"The True Paradise is the Paradise We Lost" ይላል ፕሩስት። ዉብ አለም ያጣነዉ ብቻ ነዉ እንደማለት።
ሁሌም ሰዎች ይሸጡልን የሚፈልጉት የምኞት አለም አለ። ድሮ ድሮ "የላብ አደሩ አብዮት የሚወልደዉ እኩልነት" ነበር። " ከበርቴዉ ፣ ፊዉዳሉ" ጠላት ሆኖ መንገድ የዘጋበት። ታገሉ ፣ ገደሉ — አላዋጣም። ባህል ፣ ሃገር ፣ ዘር ፣ ሰፈር ቀያይረዉ በአለም ባለ እልፍ ቦታ ሞከሩት። ሞት እንጂ የመጣ ዉብ አለም አጡ።
ዛሬም ሌላ ዉብ አለም ይሸጣሉ። በምኞት ብቻ ያለ። የትናንት አለማቸዉ ልጅ። የዛሬዉ ጠላት በትናንቱ ጠላት እንድንረታ መሰረት ነበር አሉ። ሃይማኖት ፣ ወግ ማጥበቅ ፣ ግብታዊ ለዉጥ እምቢተኝነት ፣ አባታዊ ስርአት ፥ ትዳር ፣ እናትነት ወዘተ።
ሁሉም ነገር የማህበራሰብ ሽመና ዉጤት ( social constract ) ነዉ። አስተዳደግ እንጂ ተፈጥሮ ምን ይረባን"ን ሰበኩ።
ያ እንዲሆን " ያደግንበት መናድ አለበት። እዉነት ይትብሃል የለም። እዉነትም ፣ እዉቀትም ፣ ማንነትም አንጻራዊ ነዉ። ባሻቹ ናኙ ። ባፈረስነዉ ላይ ሁሉ እኩል የሚከበርበት ፣ እኩል ሃብት ያለበት ፣ ባሪያ መሳ የሚቀመጥበት የምናብ ሃገር እንገነባለን። " ብለዉ ተመኙ።
አይሆንም!
"The object of desire is not something that is there; it is something that is missing" ይላል Jacques Lacan.
ምኞት የማይሞላ መሻት ነዉ ሊለን።
ለግል የምናልመዉ ይሁን ፥ ማህበረስብ እንዲሆን የምንሻዉ ፤ ሁላችንም በልባችን ገነት አለን — ቢሆንልን የምንለዉ።እንዳለመታደል ጊዜ ፣ ታሪክም እንዳሳየን ብቸኛዉ ደስታ ጉጉት ብቻ ነዉ። ስናገኘዉ ፣ ስንጨብጠዉ ሁሉ ቀሊል ይሆናል። ደስታዉን ፥ ክብሩን ያጣል።
Object cause desire የሚለው ላኮን።
ሰዉ መሻቱን የሚሻ ፍጥረት ነዉ። ማግኘትን አይደለም።
ምን ወጣትነት ለተበዳይ መራራት ፥ ለአመጽ ቋፍ ላይ መሆን ቢሆን ከታሪክ ግን እናያለን። ግልብ ለዉጥ ያለንንም ያሳጣናል። ዉብ የምናብ አለም በእጃችን ላይ ያለችዉን ለዘመናት የገራናትን የረጋች አለምን ይነጥቀናል።
" Evil is precisely when you think you are fighting for the absolute good." - Hagel
@samuel_dereje
ሁሌም ሰዎች ይሸጡልን የሚፈልጉት የምኞት አለም አለ። ድሮ ድሮ "የላብ አደሩ አብዮት የሚወልደዉ እኩልነት" ነበር። " ከበርቴዉ ፣ ፊዉዳሉ" ጠላት ሆኖ መንገድ የዘጋበት። ታገሉ ፣ ገደሉ — አላዋጣም። ባህል ፣ ሃገር ፣ ዘር ፣ ሰፈር ቀያይረዉ በአለም ባለ እልፍ ቦታ ሞከሩት። ሞት እንጂ የመጣ ዉብ አለም አጡ።
ዛሬም ሌላ ዉብ አለም ይሸጣሉ። በምኞት ብቻ ያለ። የትናንት አለማቸዉ ልጅ። የዛሬዉ ጠላት በትናንቱ ጠላት እንድንረታ መሰረት ነበር አሉ። ሃይማኖት ፣ ወግ ማጥበቅ ፣ ግብታዊ ለዉጥ እምቢተኝነት ፣ አባታዊ ስርአት ፥ ትዳር ፣ እናትነት ወዘተ።
ሁሉም ነገር የማህበራሰብ ሽመና ዉጤት ( social constract ) ነዉ። አስተዳደግ እንጂ ተፈጥሮ ምን ይረባን"ን ሰበኩ።
ያ እንዲሆን " ያደግንበት መናድ አለበት። እዉነት ይትብሃል የለም። እዉነትም ፣ እዉቀትም ፣ ማንነትም አንጻራዊ ነዉ። ባሻቹ ናኙ ። ባፈረስነዉ ላይ ሁሉ እኩል የሚከበርበት ፣ እኩል ሃብት ያለበት ፣ ባሪያ መሳ የሚቀመጥበት የምናብ ሃገር እንገነባለን። " ብለዉ ተመኙ።
አይሆንም!
"The object of desire is not something that is there; it is something that is missing" ይላል Jacques Lacan.
ምኞት የማይሞላ መሻት ነዉ ሊለን።
ለግል የምናልመዉ ይሁን ፥ ማህበረስብ እንዲሆን የምንሻዉ ፤ ሁላችንም በልባችን ገነት አለን — ቢሆንልን የምንለዉ።እንዳለመታደል ጊዜ ፣ ታሪክም እንዳሳየን ብቸኛዉ ደስታ ጉጉት ብቻ ነዉ። ስናገኘዉ ፣ ስንጨብጠዉ ሁሉ ቀሊል ይሆናል። ደስታዉን ፥ ክብሩን ያጣል።
Object cause desire የሚለው ላኮን።
ሰዉ መሻቱን የሚሻ ፍጥረት ነዉ። ማግኘትን አይደለም።
ምን ወጣትነት ለተበዳይ መራራት ፥ ለአመጽ ቋፍ ላይ መሆን ቢሆን ከታሪክ ግን እናያለን። ግልብ ለዉጥ ያለንንም ያሳጣናል። ዉብ የምናብ አለም በእጃችን ላይ ያለችዉን ለዘመናት የገራናትን የረጋች አለምን ይነጥቀናል።
" Evil is precisely when you think you are fighting for the absolute good." - Hagel
@samuel_dereje