ሲገባኝ በጉድጓድ የተጣለ ሁሉ በክብር ዙፋን አይሾምም። ለካ ገድለ ዮሴፍ የጥቂቶች እድል ነበር። በየተጣለበት ጉድጓድ ጊንጥ የነደፈዉ ፥ የሌት አዉሬ የገደለዉ እልፍ አለ ።
በጎሊያድ የተቀሉ ብዙ ዳዊቶች ተረስተዋል። አንበሳ ስለበላቸዉ እልፍ ዳንኤሎች ያላፈሰስነዉ እንባ አለ። ተራራዉ ስለለገመበት ስሞኦን ማን ዘመረ?
ለስኬት ነዉ የተፈጠርከዉ ያሉህን መካሪዎች ቂል በልልኝ።
አትሞኝ! ለሞከረ ፥ ለጣረ ሁሉ ይብራል ይሉት ተረት ተረት ነዉ። ከጣረዉ ፥ ከሞከረዉ ለቀናለት ለጥቂቱ "ምንአልባት" ይበራል። ግን ላልጣረ ፥ ላልሞከረ በርግጠኝነት ይጨልማል።
@samuel_dereje