~
1- የግብረ ስጋ ግንኙነት መፈፀም፣
2- የዘር ፈሳሽን ሆን ብሎ ማውጣት፣
3- መብላትና መጠጣት፣
4- በአፍ መድሃኒት መዋጥ፣
5- ሲጋራና መሰል ነገሮችን ማጨስ፣
6- የወር አበባ ወይም የወሊድ ደም መምጣት፣
7- ፆምን የማቋረጥ ቁርጠኛ ውሳኔ ላይ መድረስ (ባይበላም ባይጠጣም)
እነዚህ ነገሮችን ፆምን የሚያበላሹት የሚያፈርሱ እንደሆነ እያወቀ፣ አስታውሶ እና በምርጫው በቀኑ ክፍለ ጊዜ ከፈፀማቸው ነው።
* የሚያፈርሱ መሆናቸውን ሳያውቅ ቢፈፅም ፆሙ አይበላሽም። ልክ እንደዚሁ ያልነጋ መስሎት ወይም ፀሐይ የገባ መስሎት ቢፈፅምም ፆሙ አይበላሻም።
* የሚያፈርሱ መሆናቸውን እያወቀ ነገር ግን ረስቶ ቢፈፅም ፆሙ አይበላሽም።
* የሚያፈርሱ መሆናቸውን እየወቀ ግን ተገዶ ቢፈፅም ፆሙ አይበላሽም።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor