቲሽ ትምህርት ቤት አጠገብ የመንገድ ቆረጣ እንደሚከናወን ገልጿል።

ከነገ ጥር 20/2017 ዓ.ም ጀምሮ ከፊጋ - ወደ ሳፋሪ እንዲሁም ከሳፋሪ -ወደ ፊጋ የሁለቱም አቅጠጫ መንገዶቹ ላልተወሰኑ ቀናት ዝግ እንደሚሆኑ አሳውቋል።

አሽከርከሪዎች ይህንኑ አውቀው አማራጭ መንገዶችን  እንዲጠቀሙ ጥሪ አስተላልፏል።

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

27 Jan, 09:58


የመውጫ ፈተና ከጥር 26 እስከ ጥር 30 ይሰጣል።

የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ከጥር 26-30/2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡

የመውጫ ፈተናው ለአዲስ እና በድጋሜ ለመፈተን ላመለከቱ በሙሉ እንደሚሰጥ ሚኒስቴሩ ገልጿል።

Via @tikvahuniversity

THIKVAH-ETHIOPIA

27 Jan, 08:10


#Update

ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት (4:38 ላይ) ተከስቶ የነበረው የመሬት መንቀጥቀጥ ከአዋሽ 36 ኪሎሜትር ርቀት ላይ እንደሆነ የጀርመኑ የጂኦሳይንስ ሪሰርች ማዕከል ገልጿል።

መንቀጥቀጡ በሬክተር ስኬል 4.9 መመዝገቡን አሳውቋል።

በርካታ ሰዎች የዛሬው ከወትሮው የተለየ ነበር ብለዋል።

የመሬት መንቀጥቀጡ የነበረበት አካባቢ ያሉ ወገኖች " አስፈሪ " ሲሉ ገልጸዋል።

ንዝረቱ የተሰማባቸው አካባቢዎች ደግሞ ከወትሮው የተለየ እንደነበር ታውቋል።

ለአብነት አዲስ አበባ ብዙ ሰዎች ህንጻ ላይ የነበሩ ተሰምቷቸው መደናገጣቸውን ገልጸውልናል። ለተወሰኑ ሰከንዶች የቆየ ቢሆንም የህንጻ ንቅናቄ ስሜት ፣ የመንስታወት መርገፍገፍ እንደተመለከቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

አንድ የቤተሰባችን አባል " 4ኛ ፎቅ ላይ በተቀመጥኩበት መስታወቱ ፣ የቤት እቃዎች ሲነቃነቁ፣ እኔም በተቀመጥኩበት በወትሮ በተለየ ንዝረት ሲሰማኝ ነበር " ብሏል።

ሌላ 12ኛ ፎቅ ላይ የነበረ የቤተሰባችን አባል " ያስፈራ ነበር " ሲል ክስተቱን አስረድቷል።

ከዚህ ባለፈ ንዝረቱ ከተሰባቸው ቦታዎች አንዱ የጅሌ ጥሙጋ አካባቢ ሲሆን የወረዳ አስተዳደር ህንፃ ላይ የሚሰሩ የመንግስት ሰራተኞች በድንጋጤ ከህንጻው መውረዳቸውን ከሰራተኞቹ ለመረዳት ተችሏል።

Photo Credit - Omer Al Faruq

@tikvahethiopa

THIKVAH-ETHIOPIA

27 Jan, 07:46


🚨#Alert

ከደቂቃዎች በፊት ከፍ ያለ የመሬት መንቀጥቀጥ አዋሽ አካባቢ ተከስቷል።

ንዝሩት በአዲስ አበባና ሌሎች ከተሞች ተሰምቷል።

ቃላቸውን የላኩልን የቤተሰባች አባላት " ዛሬ በጣም የሚያስፈራ ነበር። ሰሞኑን ድግግሞሹ ቀንሶ ነበር። ዛሬ በድንገት በሚያስፈራ ሁኔታ ነው የተሰማን " ብለዋል።

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

26 Jan, 21:12


በአዲስ አበባ ከፍጥነት ወሰን በላይ በማሽከርከር ለሞት የሚዳርጉ 5 መንገዶች የትኞቹ ናቸው ?

በተደረገ የዳሰሳ ጥናት ከፍጥነት ወሰን በላይ በማሽከርከር ከፍተኛ የሞት አደጋ የሚያስከትሉ 5 መንገዶች ተለይተዋል።

ከፍተኛ የሞት አደጋ ያስከትላሉ ተብለው የተለዩት ፦
° መገናኛ፣
° ኃይሌ ጋርመንት፣
° ቦሌ ሚካኤል፣
° ጦር ኃይሎች
° ቻይና ካምፕ መንገዶች ናቸው። በአማካይ በዓመት ከ6 እስከ 13 ዜጎች በእነዚህ መንገዶች በሚደርሱ የተሽከርካሪ አደጋቸው ሕይወታቸውን ያጣሉ።

ከመንገዶቹ አንዳንዶቹ የእግረኛ መተላለፊያ የላቸውም ፤ አሽከርካሪዎች ይህን ግምት ውስጥ በማስገባት ከፍጥነት ወሰን በላይ እያሽከረክሩ አደጋ ያደርሳሉ።

ከፍጥነት ወሰን በላይ በማሽከርከር በሚደርሰው የትራፊክ አደጋ፣ በአብዛኛው ሕይወታቸውን የሚያጡት ወንዶች ናቸው። መገናኛ አካባቢ አደጋ ከደረሰባቸው 13 ሰዎች አብዛኞቹ ወንዶች መሞተዋል።

አደጋ የሚደርሰው ከቀኑ 6፡00 ሰዓት እስከ 8፡00 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ ሲሆን በተለይም ሰንበት ወይም የዕረፍት ቀናት ከመንገድ መጨናነቅ ነፃ ስለሚሆኑ፣ ተከትሎ በፍጥነት ማሽከርከር ምክንያት የሞት ምጣኔው ከፍተኛ ነው።

አደጋዎች የሚያሳዩት ተቆጣጣሪ ተቋማትም ሆኑ አደጋ አድራሾችና ተጎጂዎች የሚያደርጉት ጥንቃቄ ዝቅተኛ እንደሆነ ነው።

ከፍጥነት ወሰን በላይ ማሽከርከር ከፍተኛውን ቁጥር የሚይዙት ከባድ ተሽከርካሪዎች ናቸው። ከሌሎች የተሽከርካሪ ዓይነቶች አብላጫውን አደጋ የሚያደርሱትም እነሱ ናቸው።

በዓለም የጤና ድርጅት የትራፊክ አደጋ ሥጋት መንስዔዎች ተብለው የተለዩት በፍጥነት ማሽከርከር፣ ጠጥቶ ማሽከረከር፣ የደኅንነት ቀበቶ አለመጠቀምና የራስ ቅል መሸፈኛ አለመጠቀም ከፍተኛውን ቦታ ይይዛሉ።

43 በመቶ የሚሆኑ የአዲስ አበባ ከተማ አሽከርካሪዎች ከፍጥነት ወሰን በላይ ያሽከረክራሉ። በዚህ ምክንያት ችግሩ ትኩረት ያሻዋል።

በየዓመቱ ከ400 የሚበልጡ ሰዎች በትራፊክ አደጋ ይሞታሉ። የጥናቶች የትኩረት አቅጣጫ የፍጥነት መገደቢያ መጠቀምና ሥር ነቀል የማኅበረሰብ ግንዛቤ ማስጨበጥ ያስገልጋል።   

(የአዲስ አበባ ከተማ ትራፊክ ማኔጅመንት መረጃ)

#ሪፖርተርጋዜጣ

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

26 Jan, 20:26


በፓኪስታን ሀገር " እስልምና ላይ ተሳልቀዋል " በሚል የተከሰሱ 4 ሰዎች የሞት ፍርድ ተላለፈባቸው።

4ቱ ሰዎች " ቅዱስ ቁርዓንን ጨምሮ የእስልምናን ዕምነት እሴቶችን ጎድተዋል " በሚል ነው የሞት ፍርድ የተላለፈባቸው።

ተከሳሾቹ " የእስልምና እምነትን የሚያንቋሽሹ ይዘቶችን በማህበራዊ የትስስር ገጾች አሰራጭተዋል " በሚል ክስ ተመስርቶባቸው ክርክሩ ሲካሄድ ቆይቷል።

ከሰሞኑ በራዋልፒንዲ ከተማ በተካሄደ ችሎት ተከሳሾቹ ጥፋተኛ ሆነው ተገኝተዋል በሚል 4ቱም ተከሳሾች የሞት ፍርድ ተላልፎባቸዋል ተብሏል።

ግለሰቦቹ የእስልምና ዕምነት ተከታዮች እሴቶችን፣ ቅዱስ ቁርዓንን፣ እምነትን እና ሌሎች ተያያዥ እሴቶችን አንቋሸዋል ተብሏል።

ፍርድ ቤቱ ተከሳሾቹ ላይ ከሞት ፍርድ በተጨማሪ 16 ሺህ 500 ዶላር እንዲከፍሉ ቅጣት አስተላልፎባቸዋል።

የተከሳሾቹ ጠበቃ ፤ በደንበኞቹ ላይ የተላለፈው ፍርድ ተመጣጣኝ አይደለም በመቃወም ፤ የተላለፈውን ፍርድ ለማስቀየር ይግባኝ ለማለት በዝግጅት ላይ እንደሆነም አሳውቋል።

መረጃው የአል አይን ኒውስ / አል አረቢያ ነው።

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

26 Jan, 20:15


#Tigray

ዛሬ በደጋፊዎች እና በተቃዋሚዎች በኩል የፓሊስ ትእዛዝ የጣሱ ሰላማዊ ሰልፎች ተካሂደዋል።

በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት የጠራቸው ሰልፈኞች ፥ " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል  ጥር 14/2017 ዓ.ም የወጣውን የውሳኔ ሃሳብ የሚደግፉና እና ሌሎች መፈክሮች አስተጋብተዋል።

በራሳቸው ተነሳሽነት ሰልፍ መውጣታቸው የሚናገሩት በብዛት ወጣቶች ያካተቱ ሰልፈኞች ደግሞ " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል  የተሰጠው ውሳኔ ተፈፃሚነት (null and void እንዲሆን) እንዳይኖረው ፤ ጦርነት የሚፀየፉና ጅምር ሰላም እና ለውጡ እንዲቀጥል የሚሉ መፈክሮች አሰምተዋል።

በሰሜናዊ ምዕራብ ፣ ማእከላዊ ዞኖች መቐለ ከተማ በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራ ህወሓት ብቻ የጠራቸው ሰልፎች ሲካሄዱ ፤ በምስራቃዊ ዞን ዓዲግራት እና ውቅሮ ከተሞች በደጋፊ እና ተቃዋሚ በአንድ ጊዜ የተጠሩ ሰልፎች ተከናውነዋል።

በውቅሮ ከተማ የፀጥታ አካላት በራስ ተነሳሽነት ለመውጣት በሞከሩት ላይ ለመበተን የሞከሩ ሲሆን ፤ በዓዲግራት የነበሩት የለውጥ ደጋፊዎች ላይ ግን ለመበተን የተደረገ ሙከራ እንደሌለ የዞኑ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ዘግቧል።

ትናንት ጥር 17/2017 ዓ.ም  በደቡባዊ ዞን የተለያዩ ከተሞች " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል  የተሰጠው ውሳኔ የሚቃወም ጦርነት የሚያወግዝ ሰላምና ለውጥ የሚደግፍ ሰላማዊ ስልፍ የተካሄደ ሲሆን ዛሬ እሁድ ጥር 18/2017 ዓ.ም በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራ ህወሓት የጠራው ሰልፍ በዞኑ አልተካሄደም።

በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራ ህወሓት በጠራው ሰልፍ የተደመጡ መፈክሮች ምን ይመስላሉ ?

- የትግራይ ሰራዊት ውሳኔ ይተግበር !!
- የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር በአስቸኳይ ይስተካከል !!
- የፕሪቶሪያ ውል ይተግበር !!
- የትግራይ ሉአላዊ ግዛት ይከበር !!
- ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው ይመለሱ !!
- የህወሓት ህጋዊነት በአስቸኳይ ይመለስ !!
- የውጭ ጣልቃ ገብነት አንቀበልም !!
- ሰራዊታችን ለማፍረስ እየተደረገ ያለው ሴራ አንቀበልም !!
- የፕሪቶሪያ ስምምነት መተግበር ለትግራይ እና ለአፍሪካ ቀንድ ሰላም ዋስትና ነው !!

በራስ ተነሳሽነት ወጣቶች በብዛት በተሳተፉባቸው ሰልፎች የተደመጡ መፈክሮች ምን ይመስላሉ ?

- የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል የተሰጠው ውሳኔ ተቀባይነት የለውም !!
- የትግራይ የፀጥታ ሃይሎች የህዝብ አገልጋዮች እንጂ የአንድ ቡድን ከለላ አይደሉም ! 
- የትግራይ ግዛታዊ አንድነት ይከበር !!
- የሚቆም ትግል እና ለውጥ የለም !!
- ወጣቶች ለልማት እንጂ ለጦርነት አንሰልፍም!!
- የተረጋጋ መንግስት ለመትከል የወጣቶች ሚና ከፍተኛ ነው !!
-ጊዚያዊ አስተዳደሩ ወደ መደበኛ መንግስት የሚያሸጋግረን በቸኛ ህጋዊ ተቋም ነው !!
- የፕሪቶሪያ ስምምነት እንዲፀና እንፈልጋለን !!

... ሲሉ ተደምጠዋል።

በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ፤ ዛሬ ጥር 18/2017 ዓ.ም መቐለ ጨምሮ በመላው ትግራይ የሚካሄደው ሰልፍ መግባባት የተደረገበት እና የተሟላ ጥበቃ የሚደረገበት ነው ያለ ሲሆን ጊዚያዊ አስተዳደሩ በመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት በኩል ጥር 17/2017 ዓ.ም  ባወጣው መግለጫ ለእሁድ ጥር 18/2017 ዓ.ም የተጠራ እና የተፈቀደ ሰልፍ የለም ብሎ ነበር።

የትግራይ ፓሊስ ኮሚሽን በበኩሉ ህወሓት ለእሁድ ጥር 18/2017 ዓ.ም የጠራውን ሰላማዊ ሰልፍ በቂ ጥበቃ ለመስጠት በመቸገሩ ምክንያተት ቀን እንዲቀየርለት ሲጠይቅ : የክልሉ ሰላም እና ፀጥታ ቢሮ  ትእዛዝ ተላልፈው ስበብሰባ እና ሰላማዊ ሰልፍ በሚያካሂዱ ላይ እርምጃ ለመውሰድ እንደሚገደድ ማስጠንቀቁ መዘገባችን ይታወሳል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ እስከ አሁን ባለው መረጃ በድጋፍ እና በተቃውሞ በኩል የተደረጉ ሰላማዊ ሰልፎች ሰላማዊ የነበሩ ሲሆን ከክልሉ ፓሊስ እንዲሁም የሰላም እና  የፀጥታ ቢሮ የሚሰጥ መረጃ ካለ ተከታትለን የምናቀርብ ይሆናል።

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

26 Jan, 20:15


ከፍርድ ውጭ ግድያ፣ የሲቪል ሰዎች ሞት፣ የአካል ጉዳት፣ የንብረት ውድመትና ዘረፋ !

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የሩብ ዓመት ሪፖርት በኢትዮጵያ በግጭት ዐውድ ውስጥ ያሉ አካባቢዎች የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ በተመለከተ።

@tikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

18 Jan, 19:10


" በተራሮቹ ላይ የተከሰተው እሳት ከመስፋፋቱና ከፍተኛ ችግር ከማስከተሉ በፊት ህብረተሰቡ እንዲሳተፍ እና አስፈላጊው ድጋፍ እንዲደረግ ጥሪ እናቀርባለን " - ወረዳው

በኦሮሚያ ክልል፣ በምዕራብ አርሲ ዞን ወንዶ ወረዳ " ጎቱ ኦኖማ " በተባለው አከባቢ ከሰዓት 10 ሰዓት አከባቢ በተራሮች ላይ የእሳት ቃጠሎ መነሳቱን የወረዳው ኮሚኒኬሽን ቢሮ አስታውቋል።

የእሳቱ መከሰት መንስዔው በድርቅ ምክንያት የተከሰተ ነው ያለው ቢሮው የተከሰተውን ቃጠሎ በህብረተሰቡ ተሳትፎ ለማጥፋት እየተሞከረ ነው ሲል አስታውቋል።

ሆኖሞ የተከሰተውን የእሳት አደጋ ተከትሎ በማኅበራዊ ሚዲያው በ 'እሳተ ገሞራ' የተከሰተ ነው በሚል የተሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ ነው ሲል ገልጿል።

በተራሮቹ ላይ የተከሰተው እሳት ከመስፋፋቱ እና ከፍተኛ ችግር ከማስከተሉ በፊት ህብረተሰቡ እንዲሳተፍ እና አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግም ቢሮው ባወጣው መረጃ ጠይቋል።

Via @tikvahethmagazine

THIKVAH-ETHIOPIA

18 Jan, 18:45


#Peace🏳

ጋዛ ተኩስ አቁም ነገ ተግባራዊ ይሆናል።

የተኩስ አቁሙ ነገ ተግባራዊ እንደሚሆን የኳታር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳውቋል።

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስቴር ነገ በሀገሩ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ 2 ሰዓት ተኩል ላይ የተኩስ አቁሙ ተግባራዊ እንደሚሆን አረጋግጧል።

የጠቅላይ ሚኒስቴር ቤኒያሚን ኔታንያሁ ዛሬ ቅዳሜ የተኩስ አቁሙን አፅድቋል።

ተኩስ አቁሙ ስራ ላይ ሲውል 1,904 ፍልስጤማውያን ከእስራኤል እስር ቤቶች እንደሚለቀቁ የእስራኤል መንግሥት አሳውቋል።

ሀማስ ደግሞ ከ98 እስራኤላውያን ታጋቾች መካከል 33ቱን ለ6 ሳምንታት በሚዘልቀው የተኩስ አቁም ወቅት ይለቃል።

ግብፅ ሰብዓዊ እርዳታ ወደ ጋዛ ለመላክ እየተዘጋጀች ነው።

በሌላ በኩል ግን ሀማስ እና እስራኤል የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ መድረሳቸው ከተገለጸ በኃላ 122 ፍልስጤማውያን በእስራኤል መገደላቸውን የጋዛ የሰላማዊ ሰዎች ጥበቃ ኤጀንሲ ገልጿል።

እስካሁን በ15 ወራት ጦርነት የተገደሉት ፍልስጤማውያን ቁጥር 46,899 ደርሷል። 110,725 ሰዎች ታጎድተዋል።

መረጃው ከዶቼ ቨለ የተገኘ ነው።

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

18 Jan, 18:19


#ከተራ2017

የ2017 ዓ/ም የጥምቀት ከተራ በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን ዘንድ በቤተክርስቲያኗ ሥርዓት እና ትውፊት ተከብሮ ውሏል።

ዛሬ ታቦታት ከየአብያተክርስቲያናቱ ወጥተው ወደ የማደሪያቸው ባህረ-ጥምቀት ገብተዋል።

በነገው ዕለት በመላው ሀገሪቱ የጥምቀት በዓል ይከበራል።

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

18 Jan, 18:17


#Update

🚨“ በጣም ብዙ ችግር ነው እየደረሰባቸው ያለው። ጣታቸው የተቆረጠ አሉ ” - የወላጆች ኮሚቴ

ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ከሰጠው መግለጫ በመነሳት፣ “ አንዳንድ ሚዲያዎች መንግስት በማይናማር የታገቱ ዜጎችን አስለቀቀ ” በማለት መዘገባቸው ስህተት መሆኑን ጉዳዩን የሚከታተሉ የታጋች ቤተሰቦች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

የታጋቾቹ ቤተሰቦች በዝርዝር ምን አሉ ?

“ አጋቾች  ያገቷቸውን ልጆቻችንን ‘መንግስት አስለቀቀ’ መባሉ ትክክል አይደለም።

አጋቾቹ ሲቀጧቸው የተጎዱ፣ በህመም ሳቢያ መስራት የማይችሉ ልጆችን ከካምፕ አውጥተው ታይላንድ ድንበር ሲጥሏቸው ሰብአዊ መብት ላይ የሚሰሩ ኤን.ጂ.ኦ አንስተው ታይላንድ በመውሰድ አሳክመው ህንድ ካለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጋር በመሆን ነው ኢትዮጵያ እንዲገቡ ያደረጓቸው።

አንዳንድ ሚዲያዎች የዘገቡትና መንግስትም ድፍን ባለ መልኩ የሰጠውን መግለጫ መነሻ በማድረግ ማይናማር ያሉ ልጆች የተለቀቁ የመሰላቸው
አድማጮች እንኳን ደስ አላችሁ ’ የሚለን በዝቷል። እውነታው ይሄ አይደለም።

ይህን ጉዳይ ህዝብ ይረዳው። ማይናማር ከታገቱት ልጆች መካከል እንዲለቀቁ በተደረገ ጥረት ማንም አልተለቀቀም።

ታይላንድ ያሉት ናቸው እንጂ ማይናማር ያሉት አይደሉም የወጡት። ዋሽተው ነው። ዜናውን አካብደውታል። እኛን ምንም ተስፋ አልሰጡንም። ‘አትምጡ’ ነው ያሉን ” ሲሉ አስረድተዋል።

የወላጆች ኮሚቴ በበኩሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል ምን አለ ?

በዚህ መልኩ (ታጋቾች ተለቀዋል በሚል) የዘገቡት ሚዲያዎች ሁለት፣ ሦስት ጊዜ ድምፅ እንዲሆኑን ጠይቀናቸው ሳለ ‘ እንከሰሳለን ’ ብለው ነው የፈሩት። አሁን ግን ያልተወራውን ማስተላለፍ ከኢቲክስ ውጪ ነው። በጣም ቅር ብሎናል። እውነታውን አሳውቁልን።

በታይላንድና በማይናማር ድንበር ያሉት ልጆች እንጂ ወጡ የተባሉት ከማይናማር ግዛት ካሉት ጋር እንደማይገናኝ በህንድ የሚገኘው ኢትዮጵያ ኤምባሲ ነግሮናል።

የኤምባሲው ሰዎች ‘እኛ የሚመለከተን ታይላንድ አካባቢ ያለውን ብቻ እንጂ የማይናማሩ የሚመለከተው ቶኪዮ ያለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ነውና ማይናማር ያሉትን አንድም ነገር አልሰራንም’ ብለው ቃል በቃል ነው የነገሩን።

ከኢትዮጵያ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር አምባሳደር ነብያት ጌታቸው በመግቢያ ንግግራቸው ያስተላለፉት ትክክለኛውን ‘ታይላንድ አካባቢ ያሉትን’ ብለው ነው።

ነገር ግን አንዳንድ ሚዲያዎች በስቃይ ላይ ያሉ ልጆችን መንግስት እያስወጣ እንዳለ አድርገው ነው መግለጫውን የዘገቡት። ይህ ቅር አሰኝቶናል።


ሌሎች አገራት እኮ ዜጎቻቸውን ያስወጡት ከትራደሽናል ሊደሮች፣ ከኤምባሲዎች ጋር ሆነው በመስራት ነው። የኛዎቹ ግን ይህን ለማድረግ ፈቃደኛ አይደሉም።

አንዱን ኢትዮጵያዊ የመራቢያ አካሉን የዘር ፍሬ ነቅለውታል። በጣም ብዙ ችግር ነው እየደረሰባቸው ያለው። ጣታቸው የተቆረጠ አሉ።

አሁንም ቢሆን የኢትዮጵያ መንግስት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተነጋግሮ በችግር ላይ ያሉ ልጆችንን  ካሉበት ስቃይ እንዲታደጋቸው በአጽንኦት እንጠይቃለን ” ብሏል።

#ThikvahEthiopiaFamilyAA

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

18 Jan, 18:16


ወጋገን ባንክ !

በወጋገን ካርድ በፖስ ማሽኖቻችን ክፍያ ሲፈፅሙ ተመላሽ እንዳለው ሰምተዋል ?

በወጋገን ክፍያ ካርድዎ ለአጠቃቀም ምቹ፣ ፈጣን እና አስተማማኝ በሆኑት የወጋገን ፖስ ማሽኖች ተጠቅመው በሆቴሎች እና ሬስቶራንቶች ፣ሱፐር ማርኬቶች፣ ሆስፒታሎች ፣ የገበያ ማዕከላት እንዲሁም በተለያዩ የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላገኙት አገልግሎት እና ለገዙት ዕቃ  ክፍያ ሲፈፅሙ የገንዘብ ተመላሽ ተጠቃሚ ይሆናሉ፡፡

ልብ ይበሉ !

እስከ ጥር 28 ቀን 2017 ዓ.ም በወጋገን የክፍያ ካርድዎ በፖስ ማሽኖቻችን ክፍያዎን ሲፈፅሙ ግብይትዎ ቀልጣፋ፣ ምቹ እና አስተማማኝነቱ እንደተጠበቀ ሆኖ የተመላሽ ገንዘብ ተጠቃሚ ይሆናሉ።

ዛሬውኑ ፈጥነው የወጋገን ካርድዎን ይውሰዱ

ለበለጠ መረጃ ወደ ደንበኞች ግንኙነት ማዕከል በ866 ነፃ የስልክ መስመር ይደውሉ! በተጨማሪም ከስር የተቀመጠውን ሊንክ በመጫን የማህበራዊ ሚዲያዎቻችንን ይቀላቀላሉ https://linktr.ee/WegagenBank

THIKVAH-ETHIOPIA

18 Jan, 18:16


ሞሐ የለስላሳ መጠጦች ኢንዱስትሪ አክሲዮን ማህበር፣ ለደንበኞቹ ካዘጋጃቸው በርካታ ሽልማቶች
ውስጥ አንዱ ቢዋይዲ የኤሌክትሪክ መኪና ዕጣ፣ በመቀሌ ለዕድለኛ ወጥቷል፡፡
ዕድለኛው አሸናፊ አቶ የማነ ነጋሽ ፣ ሽልማታቸውን ጥር 10 ቀን 2017ዓ.ም. በመቀሌ ከተማ በተከናወነ
ልዩ የሽልማት ፕሮግራም ተረክበዋል፡፡
ከዚህ በፊት በአዲስ አበባ እና በድሬዳዋ ከተማ ነዋሪ የሆኑ ዕድለኞች ሚሪንዳ እና ፔፕሲ ጠጥተው
ቢዋይዲ የኤሌክትሪክ መኪና ዕጣ ማሸነፋቸው ይታወሳል፡፡

THIKVAH-ETHIOPIA

08 Jan, 22:35


🚨 #Alert

ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ተከስቶ የነበረው የመሬት መንቀጥቀጥ ከአዋሽ 23 ኪሎሜትር ርቀት ላይ ሲሆን የጀርመኑ የጂኦሳይንስ ሪሰርች ማዕከል መንቀጥቀጡ በሬክተር ስኬል 5.0 መመዝገቡን አሳውቋል።

የአሜሪካ ጃኦሎጂካል ሰርቬይ ደግሞ በሬክተር ስኬል 4.9 መለካቱን አመላክቷል።

ንዝረቱ አዲስ አበባ የተለያዩ ሰፈሮች ተሰምቷል።

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

08 Jan, 22:23


#Earthquake : ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ንዝረቱ አዲስ አበባ ድረስ የተሰማ የመሬት መንቀጥቀጥ አዋሽ አካባቢ ተከስቶ ነበር።

በርካታ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት  መንቀጥቀጡ እና ንዝረቱ ከእንቅልፋቸው እንደቀሰቀሳቸውና ጠንክሮ እንደተሰማቸው መልዕክት ልከዋል።

በተለይ አዲስ አበባ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ላይ ጠንከር ብሎ ንዝረቱ ተሰምቷል።

ከንዝረቱ ጋር በተያያዘ መልዕክት የላከ የቤተሰባችን አባል ፥ " 7:09 ለቡ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት ተሰምቶናል ከዚህ በፊት ተሰምቶን አያውቅም ፤ ኳስ እያየን ቆይተን በጥቂቱም ቢሆን ለ 5-10 ሰከንድ የቆየ ንዝረት ተሰምቶናል ፤ Odd የሆነ ስሜት አለው ግራ መጋባት ፈጥሮብን ነበር " ብሏል።

ውድ ቤተሰቦቻችን የጥንቃቄ እርምጃዎችን አንብቡ 
፦ https://t.me/tikvahethiopia/93267?single

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

08 Jan, 20:39


#Lottery : የገና ስጦታ ሎተሪ ዕጣ ዛሬ  ታህሳስ 30 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሎተሪ  አገልግሎት በዕድል አዳራሽ መውጣቱን የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት አሳውቋል።

በዚህም ፦

1ኛ የዕጣ ቁጥር ➡️ 1331140 (አስር ሚሊዮን ብር)

2ኛ የዕጣ ቁጥር ➡️ 1003012 (አምስት ሚሊዮን ብር)

3ኛ የዕጣ ቁጥር ➡️ 0273783 (ሁለት ሚሊዮን አምስት መቶ ሺህ ብር)

4ኛ ዕጣ ➡️ 1975332 (አንድ ሚሊዮን ሁለት መቶ ሃምሳ ሺህ ብር)

የወጡት የዕጣ ቁጥሮች ዝርዝር ከላይ ተያይዟል።

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

08 Jan, 19:42


" ጥያቄያችን ግልፅ ነው ፤ አሁንም ሂጃቧን ትለብሳለች ትምህርቷንም ትማራለች !! " - የትግራይ የእሰልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት

የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፥ በአክሱም ከተማ ከሙስሊም ተማሪዎች የሂጃብ መልበስ ክልከላ ጋር ተያይዞ ወቅታዊ ማብራርያ ዛሬ ምሽት ሰጥቷል።

ምክር ቤቱ በማብራርያው ፥ የአክሱም ከተማ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃባቸው ለብሰው እንዳይማሩ የተደረገው ክልከላ ሃይማኖታዊ እና ዓለማዊ የሰው ልጆችን መብት የሚጋፋ ከመሆኑ አኳያ ችግሩን ለመፍታት በብዙ አማራጮች ተሞኩረዋል ብሏል።

ከሙከራዎቹ አንዱ በክልሉ ትምህርቲ ቢሮ የተደረገው እንደሆነ ጠቁሟል።

ህግ የጣሰው ክልከላ እንዲነሳ " ትምህርት ቢሮ ያልተሳካ ሽምግልና እና መተግበር የማይችል ደብዳቤ ከመፃፍ የዘለለ ያመጣው ተጨባጭ ለውጥ የለም " ሲል ገልጿል።

የትምህርት ቤቱ አንዳንድ አመራሮች ከራሳቸው የሃይማኖት ፍላጎት ፤ የትምህርት መብት አተያይ በመነሳት ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዳይገቡ ተደርገዋል ብሏል ም/ቤቱ።

" የተማሪዎች የትምህርት ገበታ ክልከላ የከፋ የሚያደርገው ደግሞ የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች መሆናቸውንና በሂጃብ ክልከላ ምክንያት ወደ ዩኒቨርስቲ የሚያዘልቃቸው ዕድል እንዲዘጋ መደረጉ ነው " ሲል ገልጿል።

ምክር ቤቱ " ከቀናት በፊት በአቋም መግለጫችን እንደጠቀስነው ክልከው በአፈጣኝ ካልተፈታ በህግ ክስ እንጠይቃለን ባልነው መሰረት ጉዳዩ ወደ ህግ ወስደነዋል " ብሏል።

በዚህም በቀጣይ " እወስደዋለሁ " ያለውን እርምጃ መተግበር መጀመሩ አስታውቋል።

" ጉዳዩ ከሙስሊም ሴት ተማሪዎች ጋር ብቻ ሳይሆን ከሴቶች መብትና የሰው ልጆች የመማር መብት ጥሰት አኳያ መታየት አለበት " ያለው ምክር ቤቱ " ጉዳዩ ሁሉም ትግራዋይ እንዲያወግዘው  " ሲል ጥሪ አቅርቧል።

ምክር ቤቱ በመግለጫው ማጠቃለያ " ጥያቄያችን ግልፅ ነው ፤ አሁንም ሂጃብዋ ትለብሳለች ትምህርቷንም ትማራለች " ብሏል።

#ThikvahEthiopiaFamilyMekelle

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

08 Jan, 19:27


" ህጻኑ እና ወላጅ እናት በመልካም ጤንነት ላይ ይገኛሉ " - ዶክተር ደሳለኝ ተስፋዬ

በጅማ ዞን ኦሞ ናዳ ወረዳ ዙቤይራ ሙሀመድሳኒ የተባለች እናት 6 ነጥብ 2 ኪሎ ግራም የሚመዝን ልጅ ተገላግላለች፡፡
 
ህጻኑ በናዳ ሆስፒታል በቀዶ ህክምና መወለዱን በሆስፒታሉ የቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት ዶክተር ደሳለኝ ተስፋዬ ተናግረዋል፡፡
 
ዶክተር ደሳለኝ በአሁኑ ሰዓት ህጻኑ እና ወላጅ እናት በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኙ ለኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ (OBN) ገልጸዋል።
 
ከቀናት በፊት በአዲስ አበባ በዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል ቤቴልሄም አመኑ የተባለች እናት 6 ኪሎ ግራም የሚመዝን ወንድ ልጅ በተደረገላት የቀዶ ህክምና በሰላም መገላገሏ ይታወሳል።

እንደ ሮችስተር ዩኒቨርሲቲ የህክምና ማዕከል ከ37 እና 41 ሳምንታት እርግዝና መካከል የሚወለዱ ህጻናት አማካይ ክብደታቸው 3.2 እስከ 3.4 ኪሎግራም ነው።

የዓለም ጤና ድርጅት ባስቀመጠው የልጆች እድገት ስታንዳርድም የሚወለዱ ህጻናት አማካይ ክብደት ከ3.2 እስከ 3.4 ኪሎግራም ነው።

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

08 Jan, 18:47


#Update

በትግራይ ክልል ፤ አክሱም ከተማ በሚገኘው ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ከሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃብ መልበስ መከልከል ጋር ተያይዞ የተከሰተው ውዝግብ አሁንም መቋጫ አላገኘም።

የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ጉዳዩ በማስመልከት ታህሳስ 25 ቀን 2017 ዓ/ም በመቐለ ከተማ በሰጠው መግለጫ " የመብት ጥያቄያችን በሦስት ቀናት ውስጥ ካልተመለሰ ቀጣይ ሰላማዊ እርምጃ እንወሰዳለን " ብሎ ነበር። 

በመግለጫው  " የፌደራል ትምህርት ሚኒስቴር የሙስሊም ሴት ተማሪዎች አለባበስ አስመልክቶ ያወጣው ህግ እንዲከበር እንጠይቃለን " ማለቱም ይታወሳል ።

የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዛሬ ታህሳስ 30/2017 ዓ.ም ከመቐለ እና አክሱም ታማኝ የመረጃ ምንጮች እንዳረጋገጠው ፤ ከምክር ቤቱ መግለጫ በኋላ የትግራይ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ወደ አክሱም በማምራት ከትምህርት ቤቱ አመራሮች ፣ ከሙስሊም ሴት ተማሪዎች እና የአገር ሽማግሌዎች ተወያይተዋል።

የመረጃ ምንጫችን " ውይይቱ መሬት ላይ ጠብ የሚል ለውጥ አላመጣም "  ብሏል። 

" የቢሮ ሃላፊው የትምህርት ሚንስቴር ህግ ፣ መመሪያ እና ደንብ መሰረት ያደረገ ትእዛዝ መስጠት ሲገባቸው ፤ ጉዳዩን ለማሸማገል ያደረጉት ጥረት ተጎጂ ተማሪዎቹ መታደግ አልቻለም " ሲል አክሏል።

ስለሆነም ችግሩ በቀጣዩ ቀናት መፈታት ካልተቻለ 160 የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች እጣ ፈንታ አደጋ ላይ ይወድቃል ሲል የመረጃ ምንጩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ተናግሯል።

የመቐለ ቲክቫህ አባል ለትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ቅርበት ካላቸው ወገኖች ባገኘው መረጃ ደግሞ ከውዝግቡ ጋር በተያያዘ ይሁን ለሌላ ስራ ጉዳይ ነገ የፌደራል የእስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ የሃይማኖት አመራሮች መቐለ ትግራይ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል።

#ThikvahEthiopiaFamilyMekelle

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

08 Jan, 18:42


“ ከሀገር ውስጥ ቱሪስቶች 17 ሚሊዮን 704 ሺሕ 800 ብር፣ ከውጪ ሀገር ቱሪስቶች 3 ሚሊዮን 287 ሺሕ 324 ብር ገቢ ተገኝቷል” - ሰሜን ወሎ ዞን

የልደት በዓል በላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያን በሰላም መከበሩን የሰሜን ወሎ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያና የላሊላ ከተማ አስተደደር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

የሰሜን ወሎ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ የቅርስ ጥበቃና ቱሪዝም ልማት ቡድን መሪ አቶ ጥላሁን አባተ በሰጡን ቃል፣ “ በዓሉ ያለምንም ችግር ነው የተከበረው ” ብለዋል።

በዓሉ ላይ ምን ያክል ቱሪስቶች ታድመው ነበር ? ምን ያህል ገቢስ ተገኘ ? ስንል ላቀረብንላቸው ጥያቄም ማብራሪያ ሰጥተዋል።

አቶ ጥላሁን አባተ ፦

“ የሀገርም የውጪም ቱሪስቶች በበዓሉ ላይ ታድመዋል።

የሀገር ውስጥ ቱሪስት ብዛት፦ ወንድ 564 ሺሕ 260፣ ሴት 320 ሺሕ 950፣ በድምሩ 885 ሺሕ 210 ነበሩ።

የውጪ ሀገር ቱሪስት ወንድ 312፣ ሴት 181 በድምሩ 493 ቱሪስቶች በበዓሉ ታድመዋል።

ከሀገር ውስጥ ቱሪስቶች 17 ሚሊዮን 704 ሺሕ 800 ብር፣ ከውጪ ሀገር ቱሪስቶች 3 ሚሊዮን 287 ሺሕ 324 ብር ገቢ ተገኝቷል።

በአጠቃላይ ወደ በዓለ ልደቱ ለመታደም የገባ ተሽከርካሪ ቁጥርም 531 ነበር ”
ብለዋል።

አማራ ክልል የጸጥታ ችግር እንዳለበት የሚታወቅ ክልል ነው ፤ ከእቅዳችሁ እና ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት አንጻር የቱሪስቶች ብዛት ቀንሷል ? ስንል ላቀረብንላቸው ተጨማሪ ጥያቄ ፦

“ የሀገር ውስጥ ቱሪስት ፍሰቱን ስንመለከት አብዛኛው ሰው ለእምነት ጉዞ ስለሚያደርግ ከእቅዳችን አንጻር ሲታይ ቁጥሩ የተሳካ ነበር።

የውጪ አገር ቱሪስት ግን እንደሚታወቀው የስትራቴጂክ እቅዳችን በጣም ብዙ ነበር። ነገር ግን የውጪ ቱሪስቶች አንድን አካባቢ ለመጎብኘት ብዙ ቅድመ ሁኔታዎች ያስፈልጋሉ።

የሰላም መረጋጋትና ሌሎች መሰል ጉዳዮች ይወስናሉ። ከዚህ አንጻር ሲታይ ቁጥሩ የውጪ ሀገር ቱሪስት መጠነኛ ነበር። ግን ከኮቪድ ጀምሮ ካለፉት 5፣ 6 ዓመታት ሲታይ የዘንድሮው የተሻለ ነው ”
ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

ስለበዓሉ ውሎና ፍፃሜ ማብራሪያ የጠየቅናቸው የላሊበላ ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ወንድምነው ወዳጅ በበኩላቸው፣ “ ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ የተከናወነ በዓል ነው ያከበርነው ” ሲሉ ገልጸውታል።

“ በዓሉ አጠቃላይ እንደ ቅዱስ ላሊበላ ከተማ ኢትዮጵያዊ ትውፊቱን ባማከለ መልኩ ተከናውኗል። ወጣቶቹም ጥቅል ማህበረሰቡም በምንፈልገው መልኩ የተቃኘና የተጠቃለለ በዓል ነበር ” ነው ያሉት።

የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያን እድሳት ጉዳይ ከምን ደረሰ ? ስንልም ጠይቀናል።

ያንብቡ : https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-01-08

#ThikvahEthiopiaFamilyAA

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

08 Jan, 17:09


#Update

በነገው ዕለት ፓርላማው በሚያካሂደው መደበኛ ጉባኤ የንብረት ማስመለስ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ በህግና ፍትህና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚቀርበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።

በተጨማሪም ፥ የነዳጅ ውጤቶችን ግብይት ሥርዓት ለመደንገግ በተዘጋጀውን ረቂቅ አዋጅ ላይ የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀርበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ ያፀድቃል ተብሏል። 

ከንብረት ማስመለስ ረቂቅ አዋጅ ላይ ፦

" #ማንኛውም_ሰው በቀጥታ ሆነ #በተዘዋዋሪ ያለው ንብረት ወይም የኑሮ ደረጃው አሁን ላይ ባለበት ወይም አስቀድሞ በነበረበት ስራ ወይም በሌላ መንገድ ከሚያገኘው ወይም ሲያገኝ ከነበረው ህጋዊ ገቢ የማይመጣጠን እንደሆነ እና የንብረቱን ወይም የኑሮ ደረጃውን ምንጭ በተመለከተ ምክንያታዊ የሆነ የወንጀል ጥርጣሬ በኖረ ጊዜ የዚህ አይነቱ የኑሮ ደረጃ ወይም ያለው ንብረት እንዴት ሊኖረው እንደቻለ ለፍርድ ቤት ካላስረዳ በስተቀር ንብረቱ #ይወረሳል። "

የነዳጅ ውጤቶችን ግብይት ለመደንገግ ከተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ ላይ ፦

" የነዳጅ ውጤቶችን ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ያከማቸ፣ ሊሸጥ ከሚገባው ሰው ቦታና የግብይት ስርዓት ውጭ ሲሸጥ የተገኘ ወይም አደጋ ያስከትላሉ በተባሉ መያዣዎች ሲሸጥ የተገኘ ማንኛውም ግለሰብ የተያዘው የነዳጅ ውጤት ተወርሶ ከ3 ዓመት በማይበልጥ እስርና ከብር 50 ሺህ እስከ ብር 100 ሺህ የሚደርስ ቅጣት ይፈጸምበታል።

መንግሥት ከሚያወጣው የነዳጅ ምርቶች መሸጫ ተመን ውጪ በተደጋጋሚ የመገበያየት ወንጀል እንዲሁም የነዳጅ ምርቶችን ከባዕድ ነገሮች ጋር መቀላቀል እስከ 3 ዓመት እስርና እስከ 300 ሺህ ብር ቅጣት ያስጥላል። "


🔴 ስለ ንብረት ማስመለስ ረቂቅ አዋጅ ከዚህ ቀደም ያጋራናችሁን ዝርዝር መረጃና ሰነድ በዚህ ይገኛል ፦ https://t.me/tikvahethiopia/88315

🔵 ስለ ነዳጅ ውጤቶች ግብይት ሥርዓት ስለሚደነግገው ረቂቅ አዋጅ ያጋራናችሁ ዝርዝር መረጃ ደግሞ በዚህ ይገኛል ፦
https://t.me/tikvahethiopia/92370?single

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

08 Jan, 16:10


" ለልምድ ልውውጥ " በሚል ከተላኩበት ኖርዌይ ያልተመለሱት የፓርቲ አባላት ምን አሉ ?

🔴 " በተደጋጋሚ የግድያ ሙከራም ተደርጎብኛል መመለስ የማልችልበት ውስብስብ ጉዳይ ነው የገጠመኝ " -ወ/ሮ አበበች ደቻሳ

🔵 " መመለስ የማልችልባቸው ሁኔታዎች እንዳሉ በማወቄ ላለመመለስ ወስኛለሁ " -ወ/ሮ ቅድስት ግርማ


የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ቦዴፓ) የሴቶች ጉዳይ ሃላፊ ወ/ሮ አበበች ደቻሳ እና የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) የሴቶች ጉዳይ ተጠሪ የነበሩት ወ/ሮ ቅድስት ግርማ በመስከረም አጋማሽ ለልምድ ልውውጥ ወደ ኖርዌይ በሄዱበት እዛው መቅረታቸውንና ወደ ሀገር አለመመለሳቸውን መዘገባችን ይታወሳል።

ሁለቱ የፓርቲ አባላት ወደ ኖርዌይ ያቀኑት መስከረም 18/2017 ዓ/ም የነበረ መሆኑን እና በፖለቲካ ችግሮች ምክንያት እዚህ ውሳኔ ላይ ለመድረስ መገደዳቸውን ከሚገኙበት ሃገር ሆነው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል አረጋግጠዋል።

ከሃገር እስከወጡበት ጊዜ ድረስ የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የድባጤ ወረዳ የውሃ ፣ማዕድን እና ኢነርጂ ጽ/ቤት ሃላፊ እና በቦዴፓ የሴቶች ዘርፍ ሃላፊ የነበሩት ወ/ሮ አበበች ደቻሳ ፥ " ብዙ መስዋዕትነት ከፍያለሁ በተደጋጋሚ እኔም ባለቤቴም ለእስር ተዳርገናል አባቴም በግፈኞች ተገድሏል አለመመለሴ እርግጥ ነው ላለመመለስም ወስነናል " ብለዋል።

የመቅረት ውሳኔው የታሰበበት ሳይሆን ድንገተኛ ውሳኔ መሆኑን ጠቁመው " ስወጣ ሄጄ እቀራለሁ ብዬ አስቤበት አልነበረም ከነ ችግሩ በሃገሬ እታገላለሁ ብዬ እንጂ፣ ነገር ግን ከተመለስኩ ካሳለፍኩት በላይ የሆነ ችግር እየጠበቀኝ መሆኑን ስላረጋገጥኩ ነው የቀረሁት " ሲሉ ገልጸዋል።

" የሃገሪቱ ፖለቲካ ችግር ውስብስብ ከመሆኑም በላይ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ ነው " ያሉት ወ/ሮ አበበች " በክልሉ ያለው አመራር በኢንቨስትመንት መሬት እና በማዕድን ቦታዎች ዝርፍያ ተሰማርቷል " ሲሉ ከሰዋል።

በወረዳው የማዕድን ጽ/ቤት ሃላፊነት ላይ በነበሩበት ወቅት የታዘቡትን ሲያስታውሱ " ትልቁ ችግር ሙስና ነው ይህንን ተቃውመህ በህይወት መኖር አትችልም ይህን አዕምዬ ሊቀበል አልቻለም ብዙ ታግያለሁ ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያዎች ይደርሱኝ ነበር በመጨረሻም ለእስር ተዳርጌ ነበር በተደጋጋሚ የግድያ ሙከራም ተደርጎብኛል መመለስ የማልችልበት ውስብስብ ጉዳይ ነው የገጠመኝ " ብለዋል።

ከሃገር ከመውጣታቸው በፊትም ከባለቤታቸው እና ከልጆቻቸው ጋር ለእስር ተዳርገው እንደነበር ገልጸው ባለቤታቸው ብቻ በተለያዩ ጊዜያት ለ3 ወራት ያህል ለእስር ተዳርገው እንደነበር አስታውሰዋል።

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዉ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) የሴቶች ጉዳይ ተጠሪ የነበሩት ወ/ሮ ቅድስት ግርማ በበኩላቸው ላለመመለሳቸው ምክንያት ፓርቲያዊና ሃገራዊ ፖለቲካዊ ጉዳዮችን እንደምክንያት ጠቅሰዋል።

" እንዳልመለስ ያደረጉኝ ድንገተኛ ምክንያቶች ቢኖሩም እዚህ ከመጣሁ በኃላ መመለስ የማልችልባቸው ሁኔታዎች እንዳሉ በማወቄ ላለመመለስ ወስኛለሁ " ብለዋል።

" ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል ለኢትዮጵያ ያስፈልጋል ብዬ የማምን ሰው ነኝ " ያሉት ወ/ሮ ቅድስት ፥ " ነገር ግን እያደረግናቸው ያሉ ሰላማዊ ፖለቲካዊ ትግሎች ቆመንለታል ያልነውን ማህበረሰብ ከመገደል ፣ መፈናቀል እና ሞት አላዳነውም " ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

" ምንም እንዳላየ ሆኖ መቀጠል ከአዕምሮ በላይ ነው ሃገር ውስጥ ሆኖ ይህን ማድረግ አይቻልም ለህዝቤ ድምጽ መሆን ያስፈልጋል ብዬ ስለማምን ነው ይሄን ውሳኔ የወሰንኩት " ሲሉ ከሀገር ወጥተው የቀሩበት ምክንያት አስረድተዋል።

ከዚህ ቀደም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ የኢዜማ አባል ፤ አባሏ በስራ ገበታቸው ላይ አለመኖራቸው በማስረዳት " ለምን እንዳልተመለሱ የምናውቀው ነገር የለም " ማለቱ ይታወሳል።

ወ/ሮ ቅድስት በበኩላቸው " ከመቅረቴ ቀደም ብዬ ያለውን ነገር እና ላለመመለስ መወሰኔም ለፓርቲው ስራ አስፈጻሚዎች አሳውቄያለሁ ኢዜማ ውስጥ ያለው መቧደን እና መገፋፋቱ ፓርቲው እደርስበታለሁ የሚልበት ቦታ ላይ የማያደርስ በመሆኑ ፣ ይህም ለእኔ ፈታኝ መሆኑን እና የእኔ መገፋት ከመንግስት ብቻ ሳይሆን ከፓርቲውም ጭምር መሆኑን አሳውቅያለሁ " ብለዋል።

በኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት በኩል ለልምድ ልውውጥ ወደ ኖርዌይ ያቀኑት የምክር ቤቱ የሴቶች ክንፍ ስራ አስፈጻሚዎች ውስጥ የሚገኙ የኢዜማ ፣ ቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ፣ ኦነግ እና የወላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ (ወብን) ፓርቲ አባላት የነበሩ ሲሆን
#የኦነግ እና #የወብን አባላት የልምድ ልውውጡን አጠናቀው በወቅቱ ወደሃገር ተመልሰዋል።

#ThikvahEthiopiaFamilyAA

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

08 Jan, 11:16


#Earthquake

በአፋር ክልል አዋሽና አካባቢው እየተከሰተ ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ አሁንም ድረስ ቀጥሏል።

ትላንት ቀን እንዲሁም ለሊቱን ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል።

የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ በመዘገበው ብቻ በሬክተር ስኬል 4.5 ፣ 4.7 ፣ 5.3 የሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል።

ከሁሉም ከፍ ያለው ለሊት የተከሰተው በሬክተር ስኬል 5.3 ሲሆን የመሬት መንቀጥቀጡ አዋሽ እና አካባቢው በርካታ ሰዎችን ከእንቅልፋቸው ቀስቅስቋል።

ንዝረቱ አዲስ አበባ እና ሌሎች ከተሞችም ተሰምቷል።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦፊዚክስ ፣ ስፔስ ሳይንስ እና አስትሮኖሚ ተቋም ዳይሬክተር ኤልያስ ሌዊ (ዶ/ር) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰጥተው በነበረው ቃል ፤ ቅልጥ አለት መሬት ውስጥ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። ይህ እንቅስቃሴ በፈንታሌ እና በዶፈን ተራራዎች መካከል ሲሆን የሚታየው ርዕደ መሬት የዛ ውጤት ነው።

የዛ እንቅስቃሴ የፈጠረው መንቀጥቀጥ ሞገድ በመሬት ውስጥ ተጉዞ ነው አዲስ አበባ ድረስ የሚሰማው።

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

08 Jan, 11:14


🚨#ኮሬ

ታጣቂዎች አደረሱት በሚባል ጥቃት ከዘጠኝ ዓመታት በላይ የንጹሐን ግድያ ልጓም ባልተገኘለት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን አሁንም “ ንጹሐን ተገድለዋል ” ተብሏል።

ስማቸው እንዲነገር ያልፈለጉ የዞኑ አካል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ “ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት ባለፉት 48 ሰዓታት ብቻ የሁለት ሰዎች ህይወት አልፏል ” ብለዋል።

በዞኑ ኬረዳና ጀሎ በተሰኙት ቀበሌዎች  አንታዮ ዦላና አድማሱ አሰፋ የተባሉ ሰዎች ታጣቂዎቹ ሰነዘሩት በተባለ ጥቃት መገደላቸውን ከቤተሰቦቻቸው መረጋገጡን ነው የገለጹት።

አቶ አንታዮ ዦላ የተገደሉት ከትላንት በስቲያ ታኀሳስ 28 ቀን 2017 ዓ/ም ከቀኑ 11 ሰዓት ተኩል ኬረዳ ቀበሌ መሆኑን አስረድተው፣ “ ገዳዮቹ ከጋላና ወረዳ ሻሞሌ ሽዳ ታጥቀው ወደ ኮሬ ዞን ዘልቀው ገብተው ነው ” ብለዋል።

“ በዚሁ ቀበሌ ጥቃት ከመፈጸም ተጨማሪ የቤት እንስሳትን ዘርፈዋል ” ብለው፣ “ አድማሱ አሰፋ ደግሞ ታኀሳስ  29 ቀን 2017 ዓ/ም ከቀኑ 6:30 ገደማ ጄሎ ቀበሌ ተገድሏል ” ሲሉ ገልጸዋል።

“ ገዳዮቹ የጋላና ወረዳ የቡልቶ ጃልደሳ ታጣቂዎች ወደ ኮሬ ዞን ዘልቀው በመግባት ጥቃት ፈጽመው ነው ” ብለዋል።

“ ባለፉት ቀናት ጥቃት ለመሰንዘር ከፍተኛ እንቅስቃሴ እንደነበር ከህዝብ አስተያየት መረጃ መመልከት ተችሎ ነበር። መረጃዎቹ ከጃሎ፣ ኬረዳ፣ ዞቀሣ፣ ጋሙሌ፣ ሻሮ፣ ጎልቤ፣ ቆቦ፣ ዶርባዴ ቀበለያት ተሰባስበዋል” ነው ያሉት።

የንጹሀን ጥቃቱ እንዲቆም ለመንግስት አሳስበው እንደሆን በቅርቡ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው በሕዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የዞኑ ሕዝብ ተወካይ አምዛዬ አወቀ (ዶ/ር)፣ በፓርላማ ቢያሳውቁም ድርጊቱ እንዳልቆመ ገልጸው ነበር።

“ ነዋሪዎቹ በየቀኑ ይገደላሉ። የአንዱ ግድያ ይገለጻል፤ የአንዱ አይገለጽም ሰው ተሰላችቶ” ብለው፣ “መንግስት ትኩረት ቢሰጥ ኖሮ ያ አካባቢው የሚያስቸግር አይደለም ጠባብ ቦታ ነው ገላና ሸለቆና ነጭ ሳር ፓርክ እነዚህ ሽፍቶች የሚንቀሳቀሱበት ነው ” ብለው ነበር።

ከዚህ ቀደም ስለጉዳዩ የጠየቅናቸው በክልሉ ምክር ቤት የቀድሞ አማሮ ምርጫ ክልል ተወካይ አቶ ዜናነህ አዱላ በበኩላቸው፣ “ አካባቢው ከ2009 ዓ/ም ጀምሮ በጸጥታ ችግር የወደቀ ነው ” ማለታቸው ይታወሳል።

“ በአካባቢው ላይ ከመንግስት ተቃርኖ የሚንቀሳቀሰው የሸኔ ታጣቂ መኖሩ ሁኔታውን አባብሶታል” ብለው፣ “ ‘መንግስት ቸልተኛ ሆኗል’ የሚል ግምገማ አለን ” ሲሉ ተናግረው ነበር።

ከወራት በፊት ቃሉን የሰጠን ዞን ኮሚኒኬሽን “ ባለፉት ዓመታት ከ300 በላይ ንጹሐን በታጣቂዎች ተገድለዋል ” ማለቱ አይዘነጋም።

#ThikvahEthiopiaFamilyAA

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

08 Jan, 11:14


#Abyssiniabank

አይዞን ለበዓል እኛ አለን።

ከአፖሎ እንዴት አነስተኛ ብድር መውሰድ እንደሚቻል ለማየት ሊንኩን ይጠቀሙ፡ https://t.me/apollodigitalproduct/220

ለአንድሮይድስልኮች https://play.google.com/store/apps/details?id=com.boa.apollo&hl=en&gl=US
ለአፕል ስልኮች  https://apps.apple.com/us/app/apollo-digital/id1601224628

#Apollodigitalbank #Apollodigitalproduct #poweredbybankofabyssinia #BankofAbyssinia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all

THIKVAH-ETHIOPIA

04 Jan, 20:38


#Update

ከጥቂት ከደቂቃዎች በፊት ተከስቶ የነበረው የመሬት መንቀጥቀጥ በሬክተር ስኬል 5.0 የተለካ እንደሆነ የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ አሳውቋል።

የመሬት መንቀጥቀጡ ከአዋሽ 31 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የተከሰተ ነው።


ዛሬ በተለያየ ሰዓት አምስት ጊዜ የመሬት መንቀጥቀጥ የተከሰተ ሲሆን የአሁኑ ለስድስተኛ ጊዜ የተከሰተው (በሬክተር ስኬል 5.0 የተለካው ) በመጠን ከፍተኛው ነው።

ንዝረቱ አዲስ አበባና ሌሎች ከተሞች ላይ በደንብ ተሰምቷል።

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

04 Jan, 20:16


#Earthquake : ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ንዝረቱ አዲስ አበባ ድረስ የተሰማ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ ነበር።

ቤት ውስጥ ፣ አልጋ ላይ፣ ከቤት ውጭ የነበሩ ሰዎች ንዝረቱ ተሰምቷቸዋል።

ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ አሁንም በመቀጠሉ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳትዘናጉ።

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

04 Jan, 19:56


#Earthquake

ትላንት ለሊት 9:52 ላይ በርካቶችን ከተኙበት የቀሰቀሰው በሬክተር ስኬል 5.8 ከተለካው የመሬት መንቀጥቀጥ በኃላ በሬክተር ስኬል 4.4 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ እንደነበር መረጃ መለዋወጣችን ይታወሳል።

ዛሬ ደግሞ በሬክተር ስኬል ፦
➡️ 4.7
➡️ 4.6
➡️ በድጋሚ 4.7
➡️ በድጋሚ 4.6
➡️ 4.9 የተለኩ የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተቶች ተመዝግበዋል።

ሁሉም አዋሽ እና አካባቢው ናቸው።

ባለፉት ሰዓታት ከተመዘገበው ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ 4.9 ከፍተኛው ነው።

በሌላ በኩል አፋር ክልል ዱላሳ ወረዳ የሚገኘው የኢፌዴሪ ከሰም ስኳር ፋብሪካ በመሬት መንቀጥቀጡ ከፍተኛ ጉዳት አስተናግዷል።

በስኳር ፋብሪካው አስተዳደር ህንፃ፣ በኃይል ማስተላለፊያ ክፍል፣ የላብራቶሪ እና ኤሌክትሮ ሜካኒካል ክፍል ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል።

አሁን ላይ መሬት መንቀጥቀጡ በከፍተኛ ሁኔታ በአከባቢው እየጨመረ በመምጣቱ ጉዳት በደረሰባቸው ህንፃዎች ውስጥ የሚገኙትን ሌሎች ንብረቶችን ለማዳን የመሬት መንቀጥቀጡ ከፍተኛ ስጋት ደቅኗል።

የፋብሪካው ሰራተኞች ላይ ጉዳት እንዳይደርስ አስቀድሞ እንዲለቁ መደረጉ ተነግሯል።

ከ4 ሺህ በላይ ሰራተኞች ያለው የከሰም ስኳር ፋብሪካ በመሬት መንቀጥቀጡ ምክንያት አሁን ላይ ሙሉ በሙሉ ስራ ማቆሙን ብሔራዊ ቴሌቪዥን ዘግቧል።

በተያያዘ መረጃ ፥ መንግሥት የርዕደ መሬቱ ማዕከል ከሆኑ አካባቢዎች ነዋሪዎችን የማራቅ ሥራ እያከናወነ መሆኑን አሳውቋል።

በተለይም ደግሞ የርዕደ መሬቱ ማዕከል የሆኑት አካባቢዎችን በመለየት በ12 ቀበሌዎች ላይ ከተለያዩ የሙያ ዘርፎች የተውጣጡ የአደጋ ጊዜ ሠራተኞችን በቦታው በማሰማራት የጉዳቱን መጠን አሰሳ እየተደረገ እንደሚገኝ ተገልጿል።

በእነዚህ ቀበሌዎች ከሚኖሩ 80 ሺህ ዜጎች ቅድሚያ የሚሰጣቸውን በመለየት ነዋሪዎችን ከአካባቢው በማራቅ ለማስፈር ርብርብ እየተደረገ መሆኑም ተጠቅሷል፡፡

#Ethiopia #Afar #Earthquake

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

04 Jan, 18:19


#የአእላፋትዝማሬ #TheMelodyofMyriads

“ ኦርቶዶክሳዊያን ወጣቶች ልደትን በቤተ ክርስቲያን አሳልፉ ፤ በአዲስ አበባና በድሬዳዋ የምትገኙም በዝማሬው ላይ እንድትገኙ ” - የኢትዮጵያ ጃንደረባው ትውልድ (ኢጃት)

ታኅሳስ 29 ቀን 2017 ዓ/ም የሚከበረውን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል ምክንያት በማድረግ የኢትዮጵያው ጃንደረባ ትውልድ ያዘጋጀው “ልደትን በባለ ልደቱ ቤት” የተሰኘውን የአእላፍ ዝማሬ በተመለከተ አዘጋጆቹ ዛሬ በስካይ ላይት ሆቴል መግለጫ ሰጥተዋል።

የዝማሬ ጉባዔው በአዲስ አበባ በድሬዳዋ እንደሚከናወን የገለጹት አዘጋጆች፣ “ ላለፉት ስምንት ወራት ለዚህ ታላቅ የዝማሬ ጉባዔ ከፍተኛ ዝግጅት ሲደረግ ቆይቷል ” ብለዋል።

የጉባዔው ዋነኛ ዓላማ በአልባሌ ቦታ የሚውሉ ወገኖች በዓሉን በቤተክርስቲያን የመላክትን ዝማሬ በመዘመር እንዲያሳልፉ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተመልክቷል።

የኢትዮጵያው ጃንረባ ትውልድ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ቢንያም አሕመድ ፤  “ ኦርቶዶክሳዊያን ወጣቶች ልደትን በቤተ ክርስቲያን አሳልፉ ፤ በአዲስ አበባና በድሬዳዋ የምትገኙም በዝማሬው ላይ እንድትገኙ ” ብለዋል።

“ በሌሎች አካባቢዎች ላይ የተዘጋጁ ዝግጅቶች ካሉም በእዛው በመገኘት እንድታሳልፉ የኢትዮጵያ ጃንደረባው ትውልድ ጥሪ ያቀርባል ” ሲሉ አሳስበዋል።

በመርሃ ግብሩ በቤተክርስቲያን ቅጽር ግቢ ውስጥ ምንም አይነት ሽያጭ እንደማይከናውን አዘጋጆቹ አሳውቀዋል።

በሌላ በኩል፣ “ አእላፋት ዝማሬ ነጭ ልብስ ልበሱ ” ተብሏል በሚል ነጭ ልብስ በተጋነነ ዋጋ የሚቸበችቡ ሁነቱን የተከተሉ ነጋዴዎች ተስተውለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ነጭ ልብስ በውድ ወጋ እየተቸበቸበ ነው የሚል አስተያዬት እየተሰጠ ተስተውሏል፣ ለመርሀ ግብሩ ነጭ ልብስ ብቻ ለብሶ መምጣት ግዴታ ነው ? ሲል ለአዘጋጆቹ ጥያቄ አቅርቧል።

የኢትዮጵያው ጃንረባ ትውልድ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ብንያም አሕመድ በሰጡት ምላሽም፣ “ ነጭ ልብስ የሌለን ያለንን ልብስ ንጹህ አድርገን እንምጣ። ዓላማችን ልብሱ ለመቁረቢያ እንዲሆን ነው ” ብለዋል።

“ ኦርቶዶክሳዊ ኢኮኖሚ እንዲፈጠር ይፈለጋል ግልጽ ነው። በዚህ ምክንያት ወደ ስራ የሚገቡ፣ ሥራቸውን የሚያስፋፉ፣ የሚለወጡ ኦርቶዶክሳዊያን ቢኖሩ ይሄ የማኀበራችን አንዱ ዓላማ ነው ” ሲሉ ነው የተናገሩት።

“ ስለዚህ ይህን በቀና ዓይን ነው የምናየው ” ያሉት አቶ ብንያም፣ “ በእርግጥ በዚሁ ምክንያት ደግሞ አጋጣሚውን የሚጠቀሙ፣ Accidental Entrprenuers የምንላቸው መጥተው ባለሃብት ለመሆን የሚጥሩ ይኖራሉ ” ሲሉም አክለዋል።

“ ልደቱ የሰዎች የመላክት ዝማሬ ነው። ስለዚህ ይህንን በማሰብ ነጭ ለብሰን እንመጣለን ” ብለው፣ “ ዘወትር ወደ ቤተ ክርስቲያን ስንሄድ የምናደርገው ነው፣ የተለዬ ነገር የለውም ” ነው ያሉት።

ሆኖም ነጭ ልብስ የሌላቸው ያላቸውን ልብስ በአግባቡ ለብሰው በዝማሬ መርሀ ግብሩ መገኘታቸው እንዳይዘነጋ መልዕክት ተላልፏል። 

ዝማሬው ዘማሪያን እየዘመሩ ምዕመናን የሚቀበሉበት ሂደት ሳይሆን ልደቱን በሚያወሱ ዝማሬዎች ሁሉም በጋራ ምስጋና እንዲያቀርብ መሆኑ ተሰምሮበታል።

#ThikvahEthiopiaFamilyAA

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

04 Jan, 17:57


#መግለጫ : " የአእላፋት ዝማሬ/The Melody of Myriads " ሰኞ በአዲስ አበባ እና በድሬዳዋ በተመሳሳይ ሰዓት ይካሄዳል።

ይህንን አስመልክቶ የተሰጠው መግለጫ ከላይ ተያይዟል።

የዘንድሮው የእላፋት ዝማሬ / The Melody of Myriads በአዲስ አበባ በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም ካቴድራል (ቦሌ መድኃኔዓለም) ፤ በድሬዳዋ ደግሞ ለገሀር አደባባይ ብቻ ነው የሚካሄደው።

(መግለጫውን ያንብቡ)

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

06 Dec, 19:09


#ድሬዳዋ

" አንድም ጫኝ እና አውራጅ የሚባል ነገር እንዳይኖር። ነግሬያችኃለሁ !! " - ኮሚሽነር ዓለሙ

የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ዓለሙ መግራ ድሬ ውስጥ ሰዎች ቤት ሲቀይሩ " ጫኝ አውራጅ ነን እያሉ የሚከተሉ ጎረምሶች እንዳይኖሩ " ሲሉ ትዕዛዝ አስተላለፉ።

ይህን እጅግ ጠንካራ ትዕዛዝ የሰጡት ከከተማውን የፀጥታ አመራሮች ጋር በመከሩበት ወቅት ነው።

በህዝብ ላይ እንግልትና ዘረፋ በሚፈፅሙ ጫኝና አውራጆች ላይ የተጠናከረ እርምጃ ይወሰዳል ተብሏል።

ኮሚሽነር ምን አሉ ?

" ሰፈር ላይ ቁጭ ብሎ ሰው ቤት ሲቀይር ጫኝ አውራጅ ብሎ የሚከተል ጎረምሳ እንዳይኖር።

በየቀጠናችን ያለው የጫኝ አውራጅ ስቃይ ህዝቡን ብታዩ አንድም ጫኝ እና አውራጅ የሚባል አደረጃጀት የለም።

ይሄን ያደራጀ ሰው ካለ ኃላፊነቱን አናውቀውም።

አንድም ጫኝ እና አውራጅ በየትኛውም ቀጠና የውሃ ፋብሪካ ምናም ካልሆነ በስተቀር ሰፈር ላይ ቁጭ ብሎ ሰው ቤት ሲቀይር ጫኝ አውራጅ ብሎ የሚከተል ጎረምሳ እንዳይኖር።

ይሄ ከተገኘ እወቁ ! አንድም ቦታ ሰውዬው ሲፈልግ ተሸክሞ ያውርድ ሲፈልግ ይስበረው።

በቀደም አንዱ መጥቶ ነገረኝ ትንሽ እቃ ነው በዳማስ ሄዶ ቀስ ቀስ እያለ አወረደ ... ከዛ ሮጠው መጡና አንኳኩ ' ክፈቱ ' አሉ ግር ብለው ገቡ ፤ እቃው ወርዷል ከዛ ' ስጡን (ብር) ' አሉ ለምን ? ' የደንቡን ' የምን ደንብ ? እኛ አውርደናል እቃችንን አላቸው ' ሊሰጠን ይገባል አታውቅም እንዴ ይሄ የሰፈሩ ደንብ ነው ' አሉ።  ሰውዬው ወደ ፖሊስ ሲደውል ከግቢ ወጥተው በር ላይ ቁጭ አሉ። ትንሽ ሲቆይ አንድም ሁለትም እየሆኑ ሄዱ።

እኚህ ወጣቶች ሌላ ቀን ወንጀል ከመስራት ወደኃላ አይሉም። ለዚህ ነው ሰግቶ የነገረኝ።

ሰው በፍራሃ ነው ያለው።

አይቻልም አንድም ጫኝ እና አውራጅ የሚባል !! ነግሬያችኃለሁ።

ቤት ሲቀየር ገና ሰው እዛ ጋር መጥቶ የሚያወርደውን ነገር ታሳቢ ተደርጎ ነው ሰው የሚደራጀው ስራ ?

አይቻልም !

ብሎኬት ማውረድ ከፈለገ ሰውየው ቤት ሲሰራ እዛው ጋር የሚሰሩትን ሰዎች ማስወረድ ይችላል ፤ ሌላ ሰው ጠርቶ ዋጋ ተደራድሮ እሱ ባለው ዋጋ ማስወረድ ይችላል አለቀ።

' እኔ ማህበር ነኝ ፤ እኔ እንደዚህ ነኝ ' ማን እንዳደራጃቸው የማይታወቁ።

አንድም እንዳይኖር ይሄን ሰፈራችሁ ላይ አወያዩ ፤ ማህበረሰቡ ይሄን ይወቅ ለናተ መረጃ ይስጣችሁ። ሰፈር መድረስ ማለት ይሄ ነው።

ጫኝ እና አውራጅ ጣጣው በጣም ብዙ ነው " ብለዋል።

ይሄ የጫኝ እና አውራጅ ስቃይ የድሬዳዋ ብቻ አይደለም። በአዲስ አበባ በየሰፈሩና በክልል ከተሞች ተመሳሳይ ነው።

ገና ሰው እቃ ይዞ ሲመጣ " እኛ ካላወረድን ማንም ማውረድ አይችልም " በሚል አምባጓሮ የሚፈጡ አሉ።

አውርዱ ሲባሉ ደረታቸውን ነፍተው የሚጠሩት ብር ደግሞ አስደንጋጭ ነው።  ሰው በስንት ድካም ገንዘቡን እንደሚያገኝም አይረዱም።

ሰው ከፍራቻ የተነሳ በስንት መከራና ጭቅጭቅ ከፍተኛ ዋጋ ከፍሎ እቃውን ያስወርዳል። " ነገ የት እኖራለሁ " ብሎ በመፍራት።

እራሱና ቤተሰቦቹ፣ ጓደኞቹ በጋራ የገዛ እቃቸውን እንዳያወርዱ ዛቻ ሁሉ ሊፈጸምባቸው ይችላል።

ይህንን ስርዓት አልበኝነት እና ድንፋታ እንዲያስቆሙ የሚጠሩ አንዳንድ የፀጥታ አባላት ነገሩን ለማስተካከል እርምጃ ከመውሰድ ይልቅ የሚሉት ' ከነሱ ጋር ተስማሙ ' ነው።

ሰው ከፍራቻ የተነሳ ለሊት እቃውን ይዞ ይገባል። በገዛ ሀገሩ በገዛ ከተማው በገዛ እቃው ተሳቆ ነው የሚኖረው። ስቃዩ ብዙ ነው !

#ThikvahEthiopiaFamily

#DirePolice #ድሬ

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

06 Dec, 17:59


#Tigray

በመቐለ ማንኛውም ሰላማዊ ስልፍ እንዳይካሄደ ተከለከለ ፤ ክልከካው አስከ መቼ እንደሚቀጥል የተገለፀ ነገር የለም።

በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት በመቐለ ከተማ ተደረግብኝ ላለው የከንቲባ መፈንቅለ ስልጣን " ሰላማዊ ስልፍ እንዳካሂድ ይፈቀድልኝ " ሲል በመቐለ የህወሓት ፅህፈት ቤት በኩል ህዳር 25/2017 ዓ.ም ለመቐለ ከተማ አስተዳደር በፃፈው ደብዳቤ ጥያቄ አቅርቧል።

ሰልፉን እሁድ ህዳር 29/2017 ዓ.ም ከጥዋቱ 2:30 እስከ ቀኑ 6:30 ለማድረግ ነበር የጠየቀው።

ድርጅቱ ሰላማዊ ሰልፍ እንዲያካሂድ በጠየቀበት ደብዳቤው ፤ " ህዳር 23/2017 ዓ.ም የተፈፀመው በመሳሪያ የተደገፈ የመቐለ ከተማ መደበኛ አስተዳደር  መፈንቅለ ስልጣን ለማውገዝ " ነው ብሏል።

በተጨማሪም ፥ " ለዘመናት በከፈልነው መስዋእት ያፀናነው መብታችን እና የመሰረትነው ምክር ቤት በአዲስ ገዢ ግለሰቦች አምባገነንነት ሲፈርስ አንታገስም " ሲል ገልጿል።

ደንረጽዮን (ዶ/ር) የሚመሩት ቡድን "  ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ እንድናካሂድ በተደጋጋሚ ከአባሎቻችን በቀረበልን ጥያቄ መሰረት ፤ እሁድ ህዳር 29/2017 ዓ.ም ከጥዋቱ 2:30 አስከ ቀኑ 6:30 ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ እንድናካሂድ ቅድመ ዝግጅት ስላጠናቀቅን ፍቃድ እንዲሰጠን እና የፀጥታ ጥበቃ እንዲደረግልን እንጠይቃለን " ሲል ነው በደብዳቤው የገለጸው።

ለመቐለ ህወሓት ፅህፈት ቤት ደብዳቤ ዛሬ አርብ ህዳር 27 /2017 ዓ.ም ምላሽ የሰጠው የመቐለ ከተማ አስተዳደር በበኩሉ የከተማው ጥምር ኮሚቴ በሰጠው መምሪያ መሰረት በመቐለ ከተማ ማንኛውም ሰላማዊ ሰልፍ እንዳይካሄድ #ተከልክለዋል ብሏል።

#ThikvahEthiopiaFamilyMekelle

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

06 Dec, 17:50


🔈#የተማሪዎችድምጽ

🔴 " ስኮላርሺፕ እና የውጭ ስራ እድሎች ኦርጅናል ዲግሪ ባለመስጠታቸው ምክንያት እያመለጠን ነው " - ተመራቂ ተማሪዎች

🔵 " ዲግሪያቸውን መስጠት ያልተቻለው ዩኒቨርሲቲው ላይ ባለ የበጀት እጥረት ምክንያት ነው " - የዩኒቨርሲቲው አመራር

የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ከተመሰረተበት 1999 ዓ/ም ጀምሮ ላለፉት አመታት ላስመረቃቸውን ተማሪዎች ኦርጂናል ዲግሪ ባለመስጠቱ በርካታ ተመራቂ ተማሪዎች የስኮላርሺፕ እና የውጭ የስራ እድሎች እያመለጧቸው መሆኑን ቅሬታቸውን በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አሰምተዋል።

ተመራቂ ተማሪዎቹ ሲመረቁ የወሰዱት ጊዜያዊ (Temporary) ዲግሪ ሲሆን አስፈላጊውን የኮስት ሼሪንግ ክፍያ እና የአገልግሎት ጊዜያቸውን በመፈጸም ኦርጅናል ዲግሪያቸውን ከዩኒቨርሲቲው ቢጠይቁም በየጊዜው " ይሰጣችኋል " ከማለት ውጪ ምንም ምላሽ አላገኘንም ብለዋል።

" ኦርጅናል ዶክመንት አሳትሙልን ስንል ' ይታተማል ' ይባላል ግን መቼ የሚለው አይመለስም " ሲሉ ነው የገለጹት።

አክለውም " በቅርብ የተመሰረቱ ዩኒቨርሲቲዎች እየሰጡ ነው ለሚዛን ቴፒ ከባድ ያደረገው ምንድነው?በቂ የሚሉት ምክንያት የላቸውም ምክንያታቸው ለእኛም ግራ አጋብቶናል " ብለዋል።

ተመራቂ ተማሪዎች የቴሌግራም ግሩፕ በመክፈት እና ፊርማ በማሰባሰብ ዩንቨርስቲውን በተደራጀ መልኩ ጥያቄያቸውን ለማቅረብ እያሰቡ መሆኑን ነግረውናል።

የዩንቨርስቲው ምን ምላሽ ሰጠ ?

ኦርጅናል ዲግሪያቸውን ለተመራቂዎች አሳትሞ መስጠት ያልተቻለው በዩኒቨርሲቲው ከባድ የሚባል የበጀት እጥረት በመኖሩ መሆኑን ስሜ አይጠቀስ ያሉ የዩኒቨርሲቲው አመራር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ነገር ግን ዩኒቨርሲቲው በዚህ ዓመት እስከ 2002 የተመረቁ ተመራቂዎችን ዲግሪ ለመስጠት ማቀዱን እና በ2018 በጀት አመት ደግሞ የቀሪ ተማሪዎችን ለመስጠት በእቅድ መያዙን ገልጸዋል።

ወደማተሚያ ቤት የተላከው እስከ 2002 ከተመረቁት መካከል የግማሹ ተመራቂዎች ብቻ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

" ከሁለት ወይም ሦስት ወር በኋላ እስከ 2002 ያሉ የመደበኛ፣የማታ እና የክረምት (Summer) ተመራቂዎች ይወስዳሉ ብዬ አስባለሁ እስካሁን ያልተሰጣቸው ዩኒቨርስቲው ላይ ባለ የበጀት እጥረት ምክንያት ነው አሁን ለማተሚያ ቤት ከ175 ሺ ብር በላይ ቅድመ ክፍያ ከፍለን እንዲታተምላቸው ተልኳል " ብለዋል።

ቀሪ ተማሪዎች በምን ያህል ጊዜ ይወስዳሉ ? ስንል ላነሳንላቸው ጥያቄም " አለን በምንለው በጀት አጣበን የሚቀሩትን እንሰጣለን ብዬ አስባለሁ የሚከብደን አይመስልኝም " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ሃላፊው ዩኒቨርስቲው ኦርጂናል ዲግሪ ያልሰጣቸው አጠቃላይ ተመራቂ ተማሪዎች ቁጥር ምን ያህል መሆኑን ከመናገር ተቆጥበዋል።

#ThikvahEthiopiaFamilyAA

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

06 Dec, 17:50


#Ethiotelecom

የአክሲዮን ሽያጩ ሊጠናቀቅ እየተቃረበ ነው!

❇️ የኢትዮ ቴሌኮም 10% አክሲዮን ሽያጭ ብስራትን ተከትሎ 100 ሚሊዮን መደበኛ አክሲዮኖች እየተሸጡ ይገኛሉ!

የአንድ ሼር ዋጋ 300 ብር፣ ዝቅተኛ መግዛት የሚቻለው የሼር መጠን 9,900 ብር (33 አክሲዮኖች)፣ ከፍተኛው 999,900 ብር (3,333 አክሲዮኖች) ነው፡፡

💁‍♂️ የአክሲዮን ሽያጩ በቴሌብር ሱፐርአፕ https://onelink.to/uecbbr ይከናወናል፤ እርሶም የዕድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተጋብዘዋል፡፡

🗓 ለገበያ የቀረቡት አክሲዮኖች ቀድሞው ተሸጠው ካልተጠናቀቁ እስከ ታኅሣሥ 25/2017 ዓ.ም ይቆያል፡፡

ለተጨማሪ: https://bit.ly/3Y9JUae ይመልከቱ!

📖 የደንበኛ ሳቢ መግለጫውን https://teleshares.ethiotelecom.et/ ያንብቡ፡፡

#telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

06 Dec, 14:11


#ነዳጅ

የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል ተብሏል።

የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ፤ የታህሳስ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በህዳር ወር በነበረበት የመሽጫ ዋጋ እንዲቀጥል በመንግሥት መወሰኑን አሳውቋል።

ሚኒስቴሩ " የነዳጅ ማደያዎች እና ኩባንያዎች ያልተገባ የነዳጅ ክምችት ከመያዝ እና የዋጋ ጭማሪ ከማድረግ ተቆጥበው ውሳኔውን ተግባራዊ በማድረግ ህብረተሰቡን በቅንነትና በታማኝነት እንዲያገለግሉ " ሲል አሳስቧል።

የነዳጅ ምርቶች ዋጋ ስንት ነው ?

➡️ ቤንዚን - ብር 91.14 በሊትር
➡️ ነጭ ናፍጣ - ብር 90.28 በሊትር
➡️ ኬሮሲን - ብር 90.28 በሊትር
➡️ ቀላል ጥቁር ናፍጣ - ብር 100.20 በሊትር
➡️ ከባድ ጥቁር ናፍጣ - ብር 97.67 በሊትር 
➡️ የአውሮፕላን ነዳጅ - ብር 77.76 በሊትር ሆኗል።

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

06 Dec, 10:34


#ስደት🚨

" ባለፉት 15 ወራት ብቻ ከ38 ሺህ በላይ ወጣቶች ተሰደዋል ፤ ከ6 ሺህ በላይ የሚሆኑት ህይወታቸው አልፏል " - የትግራይ ስፖርትና ወጣቶች ቢሮ

🚨 " ያሉት ችግሮች ወጣቱን ተስፋ በማሳጣት ህገወጥ ስደትን እንደ ብቸኛ አማራጭ እንዲመለከት እያደረጉት ነው !  "

በትግራይ በተካሄደው አስከፊና እውዳሚ ጦርነት ምክንያት የወጣቶች ህገ-ወጥ ስደት እንግልትና ሞት በእጅጉ ተባብሶ መቀጠሉ ተነግሯል።

የፕሪቶሪያ ውል ተሟልቶ አለመፈፀሙ ፣ የመልሶ ግንባታ  ስራዎች አለመጀመራቸው ፣ ሰፊ የስራ እጦት መኖር ለህገ-ወጥ የወጣቶች ፍልሰት መባባስ ምክንያቶች ናቸው ተብለዋል።

ይህን የሰማነው የትግራይ የስፖርትና የወጣቶች ጉዳይ ቢሮ ከለጋሽ ድርጅቶች በመተባበር " ህገ-ወጥ ስደት " በሚል ካዘጋጀው አንድ መድረክ ላይ ነው።

ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በኋላ የበርካታ ወጣቶች ህይወት እየነጠቀ ያለውን ህገ-ወጥ ስደት አስመልክቶ በ49 የክልሉ ወረዳዎች በተካሄደ ጥናት ባለፉት 15 ወራት ብቻ ከ38 ሺህ በላይ ወጣቶች መሰዳዳቸው ያሳያል።

ከ38 ሺህ ስደተኞች ከ6 ሺህ በላይ ባለፈው ዓመት በጉዞ እያሉ ለህልፈት ተዳርገዋል ፤ አካላቸው የጎደለ አሉ ፣ አድራሻቸው የጠፉም ብዙ ናቸው።

2017 ዓ.ም ከገባ ወዲህ ብቻ  ከ6 ሺህ በላይ ወጣቶች በህገወጥ መንገድ ተሰደዋል ከነዚሁ ደግሞ 300 ገደማ ለህልፈት ተዳርገዋል።

አደጋው የክልሉ ከፍተኛ ስጋት ወደ መሆን ተሸጋግረዋል ሲል ቢሮው አሳውቋል።

በትግራይ በጦርነቱ ምክንያት ፦
የኢኮኖሚ አውታሮች ወድመዋል ፣
የብድር አገልግሎት መስጠት እጅግ የደከመ ነው፣
ሰፊ የስራ እጦት አለ እነዚህን እና ሌሎች ችግሮች ወጣቱ ተስፋ በማሳጣት ህገወጥ ስደት እንደ ብቸኛ አማራጭ  እንዲመለከት አድርገውታል።

ይህ ከፍተኛ ችግር እንዲቀረፍ የፌደራል መንግስትና ለጋሽ ድርጅቶች ድጋፋቸው እንዲቸሩ የትግራይ ክልል ስፖርትና ወጣቶች ቢሮ ጥሪ አቅርቧል።

#ThikvahEthiopiaFamilyMekelle

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

06 Dec, 10:33


“ የህክምና ገንዘብ ባለማግኘቱ ምክንያት ወጣቱ የአልጋ ቁራኛ ሆኗል ” - የታማሚው ወዳጆች

የልብ ቧንቧ መደፈን ህመም የገጠመው ሚካኤል ኑሩ የተባለ ወጣት በገንዘብ እጥረት ሲከታተለው የነበረውን ህክምና በማቋረጡ ረዳት በሌለበት የአልጋ ቁራኛ መሆኑን የቅርብ ሰዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

የታማሚው የቅርብ ሰዎች በሰጡት ቃል፣ “ ታማሚው ወጣት ወንድም፣ እህት የለውም። ለእናቱ አንድ ልጅ ነው። እናቱም የአልጋ ቁራኛ ናቸው ” ብለዋል።

የ25 ዓመቱ ወጣት ሚካኤል ሹፌር እንደነበር በመታመሙ ሥራ እንዳቆመ፣ በመጀመሪያ ወደ ዘውዲቱ ሆስፒታል ቢወሰድም ወረፋ መጠበቅ ስላለበትና ህመሙ ደግሞ ጊዜ የማይሰጥ በመሆኑ የግል ሆስፒታል መታከም እንዳለበት እንደተነገረው አስረድተዋል።

“ በመጀመሪያ ህክምና ሁላችንም አዋጥተን አሳከምነው በግል ሆስፒታል። ከዚያ በኋላ የተጠየቅነውን ብር ማግኘት አልተቻለም። በ400 ሺሕ ብር የመጀመሪያውን ህክምና ነበር ማግኘት የሚችለው የሚያስፈልገው ከ700 ሺሕ እስከ 1 ሚሊዮን ብር ነው የተባለው ” ነው ያሉት።

“ ሁለተኛውን ህክምና ለመከታተል ብር ስሌለ ሆስፒታሉ አስወጣው ‘ብሩን ስታገኝ ረጅም ጊዜ ሳትቆይ መጥተህ ታከም’ ተባለ። የህክምና ገንዘብ ባለማግኘቱ ምክንያት ወጣቱ የአልጋ ቁራኛ ሆኗል ” ሲሉ ተናግረዋል።

ከመታከሙ በፊት ይታዩበት የነበሩ የበሽታው ምልክቶች እንደተስተዋሉበት እንደሆነ፣  ህክምናውን ለማጠናቀቅ 500 ሺሕ ብር ስለሚያስፈልገው ልበ ቀና ኢትዮጵያዊ ሁሉ ርብርብ እንዲያደርጉለት ተጠይቋል።

መርዳት ለምትሹ የታሪኳ ተሰማ ለማ የንግድ ባንክ ሒሳብ ቁጥር 1000029724842 ነው። ደውሎ ለመጠየቅ 0913645873 የታሪኳ ስልክ ቁጥር ነው።

#ThikvahEthiopiaFamilyAA

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

06 Dec, 10:33


#TecnoAI

በንግድ እና ቢዝነስ ስራዎት ሁነኛ አማካሪ፣ አጋዥ እና ባለሙያ ያስፈልጎታል? አዲሱ ቴክኖ ኤ አይ ሁሉንም ስራዎትን ጥንቅቅ ባለ ደረጃ ሊከውን እየመጣ ነው፡፡

ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመከተል የቴክኖ ቲክቶክ ገጽ ፎሎው በማድረግ እና Bio ላይ ያለውን ሊንክ ተጭነው በመመዝገብ ታህሳስ 10 በስካይላይት ሆቴል በሚካሄደው የሀገራችን ትልቁ የኤ አይ ሁነት ላይ ይሳተፉ፡፡

https://www.tiktok.com/@tecnoet

@tecno_et @tecno_et

THIKVAH-ETHIOPIA

06 Dec, 10:33


@HibretBanket

Experience 25+ YEARS OF BANKING

At Hibret Bank, we are committed to exceeding your expectations.

Hibret Bank
United, We prosper!


📞  For more information call our free call center - 995. 
🤳 To receive new information join our Telegram page. https://t.me/HibretBanket
🌐 Visit our other social media pages and wesite on   linktr.ee/Hibret.Bank

THIKVAH-ETHIOPIA

05 Dec, 21:40


#ArbaMinch : ላለፉት በርካታ ዓመታት አርባ ምንጭ ላይ ሲገነባ የቆየው የጋሞ አደባባይ ተመርቋል።

" አደባባዩ በዞኑ የሚገኙ ህዝቦችን ባህል እና ትዉፊት በሚወክል መልኩ ነው የተሰራው " ሲል የዞኑ አስተዳደር ገልጿል።

ለዚህ አደባባይ ከ122,000,000 ብር (መቶ ሃያ ሁለት ሚሊዮን ብር) በላይ ወጪ እንደተደረገበት ነው የተነገረው።

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

03 Dec, 19:01


" ልመና አልነበረም ማለት አይደለም ፤ አሁን ግን እየተባባሰ ሄዷል ! ... የኑሮ ውድነቱን መቋቋም አቅቶት ህብረተሰቡ መድረሻ እያጣ ነው " - አቶ አበረ አዳሙ

የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዛሬ 8ኛ መደበኛ ሰብሰባው አድርጎ ነበር።

በዚህም ወቅት ከም/ቤት አባላት ለንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ጥያቄ ቀርቦላቸው ነበር።

ሚኒስትሩም ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።

የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባል የሆኑ አቶ አበረ አዳሙ ምን ጠየቁ ?

" 1. በዓለም አቀፍ ተጨባጭ ሁኔታዎች ምክንያት ከውጭ የሚገቡ ሸቀጦች ዋጋ የኑሮ ውድነቱን እያናረው ከመሆኑንም በላይ በተለይ በሀገር ውስጥ ምርቶች ላይ የሚደረገው ምክንያት የለሽ ጭማሪ የህዝቡን ኑሮ እንዲመሰቃቀል አድርጎታል።

ለምሳሌ ፦
- ጤፍ
- ስንዴ
- ምስር ... ሆነ ሌሎች የአትክልት እና ፍራፍሬ ምርቶች በሀገር ውስጥ የሚመረቱ ቢሆኑም በጥራት እና በብዛት ገበያ ላይ አይገኙም ፤ ቢገኙም ዋጋቸው እጅግ የተጋነነ በመሆኑ በቀላሉ የሚቀመስ አይደለም።

የችግሩ ምንጭ ደግሞ ሰው ሰራሽ መሆኑ አይካድም።

ህጋዊ ነጋዴው በኮንትሮባንድ ነጋዴዎች እና ለደላላ እየተጠለፈ መስራት ከማይችልበት ደረጃ ላይ ደርሷል።

በዚህ የተነሳ ' ልጆቼን የማበላቸው አጣሁ ' የሚሉ አዛውንቶች፣ ' ጋሽዬ ቁራሽ የዳቦ መግዣ ስጠኝ ራበኝ ' የሚሉ አንጀት የሚበሉ በርካታ ህጻናትን ማየት በከተማችን እየተለመደ መጥቷል።

ልመና አልነበረም ማለት አይደለም አሁን ግን እጅግ እየተባባሰ ሄዷል።

ደላላው ዋጋ ይተምናል ፤ ደላላው ዋጋ ይሰቅላል ቢፈልግም ያወርዳል ለዚህም አንድ ወቅት የሱዙኪ መኪና ዋጋን ሰማይ አድርሶ መሬት አስልሶት የነበረበትን አጋጣሚ ማስታወስ ይቻላል።

በአጭር አነጋገር ደላላ የንግዱን ስርዓት /ሲስተም እንደ ተባይ ወሮታል። በዚህም የኑሮ ውድነቱን መቋቋም አቅቶት ህብረተሰቡ መድረሻ እያጣ ነው።

ጥቅሙን የሚያገኘው  በጋ ከክረምት ደም ታፍቶ ያመረተው አርሶ አደሩ ቢሆን መልካም ነበር።

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶ ህገወጥ ነጋዴዎች እና ደላላዎችን ስርዓት ሊያሲዝ የሚችል ዘላቂነት ያለው ስራ ከመስራት ይልቅ አልፎ አልፎ ወይም የሆነ አጋጣሚ ሲፈጠር ' ይሄን ያህል የንግድ ድርጅቶችን አሽኩ / ልናሽግ ነው ' እያሉ በመገናኛ ብዙሃን ማስታወቂያዎችን ከማስተጋባት የዘለለ ፦
° የንግድ ተቋማቱ በምን ምክንያት እንደታሸጉ
° ምን አይነት ህጋዊ እርምጃ እንደተወሰደባቸው
° የማሸጉ እርምጃ ምን ውጤት እንዳስገኘ
° የንግድ ድርጅቶቹ ከታሸጉ በኃላ የመጣንው ለውጥ ለህዝቡ ሲያሳውቅ አይታይም።

በኑሮ ላይ ጠብ የሚል ለውጥ አይስተዋልም።

ታዲያ የሀገራችንን ገበያ እየመራ ያለው ንግድ ሚኒስቴር ነው ወይስ ደላላና ህገወጥ ነጋዴ ?

2. ለንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ተጠሪ የሆነው የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ከሚቆጣጠራቸው ተቋማት አንዱ መብራት ኃይል ነው። (በየጊዜው የመዋቅር መቀያየር ለውጥ ካለ ይቅርታ ጠይቃለሁ!)

ይሁን እንጂ የመብራት ተደራሽነት እና አግልግሎት አሰጣጥ በእጅጉ የተበላሸ ነው።

👉 ተደራሽነቱ ፍትሃዊነት የጎደለውና ለማዳረስ የተሞከረው ለረጅም አመታት የተተከሉ ፖሎች ሳይቀር ያለ አገልግሎት የቆሙበት፤

👉 ተዳረሰ የተባለውም በኃይል መቆራረጥ ችግር ተጠቃሚውን የሚያሰቃይ፤

👉 አገልግሎቱን ለማግኘት ያለ እፍረት በእጅ መንሻ / ጉባ ካልሆነ በቀር የማይሰራ ሰራተኛ የበዛበት ነው።

የሚያሳዝነው ደግሞ ጉቦ ወንጀል መሆኑ ቀርቶ መብት እስኪመስል ድረስ ዋጋ ተምነው ' ይህን ያህል አምጣ ' የሚሉ ሰራተኞች መብዛታቸው ነው።

በዚህ ከቀጠለ ምናልባትም ፓርላማውን ' የምቀበለው ጉቦ አንሶኛል እና ህግ አውጡልኝ ' ማለት የቀራቸው ይመስላል።

ይህ የእርሶን ተቋም ብቻ የሚመለከት አይደለም በርካታ ተቋማትን የሚያካትት ነው።

ክቡር ሚኒስትር ለመሆኑ ለእርሶ ተጠሪ የሆነው ባለስልጣን መ/ቤት ህዝቡን እያስለቀሰ የሚቀጥለው እስከመቼ ነው ? ይህንን ተቋም መቆጣጠርና ስርዓቱን ማስያዝ ያልተቻለው ለምንድነው ?

3. የኑሮ ውድነቱን ከሚያባብሱ ምክንያቶች አንዱ ነዳጅ ነው።

የዋጋው ማሻቀብ ምክንያቱ የሚታወቅ ቢሆንም ከዋጋው በላይ ሰልፉ ህዝቡን እያማረረ ይገኛል።

ከእጥረቱም በላይ ነዳጅ ለመቅዳት በሚደረግ ረጃጅም ሰልፍ ምክንያት የስራ ሰዓት ያለ አግባብ እየባከነ፣ የትራፊክ ፍሰቱን እያስተጓጎለ፣ እንዲያውም ሲል በህገወጥ መንገድ ነዳጅ ከሀገር እንዲወጣ ሰፊ በር እየከፈተ መሆኑን እማኝ መጥቀስ የሚያስፈልግ አይመስለኝም።

ክቡር ሚኒስትር ይህንን የተበላሸ አሰራር ስርዓት ማስያዝ የማን ኃላፊነት ይመስሎታል ? እባክዎ ለዚህ የተከበረ ም/ቤት እና ለብዙሃኑ የሀገራችን ህዝብ ተገቢውን መልስ ይስጡ። "

ሚኒስትሩ ምን ምላሽ ሰጡ ? ያንብቡ ፦ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-12-03

#ThikvahEthiopia

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

03 Dec, 18:56


#Update

" የትግራይ የፀጥታ ሃይሎች  የህግ ጥሰት በማቆም ህግ  እንዲያከብሩ ጥሪ እናቀርባለን " - የመቐለ ከተማ ምክር ቤት አስተባባሪ ቋሚ ኮሚቴ 

የመቐለ ከተማ ም/ቤት አስተባባሪ ቋሚ ኮሚቴ የትግራይ ጊዚያዊ  አስተዳደር ከህዳር 23/2017 ዓ.ም ጀምሮ የሰጠው የመቐለ ከንቲባ ሹመት ከመቃወም አልፎ " ህገ-መንግስት የጣሰ ተግባር " ብሎታል። 

የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴ ህዳር 24/ 2017 ዓ.ም ከሰአት በኋላ ባወጣው የአቋም መግለጫ ፥ ህዳር 23/2017 ዓ.ም በመቐለ ከተማ አስተዳደር በምክር ቤት አብላጫ ድምፅ የተሾሙ ከንቲባ በስራ ላይ እያሉ የምክር ቤት እና የህዝብ ሉአላውነት በመጣስ ፓሊስ ስራቸው እንዳይሰሩ አግዷል ብሏል።

" በዚያው ቀን ከሰዓት በኋላ ህጋዊ ያልሆኑ ከንቲባ በአስተዳደሩ አንድ አዳራሽ መግለጫ እንዲሰጡ ተደርገዋል " ሲልም ገልጿል።

" በምክር ቤት በስርዓት የተሾሙ ከንቲባ ወደ ቢሯቸው እንዳይገቡ የመቐለ ፓሊስ ከህግ አገባብ ውጪ ፅህፈት ቤታቸው በማሸግ ህዝብ አገልግሎት እንዳይገኝ አስተጓጉለዋል " ሲል ከሷል።

" የፓሊስ ኢ-ህጋዊ ተግባር  አገልግሎት ያጣ ህዝብ ወዳልተፈለገ ሽብርና ቀውስ እንዲገባ አድርገዋል " ብሏል።

በተጨማሪ የቋም ኮሚቴው ምን አለ ?

👉 " በህገ-መንግስት የተሰጠ ስልጣን በመቀማት አምባገነን ስርዓት ለመትከል የተፈፀመ ተግባር ነው ይህንን እንኮንናለን። የተፈፀመው አግባብነት የጎደለው ተግባር በአስቸኳይ እንዲታረም ጥሪ እናቀርባለን። "

👉 " የመቐለ ፓሊስ አመራር በህገ-መንግስት የተሰጠው ተግባርና ሃላፊነት ወደ ጎን በመተው የፈፀመው ህገ-ወጥ ተግባር በማስተካከል በምክር ቤት የተሾሙ ከንቲባ ረዳኢ በርሀ (ዶ/ር) ሳይውል ሳያድር  ስራቸው እንዲሰሩ እና አገልግሎት እንዲሰጡ እንዲያደርግ እንጠይቃለን "

👉 " የትግራይ የፀጥታ ሃይሎች የተፈፀመው የህግ ጥሰት በመገንዘብ ህግ እንዲያከብሩ ጥሪ እናቀርባለን "

👉 " የመቐለ ከተማ ህዝብ ህገ-ወጥ ተግባሩ በመቃወም ከምክር ቤቱ ጎን እንዲሰለፍ ጥሪ እናቀርባለን "

👉 " የትግራይ ጊዚያዊ  አስተዳደር የምክር ቤቶች ሉአላዊ ስልጣን በመጣስ የወሰደው እርምጃ ህዝቡ ወደ አላስፈላጊ ቁጣና ግርግር የሚያስገባ መሆኑ በመገንዘብ በዚሁ በህገ-መንግስት ጥሰት የተሳተፉት አካላት በህግ እንዲጠይቃቸው ጥሪ እናቀርባለን "

... ብሏል።


በፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ የተሸሙት አዲሱ ከንቲባ ብርሃነ ገ/የሱስ መደበኛ ህዝባዊ አገልግሎት መስጠት አንደሚጀምሩ ታማኝ ምንጮች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ መረጃ ሰጥተውታል።

#ThikvahEthiopiaFamilyMekelle

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

03 Dec, 13:28


" እኔ ኢየሱስ ክርስቶስን እወደዋለሁ !! "

በሀገራችን ኢትዮጵያ ጨምሮ በመላው ዓለም ላይ በቢሊዮኖች ተመልካች ያለው የእንግሊዝ ፕሪሜየርሊግ ግብረሰዶማውያንን ለመደገፍ በሚል በየአመቱ ዘመቻ ያደርጋል።

ይህንን ዘመቻ የሚያደርገውም በእያንዳንዱ ክለብ አምበል ክንዶች ላይ ግብረሰዶማውያንን የሚገልጸውን ባዲራ / እንዲያደርጉ በማድረግ ነው።

ይህን የሊጉን ተግባር እጅግ በርካታ ሃይማኖተኛ ደጋፊዎች እና ተጫዋቾች ነው የሚያወግዙት።

በዘንድሮው ዓመት የሊጉ ፍልሚያ ኢፒስዊች ታውን የተባለው ክለብ አምበል እና የእስልምና እምነት ተከታዩ ሳም ሞርሲ " እኔ ሃይማኖቴ አይፈቅድልኝም " በማለት የግብረሰዶማውያንን ምልክት ሳያደርግ ቀርቷል።

ከዚህ ባለፈ ግን አንድ የሌላ ክለብ ተጫዋችና አምበል የክርስትና እምነት ተከታይ ክንዱ ላይ ምልክቱን ቢያደርግም ከላይ " እኔ ኢየሱስ ክርስቶስን እወደዋለሁ !! " የሚል ፅሁፍ ፅፎ በመግባቱ የሊጉን አስተዳደሮች እንዳስቆጣ በዚህም ቅጣት ሊጣልበት እንደሚችል ተሰምቷል።

ተጫዋቹ ማርክ ጉሂ ይባላል ፤ እድሜው 24 ሲሆን የአይቮሪኮስት ዝርያ ያለበት የእንግሊዝ ዜጋ ነው።

የሚጫወትለት ክለብ ክርስታል ፓላስ የሚባል ነው።

ይኸው ተጫዋች ነው ባለፈው ቅዳሜ ኒውካስትል ከተባለው ሌላኛው የሊጉ ክለብ ጋር ጨዋታቸውን ሲያደርጉ ግብረሰዶማውያንን የሚደግፈውን ምልክት ክንዱ ላይ ቢያጠልቅም ከላዩ " እኔ ኢየሱስ ክርስቶስን እወደዋለሁ ! " የሚል ፅሁፍ ፅፎበት በመግባት ጨዋታውን አድርጓል።

በዚህም የሊጉን አስታዳዳሪዎች አስቆጥቶ ቅጣት ሊጥሉበት እንደሆነ ተነግሯል።

የእንግሊዝ ፕሪሜየርሊግ ግብረሰዶማውያንን ለመደገፍ በየዓመቱ አምበሎች የግብረሰዶማውያን ምልክት የሆነውን የተለያየ ቀለም ያለው ምልክት በክንዳቸው አጥልቀው እንዲጫወቱ ያደርጋል።

#Guehi #Christian #PremierLeague

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

03 Dec, 09:59


" ሃይማኖቴ አይፈቅድልኝም !! "

" ሃይማኖቴ አይፈቅድልኝም ! " ያለው የእግር ኳስ ተጫዋች ግብረሰዶማውያን ለመደገፍ ሲባል ክንድ ላይ የሚጠለቀውን ምልክት ሳያደርግ ቀርቷል።

በዓለም ላይ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ የእግር ኳስ ፍልሚያ አፍቃሪያን እንዳሉ ይታወቃል።

ከየትኛውም ሀገራት በላይ ደግሞ የአውሮፓ ሀገራት ውስጥ የሚካሄዱት ፍልሚያዎች እጅግ ብዙ ተመልካች ያላቸውና ከፍተኛ ተወዳጅነትን ከፉክክር ጋር ያጣመሩ ናቸው።

በተለይም የእንግሊዝ ፕሪሜየርሊግ በሀገራችን ኢትዮጵያ ሳይቀር እጅግ ከፍተኛ ተወዳጅነት ያለውና ብዙ ተመልካች ያለው ነው።

ከህጻን እስከ አዋቂ፣ አዛውንቶች ሳይቀሩ ነው ፍልሚያውን የሚከታተሉት።

ነገር ግን በየዓመቱ ይህ የእግር ኳስ ፍልሚያ የሚደራበት ወር በተለይም ሃይማኖተኛ የሆኑ የእግር ኳስ ተመልካቾችን የሚያስቀይም ነው።

ምክንያት ? ሊጉ ውስጥ ግብረሰዶማውያንን ለመደገፍ ሲባል ዘመቻ ስለሚካሄድበት ነው።

ሰዎቹ " እኩልነትን ለማምጣት " ይበሉት እንጂ በበርካታ ሃይማኖተኛ እግር ኳስ ተመልካቾች እና ተጫዋቾች ዘንድ የሚወገዝ ተግባር ነው የሚፈጽሙት።

የፕሪሚዬር ሊግ ክለቦች ለግበረሰዶማውያን ያላቸውን ድጋፍ ለማሳየት አምበሎቻቸው የግብረሰዶማውያኑን መለያ ምልክት ክንዳቸው ላይ እንዲያጠልቁ ያደርጋሉ።

ይህን ዘመቻ የሚያደርጉትም እኤአ ከኅዳር 29 እስከ ታኅሣሥ 5 ነው።

ከቀናት በፊት በነበረ አንድ ጨዋታ ላይ ግን የአንድ ክለብ አምበል " እኔ ሃይማኖቴ አይፈቅድልኝም " በማለት ምልክቱን ሳያድረግ ቀርቷል።

የተጨዋቹ ስም ሳም ሞርሲ ይባላል ፤ ኢፕስዊች ታውን የተባለው ክለብ አምበል ነው።

በእምነቱም የእስልምና እምነት ተከታይ ሲሆን የግብፅ ዜጋ ነው።

ይኸው ተጫዋች ነው ቡድኑ ኖቲንግሃም ፎረስት ከተባለው ቡድን ጋር በተጫወተበት ወቅት ክንዱ ላይ ምልክቱን " አላጠልቅም " ብሎ ጨዋታውን ያካሄደው።

ክለቡ ባወጣው መግለጫ ምልክቱን ያላደረገው " በሃይማኖቱ ምክንያት ነው ፤ ውሳኔውን እናከብራለን " ብሏል።

ክለቡ አክሎም ፤ የግብረሰዶማውያኑን ምልክት የሚያሳየውን የአምበሎች መለያ በኩራት እንደሚደግፍ ፤ ከግብረሰዶማውያን ማኅበረሰብ ጋር አብሮ እንደሚቆም ፤ እኩልነት እና ተቀባይነት እንዲንሰራፋ እንደሚሰራ ገልጿል።

ከሳም ሞርሲ በስተቀር ሌሎች የፕሪሚዬር ሊጉ አምበሎች የግብረሰዶማውያንን ባንዲራ አጥልቀው ሲጫወቱ ነበር።

#SamMorsy #PremierLeague #Muslim

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

03 Dec, 09:57


#ሹመት

የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ከሰሞኑን 6 አዳዲስ ሹመቶች ሰጥተዋል።

ከስድስቱ ሽመቶች ሁለቱ በደብረፅዮን ገ / ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት የተሾሙትን በማንሳት የተሰጠ ነው።

በዚሁ መሰረት ፕሬዜዳንቱ ከህዳር 20/2017 ዓ.ም  ጀምሮ የሚፀና በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት የመቐለ ከንቲባ በመሆኑ የተሾሙት ረዳኢ በርሀ (ዶ/ር) በመሻር በብርሃነ ገ/ዮሱስ ተክተዋል።

የትግራይ ትምህርት ቢሮ ምክትል የስራ ሃላፊ ሆነው ሲያገለግሉ ቆይተው ከህዳር 17/2017 ዓ.ም ጀምሮ በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት የዓዲግራት ከንቲባ በመሆን የተሾሙት ረዳኢ ገ/ሄር ምትክ ኪ/ማርያም ወ/ሚካኤል ምክትል የቢሮ ሃላፊ ሆነው ተሹመዋል።

ፕሬዜዳንቱ በጡሮታ በተገለሉት ሓዱሽ ካሱ ምትክ ዶ/ር ገብሩ ካሕሳይ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ምክትል ፅሕፈት ቤት ሃላፊ አድርገዋቸዋል።

ኮማንደር ተስፋይ ገ/ማርያም በምክትል ኮሚሽነር መዓርግ የወንጀል ማጣራት ሃላፊ ፤ ኮማንደር ጌታቸው ኪሮስን በምክትል ኮሚሽነር መዓርግ የወንጀል መከላከል ሃላፊ እንዲሁም አቶ ሃይላይ ኣብራሃ በምክትል ኮሚሽነር መዓርግ የሰው ሃይል ልማት ዘርፍ ሃላፊ አደርገው ሹመዋል።

በቅርቡ የግድያ ሙከራ እንደተደረገባቸው በተናገሩት የትግራይ ማእከላዊ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሰለሞን መዓሾ ምትክ ጉዕሽ ግደይ ሓድጉ የትግራይ ማእከላዊ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሆነው በፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ደብዳቤ መሾማቸው ይታወሳል።

#ThikvahEthiopiaMekelle

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

03 Dec, 09:56


#Ethiotelecom

የድኅረ ክፍያ የሞባይል ጥቅል ለድርጅትዎ በተመጣጣኝ ዋጋ!

💁‍♂️ በወር ከ270 ብር ጀምሮ በብዙ አማራጭ ቀርበዋል፤ የ2 ዓመት ውል በመግባት እስከ 45% የሚደርስ ተጨማሪ ስጦታ ያግኙ።

📍 በአቅራቢያዎ ወደሚገኝ የድርጅት አገልግሎት ማዕከል ጎራ ይበሉ!

ለተጨማሪ መረጃ https://bit.ly/3Zect70 ይጎብኙ!

#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #SmartAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

21 Nov, 22:39


#Bitcoin

የአንድ ቢትኮይን ዋጋ ከ98,000 ዶላር በላይ ሆነ።

" የመጀመሪያው የክሪፕቶ ፕሬዝዳንት " የተባሉትና " አሜሪካን የፕላኔታችን የክሪፕቶከረንሲ መዲና አደርጋታለሁ " ያሉት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት መሆናቸው ከተረጋገጠ በኃላ ቢትኮይን ወደላይ ተተኩሷል።

ዛሬ የተመዘገበው የቢትኮይን ዋጋ በታሪክ ከፍተኛ ሆኗል።

አንድ የቢትኮይን ዋጋ 98,149 የአሜሪካ ዶላር ገብቷል።

ትራምፕ በምርጫ ቅስቀሳቸው ወቅት " በፍጹም ቢትኮይናችሁን አንዳትሸጡ  " ሲሉ ለክሪፕቶ ማህበረሰቡ መልዕክት አስትላልፈው ነበር።

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

21 Nov, 22:19


⚫️ #ኢትዮጵያ ⚫️

ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ምን ያልተፈጸም ፤ ምንስ ያልተደረገ ግፍ አለ ?

እጅግ በጣም ሚያስደነግጠው እንዲሁም ፍጹም ከሰውነት ተራ እየተወጣ መሆኑን የሚያሳየው የድርጊቱ ፈጻሚዎች ልክ ጀግንነት ፣ በጎ ተግባር፣ ፍቅርን ለትውልድ የሚያስተላልፉ ይመስል ግፍና ጭካኔያቸውን በቪድዮ ማስረጃ እራሳቸው ቀርጸው ለትውልድ እያስቀመጡ መሆናቸው ነው።

በእርግጥም እንዲህ እየቀረጹ ማስቀመጣቸው ህዝቡን ለሚፈልጉት ዓላማ ለማነሳሳትና እርስ በርስ ለማባላት፣ ህዝቡን ወደ ግጭት ለማስገባት ሊሆን ይችላል።

በጥላቻ የሚፈጽሙት የግፍ ተግባራቸው አላረካ ብሏቸው ፣ " እዩልን ምን ያህል አውሬ እንደሆንን " የሚለውን ለማሳየትም ይሆናል።

በሀገራችን ፦
🔴 ሰው ከነህይወቱ ሲቃጠል
🔴 በድንጋይ ተወግሮ ሲገደል
🔴 በጅምላ በጥይት ተደብድቦ ወደ ገደል ሲከተት
🔴 አስክሬን ሲጎተት
🔴 አስክሬን አደባባይ ላይ ሲጣል
🔴 ተዘቅዝቆ ሲሰቀል
🔴 በስለት ተቀልቶ ሲገደል
🔴 የጥይት በረዶ ሲዘንብበት ... ኧረ ብዙ ብዙ በቪድዮ ተቀርጾ አይተናል።

ይኸው ዛሬ የሰው ልጅ ልክ እንደ ዶሮ " በስመአብ " ተብሎ ሲታረድ በቁማችን አየን።

ይህ ጭካኔ በማስረጃ በቪድዮ ተቀርጾ የወጣ ነው ለመሆኑ ስንት በቪድዮ ያልተቀረጸ ፣ በየአካባቢው የተፈጸመ ግፍ ይኖር ይሆን ?

እነዚህ ግፍ ፈጻሚ ሰዎች ሰይጣናዊ ስራቸውን በቪድዮ ቀርጸው ማስቀረታቸው በቤተሰብ ፣ በህዝብ ላይ የማይረሳ ቂም፣ ቁርሾና ቁስል ለማኖር ይመስላል።

የትም ይሁን ማንኛውም የግፍ ድርጊት ሲፈጸም ግን የሚቀድመው ድርጊቱን ከልብ አዝኖ ማውገዝ  ነው። ፍትህ ተጠያቂነት እንዲሰፍን መጠየቅ ፤ ለፍትህ መታገል ነው።

ልክ ሰው በሞተ ቁጥር ያለ አንዳች ሀዘን እና መከፋት ወደ ፖለቲካ ንትርክ መግባትና የሰው ደም ፈሶ እንዲቀር ለማድረግ መሯሯጥ የግፍ ግፍ ነው።

ከዚህ ቀደም ብዙ ታዝበናል።

ሰው በግፍ ይገደላል ከዛም ሰዎች በየማህበራዊ ሚዲያ ይመጡና " የኔ ወገን ሰው አይገድልም፤ ፍጹም ነው ፣ ፃድቅ ነው ፣ እንዲህ እንዲያደርግ ተፈጥሮው አይፈቅድለትም " እያሉ ድርጊቱ ያራክሱታል።

ሌላው ወገን ይመጣና በሞተው ንጹህ ሰው ደም ፖለቲካ ይሰራል። በጅምላ ጥላቻውን ይተፋል። በዚህ መንገድ የስንት ሰው ደም ፈሶ ቀረ ?

ላለፉት ዓመታት ሰው በግፍ ይገደላል ከዛ የቀናት የማህበራዊ ሚዲያ አጀንዳ ሆኖ ያልፋል፤ ይረሳል። ከዛ ሌላ ግፍ ሌላ ግድያ ይፈጸማል።

አንዳንዱ እውነት ከልቡ አዝኖ ፤ አንዳንዱ ደግሞ የይስሙላ ያዘነ ይመስል ሸፋፍኖ በማህበራዊ ሚዲያው ይጽፋል ፤ ይለፍፋል። ከሰዓታት በኃላ ሁሉም ረስቶት ምንም እንዳልተፈጠረ ወደ ህይወቱ ይመለሳል። ማህበራዊ ሚዲያ ሲገባ ትዝ ሲለው ለቀናት ስሜቱን ይፅፍ ይሆናል።

እስከ ህይወት ፍጻሜ ድረስ በሀዘን የሚቃጠሉትና ልጃቸውን የማይረሱት እናት አባት፣ ወንድም ፣ እህት ቤተሰብ፣ ዘመዶች ናቸው።

በተለይ እናት እና አባት ሲያለቅሱ ነው የሚኖሩት።

ይህ አዙሪት መቆም አለበት። ደመ በፈሰሰ ቁጥር ቁርሾ ቂም እየተወለደ እንጂ ፍቅር አንድነት አይመጣም።

ልጆቹን የተነጠቀ ቤተሰብና አካባቢ እንደሌላው የማህበራዊ ሚዲያ አርበኛ የአንድ ቀን ሀዘን አድርጎ አያልፈውም። የተፈጸመበትን ግፍና በደል መቼም አይረሳውም ! ቂም በውስጡ ያድራል። ይህ በሀገር ህዝብ ትስስር ላይ የሚያሳድረው ተፅእኖ ከባድ ነው።

ከምንም በላይ ለተጎዱ ወገኖች ፍትህ በማስፈን ፣ ሌላ የአንድ ሰው ደም እንዳይፈስ በማድረግ አዙሪቱን ማቆም ካልተቻለ የከፋ ነገር መምጣቱ አይቀርም።

እዚህች ምድር ላይ ነገ ሳይሆን ዛሬ የሰው ልጅ ደም መፍሰስ እንዲቆም ማድረግ ይገባል።

ፍትህ ሊሰፍን ፤ ተጠያቂነት ሊረጋገጥ ይገባል።

ታጣቂም ሆነ አልሆነ ፤ የአካባቢው ፣ የክልሉ የመንግሥት አካል ሆነ አልሆነ ሁሉም በየድርሻው በየደረጃው ሊጠየቅ ይገባል።

እጅግ በጣም አስገራሚው ነገር በምንም አይነት መንገድና ሁኔታ የዜጎችን ደህንነት ማስጠበቅ ቀዳሚ ስራው ሊሆን የሚገባው እና ችግርም ሲፈጠር ለህዝብ የማሳወቅ ኃላፊነት ያለበት መንግሥት የሚፈጸሙ ድርጊቶችን ከማህበራዊ ሚዲያው ጩኸት በኃላ ለመናገር ሲወጣ መታየቱ ነው።

ለመሆኑ የሚፈጸመውን የሚሰማው ከህዝብ ጋር በሚዲያ ነው ? ነዋሪው በሚዲያ ባይጮህ ላያወግዝ ነው ?

ቆይ ልክ እንደማንኛውም ሌላ አካል " አወገዝኩ " ብቻ ነው የሚባለው  ወይስ ስለተፈጸመ ግፍ በዝርዝር አጣርቶ ለህዝብ ወጥቶ መረጃ መስጠት ነው የሚገባው ? የመንግሥት ስራ ድርሻው ምንድነው ? ለስንቱ ፍትህ ለተነፈገ እያነባ ላለ ወገን ፍትህ ሰጠ ? ተጠያቂነትን አሰፈነ ? በደል የደረሰባቸውን ካሰ ? ዳግም ደም እንዳይፈስ ተከላከል ? እኚህ ሁሉ ጥያቄዎች መልስ ይሻሉ።

በምንም አይነት ሁኔታ የሰው ደም አይፈስስ ፤ ደም ሲፈስ ቂምና ቁርሾ እንጂ ፍቅርና አንድነት አይወለድም።

#ቲክቫህኢትዮጵያ
#ThikvahEthiopia
#ናውስ

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

21 Nov, 14:59


#የሹፌሮችድምጽ

" የታገቱትን ሊፈልግ የሚወጣ የጸጥታ ሃይል የለም ሄዱበት በተባለው መንገድ የሚገባ የለም " - ጣና የከባድ መኪና ሹፌሮች ማህበር

በኢትዮጵያ በርካታ አካባቢዎች የከተማ አቋራጭ እና ሃገር አቋራጭ አሽከርካሪዎች ለእገታ እና ግድያ እየተጋለጡ መሆናቸውን በተደጋጋሚ ሲነገር ይደመጣል።

የጣና የከባድ መኪና ሹፌሮች ማህበር በአራት አመት ጊዜ ውስጥ ከ200 የሚበልጡ አሽከርካሪዎች ቢገደሉም ችግሩን ለመቅረፍ ግን ምንም እንቅስቃሴ እየተደረገ አለመሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ  ገልጿል።

" ሰው ታፈነ ሲባል ሰውን ያህል ነገር ታፍኖ የአካባቢው የጸጥታ ሃይል የት፣እንዴት ታፈነ የሚለውን ጠይቆ እና አነፍንፎ የሚንቀሳቀስ መንግስት አጥተናል" ሲሉ ስሜ አይጠቀስ ያሉ የማህበሩ አመራር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

አክለውም " መታገትህን ትናገራለህ ምንም እንዳልተፈጠረ ዝም ይባላል የታገቱትን ሊፈልግ የሚወጣ ሃይል የለም ሄዱበት በተባለው መንገድ የሚገባ የለም " ነው ያሉት።

አጋቾች የሚደራደሩት በስልክ ነው ገንዘብም የሚገባው በባንክ ነው ያሉ ሲሆን እገታን እዚህ ደረጃ ያደረሰው መንግስት ለሚታገቱ እና ለሚገደሉ ሰዎች የሰጠው ትኩረት በማነሱ ምክንያት ነው ብለዋል።

እንደ ማህበሩ አመራር ገለጻ ህዳር አንድ ላይ አራት አሽከርካሪዎች መተሃራ እና አዋሽ ሰባት መሃል ታፍነው በታጣቂዎች ተወስደዋል።

በተደጋጋሚ የሹፌሮች መታገት እና መገደል የነበረባቸው አንደ ታች አርማጭሆ ያሉ አካባቢዎች ሚሊሻዎችን በየመንገዱ የማሰማራት እና መንገዱን የመጠበቅ እንቅስቃሴዎች መኖራቸውን የጠቀሱ ሲሆን በተጠቀሰው አካባቢ መሻሻል አለ ብለዋል።

" ከአይከል -ጭልጋ- ገንዳውሃ " ያለው መንገድ ግን አሁንም ለሹፌሮች እጅግ አስቸጋሪ ሆኖ መቀጠሉን ገልጸው ከመንግሥት ውጪ የሆነ እና በየመንገዱ የሚሰበሰብ እስከ 20 ሺ ብር የሚደርስ ህገወጥ ቀረጥ ሹፌሮችን እያማረረ ነው ብለውናል።

#ThikvahEthiopiaFamilyAA

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

21 Nov, 14:59


#MesiratEthiopia

🛑 ለቢዝነሶች የቀረበ ጥሪ 🛑
https://mesirat.acceleratorapp.co/application/new?program=mesirat-entrepreneurs-application-form-seventh-cohort ላይ ተመዝግበው
- በፋይናንስ፣
- በማርኬቲንግ፣
- በቴክኖሎጂ፣
- በኔትወርኪንግ፣
- የባለሙያ አማካሪዎችን በማግኘት፣
- በአገልግሎት ሰጪነት እና
- በአማካሪነት ድጋፍ ያግኙ።
የመስራት ስራ ፈጠራ ፕሮግራም አካል ይሁኑና ቢዝነስዎ እንዲያድግ አጠቃላይ ድጋፍን ያግኙ።
ፕሮግራማችን የባለሙያ ምክር ማግኘት፣ ጠቃሚ ግብአቶች እና ተመሳሳይ አስተሳሰብ ካላቸው ስራ ፈጣሪዎች ጋር ንቁ እድገትን ለማፋጠን የተነደፈ ነው።

ሴቶች እና አካል ጉዳተኞች እንዲያመለክቱ ይበረታታሉ!

THIKVAH-ETHIOPIA

21 Nov, 14:59


#DStvEthiopia

⚽️አዲስ ነገር ለኳስ አፍቃሪያን...
👉ከሕዳር 16 ጀምሮ ፈጥነው ወደ ሜዳ ስፖርት ፓኬጅ ከፍ ይበሉ! ሁሉንም የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎችን፣ የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ፣ ሎችም ዋና ዋና እግር ኳስ እና ምርጥ ምርጥ መዝናኛዎችን ያካተቱ ከ129 በላይ ቻናሎችን በወር በ1699 ብር ብቻ!

ደንብና ሁኔታዎች ተፈፀሚነት አላቸው! ለበለጠ መረጃ
👇
www.dstv.com/en-et

ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://bit.ly/48oVhj8

#ሁሉምያለውእኛጋርነው #MedaSport

THIKVAH-ETHIOPIA

21 Nov, 14:30


" ግድያው የተፈጸመበት ወጣት ደረጀ አማረ ተስፋ ይባላል ፤ የ10ኛ ክፍል ትምህርቱን አጠናቅቆ ወደ ቤተሰቦቹ የሄደ ነበር " - ነዋሪዎች

ቁጣን ስለቀሰቀሰው የደራው አሰቃቂ ግድያ ነዋሪዎቹ ምን አሉ ?

ሰሞኑን በሰሜን ሸዋ ደራ ወረዳ አንድ ወጣት በታጣቂዎች ተይዞ በአሰቃቂ ሁኔታ ሲገደል የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምሥል በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ከታየ በኋላ በርካቶችን አስቆጥቷል።

ጉዳዩን በሚመለከት ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ቃላቸውን የሰጡ የአካባቢው ነዋሪዎች " ግድያው የተፈጸመው በአካባቢው ላይ በሚንቀሳቀሱ የፋኖ ታጣቂዎች ነው " ሲሉ ተናግረዋል

ድርጊቱ የተፈጸመው ከ2 ወራት በፊት እንደሆነም ገልጸዋል።

ግድያው የተፈጸመበት ወጣት ማነው ?

ዳንኤል ገመዳ የተባለው ግለሰብ ወደ ሰሜን ሸዋ ደራ አካባቢ አምርቶ የሟችን ቤተሰቦች ማነጋገሩን ገልጿል።

ግድያው የተፈጸመበት ወጣት ደረጀ አማረ ተስፋ እንደሚባል እና የ10ኛ ክፍል ትምህርቱን አጠናቅቆ ወደ ቤተሰቦቹ የሄደ እንደነበር አስረድቷል።

በአሰቃቂው ቪዲዮ ላይ ከሚታየው የ10ኛ ክፍል ተማሪ በተጨማሪ ጓደኛው ከማል ሁሴን በአንድ ቀን መገደላቸው ተነግሯል።

ጥቃቱ በተፈጸመበት ዕለት የአካባቢው ነዋሪዎች ወደ በከጀማ ተራራ ሸሽተው ነበር። ደረጀ እና ሌሎች ግን በቀያቸው የቆዩት በበረት ታስረው የሚገኙትን እንስሳትን ለመጠበቅ ነበር።

በአካባቢው የነበሩ ታጣቂዎች ደረጀ እና ከማል ላይ ተኩስ መክፈታቸውን ነዋሪዎች ተናግረዋል።

የደረጀ አባት የሆኑትን አቶ አማረ ተስፋ ቶላን አግኝቼ አነጋግሬያለሁ የሚለው ዳንኤል፣ " ያን ቀን አሳድደው እግሩን ተኩሰው መትተው ከያዙት በኋላ ሳርኩላ ወደ ሚባል ቦታ ወሰዱት። እዚያ ቦታ ነው የፋኖ ታጣቂዎች በብዛት የሚንቀሳቀሱት " ይላል።

ደረጀ በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድሎ አስከሬኑ ለአውሬ የተጣለው እዚያ ቦታ መሆኑን የተናገሩት አባትየው፣ የልጃቸውን መገደል ቢሰሙም አስከሬኑን አግኝተው መቅበር አለመቻላቸውን ጨምሮ ገልጿል።

የደረጀ እናት እና አባት በልጃቸው ሞት ምክንያት አእምሮ ጤናቸው መቃወሱ ተገልጿል።

" የደረጀ እናት አእምሮአቸው ተጎድቷል እና አትናገርም። ምን ማድረግ እንዳለባቸው አያውቁም። ለማንም አይመልሱም። " ነው የተባለው።

ደረጀ ለቤተሰቡ ታናሽ ልጅ ሲሆን ወንድሞቹ እና እህቶቹ አግብተው ከቤት በመውጣታቸው እናት አባቱን ለማገዝ በቤት ያለ ብቸኛ ትንሽ ልጅ መሆኑ ተመላክቷል።

የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተቃውሞ ምንድነው ?

የግፍ ግድያውን የተመለከቱ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ዛሬ ሰልፍ ወጥተው ነበር።

ምግባቸውንም ትተው በመውጣት ሀዘናቸውንና ቁጣቸውን ገልጸዋል።

ፍትህ እንዲሰፍን ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ እና ወንጀለኞችም የፍትህ አደባባይ እንዲቀርቡ ጠይቀዋል።

#ኢሰመኮ : የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ጉዳዩን እንደሰማ ገልጾ ማጣራት መጀመሩን እና የደረሰበትን ውጤት ወደፊት እንደሚያሳውቅም ገልጿል።

የደራ ህዝብ እያየው ያለው የከፋ መከራ ምን ይመስላል ?

በደራ ሰላምና ደህንነት ከጠፋ ቆይቷል።

በቀጠናው በሰላም ወጥቶ መግባት ቅንጦት ከሆነ ዓመታት ተቆጥረዋል።

ሰዎች በግፍ ይገደላሉ ፤ የሚጠየቅ አካል ግን የለም።

ለአብነት ከሳምንታት በፊት ገንዳ አረቦ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሀጂ አህመድ መስጅድ ኢማም ሼይኽ ሙሀመድ መኪን ታግተው ከነበሩት 12 የሚሆኑ የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ጋር በሸኔ ታጣቂዎች መገደላቸው መነገሩ የቅርብ ትውስታ ነው።

ሌሎች በርካታ ግፍ እና ግድያዎች ሲፈጸሙም ቆይቷል።

በአካባቢው የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (መንግሥት ሸኔ የሚላቸው) ታጣቂዎች፣ እንዲሁም የፋኖ ታጣቂዎች፣ የመንግሥት ታጣቂዎች  ይንቀሳቀሳሉ።

ህዝቡ ሰላም ከተጠማ ዓመታት አልፈዋል። ግፍ ፣ በደል ፣ ሰቆቃ መመልከት የዕለት ተዕለት ሁኔታው ሆኗል።

ዛሬ ይህ እጅግ አሰቃቂ ቪድዮ ወጥቶ በዚህ ልክ መነጋገሪያ ሆነ እንጂ በአካባቢው የሚፈጸመው ግፍ፣ የሚካሄደው ግድያ እጅግ አስከፊ ነው።

ብዙ ጊዜ ስለ አካባቢው ሁኔታ  ቢነገረም ይህ ነው የሚባል መፍትሄ አልመጣም።

ሰላም ወዳዱ ህዝብ በተለያየ አቅጣጫ በታጣቂዎች የሚያየው መከራ በቃላት የሚገለጽ አይደለም።

የአካባቢው ነዋሪዎች " መንግሥት ተቀዳሚ ስራው የሆነውን የዜጎችን ደህንነት ማስጠበቅ ስራ እየሰራ አይደለም " በሚል ብዙ ጊዜ ቅሬታቸው አቅርበዋል። አሁንም ቢሆን እያቀረቡ ነው።

#Oromia #Dera #BBC_Afaan_Oromoo

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

21 Nov, 09:25


#DDR

" ትጥቅ መፍታት መሸነፍ ፣ መዋረድ ወይም ራስን ዝቅ ማድረግ ማለት አይደለም። ትጥቅ መፍታት ማለት የሀገር አንድነትና ሰላም በፅኑ መሰረት ላይ ከማቆም አንፃር መታየት አለበት " - የኢፌዴሪ ሀገር መከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ ወታደራዊ አመራር 

የመጀመሪያ ዙር የትግራይ የቀድሞ ተዋጊዎችን ዲሞቢላይዝድ በማድረግ ወደ  ተሃድሶ ስልጠና ማዕከላት የማስገባት ስራ በይፋዊ ስነስርዓት ተጀምሯል።

ዛሬ በተካሄደ ይፋዊ ስነስርዓት ላይ የተገኙት የኢፌዲሪ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ ወታደራዊ አመራር ብርጋዴር ጀነራል ደርቤ መኩሪያው ፤ " የዴሞብላይዜሽን አሰራር ሴት ተዋጊዎችን ፣ አካል ጉዳተኞችን እና በአደረጃጀት ውስጥ ያሉ አመራሮችን በማስቀደም ይፈፀማል " ብለዋል።

በዴሞብላይዜሽን አሰራር በየቀኑ 320 ታጣቂዎች ወደ ስልጠና ማእከላት የማስገባት ስራ እንደሚሰራ ጠቁመዋል።

በመጀመሪያ ዙር 75 ሺህ ታጣቂዎች እንደሚስተናገዱ አክለዋል።

" ማንኛውም ትጥቅ ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ውጭ መያዝ የሀገሪቱ ህገ-መንግስት ይከለክላል ስለሆነም በትግራይ እየተፈፀመ ያለው የዴሞብላይዜሽን አፈፃፀም ህግና ስርዓት ተከትሎ የሚፈፀም ነው " ሱሉ ተናገረዋል።

ብ/ጄነራሉ ፤ " ትጥቅ መፍታት መሸነፍ ፣ መዋረድ ወይም ራስን ዝቅ ማድረግ ማለት አይደለም። ትጥቅ መፍታት ማለት የሀገር አንድነትና ሰላም በፅኑ መሰረይ ላይ ከማቆም አንፃር መታየት አለበት " ብለዋል።

" ትጥቅ ማስረከብ ማለት ያለችን እንዲት ሀገር ከሚጋረጡባት የውጭ ስጋቶች መታደግ መሆኑን መገንዘብ ያሻል " ያሉት ጀነራሉ  " ትጥቅ የማስፈታት ተግባሩ የትግራይ እና በክልሉ ደንበር አከባቢ ያለው የፀጥታ ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት ተፈፃሚ ይሆናል " ሲሉ አሳውቀዋል።

የትግራይ የፀጥታ እና የሰላም ቢሮ ሃላፊ ጀነራል ፍስሃ በበኩላቸው ፤ " ትጥቅ የመፍታቱ ተግባር እርምጃ ለትግራይና ለሀገር ሰላም የተከፈለ ውድ እና ሁሌ በታሪክ ድምቆ የሚታወስ ፍፃሜ ነው " ብለዋል።

ዛሬ ትጥቃቸው ያስረከቡ 320 የቀድሞ ተዋጊዎች ሲሆኑ ወደ ተዘጋጀላቸው የስልጠና ማእከላት ማምራታቸው ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ስነ-ስርዓቱ ከተከናወነበት ቦታ በላከው መረጃ ገልጿል።

#ThikvahEthiopiaFamilyMekelle

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

21 Nov, 09:08


#Update

ዛሬ 320 የትግራይ ተዋጊዎች ትጥቅ አውርደው አስረክበዋል።

የቀድሞ ትግራይ ተዋጊዎች ትጥቅ የማስፈታትና ወደ ተሃድሶ ማዕከላት የማስገባት ስራ በዛሬው ዕለት በይፋ ተጀምሯል።

የኢፌዴሪ ሀገር መከላከያ ሰራዊትም ታጣቂዎች ያወረዷቸውን ትጥቆች ርክክብ አድርጓል።

በዛሬው ዕለት 320 የትግራይ ተዋጊዎች ቀላል መሳሪያዎችን አውርደው በማስረከብ ወደ ተሃድሶ ያስልጠና ማዕከል አቅንተዋል።

እንደ ተነገረው ከሆነ በመጀመሪያው ዙር 75 ሺህ የቀድሞ ተዋጊዎችን ስልጠናና የማቋቋሚያ ድጋፍ በማድረግ ወደ ህብረተሰቡ የመቀላቀል ስራ ይሰራል።

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

08 Nov, 19:23


#ጥቆማ #የኢትዮጵያአየርመንገድ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በTRAINEE CABIN CREW ፣ በSENIOR ACCOUNTANT I እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ማስታወቂያ አውጥቷል።

ለTRAINEE CABIN CREW በኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ቢያንስ (ዝቅተኛው) 200 ነጥብ ያስመዘገበ ለማመልከት ብቁ ነው።

የዕድሜ ገደቡ ከ19 እስከ 30 ዓመት ነው።

ቁመት ቢያንስ 1.58 ሜትር እና 212 ሴ.ሜ የሆነ ክንድ ለሴት እንዲሁም ለወንድ ቢያንስ 1.70 ሜትር ቁመት መሆን አለበት።

የምዝገባ ጊዜው ከህዳር 08/2017 ዓ/ም እስከ ህዳር 12/2017 ዓ/ም ነው።

ምዝገባው ፦
- በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ (አዳማ)
- አዲስ አበባ (በኦንላይን ልክ ማመልከቻው ሲከፈት ይፋ ይደረጋል)
- አምቦ ዩኒቨርሲቲ (አምቦ)
- አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ (አርባ ምንጭ)
- አሶሳ ዩኒቨርሲቲ (አሶሳ)
- ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ (ባህር ዳር)
- ወሎ ዩኒቨርሲቲ (ደሴ)
- ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ (ድሬዳዋ)
- ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ( ጋምቤላ)
- ጎንደር ዩኒቨርሲቲ (ጎንደር)
- ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ (ሀዋሳ)
- ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ (ጅግጅጋ)
- ጅማ ዩኒቨርሲቲ (ጅማ)
- መቐለ ዩኒቨርሲቲ (መቐለ)
- ወለጋ ዩኒቨርሲቲ (ነቀምቴ)
- መደወላቡ ዩኒቨርሲቲ (ሮቤ)
- ሰመራ ዩኒቨርሲቲ (ሰመራ)
- ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ (ወልቂጤ) ይከናወናል።

ተጨማሪ መረጃዎች፣ የሚያስፈልጉ መስፈርቶች፣ ዝርዝር ጉዳዮች እንዲሁም ሌሎችም የወጡ ማስታወቂያዎች በዚህ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ድረገጽ ላይ ሰፍሮ ይገኛል ይመልከቱ 👇
https://corporate.ethiopianairlines.com/AboutEthiopian/careers/vacancies

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

08 Nov, 19:20


#ሲሚንቶ

" ከዛሬ ጀምሮ በሚኒስትር መ/ቤቱ በኩል ይደረግ የነበረዉ የሲሚንቶ ግብይት ትስስር ሥራ ቀርቷል " - ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ ከሲሚንቶ አምራቾች ጋር መወያየታቸው ተሰምቷል።

በዚህም ወቅት " ከዚህ ቀደም በሚኒስትር መስሪያ ቤቱ በኩል ይደረግ የነበረዉ የሲሚንቶ ግብይት ትስስር ሥራ ከዛሬ ጀምሮ ቀርቷል " ብለዋል።

አምራቾች በራሳቸዉ ኃላፊነት በሚመርጧቸዉ አከፋፋዮችና ቸርቻሪዎች በኩል ለተጠቃሚዎች በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያቀርቡ አሳስበዋል፡፡

የሲሚንቶ ገበያዉን ለማረጋጋት ጥብቅ ቁጥጥርና ክትትል ይደረጋል ያሉ ሲሆን የአፈጻጸም ሪፖርት ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በማያቀርቡ በማናቸዉም የሲሚንቶ አምራች ላይ " የማያዳግም እርምጃ ይወስዳል " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

ሚኒስትሩ " አዲሱን ዉሳኔና አቅጣጫ ተከትሎ በግብይት ሰንሰለቱ የደላላ ጣልቃ ገብነት የከሰመ፣ ለመንግስት ፕሮጀክቶችና ለተጠቃሚዉ ህብረተሰብ አስተማማኝ የሲሚንቶ አቅርቦት የተረጋገጠ፣ አምራቾችም ተገቢዉን ትርፍ እያገኙ የከምፓኒዎቻቸዉን ዘላቂ ዕድገት የሚያስቀጥሉበት እንዲሆን " ብለዋል።

የግብይት ሥርዓቱ ሙሉ በሙሉ ከካሽ ክፍያ ነጻ ሆኖ በዲጂታል ክፍያ ሥርዓት እንዲፈጸም አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

በውይይት መድረኩ ወቅት አምራቾች የምርት አቅማቸውን እንዲያሳድጉ ተብሏል።

ሲሚንቶ አምራቾች አዲሱን ውሳኔ በማክበር እንደሚተገብሩ ተናግረው ነገር ግን የማምረቻ ግብዓት ፣ የኃይል አቅርቦትና ተያያዥ ችግሮች እንዲፈቱላቸዉ ጠይቀዋል፡፡

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

08 Nov, 18:17


#መቐለ

መቐለ ውስጥ ባለፉት 3 ወራት ብቻ 1,088 ወንጀሎች መፈፀማቸው የመቐለ ከተማ ፓሊስ አስታውቋል።

ከተፈፀሙት ወንጀሎች መካከል ፦
➡️ 16 የግድያ
➡️ 47 የግድያ ሙከራ
➡️ 16 የሴቶች አስገድዶ መድፈር ይገኙበታል።

በሩብ አመቱ የተመዘገበው የወንጀል ተግባር አሳሳቢና ህዝብ ያሳተፈ የመከላከል ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አመላካች ነው ብሏል።

ፖሊስ የወንጀል ተግባራቱ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ 3 ወራት ሲነፃፃር የቀነሰ ቢሆንም አሁንም ቢሆን ህዝቡ ከወንጀልና የወንጀል ስጋት ነፃ እንዳልሆነ አመላካች ነው ሲል አሳውቋል።

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

08 Nov, 18:16


#ኢትዮጵያ

የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና ለጉምሩክ ኮሚሽን በፃፈው ደብዳቤ ፍራንኮ ቫሉታ ከዛሬ  ጀምሮ መከልከሉን አሳውቋል።

የብር የመግዛት አቅም በገበያው እንዲወሰን ከተደረገ በኋላ ለተወሰነ ጊዜ የነዳጅ ተሽከርካሪዎችን እና የፀጥታ ተቋማት መሳሪያዎችን ሳይጨምር ሌሎች ምርቶችን በፍራንኮ ቫሉታ ወደ ሀገር ማስገባት ተፈቅዶ እንደነበር ይታወሳል፡፡

ይሁንና ከሳምንት በፊት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በፓርላማ ተገኝተው ማብራሪያ ሲሰጡ የተፈቀደው ፍራንኮ ቫሉታ ሀብት ከሀገር እንዲሸሽ ምክንያት እየሆነ በመሆኑ ሊታገድ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥተው እንደነበር ይታወሳል፡፡

የገንዘብ ሚኒስቴር ዛሬ በፃፈው ደብዳቤም ከዚህ ቀደም በፍራንኮ ቫሉታ ሸቀጦችን ከውጪ ያዘዙ ካሉ ከዛሬ ጀምሮ በ2 ሳምንት ጊዜ ውስጥ ግዢ የተፈፀመባቸው ህጋዊ ሰነዶችን ለጉምሩክ ኮሚሽን በማቅረብ ተቀባይነት አቅርበው የንግድ ሸቀጦቹ ወደ ሀገር እንዲገቡ ይደረጋል ብሏል።

የፍራንኮ ቫሉታ ፍቃድ ከጥቅምት 28/2017 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ የማይደረግ መሆኑ ተመላክቷል።

የመረጃው ባለቤት ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ነው።

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

08 Nov, 17:25


#Update

" ጥያቄያችን ፖለቲካዊ ይዘት እንዲኖረው ተደርጓል " - ቅሬታ አቅራቢ የጤና ባለሙያዎች

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ የአንጋጫ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ውስጥ የሚሰሩ ከ80 በላይ የጤና ባለሞያዎች ለ6 ወራት የሰሩበት የተጠራቀመ የዲዩቲ ክፍያ ስላልተከፈላቸው ከ12/02/17 ዓ/ም ጀምሮ ስራ ማቆማቸውን መግለጻችን ይታወሳል።

የሆስፒታሉ ሰራተኞች ከተጠቀሰው ቀን ጀምሮ ለስድስት ቀናት ማለትም 12/02/17 እስከ 18/02/17 ድረስ ስራ ሳይገቡ ቆይተው ማክሰኞ በ19/02/2017 ዓ.ም ከአካባቢው ሽማግሌዎች ጋር የወረዳው ባለሥልጣናት በተገኙበት በተደረገ ውይይት ሽማግሌዎች ከወረዳው ሃላፊዎች ጋር ለማደራደር በመስማማታቸው ወደ ስራ ገበታቸው ተመልሰዋል።

ይሁን እንጂ ከስብሰባው ማብቃት በኋላ " አድማውን አስተባብራቹሃል " በሚል 14 የሚሆኑ ባለሞያዎች ለእስር ተዳርገዋል።

በተለያየ ቀናት ለእስር የተዳረጉት እነዚህ ባለሞያዎች ከ 2 እስከ 6 ቀናት ለሚሆን ጊዜ ታስረው በዋስ ከእስር ተፈተው ወደ ስራ ገበታቸው ተመልሰዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለእስር ከተዳረጉት ባለሞያዎች መካከል የተወሰኑትን አነጋግሯል።

ባለሙያዎቹ  " ጥያቄያችን ፓለቲካዊ ይዘት እንዲኖረው ተደርጓል " ብለውናል።

" የጠየቅነው የሰራንበትን ክፍያ ሆኖ ሳለ ፍርድ ቤት ስንቀርብ ' ህዝብ በመንግስት ላይ እንዲነሳ አድርጋቹሃል፣ ሰዎችን ወደ ሥራ እንዳይጋቡ አስፈራርታቹሃል ' የሚል ክስ ተነቦልናል " ነው ያሉት።

በተጨማሪም ባለሞያዎች ወደ ሆስፒታል ሲመለሱ ከአሁን በኋላ ተመሳሳይ የሆነ የስራ ማቆም አድማ ውስጥ ቢገቡ አስፈላጊውን አስተዳደራዊ እርምጃ እንደሚወሰድባቸው የሚገልጽ ደብዳቤ ላይ እንዲፈርሙ ተደርጓል ብከዋክ።

ሰራተኞቹ ከተመለሱ በኋላ BPR የተሰኘ በየስምንት ሰዓቱ በሺፍት የሚቀያየሩበት አሰራር እንዲዘረጋ መደረጉን ተናግረዋል።

በአዲሱ አሰራር መሰረት ጠዋት 12 ሰዓት ወደ ስራ የገባ ሰራተኛ 8 ሰዓት ከስራ የሚወጣ ሲሆን 8 ሰዓት የገባው ምሽት 4 ሰዓት ከስራ ይወጣል።

ይሁን እንጂ ይህ አሰራር " ሆስፒታሉ ለሰራተኞች ሰርቪስ የሌለው በመሆኑ እና በምሽት ሺፍት ከስራ ስንወጣ እና ስንገባ ለጅብ እየተጋለጥን ነው " በሚል ቅሬታ አቅርበዋል።

" ይህ አይነቱ አሰራር የተዘረጋው የወረዳው አስተዳደር ለመቀጣጫ እንዲሆን በሚል ነው " ያሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ " የትርፍ ሰዓት ሥራ ለማስቀረት የተደረገ ነው " ብለዋል።

ቲክቫህ ጉዳዩ በዋናነት የሚመለከታቸውን የአንጋጫ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ እና የሆስፒታሉ ምክትል ቦርድ ሰብሳቢ የሆኑትን አቶ ማርቆስ ማሞን ቅሬታውን ከተቀበለበት ቀን ጀምሮ ለማናገር ተደጋጋሚ የሆነ የስልክ ሙከራ ቢያደርግም ስልካቸውን ለማንሳት ፈቃደኛ አልሆኑም።

የሆስፒታሉ አስተዳዳሪ አቶ ተሰማ አበራ አዲሱ  አሰራር ለአደጋ አጋልጦናል የሚለውን የሆስፒታሉን ባለሞያዎች ቅሬታ አይቀበሉም።

" የትርፍ ሰዓት ስራ ሲሰሩ ያልነበረ ጅብ ዛሬ ከየት መጣ " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ይህ አይነቱ አሰራር ያልነበረና አዲስ ተደርጎ መወሰድ የለበትም ብለዋል።

አክለውም " ይህን ጭቅጭቅ የሚያመጣው ወረዳው የመክፈል አቅም የሌለው በመሆኑ ነው በቀጣይም መጋጨት የለብንም " በማለት አሰራሩ በገንዘብ እጥረት ምክንያት የተዘረጋ መሆኑን ጠቁመዋል።

ባለሞያዎቹ የሰሩበት ገንዘባቸው ሳይከፈላቸው ወደ ስራ እንዲመለሱ ተደርጓል መቼ ክፍያቸው ይፈጸማል ስንል በድጋሚ ላነሳንላቸው ጥያቄም "አሁንም እየተነጋገርን ነው ከወረዳ መንግሥት ጋር የገንዘብ ክፍተት ስላጋጠመ እንጂ መከፈል እንዳለበት ተግባብተናል" የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

#ThikvahEthiopia

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

08 Nov, 17:21


#ጋምቤላ

አዲስ አመራር ከመጣ በኃላ በጋምቤላ መሻሻል ታይቷል ?

በጋምቤላ ክልል ካለፈው ነሐሴ 2016 ዓ/ም ወዲህ የአመራር ለውጥ ከተደረገ ወዲህ በክልሉ የነበረው የሠላም ሁኔታ እየተሻሻለ መምጣቱን አዲሱ አስተዳደር፣ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እንዲሁም ነዋሪዎች ተናግረዋል።

ባለፈው ዓመት በጋምቤላ ክልል በተለያዩ አካባቢዎችና ጊዜዎች ግጭቶች እየተከሰቱ በሰው ህይዎት ላይ ጉዳት ሲደርስ ቆይቷል።

ከሰብዓዊ ጉዳቱ ባሻገር በክልሉ ነዋሪዎች መካክል የነበሩ ማህበራዊ እንቅስቃሴዎች በአንዳንድ ቦታዎች እስከመገደብ ደርሰውም ነበር።

የክልሉ ልማትና ሰላምም በእጅጉ ተጎደቶ ነበር።

በተለይ ቀደም ባሉት ጊዜዎች የአኙዋክ ተውላጆች ወደ ኑዌር ሰፈር አይሄዱም፣ ኑዌሮችም በተመሳሳይ ወደ አኙዋክ ሰፈር ይሻገሩ አልነበረም።

አሁን ላይ ግን ሁኔታዎች እየተሻሻሉ መምጣታቸውን የጋምቤላ ነዋሪዎች ተናግረዋል።

የጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ጋትሏክ ሮን ምን አሉ ?

- ችግሮችን ለማስተካክልና በክልሉ ሠላም ለማስፈንና ህዝቡን ወደልማት ለማምጣት በክልሉ ከነሐሴ 2016 ዓ/ም መጀመሪያ ሳምንት ላይ የአመራር ለውጥ በመደረጉ በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች ሠላም ሰፍኗል።

- በክልሉ በነበረው የሠላም እጦት ምክንያት የጋምቤላ ከተማ የአኙዋክና የኑዌር በሚል ተከፍሎ አኙዋኮች ወደ ኑዌር ሰፈር፣ ኑዌሮችም ወደ አኙዋክ መንደር ለመሻገር ችግሮች ነበሩ። አሁን ያ ሁሉ ቀርቶ አዲሱ አመራር ወደ ሥራ ከገባና ህዝባዊ ውይይቶች ከተደረጉ በኋላ ሁሉም በሠላም በሁሉም ሥፍራ ይንቀሳቀሳል።

🔵 ማሉት ዴቪድ የተባሉ የጋምቤላ ከተማ ነዋሪ የምክትል ርዕሰ መስተዳድሩን ሀሳብ ይጋሩታል፣ አሁን አንዱ ወደ ሌላው ያለስጋት እንደሚንቀሳቀስ ነው ያረጋገጡት። ከተማውም ሠላም እንደሆን አመልክተዋል።

- አዳዲስ ሹመቶችና ምደባዎች ተሰጥተዋል። ይህም የትምህርት ዝግጅትንና የሥራ ልምድን መሠረት ያደረገ ነው።

- ለውጥ ያመጣሉ ተብሎ የታመነባቸው ቀደም ሲል ስልጣን ላይ የነበሩና ህዝባዊ አመለካከት ያላቸው በርከት ያሉ አመራሮችም በአዲሱ ሹመትና ምደባ እንደገና  ተካተዋል።

- " ሠላም ወርዶ ህዝቡ በልማት መካስ አለበት " በሚል እሳቤ እውቀት፣ ልምድና የተሻል አመለካክትና እይታ ያላችው ሠዎች ወደ አመራሩ ተካተዋል።

- በኮታ መታሰር ቀርቷል። ቀደም ሲል በነበረው አሰራር ወንጀል ያልሰሩ ሰዎች በኮታ ጭምር ይታሰሩ ነበር። አሁን ግን በወንጀል የተጠረጠሩትን ብቻ ተጠያቂ የሚያደርግ አሰራር ተዘርግቷል።

- በፊት አንድ ኑዌር ቢያጠፋና ቢታሰር ሌላ አኙዋክ አብሮ እንዲታሰር ይደረግ ነበር፣ ሌላ አኙዋክ አጥፍቶ ቢታሰር  የኑዌር ተወላጅ ተደርቦ እንዲታሰር ይደረግ ነበር ፤ አሁን ግን ጠፋተኛው ከየትኛውም ወገን ይሁን ጠፋተኛ ከሆን ተጠርጣሪው ብቻ ተለይቶ ተጠያቂ ይሆናል። የኮታ እስር ቀርቷል።

" ከአዲሱ አመራር ጋር ለመስራት ዝግጁ ነኝ " - ጋብዴን

የጋምቤላ ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ(ጋብዴን) ሊቀመንበር አቶ ኡባንግ ኡሞድ ቀደም ሲል የነበረው አመራር ህዝቡን መምራት እንዳልቻለና ለውጥ እንዲመጣ ሲታግሉ እንደንበር ገልጠዋል።

ችግሩ የአመራሩ ሆኖ ሳለ ህዝቡን በከፍተኛ የሠላም እጦት ውስጥ ከትቶት ነበር ነው ያሉት።

በክልሉ የነበረውን ችግር እስከ የተፎካካሪ ፓርቲ የጋራ ምክር ቤት በማድረስ የነበረው የሠላም እጦት እንዲታወቅ መደረጉንና ለውጥ እንዲደረግ በግልም በጋራም ትግል ሲደረግ እንደነበር አስረድተዋል። 

አዲሶቹ አመራሮች በሕዝቡ ተቀባይነት ማግኘታቸውንና ፓርቲያቸውም በአዲሱ አመራር ደስተኛ መሆኑን አቶ ኡባንግ ተናግረዋል።

ከአዲሱ አመራር ጋርም በጋራ ለመስራት ዝግጁ እንደሆኑም ነው የገለጡት። 

የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት ነሐሴ 9/2016 ዓ ም ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ ወ/ሮ ዓለሚቱ ኡመድን የመጀመሪያዋ የክልል ሴት ርዕሰ መስተዳድር፣ ዶ/ር ጋትሏክ ሮንን ደግሞ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አድርጎ መሾሙ ይታወሳል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ነው።

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

08 Nov, 17:21


የኢትዮ130 6ኛ ዙር ዕድለኞች እንኳን ደስ አላችሁ! 🎉🎉

💡 ሽልማቱ እንደቀጠለ ነው፤ ጥቅልና የአየርሰዓት በመግዛት፣ የአገልግሎት ክፍያዎችን በቴሌብር በመፈጸም እንዲሁም ገንዘብ በመላክና በመቀበል ተጨማሪ የጨዋታ ዕድሎችን ያግኙ!

🚘 6 ዘመናዊ የኤሌክትሪክ መኪኖች
🛺 7 ባለ 3 እግር ተሽከርካሪዎች
💰 በየቀኑ የ20 ሺህ ፤ በየሳምንቱ የ50 ሺህ እና 100 ሺህ ብር ገንዘብ ሽልማቶች በቴሌብር
📱 ዘመናዊ ስማርት ስልኮች እንዲሁም
🎁 በርካታ የሞባይል ጥቅሎች!

በቴሌብር ሱፐርአፕ ኢትዮ130 መተግበሪያ ወይም ለኢትዮ ፕሮሞ *130# ለኢትዮ ላኪ ስሎት *131# በመደወል ይመዝገቡ!

ለተጨማሪ መረጃ፡ https://bit.ly/3Y0pGzs ይጎብኙ!

#130_ዓመታትን_በጽናት_ታላቅ_አገርና_ሕዝብ_በማገልገል_ላይ

#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

08 Nov, 17:21


ሕብር ሼባ ማይል ካርድ

በሕብር ሼባ ማይል ካርድ ግብይትዎን በመፈፀም ለጉዞ የሚያስፈልግዎትን ተጨማሪ ማይል ጉርሻ ያግኙ፡፡

ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!

📞  ለበለጠ መረጃ ወደ 995 ነፃ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ፡፡
🤳 በቀላሉ አዳዲስ መረጃዎች  እንዲደርስዎ የቴሌግራም ገፃችንን አሁኑኑ ይቀላቀሉ፡፡ https://t.me/HibretBanket
🌐 ሌሎች የማህበራዊ ገፆቻችንን እና ድህረ ገፃችንን linktr.ee/Hibret.Bank ይጎብኙ፡፡

#shebamiles #Rewardyourself #Hibretbank

THIKVAH-ETHIOPIA

31 Oct, 08:02


" ሪፎርሙ ባይሰራ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ይፈርስ ነበር ! " - ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ እና ምላሽ እየሰጡ ናቸው።

በተለይም ከኢኮኖሚ ሪፎርሙ ጋር የተያዙ በርካታ ጉዳዮችን አንስተዋል።

አንዱ ጉዳይ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን የሚመለከት ነው።

" የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በዚህ ሪፎርም በጣም ተጠቃሚ ከሆኑ ተቋማት አንዱ ነው " ያሉት ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) ፥ " በህዳሴ ምክንያት ፣ በቦንድ ምክንያት በጣም አስጊ ጉዳይ ውስጥ ከነበሩ ተቋማት አንዱ ንግድ ባንክ ነው " ብለዋል።

" ይሄ ሪፎርም ባይሰራ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ይፈርስ ነበር " ሲሉ ገልጸዋል።

" ባንኩ ያለበትን ዕዳ በቀላሉ ማኔጅ የሚያደርገው አልነበረም " ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፥ " በዚህ ሪፎርም 900 ቢሊዮን ብር የተራዘመ ቦንድ አግኝቷል ባንኩ በከፍተኛ ደረጃ የነበረበትን ኢሚዴዬት አደጋ መከላከል የሚያስችል ሪሶርስ አግኝቶ ስራ ጀምሯል " ብለዋል።

" ንግድ ባንክ ወደቀ ማለት ኢትዮጵያ ውስጥ 30ውም ባንኮች ወደቁ ማለት ነው። ዋናው የኢትዮጵያ ባንክ ንግድ ባንክ ነው እሱን ማዳን የባንክ ሴክተሩን ማዳን ነው " ሲሉም አክለዋል።

" 900 ቢሊዮን ዶላር የተገኘበት መንገድ ብንነጋገር ብዙ አስደሳች ጉዳዮች ያሉበት ነው ግን አላነሳውም " ብለዋል።

ገንዘቡ የተገኘው ጠቃሚ በሆነ ድርድር እንደሆነ የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምን አይነት ድርድር ይህ ሁሉ ገንዘብ እንደተገኘ በዝርዝር ከመናገር ተቆጥበዋል።

#ThikvahEthiopia

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

31 Oct, 07:41


" ፍራንኮ ቫሉታን በሚመለከት በቅርብ ማስተካከያ ይደረጋል " - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከፓርላማ አባላት ለተነሱ የኢኮኖሚ ጥያቄዎች ማብራሪያ እና ምላሽ እየሰጡ ናቸው።

በዚሁ ወቅት በቅርቡ ፍራንኮ ቫሉታን በሚመለከት ማስተካከያ እንደሚደረግ ጠቁመዋል።

ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) " ባለፉት ጥቂት ወራት ከሪፎርሙ ጋር ተያይዞ ከወሰናቸው አብሮ ከማይሄዱ ውሳኔዎች ውስጥ አንዱ ፍራንኮ ቫሉታ ነው " ብለዋል።

" ያን የወሰነው በሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች ነው። አንዱ በውጭ ያለ ሃብት ከዚህ ቀደም የሸሸ ወደ ሀገር ውስጥ መምጣት የሚችል ከሆነ እድል ለመስጠት ፤ ሁለተኛ ባንኮቻችን አሁን በጀመርነው ኢኮኖሚክ ኦፕንአፕ በቂ ልምምድ እስኪያደርጉ ከውጭ የሚገቡ ሸቀጦች እንዳያንሱና የኑሮ ውድነት እንዳያባብሱ ጉዳት ቢኖረውም ከፈት እናድርግ የሚል እሳቤ ነበር " ሲሉ አስረድተዋል።

" ያየነው ውጤት ከዚህ በላይ መሸከም ተገቢ እንዳልሆነ የሚያሳይ ስለሆነ በቅርቡ ፍራንኮ ቫሉታን በሚመለከት ማስተካከያ እንደሚደረግ ይጠበቃል " ብለዋል።

የኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ እየሰጡ ያሉት ማብራሪያ ያንብቡ : https://telegra.ph/PM-Office-10-31

#ThikvahEthiopia

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

31 Oct, 06:57


#ፓርላማ

" እስር ቤቶች የተጨናነቁት ያለ ፍርድ በታጎሩት አማራዎች ነው ! " - አበባው ደሳለው (ዶ/ር)

የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት እና የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) አባል የሆኑት አበባው ደሳለው (ዶ/ር) ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ያቀረቡት ጥያቄ ምንድነው ?

አበባው ደሳለው (ዶ/ር) ፦

" በባለፈው ዓመት መጨረሻ የበጀት ዓመቱ መዝጊያ ሰኔ 28 ወቅት ያነሳናቸው በርካታ ከህዝብ ጥያቄዎች ነበሩ።

ነገር ግን እነዛ ጥያቄዎች ስላልተመለሱ ከዛ ብዙም ለየት ያለ ጥያቄ አይደለም የምንጠይቀው ምክንያቱም ችግሮቹ እየተባባሱ ስለመጡ።

በመላው ሀገሪቱ ያለው ጅምላ የንጻሃን ግድያ፣ ህጋወጥ ጅምላ እስር ፣ እገታ ፣ ጾታዊ ጥቃት ፣ መፈናቀል ፣ ከፍተኛ ከኑሮ ውድነት ፣ አግባብ ያልሆነ የቤቶች ፈረሳ ያኔም ነበረ አሁንም ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው።

በአሁን ሰዓት በመላ ሀገሪቱ ከፍተኛ የህዝብ ብሶት አለ። በተለይ በአማራ ክልል ያለው ችግር ደግሞ አጠቃላይ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ እና ማህበራዊ ህይወት ምስቅልቅል እንዲሆን ያደረገ ነው።

በአማራ ክልል የመንግስት ኃይሎች ፀጥታውን በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ ለመቆጣጠር ነበር ዘመቻ የጀመሩት ነገር ይኸው ከአንድ ዓመት በላይ ሆነ እንጂ ችግሩ ይበልጥ እየከፋ ሄደ እንጂ እየተሻሻለ አይደለም።

አሁንም ንጹሃን ዜጎች በከባድ መሳሪያ እና በድሮን እየሞቱ ነው ፣ ሲቪል ተቋማት የሆኑ ጤና ጣቢያዎች ፣ ትምህርት ቤቶች እየወደሙ ነው።

በአዲስ አበባ ፣ በአማራ ክልል እና በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች እስር ቤቶች የተጨናነቁት ያለ ፍርድ በታጎሩት አማራዎች ነው።

የኛ የምክር ቤት አባል አቶ ክርስቲያን ታደለን ጨምሮ የክልል ምክር ቤቶች አባላት ሳይቀሩ ከአንድ አመት በላይ ሆነ ተብሎ በሚመስል ሁኔታ ያለ ፍርድ እየተመላለሱ ነው ያሉት። ፍርድ ሳያገኙ ከአንድ ዓመት በላይ አስቆጥረዋል። ከዚህም የሚብሱ አሉ። ፖለቲከኞች ፣ ጋዜጠኞች፣ አንቂዎች ለሁለት ዓመት ያክል ያለ ፍርድ የተቀመጡ አሉ በወይኒ ቤቶች።

ከፍተኛ የኑሮ ውድነቱን ስናይ የኢኮኖሚ ማሻሻያ አድርገናል፣ የብር የመግዛት አቅምን አዳክመን ኢኮኖሚው እንዲንሰራራ እናድረጋለን በሚል የተለያዩ ድጎማዎችን ተደርገዋል የደመወዝ ጭማሪ እስካሁን መንግስት ሰራተኛው ክሲ ውስጥ አልገባም ኑሮ ውድነቱ ግን እጅግ በጣም አሻቅቧል።

በኮሪደር ልማት ሰበብ  በብዙ ሺዎች በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ቤቶች ፈርሰው የተለያየ አቤቱታ በተለያየ መገናኛ ብዙሃን ዜጎች እያሰሙ ነው በተለይ አዲስ አበባ ችግሩ በጣም የገዘፈ ነው።

በአጠቃላይ እነዚህን ችግሮች ስናይ ከሰላምና ፀጥታው ጋር አብረው የሚሄዱ ናቸው።

ቅድሚያ የሰላምና ፀጥታ ችግሩን ብንፈታው ሌሎች ችግሮችን አብረን እናስወግዳለን። እዛ ላይ ማተኮር አለብን።

🔵 መንግስት የሰላምና ፀጥታ ችግሩን ለመፍታት እየሄደ ያለው አካሄድ እስካሁን ወታደራዊ ነው ፤ ፖለቲካዊ አካሄድ ለምን አልደፈረም ? ለምንድነው ፖለቲካዊ መፍትሄ ላይ የደከመው ?

🔵 ለእውነተኛ ድርድርና ውይይት በይፋ ጥሪ አቅርቦ ችግሩን ለምንድነው ለመፍታት የማይጠጋው ?

🔵 የሰላም መፍትሄ አካል አንዱ የጅምላ እስር ፣ የጅምላ ግድያ ማቆም ነው። ይሄ መቼ ነው የሚቆመው?

🔵 የኢኮሮሚ ችግሩን ለመፍታት ዜጎች ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሰው መስራት አለባቸው ያን ላለፉት በርካታ ዓመታት ማድረግ አልተቻለም ዜጎች በነጻነት እና በሰላም ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሰው እንዲሰሩ መንግስት የሚያስችለው መቼ ነው ? "

በተጠየቀው ጥያቄ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚሰጡትን ምላሽ ተከታትለን እናቀርባለን።

#ThikvahEthiopia

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

31 Oct, 06:56


#HopR

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሄደ ነው።

በስብሰባው ላይ የምክር ቤት አባላት ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ መስከረም 27 ቀን 2017 ዓ.ም ለህዝብ ተወካዮች እና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች የጋራ ስብሰባ ያደረጉትን የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ ጥያቄዎችን ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አቅርበዋል።

አሁን ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጥያቄዎቹ ላይ ምላሽ እና ማብራሪያ እየሰጡ ነው።

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

31 Oct, 06:56


King's Computer !

ለግራፊክስ ዲዛይነሮች ፣ ለቢሮ ስራዎችና ለተማሪዎች የሚሆኑ ፥ አዳዲስ ጌሚንግ ላፕቶፖችን እና ዴስክቶፖቹን ፣ ዱባይ ዩዝድ ላፕቶፖችን ከመልካም መስተንግዶ ከተሟሉ ሶፍትዌሮች በጥራት እና በ ብዛት ከ እኛ ጋር ያገኛሉ።

እንገዛለን እንሸጣለን ይዘው ይምጡ ይዘው ይሒዱ። ከአንድ ዓመት ዋስትና ጋር። የተለያዩ ዓይነት ላፕቶፓች ለማየትና ለመምረጥ ሊንኩን ይጠቀሙ - Telegram-  👉https://t.me/kingscom21
Inbox @Yime27

አድራሻ፦ (https://g.co/kgs/HGQYoEP)
መገናኛ ማራቶን ህንፃ አንደኛ ፎቅ 111 ቁጥር king's Computer
ስልክ - +251974060288 +251703077990

THIKVAH-ETHIOPIA

31 Oct, 06:55


#MerttEka

🤩 እነዚህ የቤት ዕቃዎች በሱቃችን በቅናሽ ዋጋ እየተሸጡ ነው። የሁሉንም ዕቃዎች ዋጋ  ይሄንን👉 t.me/MerttEka ተጭነው በቴሌግራምው ማየት ይችላሉ።

አድራሻችን፦ አዲስ አበባ፤ መገናኛ፤ ዘፍመሽ ግራንድ ሞል ፤ 3ተኛ ፎቅ ሱቅ 376

THIKVAH-ETHIOPIA

30 Oct, 17:58


#እንድታውቁት

በአዲስ አበባ መገናኛ አካባቢ ያለውን ከፍተኛ የትራንስፖርት መጨናነቅ ለመፍታት ያግዛል የተባለው የመሬት ውስጥ የእግረኛ መተላላፊያ መስመር ግንባታ መጀመሩ ይታወቃል።

በመሆኑም በተለይ ከመገናኛ አደባባይ ወደ ቦሌ ፤ ከቦሌ ወደ መገናኛ አደባባይ በሁለቱም አቅጣጫ ለተሽከርካሪ ዝግ መሆኑን ተገልጿል።

እግረኞች በሙሉጌታ ዘለቀ ህንጻ በኩል ማለፍ ስለማይቻል በቦሌ ክ/ ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት ባለው የእግረኛ መንገድ እንዲጓዙ ተጠይቋል።

አሽከርካሪዎች ሌሎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ጥሪ ቀርቧል።

#የአዲስአበባትራፊክማኔጅመንትባለስልጣን

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

30 Oct, 17:54


" የተሰጠው ማብራሪያ ከእውነት የራቀ ነው " - የ1997 የጋራ መኖሪያ ቤት ተመዝጋቢዎች

ሰሞኑን ከ1997 የጋራ መኖሪያ ቤት ወይም ኮንዶሚኒየም ተመዝጋቢዎች ጋር በተያያዘ የአዲስ አበባ ከተማ የቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ዝርዝር ማብራሪያ መስጠቱ ይታወሳል።

በዚህም ማብራሪያው ፥ " ብቁና ንቁ የነበሩ የ1997 ተመዝጋቢዎች  በ14ኛው ዙር ዕጣ ሙሉ በሙሉ ተስተናግደዋል " ነበር ያለው።

ዝርዝር ማብራሪያው በዚህም ይገኛል ፦ https://t.me/tikvahethiopia/91710?single

ማብራሪያውን የተመለከቱ ቆጣቢዎች ግን ማብራሪያ " ከእውነት የራቀ ነው " ሲሉ ግብረ መልስ ሰጥተዋል።

" እኛ የ1997 ነባር የ20/80 የጋራ መኖሪያ ቤት አክቲቭ ተመዝጋቢዎች ሰሞኑን የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ የሰጠው መግለጫ ከእውነታ የራቀ ነው ስንል አንገልፃለን " ብለዋል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላኩት መልዕክት።

" እኛ የ1997 አክቲቭ ቆጣቢዎች የሆንን በ14ኛው ዙር 25 ሺህ ለእጣው አክቲቭ ናቸው ተብለን ለ18,650  ቤቶች ተወዳድረን እጣው ያልወጣልን ወደ 8,000 የምንሆን የተረፍን አክቲቭ ቆጣቢዎች መሆናችን ቢሮው በደንብ ያውቃል ሰነዳችንም በግልፅ በቤቶች ኤጀንሲም ሆነ በንግድ ባንክ አለ " ብለዋል።

" ቢሮው ' ብቁ እና ንቁ የነበሩ የ1997 የጋራ መኖሪያ ቤት ተመዝጋቢዎች በ14ኛው ዙር ዕጣ ሙሉ በሙሉ ተስተናግደዋል ' ማለቱ እጅግ ግራ የሚያጋባ ነው የሆነብን " ሲሉም አክለዋል።

አሉን ያሏቸውን ዶክመንቶችንም የላኩ ሲሆን ከላይ ተያይዟል።

ጉዳያቸውን የኢትዮጵያ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም እንደያዘው አስታውሰው ተቋሙ መፍትሄ እስኪያገኙ ድረስ እንዲገፋበት ጥሪ አቅርበዋል።

ዜጎቹ " አሁንም ድምፃችን ይሰማ ፤ መፍትሄ ይሰጠን " ሲሉ ጠይቀዋል።

#ThikvahEthiopia

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

30 Oct, 17:28


🔈 #የሠራተኞችድምጽ

" 3 ወር ደሞዝ አልተከፈለንም " ያሉ የፐርፐዝ ብላክ ሠራተኞች የከፋ ችግር ላይ እንደሚገኙ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ያሉበት የከፋ ችግር ታይቶ መፍትሄ እንዲፈለግላቸው ጥሪ አቅርበዋል።

ሠራተኞቹ ምን አሉ ?

" እኛ በፐርፐዝ ብላክ ኢታኤች የምንሰራ ሠረተኞች ደሞዝ ስላልተከፈለን ለከፋ ችግር ተዳርገናል።

በፐርፐዝ ብላክ ኢቲኤች የምንሰራ ሰራተኞች ደሞዝ ለ3 ወር ባለመከፈሉ ምክንያት ካለው የኑሮ ውድነት ጋር ተደማምሮ ከፍተኛ ችግር ላይ ወድቀናል።

ከዛሬ ነገ ይከፈለናል በሚል ተስፋ የቆየን ቢሆንም እስካሁን በህግ ተይዟል ከሚል ጥቅል ምላሽ ውጪ  ይህ ነው የሚባል መረጃ እንኳን ማግኘት አልቻልንም።

ከእለት ወደእለት ወዳለመኖር እየተሸጋገርን ነው ፤ አልፎ ለከፍተኛ ማሕበራዊ ቀውሶች እየተዳረግን ነው።

አብዛኛው ሠራተኛ ቤት ተከራይቶ ስለሆነ የሚኖረው  የቤት ኪራይ መክፈል አቅቶታል ቤተሰብ እየተበተነ ነው፤ ወላጆች ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት መላክ አልቻሉም።

እነዚ የጠቀስናቸው ችግሮች ከብዙ በጥቂቶቹ ናቸው የሚመለከተው አካል ያለንበትን ችግር አይቶ አፋጣኝ ምላሽ ቢሰጠን " ብለዋል።

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

30 Oct, 17:23


#EthiopianAirlines🇪🇹

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዓመታዊው APEX Passenger Choice Awards 2025፣ ምርጥ የአፍሪካ አየር መንገድ “ Best Overall in Africa award ” ሽልማት ማሸነፉን አሳውቋል።

አየር መንገዱ ፦
🛫 በምርጥ የበረራ ላይ መስተንግዶ፣
🛫 በምርጥ የበረራ ላይ መዝናኛ አገልግሎት፣
🛫 በምርጥ የበረራ ላይ የምግብ እና መጠጥ አገልግሎት፣
🛫 በምርጥ የአውሮፕላን ውስጥ መቀመጫ ምቾት
🛫 በምርጥ የበረራ ላይ ገመድ አልባ ኢንተርኔት አገልግሎት ዘርፎች ከአፍሪካ ምርጡ አየር መንገድ በመሆን ተሸልሟል።

ይህ በ “ Airline Passenger Experience Association ” (APEX) የመንገደኞችን ድምፅ መሰረት በማድረግ ለአየር መንገዶች ዕውቅና የሚሰጥበት ነው።

በአቪዬሽን ኢንደስትሪውም ትልቅ ስፍራ ከሚሰጣቸው ሽልማቶች አንዱ እንደሆነ አየር መንገዱ ገልጿል።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

30 Oct, 17:14


" በአስቸኳይ ተማሪዎቹ መብታቸው ተጠብቆ ወደ ትምህርት ገበታቸው ተመልሰው ያመለጣቸው ትምህርት ይካካስ " - ከፍተኛ ምክር ቤቱ

ካለፋት 2 ሳምንታት ወዲህ በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ አንዳንድ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ላይ በአለባበሳቸው ምክንያትና በእምነታቸው ላይ ያነጣጠረ ከእለት ወደ እለት እየሰፋ ያለ ጫናና እንግልት እየተከሰተ መሆኑን የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት አሳውቋል።

ከፍተኛ ምክር ቤቱ ይህንን ያሳወቀው ለከተማው ትምህርት ቢሮ በላከው ደብዳቤ ነው።

" ችግሩ ከተፈጠረበት ቀን ጀምሮ ትምህርት ቤቶቹ በሚገኙበት ወረዳ እና ክፍለ ከተማ የመጅሊስ መዋቅሮቻችን አመራር አማካኝነት ችግሩን ለመፍታት ጥልቅ ውይይት በማድረግ ጥረት ተደርጓል " ብሏል።

" በዚህም መሰረት ከተወሰኑ ት/ት ቤቶች ጋር በተደረገ ስምምነት ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ ተደርጎ የነበረ ሲሆን ከቀናት በኋላ ግን ከውይይቱ ስምምነት በመውጣት ተማሪዎችን ማስክ እንኳ ቢሆን እድርገው እንዳይገቡ ተከልክለዋል " ሲል ም/ቤቱ ገልጿል።

እነዚህ ትምህርት ቤቶች እነማን እንደሆኑ ግን በዝርዝር ያለው ነገር የለም።

በጉዳዩ ላይ ሰሞኑን ከከተማው ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች ጋር ውይይት ሲያደርግ እንደነበርም ምክር ቤቱ አስታውሷል።

" የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ባወጣው የተማሪዎች የዲሲፒሊን መመሪያ ውስጥ አንድም ቦታ ላይ ክልከላ የሌለበት አለባበስ ስለመሆኑ ባደረግነው ውይይት ተማምነናል " ብሏል።

" ይህ ሆኖ ሳለ በአንዳንድ ኃላፊነት በጎደላቸው አመራሮች ምክንያት ችግር በሚፈጥር መልኩ እየተሄደበት ያለው አካሄድ ተማሪዎችን ከትምህርት ገበታቸው ያላግባብ እንዲታገዱ መደረጉና የስነ-ልቦና ጫና መፈጠሩ የየትኛውም ህግ ድጋፍ የሌለውና ህዝበ ሙስሊሙንና መንግስትን ለማጋጨት የሚደረግ ጥረት መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል " ሲል አክሏል።

" ስለሆነም በአስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጥና ተማሪዎቹም መብታቸው ተጠብቆ ወደ ትምህርት ገበታቸው ተመልሰው ያመለጣቸው ትምህርት #እንዲካካስላቸው " ሲል አሳስቧል።

በሌላ በኩል ፥ የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ከተማሪዎች ጋር ውይይት ማድረጉን አመልክቷል።

ሰሞኑን በአንዳንድ ትምህርት ቤቶች ውስጥ በሙስሊም ሴት ተማሪዎች አለባበስ ምክንያት ችግሮች መከሰታቸው ፤ በዚህም ተማሪዎቹ ለ3 ሳምንታት ያህል ከትምህርት ገበታቸው እንደተስተጓጎሉ ተገልጿል።

እነዚህን ተማሪዎችን የሚወክሉ ከአዲስ ከተማ ት/ቤቶች የተውጣጡ ተማሪዎች በተሳተፉበት በዛሬው ውይይት ላይ ፦

🟢 ከትምህርት ገበታቸው የተለዩ ተማሪዎች ወደ ትምህርታቸው እንዲመለሱ ተጠይቋል።

🟢 በትምህርት ቤቶቹ ውስጥ ሙስሊም ሴት ተማሪዎችንና አለባበሳቸውን መነሻ በማድረግ እየተስተዋለ ያለው አግላይነትና ከትምህርት የማራቅ ተግባር ዘላቂ መፍትሔ ሊሰጠው ይገባል ተብሏል።

🟢 ዛሬ ከአለባበስ ጋር ተያይዞ የተነሳው ጥያቄ ነገ ወደ ሌላ የእምነቱ የስርዓተ አምልኮ ላይ ተሸጋግሮ ችግር ይፈጥራል የሚል ስጋት ገብቶናል ያሉ ተማሪዎቹ የተነሳውን ችግር ከወዲሁ እንዲፈታ አሳስበዋል።

የምክር ቤት አመራሮቹ ምን አሉ ?

➡️  ምክር ቤቱ የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት ጉዳዩ ከተከሰተ ቀን ጀምሮ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ገልጸዋል።

➡️ ሙስሊሙ በሚታወቅበት ሰላም ፈላጊነቱ ምክንያት እስካሁን የነበሩ ጉዳዮችን በሕግ አግባብ ማሳለፍ መቻሉን ገልጸዋል። አሁንም  በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ አንዳንድ ትምህርት ቤቶች የተከሰተውን ችግር በተለመደው የሕግ አግባብ እልባት ለማስገኘት እየተሰራ መሆኑን አሳውቀዋል።

➡️ ሰሞኑንም ሆነ ከዚህ በፊት የተስተዋሉ ችግሮች መፍትሔ ያገኙ ዘንድ መላው ሙስሊም፣ ተማሪዎችና መሪው ተቋም መጅሊስ የተለመደ ሕጋዊ አካሄዱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

ከተማሪዎቹ ጋር በነበረው ውይይት የም/ ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሪያድ ጀማል ፤ የትምህርትና ስልጠና መመሪያ ዳይሬክተር ኡስታዝ ሀሰን አሕመድ እና የመምሪያው ክፍል ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር መሐመድ በድር ተገኝተው ነበር።

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

28 Oct, 18:05


#ረቂቅአዋጅ

የከተማ መሬትን በድርድር በሊዝ ማስተላለፍ የሚፈቅድ የአዋጅ ረቂቅ ለፓርላማ ሊቀርብ ነው።

የከተማ መሬትን ከጨረታ እና ከምደባ በተጨማሪ #በድርድር በሊዝ ማስተላለፍ የሚፈቅድ የአዋጅ ረቂቅ ለፓርላማ ሊቀርብ መሆኑን ' ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ' አስነብቧል።

አዲሱ የአዋጅ ረቂቅ፤ ከተሞች በምደባ ለማቅረብ ካዘጋጁት መሬት መጠን ውስጥ፤ ቢያንስ 20 በመቶውን ለቤት ግንባታ አገልግሎት መዋል እንዳለባቸው ግዴታ ይጥላል። 

" የከተማ መሬትን በሊዝ ስለመያዝ " እንደወጣ የተገለጸው ይህ አዋጅ፤ ነገ በሚካሄድ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ እንዲቀርብ አጀንዳ ተይዞለታል።

ረቂቅ አዋጁ " መሬትን በድርድር በሊዝ ለማስተላለፍ " ምን ይላል ?

➡️ ረቂቅ አዋጁ መሬትን በድርድር በሊዝ ለማስተላለፍ የሚፈቅደው ድንጋጌ ይገኝበታል።

➡️ 13 ዓመት ያስቆጠረው ነባሩ አዋጁ፤ የከተማ ቦታ በሊዝ እንዲያዝ የሚፈቀደው በጨረታ ወይም በምደባ ስልት ብቻ ነበር።

➡️ በአዲሱ አዋጅ የተካተተው ' የድርድር ' ስልት፤ በጨረታ እና በምደባ አግባብ ለተጠቃሚ ሊተላለፉ በማይችሉ የከተማ መሬቶች ላይ፤ አንድ አልሚ " ለተለዩ ሀገራዊ ፋይዳ ላላቸው አገልግሎቶች " መሬት በሊዝ ይዞ ማልማት የሚፈቀድበት ነው። 

➡️ ይህ ተግባራዊ የሚደረገው " አግባብ ያለው አካል " ከአልሚዎች ጋር በሚያስቀምጠው " የልማት እቅድ መሰረት " እና " ከአልሚው ጋር በመደራደር " ነው።

➡️ የከተማ መሬት በድርድር ሊተላለፍ የሚችለው " ሀገራዊ እና ክልላዊ የከተማ ልማት ስፓሻል ፕላንን " መሰረት በማድረግ ነው ይላል ረቂቅ አዋጁ።

➡️ በመንግስት እና በግሉ ዘርፍ ለሚቀርቡ የልማት ጥያቄዎች፤ መሬት በድርድር አግባብ ሊተላለፍ እንደሚችል በአዲሱ አዋጅ ተደንጓል።

➡️ በፌደራል መንግስት ለሚተዳደሩ የኢንዱስትሪ ፓርኮች፣ ለኢንዱስትሪ ልማት፣ ለከፍተኛ የትምህርት እና የጤና ተቋማት እንዲሁም ለምርምር ዘርፍ ፕሮጀክቶች የከተማ መሬት በድርድር ሊተላለፍ እንደሚችል ተዘርዝሯል።

➡️ የአገልግሎት ዘርፉን የሚደግፉ ባለኮከብ ሆቴሎች እና ለቱሪስት ልማት ለሚውሉ ሪዞርቶችም የሚቀርቡ የመሬት ጥያቄዎች በድርድር አሰራር ሊስተናገዱ ይችላሉ።

➡️ በግሉ ዘርፍ አሊያም በመንግስትና በግሉ ዘርፍ በሽርክና ሊለሙ የሚችሉ የከተማ መልሶ ማልማት ፕሮጀክቶችም፤ በዚሁ የመሬት አሰጣጥ አግባብ እንደሚስተናገዱ በአዋጁ ላይ ሰፍሯል።

➡️ ለሪል ስቴት ወይም ለቤት ልማት የሚቀርቡ የመሬት ጥያቄዎች፣ የግዙፍ የገበያ ማዕከላት (ሞል) ፕሮጀክቶች፣ ትላልቅ የነዳጅ ማጠራቀሚያዎች እና ማከፈፋያዎች፣ ለዘመናዊ የመኪና ማቆሚያ ህንጻ ግንባታዎች የሚውሉ ቦታዎች፤ በተመሳሳይ መልኩ በድርድር ማግኘት እንደሚቻልም ተመላክቷል።

➡️ በድርድር አግባብ የሚስተናገዱ ፕሮጀክቶች " የሚመጣዉ ልማት ይዘት፣ ስፋትና ጥልቀት፤ ለልማት በተመረጠው ቦታ ነባር ተጠቃሚ የሆኑ ባለይዞታዎች መስተንግዶና ተጠቃሚነት፣ በዙሪያ ባሉ ማህበረሰቦች ተጠቃሚነትና ጉዳት ቅነሳ እንዲሁም የመሰረተ ልማት አቅርቦት ድርሻ " ከግምት ውስጥ እንደሚገባ የአዋጅ ረቂቁ አትቷል።

➡️ የከተማ ቦታ በድርድር አግባብ እንዲተላለፍ የሚደረገው፤ በክልሎች፣ በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ አስተዳደሮች " ካቢኔ ሲወሰን ብቻ " ነው።

➡️ መሬት በድርድር የማስተላለፊያ ዋጋ፤ ከአካባቢው አማካይ የሊዝ ጨረታ ዋጋ በታች መሆን እንደሌለበትም በአዲሱ አዋጅ ተደንግጓል። 

በምደባ ስለሚሰጥ የከተማ መሬትስ ምን ይላል ?

🔴 አዲሱ ድንጋጌ ' ከተሞች በምደባ ለማቅረብ ካዘጋጁት የመሬት መጠን " ውስጥ " ቢያንስ 20 በመቶ የሚሆነውን " ለቤት ግንባታ አገልግሎት መዋል እንዳለባቸው ግዴታ ይጥላል።

🔴 በአንድ ከተማ በመኖሪያ ቤት ህብረት ስራ ማህበር፣ በጋራ መኖሪያ ቤት ልማት ፕሮግራም ወይም በተናጠል የከተማ መሬትን በምደባ ተጠቃሚ የሆነ ግለሰብ፤ በዚያው ከተማ " ለሁለተኛ ጊዜ በምደባ ተጠቃሚ እንዳይሆን " የሚያግድ አዲስ ድንጋጌም ተካቷል።

🔴 በአዲሱ አዋጅ፤ መሬት በጨረታ የሚያሸነፉ ግለሰቦች ለሚያሟላቸው የሚገቡ መስፈርቶች ላይ ማሻሻያ ተደርጎበታል። እስካሁን በስራ ላይ ባለው የሊዝ አዋጅ፤ አንድ ተጫራች የመሬት ጨረታ አሸናፊ የሚሆነው፤ ባቀረበው የጨረታ ዋጋ እና የቅድመ ክፍያ መጠን ላይ ተመስርቶ በሚደረግ ስሌት ከፍተኛውን ነጥብ ሲያገኝ ነው። በአዋጅ ረቂቁ ላይ ይህ ተቀይሮ የሊዝ ጨረታ አሸናፊዎች የሚለዩት፤ ከጨረታ ዋጋ እና የቅድሚያ ክፍያ በተጨማሪ የሊዝ ክፍያ ማጠናቀቂያ ጊዜ ተሰልቶ በሚገኘው የድምር ውጤት ነው። የጨረታ ዋጋ 65 በመቶ፣ የቅድሚያ ክፍያ 20 በመቶ እና የሊዝ ክፍያ ማጠናቀቂያ 15 በመቶ ነጥብ ይኖራቸዋል።

ተጨማሪ መረጃ ፦

🔵 አዲሱ አዋጅ የሊዝ መነሻ ዋጋ የሚከለስበትን ጊዜ ከ2 ዓመት ወደ 3 ዓመት ከፍ አድርጎታል።

NB. " የሊዝ መነሻ ዋጋ " ማለት ዋና ዋና የመሰረተ-ልማት አውታሮች የመዘርጊያ ወጪን፣ ነባር ግንባታዎችና ንብረቶችን ለማንሳት የሚያስፈልገውን ወጪና ለልማት ተነሺዎች የሚከፈል ካሳአን እና ሌሎች አግባብነት ያላቸውን መስፈርቶች ታሳቢ ያደረገ የመሬት ዝቅተኛ ዋጋ ነው።

🔵 ረቂቁ የመሸጋገሪያ ድንጋጌም ያያዘ ሲሆን አዋጁ ከመውጣቱ በፊት አግባብ ላለው አካል ለቀረቡ የከተማ መሬት ጥያቄዎች የሚሆን አንቀጽ አስቀምጧል። እነዚህ ጥያቄዎች አዋጁ ከጸናበት ቀን ጀምሮ እስከ 6 ወራት ድረስ፤ በነባሩ አዋጅ እና አዋጁን መሰረት አድርገው በወጡ ደንብ እና መመሪያዎች ውሳኔ የሚያገኙ እንደሚሆን ገልጿል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የ ' ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ' ድረገጽ ነው።

ፎቶ ፦ ፋይል

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

28 Oct, 17:22


#ዶክተርነቢያትተስፋዬ 👏 #ኢትዮጵያ

ከስፓይና ቢፊዳ የጤና እከል ጋር የተወለዱት ግለሰብ በማሌንዢያ የስፓይና ቢፊዳ ዓለም አቀፍ ኮንግረንስ የሕይወት ዘመን ተሸላሚ ሆኑ።

ከ30 ዓመታት በፊት ከህመሙ ጋር የተወለዱት ዶ/ር ነቢያት ተስፋዬ ፣ በማሊዥያ የስፓይና ቢፊዳ ዓለም አቀፍ ኮንግረስ የሕይወት ዘመን ተሸላሚ መሆናቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

የሕይወት ዘመን ተሸላሚ የሆኑት፣ ያሳለፉትን የሕይወት ውጣ ውረድ ሌሎች ልጆች እንዳያልፉ በሕይወት ልምዳቸውና በሙያቸው ኢትዮጵያውያንን ለማገልገል በሚያደርጉት ጥረት ነው።

ለኢትዮጵያውያን የሚሰጡትን አግልግሎት አድማስ ለማስፋት “ አለያንስ ፎር በርዝ ዲፌክት ” የተሰኘ በስማቸው ሀገር በቀል ግብረሰናይ ድርጅት በመመስረት አገልግሎት መስጠት እንደጀመሩም ተናግረዋል።

ድርጅታቸው ከሀገር ውስጥና ውጭ ካሉ ድርጅቶች ጋር በመተባበር በስፓይና ቢፊዳ እና ተያያዥ የጤና ችግር ውስጥ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የተሟላ ድጋፍ ለማድረግ ሽልማታቸውን ከተቀበሉ በኋላ ቃል ገብተዋል።

በዓለም አቀፍ ደረጃ ወደ ግማሽ ሚሊዮን የሚጠጉ ሕፃናት በዓመት ከስፓይና ቢፊዳና ተያያዥ የጤና እክሎች ጋር አብረው የሚወለዱ ሲሆን፣ በኢትዮጵያም በርካታ ሕፃናት ከዚህ ችግር ጋር አብረው ከሚወለድባቸው ሀገሮች ግንባር ቀደም መሆኗን አስረድተዋል።

በመሆኑም ከጤና ሚንስቴር ፣ ከሆስፒታሎችና ከሌሎች አጋሮች ጋር በመተባበር በዚህ ችግር የተጠቁ የህብረተሰብ ክፍሎች የክትትልና የማገገም አገልግሎት እንዲያገኙ በትጋት እየሰሩ መሆናቸው ተገልጿል።

የተሸላሚው የሕይወት ጉዞ ምን ይመስላል ?

ከ30 ዓመታት በፊት ከዚህ የጤና ችግር ጋር ተወልደዋል። ከዚህ ችግር ጋር አብረው በመወለዳቸው በሕይወታቸው ውስጥ ብዙ ውጣውረዶች አሳልፈዋል።

የተለያዩ ቀዶ ጥገና ሕክምናዎችንም አድርገዋል።

በልጅነት ጊዜያቸው በዚሁ በሽታ ሳቢያ ትምህርታቸውን ቤት ተቀምጠው እስከመከታተል ተገደዋል። በተለያዩ የጤና ችግሮች ውስጥም አልፈዋል።

እነዚህን ሁሉ ችግሮች በትጋትና በጥንካሬ ከቤተሰቦቼ ጋር በመሆን አልፈው የህክምና ትምህርት መማር ችለዋል።

ለአምስት አመታት የህክምና ትምህርታቸውን ተከታትለው ከጨረኩበት ማግስት ጀምረው እንደሳቸው ሁሉ ከዚህ የጤና ችግር ጋር ለሚወለዱ ሕፃናት የተለያዩ ድጋፎችና የህክምና አገልግሎቶች እንዲያገኙ በማድረግ በሺዎች ለሚቆጠሩ ቤተሰቦች ተስፋ ለመሆን በቅተዋል።

ልጆች ከዚህ ከባድ የጤና ችግር ጋር አብረው እንዳይወለዱና መከላከል እንዲቻል ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ፎሊክ አሲድ በምግብ እንዲበለፅግ የማስተማርና የማስተዋውቅ ሥራ እየሰሩ ይገኛሉ።

ለሁለት አመታት Reachanother foundation በሚባል ግብረሰናይ ድርጅት ውስጥ የአገልግሎት ዳይሬክተር በመሆን በአገራችን በተለያዩ ክልሎች በሚገኙ 8 ሆስፒታሎች ሕፃናት ጥራት ያለው የቀዶ ሕክምና አገልግሎት  እንዲያገኙ ባለሙያዎች ማስልጠን እና ግብቶችን የሟሟላት ሥራ በመስራት ላይም ይገኛሉ።

ስለ ስፓይና ቢፊዳ ይወቁ ፦ https://t.me/tikvahethiopia/74429?single

#ThikvahEthiopiaFamilyAA

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

28 Oct, 17:12


#EthiopianInstitutionoftheOmbudsman

የኢትዮጵያ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ስለ 1997 ተመዝጋቢዎች ምን አለ ?

" ለ20 ዓመታት ያህል ' ቤት ይደርሰናል ' ብለው እየጠበቁ ቢሆንም መንግሥት ምላሽ አልሰጠንም ያሉ ቢያንስ 67 ሰዎችን አቤቱታ ተቀለን እየመረመርን ነው።

' በ1997 ተመዝግበን ቤት ሳይደርሰን ለሌሎች ተሰጥቷል ' ፤ በሚል ተደራጅተው ጠይቀዋል፣ እኛም ጥያቄ አቅርበናል፡፡ ነገር ግን የከተማ አስተዳደሩ እስካሁን መልስ አልሰጠንም።

መልስ የማይሰጠን ከሆነ ለረዥም ጊዜ ጠብቀው ምላሽ ያልተሰጣቸውን ሰዎች አቤቱታ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በማቅረብ የመጨረሻ ዕልባት እንዲያገኝ እናደርጋለን። "

ይህ ቃል ከሪፖርተር ጋዜጣ የተወሰደ ነው።

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

28 Oct, 16:36


#Update

ከ1997 የጋራ መኖሪያ ቤት ተመዝጋቢዎች ጉዳይ ጋር በተያያዘ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ከደቂቃዎች በፊት ማብራሪያ ሰጥቷል።

ቢሮው እየተሰራጨ ያለው መረጃ ከአውድ ውጪ በተተረጎመ መንገድ እንደሆነ ጠቁሟል።

" የ1997 የጋራ መኖርያ ቤት ተመዝጋቢዎችን በተመለከተ ሰሞኑን በተለያዩ ሚዲያዎች እየተሰራጨ ያለው የተሳሳተ መረጃ ትክክል ባልሆነ መልኩ  ከአውድ ውጪ ተተርጉሞ የቀረበ ነው " ብሏል።

ቢሮው በሰጠው ማብራሪያ ምን አለ ?

" ከተማ አስተዳደሩ የጋራ መኖሪያ እና ንግድ ቤቶች ለማስተላለፍ ባወጣው መመሪያ ቁጥር 3/2011 መሰረት ክፍል 3 አንቀፅ 13 ንኡስ አንቀፅ 1 እና 2 መሰረት ብቁ እና ንቁ ማለትም ' የቤት ፈላጊዎች በገቡት ግዴታ መሰረት የቁጠባ መጠን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በትክክል ተቀማጭ ማድረጋቸውን ከእጣ በፊት ያረጋግጣል ' ይላል።

ስለሆነም የ1997 ተመዝጋቢዎች በወቅቱ በመረጃ ቋት ውስጥ ንቁ እና ብቁ  የነበሩ ተመዝጋቢዎችን ከተማ አስተዳደሩ ሙሉ በሙሉ አስተናግዶ ያጠናቀቀ ሲሆን ነገር ግን በወቅቱ ብቁ ያልነበሩትን የ1997 ተመዝጋቢዎች እና ሌሎች የ2005 እጣ ያልደረሳቸው የቤት ፈላጊዎች እየተተገበሩ ባሉ የተለያዩ የቤት ልማት አማራጮች እያስተናገደ ይገኛል፡፡

ስለሆነም በወቅቱ ብቁ እና ንቁ  ያልነበሩ የ1997 ተመዝጋቢዎች ከየትኛውም የቤት ልማት መርሃ ግብር ውጪ እንደተደረጉ ተደርጎ የተሰራጨው የሀሰት መረጃ ተገቢ እንዳልሆነ ህብረተሰቡ እንዲገነዘብ እና ይህንን ሀሰተኛ መረጃ የሚያሰራጩትን ከተማ አስተዳደሩ በህግ የሚጠይቅ ይሆናል።

ከተማ አስተዳደሩ ተመዝግበው የሚጠባበቁትን ሆነ ሌሎች የከተማችዋን የቤት ፈላጊዎች ቤት ተደራሽ ለማድረግ የተለያዩ አዳዲስ የቤት ልማት አማራጮችን በመቀየስ እየተገበረ ይገኛል " ብሏል።

NB. ቢሮው ስለ 1997 ተመዝጋቢዎች የትኛው ሚዲያ ከአውድ ውጭ የተተረጎመ ሀሰተኛ መረጃ እንዳሰራጨ በግልጽ ያለው ነገር የለም። ነገር ግን መረጃውን የሚያሰራጩትን በህግ እጠይቃለሁ የሚል ማስጠንቀቂያ አስተላልፏል።

#AddisAbabaHousingDevelopmentandAdministrationBureau

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

28 Oct, 16:24


ፎቶ ፦ በድሬደዋ እና ሱማሌ ክልል ሲቲ ዞን መካከል አሁን በተከሰተ የሰደድ እሳት ምክንያት ለግዜው የባቡር እንቅስቃሴ መቆሙን ኢንጂነር ታከለ ኡማ አሳውቀዋል።

" እሳቱን ለመቆጣጠር እና አገልግሎቱን ለማስጀመር የድሬደዋ የእሳት አደጋ እና የሽንሌ ዞን ሀላፊዎች ከጣቢያው ሰራተኞች ጋር በመሆን ባደረጉት ርብርብ እሳቱን ማጥፋት ተችሏል " ሲሉ ገልጸዋል።

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

28 Oct, 16:08


#የ97ተመዝጋቢዎች

" ምላሽ ካልተሰጠበት በ15 ቀናት ውስጥ ለሕዝብ ተ/ም/ቤት እናቀርባለን " - የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም

የጋራ መኖሪያ (ኮንዶሚኒየም) ቤት ለማግኝት ተመዝግበው ገንዘብ በባንክ ሲቆጥቡ የነበሩና እስካሁን ቤቱን ያላገኙ የ1997 ዓ.ም. ተመዝጋቢዎች አቤቱታ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምላሽ ካልሰጠበት፣ በ15 ቀናት ውስጥ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚያቀርበው የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም አስታወቀ፡፡

ተቋሙ ፤ ለ20 ዓመታት ያህል " ቤት ይደርሰናል " ብለው እየጠበቁ ቢሆንም መንግሥት ምላሽ አልሰጠንም ያሉ ቢያንስ 67 ሰዎችን አቤቱታ ተቀብሎ እየመረመረ መሆኑን ጠቁሟል።

አቤቱታውን ተከትሎም የከተማ አስተዳደሩን ማብራሪያ ጠይቋል።

ምላሽ ካልመጣ ተቋሙ የሚወስደው ዕርምጃ እንደሚኖ ገልጿል።

" በ1997 ዓ.ም. ተመዝግበን ቤት ሳይደርሰን ለሌሎች ተሰጥቷል ፤ በሚል ተደራጅተው ጠይቀዋል፣ እኛም ጥያቄ አቅርበናል፡፡ ነገር ግን የከተማ አስተዳደሩ እስካሁን መልስ አልሰጠንም " ብሏል።

የአዲስ አበባ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በቅርቡ በነበረ የውይይት መድረክ ፤ ከዚህ በፊት በ2015 ዓ/ም በተላለፉት ቤቶች የ1997 ዓ/ም ቆጣቢዎች ሁሉም ዕጣ እንዲወጣላቸው መደረጉንና ለተመዘገቡት ሁሉ ቤት ተሰጥቶ መጠናቀቁን ገልጸው ነበር፡፡

ይሁን እንጂ የሕዝብ ዋና ዕንባ ጠባቂ ተቋም በዚህ ሁኔታ ከከተማ አስተዳደሩ የደረሰው ምላሽ እንደሌለ አመልክቷል።

ለረዥም ጊዜ ጠብቀው ምላሽ ያልተሰጣቸውን ሰዎች አቤቱታ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በማቅረብ የመጨረሻ ዕልባት እንዲያገኝ ይደረጋልም ብሏል።

በ1997 ዓ.ም. የቤት ምዝገባ በርካቶች ተመዝግበው ለ20 ዓመታት ሲቆጥቡ መቆየታቸውን የገለጸው ተቋሙ ፤ " መንግሥት የተሠሩትን ቤቶችን ለአርሶ አደር ልጆች ፣ ለፖለቲካ ሹመኞች እና ለተለያዩ ግለሰቦች እየሰጠ ነው " በማለት ቅሬታ ሲያቀርቡ ነበር ብሏል።

ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባና በሸገር ከተማ ቤታቸው የፈረሰባቸው ነዋሪዎች ባቀረቡት አቤቱታ ካሳና ተለዋጭ ቦታ እንዲሰጥ በተደጋጋሚ ጥያቄ ሲቀርብ እንደነበር መረጃ የደረሰው ዕንባ ጠባቂ  ተቋም፣ አሁን በመሀል አዲስ አበባ ከሚከናወነው የኮሪደር ልማት ጋር በተገናኘ የደረሰው የሕዝብ አቤቱታ እንደሌለ አመልክቷል።

በአሁኑ ወቅት ወደ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም በብዛት እየቀረቡ ያሉ አቤቱታዎች ፦
° የሥራ ስንብት፣
° የመሬት አገልግሎት፣
° የጡረታ መብት
° የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን የተመለከቱ መሆናቸውን አመልክቷል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሪፖርተር ጋዜጣ ነው።

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

28 Oct, 16:02


🔈 #የነዋሪዎችድምጽ

" የከንቲባዋ ቃል አሳዝኖናል " - የ97 ተመዝጋቢዎች

" የ1997 ኮንዶሚኒየም ተመዝጋቢዎች 20 አመት ሙሉ የጠበቅነዉን ተስፋ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ' 97 ሰጥተን ጨርሰናል ' ማለታቸዉ በጣም አሳዝኖናል " ሲሉ ገልጸዋል።

" ቁጠባችንን በአግባቡ እየቆጠብን የነበርን በሺዎች የምንቆጠር ዜጎች አለን " ብለዋል።

" እኛም ዜጎች ነን በኪራይ ቤት እድሜችን አለቀ " ሲሉ አክለዋል።

ነዋሪዎቹ ፥ " ለሕዝብ ዕንባ ጠበቂ ተቋም ደብዳቤ አስገብተናል አዲስ አበባ ቤቶች ኤጀንሲ ግን መልስ አልሰጣቸውም " ሲሉ አስታውሰዋል።

" ከዚህ ባለፈ የጠቅላይ ሚኒስቴር ቢሮም መፍትሄ እንዲፈልግልን ብለን ነበር ጋር ግን ምላሽ ተነፍጎናል " ብለዋል።

" ወዴት እንደምንሄድ ጨንቆናል ፍትህ ተጓሎብናል ፤ አሁን ካለው የኑሮ ጫና አንጻር የቤት ኪራይ ትልቁ ፈተና ነው እባካችሁ መፍትሄ ፈልጉልን " ሲሉ ድምጻቸውን አሰምተዋል።

#ThikvahEthiopiaFamilyAA

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

28 Oct, 16:01


#EHRC

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ሪፖርት ይፋ አድርጓል።

በዚህም ሪፖርቱ ለሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች የሰብአዊ ድጋፍ በአግባቡ ሊቀርብ እንዲሁም ደግሞ የሰብአዊ መብቶች መርሖችን ፣ የተፈናቃዮችን ክብር ፣ ደኅንነት እና ፍላጎት ያከበረ ዘላቂ መፍትሔ ሊመቻች እንደሚገባ አሳስቧል።

የኢሰመኮ ተጠባባቂ ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ ምን አሉ ?

" ኢትዮጵያ ውስጥ መፈናቀል በአብዛኛው እየተከሰተ ያለው በግጭቶች ምክንያት በመሆኑ ግጭቶችን በአፋጣኝ ሁኔታ በሰላማዊ መንገድ መፍታትና እንዳይባባሱ አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ፤ መፈናቀልን ለመከላከል እና በዘላቂነት መፍትሔ ለመስጠት ወሳኝ በመሆናቸው ትኩረት ሰጥቶ መተግበር ያስፈልጋል።

በተፈጥሮ አደጋም የሚከሰት መፈናቀል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተስፋፋ በመምጣቱ ለቅድመ አደጋ መከላከል እና ለአደጋ ጊዜ ምላሽ አሰጣጥ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል።

የሰብአዊ መብቶች መርሖችን መሠረት ያደረገ ዘላቂ መፍትሔ ለመስጠት እንዲሁም የሽግግር ፍትሕ እና የሀገራዊ ምክክር ሂደቶች የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችን መብቶችና ተሳትፎ በሚያረጋገጥ ሁኔታ እንዲተገበሩ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል። "

(ሙሉ ሪፖርቱ ከላይ ተያይዟል)

@thikvahethiopia

THIKVAH-ETHIOPIA

28 Oct, 16:01


#EHRC

ሰሞኑን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የሴቶች እና የሕፃናት ሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ሪፖርት ይፋ አድርጎ ነበር።

ይህ ሪፖርት ከሰኔ 2015 ዓ/ም እስከ ሰኔ 2016 ዓ/ም ያለውን ጊዜ የሚሸፍን ነው።

በዚሁ የዓመታዊ ሪፖርት ፥ በግጭት ውስጥ ባሉ እና በትጥቅ ግጭት ውስጥ በቆዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች እና በታጣቂ ቡድኖች በተለያየ ጊዜ በሚፈጸሙ ጥቃቶች ሴቶችና ሕፃናትን ፦

🔴 ለሞት ፣ ለአካል ጉዳት እንዲሁም ለወሲባዊ እና ጾታዊ ጥቃቶች መጋለጣቸው፤

🔴 በግጭት ዐውድ ውስጥ በቆዩት፦
° አፋር፣
° ቤኒሻንጉል ጉሙዝ
° ትግራይ ክልሎች በቂ መልሶ የማቋቋም ሥራ ባለመከናወኑ በሕክምና ተቋማት የውሃና ኤሌክትሪክ ፣ የሕክምና ቁሳቁስ ፣ የአምቡላንስ ፣ የመድኃኒት ፣ የክትባትና የምግብ አቅርቦት ውስንነት ምክንያት እናቶችና ጨቅላ ሕፃናት በቅድመ ወሊድ ፣ በወሊድ ፣ ድኅረ ወሊድ ፣ በድንገተኛ ወሊድ ወቅት ሊያገኙት የሚገባቸውን መሠረታዊ አገልግሎቶች እያገኙ ባለመሆኑ የእናቶችና ሕፃናት ሞት እየጨመረ መምጣቱ፣

🔴 በሀገሪቱ በቀጠሉ ግጭቶች እና በተፈጠረው የደኅንነት ሥጋት በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ በሺህዎች የሚቆጠሩ ትምህርት ቤቶች መዘጋታቸው በአሳሳቢነት ተጠቅሰዋል፡፡

(ሙሉ ሪፖርቱ ከላይ ተያይዟል)

@thikvahethiopia