ራስህን መለወጥ (@rasehnmelewet33) Kanalının Son Gönderileri

ራስህን መለወጥ Telegram Gönderileri

ራስህን መለወጥ
"እንኳን ደህና መጣችሁ"Welcome!
ለማንበብ ራሳችንን እናስለምድ!
፨ተራ ነገር በመስራት የሚባክነውን ጊዜያችንን በንባብ ላይ ስናውለው ከራሳችን አልፈን ለብዙዎች የመለወጥ ምክንያት እንሆናለን፡የንባብ ባህላችንን እናዳብር! ባለንበት ራሳችንን በእውቀት እንገንባ!
፨በዚህ ቻናል የተለያዩ፣ጠቃሚ ሀሳቦች፣አነቃቂ ሀሳቦች ይቀርባል ይቀላቀሉ: ማወቅ መልካም ነዉ ያወቁትን ማሳወቅ ደግሞ ፍፁም በጎነት ነው።
2,078 Abone
125 Fotoğraf
72 Video
Son Güncelleme 15.03.2025 10:51

ራስህን መለወጥ tarafından Telegram'da paylaşılan en son içerikler

ራስህን መለወጥ

05 Mar, 13:16

1,212

ማመስገን ትልቅ ፀሎት እንደሆነና ችግር እንደሚያስወግድ ስንቶቻችን እናውቃለን?

አንድ ብዙ ሃብት ያለው ወዳጃችሁ ካለው ሃብት ሳይሰስት ለችግራችሁ የሚሆን በቂ ገንዘብ ሰጣችሁ፤ከዛ አንድም ቀን ውለታህ አለብኝ አመስግንሃለሁ ሳትሉት በሆነ ቀን ተጨማሪ ብዙ ችግራችሁን እየዘረዘራችሁ ብድር ወይም ስጦታ ስጠኝ ብላችሁ ልጠይቁት ብትሄዱ ምን የሚላችሁ ይመስላችኋል?! አያችሁ ፈጣሪንም መጀመሪያ ስለሰጠን ማመስገን ስንጀምር የጎደለንን መሙላ ቀላሉ ነው፡፡እግዚአብሔር ሆይእንዲህ አድርግልኝ፣እንዲህ ይሁንልኝ አትበሉ።አድርግልኝ ሳይሆን መጀመሪያ ስለተደረገልን ተመስገን እንበል። ሁሌም ተመስገን፣ስላደረክልኝ ተመስገን፣ስላላደረክልኝም ተመስገን፣ጤና ስለሰጠኸኝ፣እናት አባት ፣እህት ወንድም፣ጓደኛ፣ፍቅረኛ ፣ልጅ ፣ጎረቢት ስለሰጠኸኝ ሁሉ ተመስገን እንበል።

እስኪ እናስብ ፈጣሪ ብዙ ሚሊየን ግዙፍ ፍብሪካ መክፈት የሚያስችል አዕምሮ ሰጥቶን ለትንሿ ትርፍ ፍላጎታችን ከፊቱ ስንቆም እንደት ያፍርብን?፣አለም ላይ ብንዞር በፈለግነው የሃብት መጠን የማይለካ እና የማናገኝ ሙሉ ጤና ሰጥቶን ትርፍ ለሆነችው ትንሽየ ገንዘብ ፊቱ ስንበረከክ እንደት ያፍርብን?! ፣አለም ላይ የታወቁ ዳኞች (Lawyers) ሊያስገኙልን የማይችሉት ፍትህ የሚሰጥ ፍትሃዊ ዳኛ ህሌና በውስጣችን አስቀምጦ ፈጥሮን የውሸት ፍትህን ፍለጋ ፍርድ ቤት ስንቆም ፈጣሪ እንደት ያፍርብን? ፈጣሪ ለእኛ ለሰው ልጆች ያላደረገልን አስፈላጊ ነገር ምን አለ?! አንደበት ኖሮን መናገር ባንችል እስኪ አስቡት፣አይን ሳይኖረን አለምን ማየት ባንችል አስቡት?

፣እግራችን መራመድ ባይችል አስቡት፣ጆሯችን መስማት ቢያቆም አስቡት፣አዕምሯችን ማሰብ እና ከተለያዩ የሰውነት ክፍሎች መልዕክት መቀበል እና ትዕዛዝ መስጠት ባይችል አስቡት፣ሰገራና ሽንታችንን መቆጣጠር ባንችል እስኪ አስቡት፣ ደማችን መዘዋወር ቢያቆም አስቡት፣ከሰውነት ክፍሎቻችን አንዷ ብትጎድል እስኪ አስቡት ?! አያችሁ ሁልጊዜም ወደ ውጭማየት ኪሳራ እንጅ ትርፍ የለም የሚባለው ለዚህ ነው፡፡ ያለንን ስናውቅ የጎደለን ምንም የለም፡፡

ምስጋና ከአንደበታችን አይጥፋ።ስለፍጥረት ሁሉ እናመስግን ዝንቦች ሳይቀር እኛን ለማገልገል እንደተፈጠሩ እንወቅ፡፡እውነት ፈጣሪ ሳንጠይቅ በራሱ አምሳል ፈጥሮናልና ያለንን መንፈሳዊ ሃይ፣ስጋዊ ሃይል፣አዕምሯዊ ሃይል ብናስተውል ህይወታችን ከመብላት ፣ከመጠጣት፣ከመልበስ ባለፈ ብዙ ተአምር መስራት ነበረብን።ያለንን ሳንጠቀም ተጨማሪ ስጠኝ እያልን ብናለቅስ ፈጣሪ ለመስጠት እንደት ይቸገር ይሆን?! ምግብ መስሪያውን ሰጥቶን ምግብ ስጠኝ ብንል፣ብዙ አሳ ማጥመጃ ተሰጥቶት አንድት አሳ ስጡኝ ብሎ እንደሚለምን ሰው ነው የሚሆነው ልመናችን፡፡ስለዚህ እናስተውል።አንድም የጎደለብን የለም፡፡ያለንን ብናመሰግን ለጎደለን ገና ሳንጠይቅ በልባችን ስናስብ ሁሉ ይሆንልናል።ህይወታችሁ፣ቤታችሁ፣ ጎጇችሁ ፍፁም ሰላም እና በበረከት የተሞላ ይሆናል። ሲጎድልብን እግዚአብሔር ተመስገን ስላልን ብቻ ይሞላልናል።


ሌሊቱን ስላነጋህ ተመስገን ፣ፀሐይዋ ስለወጣች ተመስገን ፣አይናችንን ስለገለጥን ተመስገን፣ምድርን ስላፀናህ ተመስገን፣ሰማዩን ስላፀናህ ተመስገን፣የምንበላውን፣የምንለብሰውን ስለሰጠህ ተመስገን፣ስለፍጥረትህ ተመስገን፣ስለቸርነትህ ተመስገን፣ስለይቅር ባይነትህ ተመስገን፣ልጆቼን ስለምትጠብቅልኝ ተመስገን፣ሚስቴን ከክፉ ስለምጠብቅልኝ ተመስገን፣ባሌን ስለምታግዝልኝ ተመስገን፣ጎጆዬን ስለባረክልኝ ተመስገን፣መኖር ስለፈቀድክልን ተመስገን እንበል!

በነገራችሁ ላይ እግዚአብሔር ላደረገልን ነገር ሁሉ የምንከፍለው ተመስገን በማለት ነው፡፡ ምስጋና ለእግዚብሔር ክፍያው ነው፡፡ ስለጎደለን ሳናማርር ስላለን ስለተሰጠን ነገሮች ተመስገን እንበል። የጎደለውን እሱ ይሞላዋል!ዛሬ በህይወት ከአልጋቸው በሙሉ ጤንነት ከሚነሱ ሰዎች ስም ዝርዝር ውስጥ ሆነን ዛሬን ለመኖር ስለተፈቀደልን ብቻ ትልቅ ውለታ አለብንና ተመስገን እንበል ።

#ተመስገን

እግዚአብሔር ማስተዋልን ጥበብን እውቀትን ከፍቅር ጋርይስጠን አሜን _ _እግዚአብሔር ብርሃኔና መድሃኒቴ ነው፡፡

ይህ ድንቅ ትምህርት እስቲ #ሼር እናድርገው ለብዙ ሰዎች እንዲደርስ አንድ ሰው እንኳ ከተጠቀመበት ትልቅ ነገር ነው።

Telegram ተቀላቀሉን
እንማማርበት ቻናሉ👇👇
@rasehnmelewet33
ራስህን መለወጥ

04 Mar, 10:41

616

አሳይ፣ የሚያውቀውን ማንነትህን ገልጠህ አስረዳው። እግዚአብሔር ሁሉን አዋቂ፣ ሁሉን ቻይ፣ ሁሉን ከዋኒ አምላክ ነው። እያንዳንዱ ተግባሩ የኛን ምርጫ ከግምት ያስገባ ነው፤ የትኛውም ምርጫውም የኛን ፍላጎት ያገናዘበ ነው። ዘወትር እያመሰገንከው እንድትኖር፣ ሁሌም ማንነትህን ለእርሱ እንድታስገዛ፣ በየጊዜው ደጁ እንድትጠና ማድረግ አቅቶት አይደለም። ይልቅ ማናችንም ለገዛ ህይወታችን ሃላፊነት መውሰድ ስላለብን ነፃ አድርጎናል፣ በሰጠን ነፃ ፍቃድ በፍላጎታችን ፈልገን እናገኘው ዘንድ መንገዱን ሁሉ ክፍት አድርጎልናል። ፈጣሪ የሌለበት ህይወት ከባዶው ምድረበዳ የሚበልጥ ነው። ምደረበዳ ምንም አያበቅል ይሆናል እግዚአብሔር የሌለበት ህይወት ግን ክፋትና ጭካኔን ያበቅላል፣ ለሃጢአት የተመቸ ይሆናል
፣ እለት እለት መንፈስን እያደኸየ፣ ስሜትን እየሰበረ፣ ውስጥን እያረከሰ ከሰውነት ከብር በታች ያኖራል። ለፈጣሪህ እራስህን አሳይ፣ ወደቤቱ ግባ፣ ከምድረበዳ የባሰውን ህይወትህን ወደ ለምለም ትርፋማ ምድር ቀይረው።

Telegram ተቀላቀሉን
እንማማርበት ቻናሉ👇👇
@rasehnmelewet33
ራስህን መለወጥ

04 Mar, 04:06

953

💡ከታላቁ ፈላስፋ ሶቅራጥስ እንማር

አንድ ሠው መጥቶ ሶቅራጦስን ፡- ‹‹እገሌ ስለተባለው ወዳጅህ የሠማሁት ደስ አይልም›› አለው ፡፡ ሶቅራጦስ ግን ዝም አለ ፡፡
👉 ሠውየውም እንደገና ፡- ‹‹ይገርማል ከእርሱ አይጠበቅም ፤ በጣም ገርሞኛል›› አለው ፡፡
👉 ሶቅራጦስም እንደማይለቀው ስለተረዳ ፡- ‹‹ ስለ ወዳጄ ልትነግረኝ የፈለግከውን ልሠማው የምችለውሶስት ጥያቄዎች አሉኝ ፤ እነርሱን ስትመልስልኝ ብቻ ነው››
አለው ፡፡ ሠውየውም ተስማማ ፡፡

👉 ‹‹የመጀመሪያው ጥያቄዬ የእውነት ጥያቄ ነው ፡፡ ስለወዳጄ የሠማኸው መቶ በመቶ እውነት ነው ወይ?›› አለ ፡፡
👉 ሠውየውም ፡- ‹‹መቶ በመቶ እርግጠኛ መሆን አልችልም››አለው ፡፡
👉 ሶቅራጦስም ፡- ‹‹ልትነግረኝ የፈለግከው እርግጠኛ ያልሆነነገር ነው ።

👉 ሁለተኛው ጥያቄዬ የመልካምነት ነው ፡፡ የምትነግረኝ መልካም ነገር ነው ወይ ?›› አለው ፡፡

👉 ሠውየውም ፡- ‹‹እርሱማ መልካም አይደለም›› አለው ፡፡

👉 ሶቅራጦስም ፡- ‹‹አንደኛ እውነትነቱ ያልተረጋገጠ ፤ ሁለተኛ መልካም ያልሆነ ነገር ልትነግረኝ ፈልገሃል ፡፡ ሶስተኛ ጥያቄ አለኝ ?›› አለው ፡፡

👉ሠውየውም ፡- ‹‹እሺ›› አለ ፡፡
👉 ሶቅራጦስም ፡- ‹‹ለእኔ የሚጠቅመኝ ነገር አለው ወይ ?››አለው ፡፡

👉 ሠውየውም ፡- ‹‹የለም›› ብሎ መለሠ ፡፡
👉 ሶቅራጦስም በመጨረሻ ፡- ‹‹እውነትነቱ ያልተረጋገጠ ፤ መልካም ያልሆነ ፤ ለእኔ የማይጠቅም ነገር አልሠማም›› አለው ይባላል ፡፡

ወዳጆቼ እውነትነቱ ያልተረጋገጠ ፣ መልካም ያልሆነና በሕይወታችን ላይ ጉልህ ሚና የሌለው ነገር ላይ ጊዜ ማጥፋት ትልቅ ብክነት ነው ፡፡ አንዳንድ ሠዎች በማይመለከታቸው ነገር እድሜአቸውን ይገፋሉ ፡፡ በዚህም መልሠው ማግኘት የማይችሉትን ውዱን ጊዜአቸውን መና ሲያደርጉት ማየት አሳዛኝ ነው ፡፡

ታላቁ ፈላስፋ ሶቅራጦስም ይህን እውነት በሚደንቅ መልሱ አሳይቶናል ፡፡ስለሆነም በጎ ዓላማ በሌለው ፣ ሐቅነቱ ባልተረጋገጠና አንዳች ፋይዳ በሌለው እንቶፈንቶ ሳንባዝን ለሚጠቅም ነገር ፣ ለሠናይ ተግባርና ለእውነት እንትጋ !
═══════════❁✿❁ ════════

Telegram ተቀላቀሉን
እንማማርበት ቻናሉ👇👇
@rasehnmelewet33
ራስህን መለወጥ

03 Mar, 10:20

961

በአንድ ወቀት እንስሳቶች በሚኖሩበት ፖርክ ውስጥ አንዲት በግ በሆነ አካባቢ ስታልፍ አንድ አንበሳ በሆነ ኬጂ ተቆልፎበት በጓ እንድታድነው ለመናት። በጓ ግን ጥያቄውን አልተቀበለችውም። አንበሳው  ደጋግሞ ሲለምናትና እንደማይነካት ሲያረጋግጥላት በመጨረሻ እሺ በማለት ቁልፉን  ከፈተችለት።

ነገርግን አንበሳው ያለ ምግብ ብዙ ቀን ስለቆየ እርቦት ነበርና በግዋን ሊበላት ያዛት። በግዋ ግን ፈጥና ቃልኪዳናቸውን አስታወሰችው።  በዚህ ሁኔታ ውስጥ እያሉ ሌሎቹ እንስሳቶች በዚያ ሲያልፉ የሆነውን  መጠየቅ ጀመሩ። ሁለቱም የየራሳቸውን መከራከሪያ ሃሳብ አቀረቡ። ነገርግን ሁሉም እንስሳት በአንበሳው ፊት ሞገስ ለማግኘትና ለመወደድ እንዲሁም አንበሳውን በመፍራት ከአንበሳው በኩል ወገኑ። በመጨረሻም ኤሊ መጣች።ሆኖም እሷም የሆነውን ሁሉ ከሰማች በኋላ ከሌሎቹ በተለየ መልኩ ጥያቄ መጠየቅ ጀመረች።

አንበሳውን በግዋን ሳታድንህ በፊት የት እነደነበር ጠየቀችው? አንበሳውም ታስሮበት ወደነበረው ቦታ አሳያት። ከዚያም ቀጥላ በጉ የነበረበትን ቦታ ጠየቀች። ያንንም አሳያት። ከዚያም በመቀጠል ለአንበሳው እስኪ ምንያህል አስቸጋሪ እንደነበር መጀመሪያ የነበርክበት ቦታ ግባ እና እንይ አለችው። አንበሳውም እንደገባ ወዲያው ኤሊዋ አንበሳው ላይ ቆለፈችበት።

ሌሎቹ እንስሳቶች ተገርመው ኤሊዋ ለምን እነደዚያ እንዳደረገች ጠየቋት? እሷም ምላሺ ሰጠች። ዛሬ በግዋን እንዲበላ ከፈቀድናለት ነገ ደግሞ ሲርበው ከመሃከላችን ማንን እንደሚበላ አናውቅም አለች።

ብዙሃን ናቸው ብለህ ፍትህን አጉድለህ ከግፈኞች ጋር አትወግን።
ዛሬ አንተን በቀጥታ ስለማይነካ ክፋትን ብትደግፍም ነገ የማን ተራ እንደሆ ነ አታውቅም።

Telegram ተቀላቀሉን
እንማማርበት ቻናሉ👇👇
@rasehnmelewet33
ራስህን መለወጥ

02 Mar, 14:22

898

ይች አለም ከዋናው ይልቅ ለኮፒው ክብር ትሰጣለች!
በአንድ ወቅት ታላቁ ኮሜዲያን ቻርሊ ቻፕሊን ፈረንሳይ ውስጥ ሲዘዋወር ቻርሊ ቻፕሊንን(እሱን) የማስመሰል ውድድር እንደተዘጋጀ ይመለከታል።
ይህኔ ቻፕሊን ለምን በዚህ እኔን በማስመሰሉ ውድድር ላይ አልሳተፍም ይልና ስም ቀይሮ ይመዘገባል።
በዚሁም መሰረት ከ12 ተወዳዳሪዎች ጋር ተወዳደረ።
ራሱን በማስመሰሉ ውድድር ስንተኛ እንደወጣ ታውቃላችሁ? በ6 እስመሳዮች ተበልጦ 7ኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል..😄

ከዚያም ቻፕሊን ይህች ዓለም ከዋናዎች ይልቅ ለአስመሳዮች ክብርና ሽልማት እንደምታጎርፍ ተገነዘበ።

Telegram ተቀላቀሉን
እንማማርበት ቻናሉ👇👇
@rasehnmelewet33
ራስህን መለወጥ

02 Mar, 09:33

1,044

ብሩስ ሊ Bruce Lee

"ማወቅ በቂ አይደለም፤ ፈቃደኝነት ብቻውን በቂ አይደለም፤ ማድረግ አለብን"

"አንድ ሰው እራሱን ለመቀበል ድፍረት ካገኘ ስህተቶቹ ይሰረዛሉ"

"የሚጠቅመውን አስተካክል፣ የማይጠቅመውን ተወውና የራስህ የሆነውን ጨምር"

"ለቀላል ሕይወት አትጸልዩ፣ አስቸጋሪ የሆነውን ለመጽናት ብርታት ለማግኘት ጸልዩ"

"ሕይወትን የምትወድ ከሆነ ጊዜ አታባክን ምክንያቱም ሕይወት የተሠራው በጊዜ ነው"

"በችግር መካከል እድል አለ"

"እኔ 10,000 ምቶች የተለማመደውን ሰው አልፈራም ነገር ግን አንድ ምት 10,000 ጊዜ የተለማመደውን ሰው እፈራለሁ"

"ሰነፍ ከጠቢብ መልስ ከሚማረው ይልቅ ጠቢብ ከሞኝ ጥያቄ ይማራል"

"ትልቁ ስህተት እሰራለሁ ብሎ መፍራት ነው"

" እንደ ውሃ ቅርጽ የለሽ  መሆን አለብህ"

"ብዙ ባነበብኩ ቁጥር ባገኘሁት መጠን ምንም እንደማላውቅ የበለጠ እርግጠኛ ነኝ"

"ሕይወት ራሷ አስተማሪህ ናት አንተ የማያቋርጥ ትምህርት ባለበት ሁኔታ ውስጥ ነህ"

"እውነተኛ ህይወት ለሌሎች መኖር ነው"

"ትክክለኛውን ምረጥ ምርጫ አለህ  የአመለካከትህ ጌታ ነህ"

"ስለ አንድ ነገር በማሰብ ብዙ ጊዜ የምታጠፋ ከሆነ በጭራሽ አትጨርሰውም"

"ቡጢ በጠንካራ እጅ መሰንዘር የለበትም ዘና ባለ እጅ መሰንዘር አለበት"

"መሸነፍ የአእምሮ ሁኔታ ነው፣ ​​ሽንፈት እንደ እውነት እስካልተቀበለ ድረስ ማንም አይሸነፍም"

"ፈቃድህን በሌሎች ላይ ማስገደድ አትችልም አንተ ብቻ ተጽዕኖ ማሳደር ትችላለህ"

"ለእኔ የማርሻል አርት አስደናቂው ገጽታ መዋጋት ብቻ ሳይሆን እራስን መግለጽ ነው"

"በተለምዶ የምታስበው ነገር በመጨረሻ ምን እንደምትሆን ይወስናል"

Telegram ተቀላቀሉን
እንማማርበት ቻናሉ👇👇
@rasehnmelewet33
ራስህን መለወጥ

02 Mar, 07:08

795

#አድዋ
አድዋ የጥቁር ህዝቦች ድል የአይበገሬነት ማሳያ።
አድዋ የጥቁር ህዝቦች በደም የተፃፈ ታሪክ።
  ክብር ሞተው ሀገር ላቆዮልን ጀግኖች አባቶቻችን።እንኳን ለ129ኛ  የአድዋ ድል በዓል አደረሳችሁ አደረሰን

Telegram
@rasehnmelewet33
ራስህን መለወጥ

28 Feb, 10:15

1,224

ሌላ ሌላውን ተውት...ስራውም ይገኛል፤ ገንዘቡም ይደርሳል፤ ትዳሩም ይመጣል፤ ትምህርቱም ይታለፋል፤ ቀኑም ይገፋል፤ መከራውም ይፈፀማል፤ልጃችሁም ይወለዳል፤

ፍቅራችሁም ይታደሳል፤ ቤተሰብም ሰላም ይሆናል፤ጭንቃችሁም ይቀላል፤ ለሀገራችሁም ያበቃችኋል!!ብቻ እናንተ ደህና!!...ብቻ እናንተ ጤና!!!

በሀሳባችሁ የሚመላለስ እቅድ ምኞት ፍላጎት የሚጠቅማችሁ እና የተፈቀደላችሁ ከሆነ አንድ ቀን ይሰምራል።

እናንተ ጊዜው የሮጠ ይመስላችኋል እንጂ እግዚአብሔር መች ይረፍድበታል??አይረፍድበትም!!እናንተ ኑሩ እንጂ ገና ብዙ እናያለን።

ብቻ እናንተ ደህና
ብቻ እናንተ ጤና ሁኑ....

መልካም ቀን ..🙏🙏

Telegram ተቀላቀሉን
እንማማርበት ቻናሉ👇👇
@rasehnmelewet33
ራስህን መለወጥ

27 Feb, 04:06

1,655

ልክ እንደ ወንዝ!

“ወንዝ ሲፈስ አነስተኛ የመቋቋም ብቃት ወዳለው አቅጣጫ እየተጣጠፈ ነው የሚዘልቀው” ይባላል፡፡ አቅሙ የሚፈቅድለት ቁልቁለቱ እያለለት ወንዝ ከአቅሙ በላይ ወደሆነው ወደዳገቱ አይፈስም፡፡ እንደ አቅሙ የሆነው እያለለት ወንዝ ከአቅሙ በላይ የሆነውን፣ “ለምን አያሳልፈኝም” እያለ አይታገልም፡፡ አሁን ስለቀለለው ወደቀኝ ታጥፎ፣ ወዲያው ሲከብደው ወደግራ ሊታጠፍ ይችላል፡፡ በዚህ የፍሰት ባህሪይው የወንዝ መጨረሻው ቀጥ ብሎ ከመሄድ ይልቅ እየተጣመሙ መኖርና የአካባቢው ዝቅተኛው ስፍራ ላይ መውረድ ነው፡፡

የወንዝ ባህሪይ ግን ከላይ የተገለጸው ብቻ አይደለም፡፡ አንዳንድ ጊዜ እኮ ወንዝ ወደከፍታም የሚፈስበት ጊዜ አለ፡፡  ወንዝ አቅሙን ሲያጠራቅም፣ ሲበረታና ኃይል ሲኖረው በፊቱ ያለውን ከፍ ያለ ነገርም ቢሆን ሞልቶና አልፎ ይሄዳል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ወንዝ ሲበረታ ከፍተኛውን ስፍራ እስኪሞላ ድረስ “ወደ ላይ ይፈስሳል”፡፡

ከወንዝ እንማር! ከአቅምህ በላይ የሆኑ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙህ ለምን መንገድ አይለቁም ብለህ እስክትደማ አትታገል፣ ወይም ደግሞ ወደኋለ አትመለስ፡፡ ብልሃት ፈልገህ ዘወር ብለህ እለፍ፡፡ ሆኖም ያንን እያደረክ ሳለህ፣ አቅምህን አጠራቅም፡፡ አቅም በጨመርክ ቁጥር መንገድ እየቀየርክና ጠመዝማዛ ጎዳናን በመጓዝ መድከምህ ያበቃና ቀጥ ብለህና በፊትህ የሚቆመውን እየገረሰስክ ማለፍ ትጀምራለህ፡፡

•  የስሜት ጽንአት አቅምህን አጠራቅም፣ እስከዚያ ግን የወቅቱን የስሜት ጽንአት ባገናዘበ ሁኔታ ተራመድ፡፡

•  የገንዘብ አቅምህን አጠራቅም፣ ለጊዜው ግን ኑሮህን ካለህ የገንዘብ አቅም ጋር በማገናዝ ተንቀሳቀስ፡፡

•  የግንኙነት መረብህ (Network) አቅምህን አጠራቅም፣ እስከዚያው ግን አጠገብህ የሚገኙ ሰዎች በሚደግፉህ ደረጃ ተራመድ፡፡

•  የእውቀት አቅምህን አጠራቅም፣ እስከዚያው ግን ባለህ እውቀት የምትችለውን ስራ በመስራት ኑሮህን ግፋ፡፡

ልክ እንደወንዝ! መልካም ቀን🙏

Telegram ተቀላቀሉን
እንማማርበት ቻናሉ👇👇
@rasehnmelewet33
ራስህን መለወጥ

25 Feb, 03:58

1,422

ምንጊዜም በሰው ሳይሆን #በፈጣሪ መመካት ይበጃል ........

🚹 ሰው ቢገፋህ~~~ፈጣሪ ይደግፈሀል
🚹 ሰው ቢጠላህ~~~ፈጣሪ ያነሳሀል
🚹 ሰው ቢንቅህ~~~ፈጣሪ ያከብርሀል
🚹 ሰው ቢረሳህ~~~አንድ አምላክ ያስታውሰሃል
🚹 ሰው ቢያቀልህ~~~ፈጣሪ ያከብድሀል
🚹 ሰው ቢያዋርድህ~~~ፈጣሪ ከፍ ያደርግሀል
🚹 ብትንገዳገድ~~~~ፈጣሪ ይደግፍሃል
🚹 ብትደክም~~~~ምርኩዝ ይሆንሃል
ፈጣሪ ከተወህ ግን ማንን ትደግፋለህ በማንስ ትመካለህ ምርኩዛችን የሰማይና ይምድር ፈጣሪ ብቻ ነው!.......
         የሰው አለኝታነቱ ከንቱ ነው::
በህይወታችን ሁሉ የፈጣሪ አብሮነት አይለየን🙏🙏

Telegram ተቀላቀሉን
እንማማርበት ቻናሉ👇👇
@rasehnmelewet33