Dernières publications de ሞዐ ተዋሕዶ ልጆች ፔጅ (@moaetewahedob) sur Telegram

Publications du canal ሞዐ ተዋሕዶ ልጆች ፔጅ

ሞዐ ተዋሕዶ ልጆች ፔጅ
"ነፍሳችን በስጋ ስንኖር ብዙ መከራ አለባት።
እንዲሁም ከስጋችን ከተለየች በኋላ እንደሰራነው ስራ ጥሩ ወይም መጥፎ እጣፈንታዎች ይገጥሟታል።
ታዲያ በህይወት ስንኖር ነፍሳችንን የምታሻግር አንድ መንገድ አለች ይህችም ቀጥተኛዋ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ናት። "
https://t.me/MoaeTewahedoB

አስተያየት ና ጥያቄ ያለው ብቻ‼️
@sosi5555
ይህ ፔጅ ታህሳስ 30/4/2014
11,268 abonnés
3,538 photos
199 vidéos
Dernière mise à jour 06.03.2025 12:42

Le dernier contenu partagé par ሞዐ ተዋሕዶ ልጆች ፔጅ sur Telegram

ሞዐ ተዋሕዶ ልጆች ፔጅ

03 Mar, 20:48

51

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
የካቲት 25-አስቀድሞ የማያምን አሕዛብ ሆኖ ሳለ የሰማዕታት አለቃ ቅዱስ ቴዎድሮስና ክብርት እመቤታችን ተገልጠውለት እንዲጠመቅ ከነገሩት በኋላ አምኖ የተጠመቀውና በኋላም ሰማዕት የሆነው ቅዱስ እንጦኒ ዕረፍቱ ነው፡፡
+ ቅዱሳን ሰማዕታት አውሳንዮስ፣ ፊልሞንና ድንግል የሆነች ሉቅያ ምስክርነታቸውን ፈጸሙ፡፡
+ በዋሻ ውስጥ የሚኖር አባ አቡፋና ዐረፈ፡፡
ቅዱስ እንጦኒ ሰማዕት፡- ይኽህም ታላቅ ሰማዕት ከዐረቦች ወገን የቆሮስ ሰው የሆነ ባለጸጋ ሲሆን በሰማዕታት አለቃ በቅዱስ ቴዎድሮስ ገዳም አጠገብ በወንዝ ደርቻ ይኖር ነበር፡፡ አብያተ ክርስቲያናትን የሚቃወም ሆኖ ቅዱስ ቍርባንን በመስረቅ ኅብስቱን ይበላዋል፣ የከበረ ደሙንም ከጽዋው ውስጥ ይጠጣል፣ የመሠዊያውንም ልብስ ገፎ በእሳት ያቃጥለው ነበር፡፡ አንድ ቀን በቅዳሴ ጊዜ በፈረሱ ተቀምጦ ቤተ ክርስቲያን ሲገባ ቅዱስ ቴዎድሮስ በራሱ ጦር ወግቶ ገሠጸው፡፡ በሌላኛው ቀንም ከሰገነት ቤቱ ላይ ተቀምጦ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ሲመለከት ካህናቱ መሥዋዕቱን ተሸክመው ወደ መቅደስ ሲገቡ አያቸው፡፡ በጻሕሉም ውስጥ ነጭ በግ ተኝቶ ከበላዩ ነጭ ርግብ ሲጋርደው በቅዳሴውም ፍጻሜ ያ በግ በየመለያያው የተከፋፈለ ሆኖ ካህናቱም ከተከፋፈለው ሥጋውን ሲቀበሉ ደሙን ከጽዋው ውስጥ ሲቀበሉ አየና እጅግ ተደነቀ፡፡ በልቡም ‹‹የክርስቲያን ሃይማኖት እጅግ ድንቅ ነው›› ብሎ አሰበ፡፡ ዳግመኛም ያ በግ ተመልሶ እንደ ቀድሞው ሕያው ሆኖ አየ፡፡ ከዚህም በኋላ ከመቀመጫ ወርዶ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሄዶ ያየውን ሁሉ ለካህናቱ ነገራቸው፡፡ ካህናቱም ይኽ አሕዛብ ባየው ታላቅምሥጢር ተደንቀው እንዲጸልይ መከሩት፡፡
እርሱም ካህናቱ እንደመከሩት ሌሊት ሲጸልይ ሊቅ ቴዎድሮስ በፈረሱ ላይ ሆኖ ተለጠለትና ‹‹እነሆ በእኔ ላይ ሥዕሌን እስከወጋህ ድረስ ክፉ ሠራህ፣ በክብር ባለቤት በክርስቶስ ሥጋ ላይ ዘበትክ፣ አሁንም የዘላለምን ሕይወት ታገኝ ዘንድ ከክህደትህ ተመልሰህ በክብር ባለቤት በጌታችን እመን›› ብሎት ከእርሱ ተሰወረ፡፡ በማግሥቱም ይኽ አሕዛብ በፈረሱ ሆኖ ወደ ኢየሩሳሌሙ ሊቀ ጳጳሳት ገብቶ ያየውን ምሥጢር ሁሉ ነገራቸው፡፡ ሊቀ ጳጳሳቱም ‹‹በሕዝቡ ሁሉ ፊት እንዳላጠምቅህ እፈራለሁ ነገር ግን ወደ ዮርዳኖስ ወንዝ ሂድ ጌታችን የሚያጠምቅህን ይሰጥሃል›› አሉት፡፡ ወደ ዮርዳኖስን ሄዶ በቤተ ክርስቲያን ሳለ ሌሊት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ነጭ ሐር ግምጃ ለብሳ ተገልጣለት አረጋጋችው፡፡ በእጇም ይዛ አነሣችውና ሊያደርገው የሚገባውን ነገረችው፡፡ ወደ ዮርዳኖስም ወንዝ ሄዶ ሁለት ገዳማውያን አባቶችን አገኘና ፍላጎቱን ነገራቸው፡፡ በገዳማውያኑም እጅ ከተጠመቀ በኋላ ስሙን ‹‹እንጦኒ›› ብለው ሰየሙት፡፡ አመንኩሰውትም በሰላም ሸኙትና ወደ ደማስቆ ሄዶ ቤቱ ገባ፡፡
ወገኖቹም ባዩት ጊዜ ‹‹ይህ የለበስከው ምንድን ነው?›› ሲሉት ክርስቲያን መሆኑን ነገራቸው፡፡ እነርሱም ይዘው እየጎተቱና እየደበደቡ መኰንኑ ዘንድ አቀረቡት፡፡ መኰንኑም ስለ እምነቱ በመረመረው ጊዜ እንጦኒ በጌታችን የሚያምን ክርስቲያን እንደሆነ በድፍረት መሰከረ፡፡ መኰንኑም ይዞ ጽኑ ሥቃይን ካሠቃየው በኋላ በእሥር ቤት ጣለው፡፡ እንጦኒም በሥቃይ ውስጥ ሆኖ በእሥር ቤት ሳለ በላዩ ብርሃን ወረደና ‹‹እንዮንዮስ ሆይ! አክሊል ተዘጋጅቶልሃልና አትፍራ›› የሚል ቃል ሰማ፡፡ ብርሃን የለበሱ ሁለት አረጋውያን መጥተው በራሱ ላይ የብርሃን አክሊል አኖሩ፡፡ በነጋም ጊዜ አደባባይ ወስደው ራሱን በሰይፍ ቆረጡትና በእንጨት ላይ ሰቀሉት፡፡ በሌሊትም በላዩ ብርሃን ሲወርድ አይተው በፍርሃት ሆነው ከተሰቀለበት አውርደው ጤግሮስ አቅራቢያ ቀበሩት፡፡ ከቅዱስ ሥጋውም ብዙ አስገራሚ ተአምራት ተገልጠው ታዩ፡፡ የሰማዕቱ የቅዱስ እንጦኒ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!
+ + +
ቅዱሳን ሰማዕታት አውሳንዮስ፣ ፊልሞና እና ቅድስት ሉቅያ፡- እነዚህም ቅዱሳም በአፍራቅያ አገር ሳለ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ አስተምሮ ያሳመናቸው ናቸው፡፡ ከሃድያንም ዝሑራ በሚባል ኮከብ ስም ለአርታዳሚ ጣዖት በዓልን ባደረጉ ጊዜ እነዚህ ሦስት ክርስቲያኖች በከሃድያኑ ስሕተት ሊዘብቱባቸው ወደ ጣዖት ቤቱ ገቡ፡፡ ጣዖት አምላኪዎቹም ለጣዖቶቻቸው መሥዋዕት ሲያቀርቡና ሲያመሰግኗቸው እነዚህ ክርስቲያኖች ባዩአቸው ጊዜ ሰዎቹ ዕውነተኛውን አምላክ ጌታችንን ክደው ጣዖታትን በማምለካቸው መንፈሳዊ ቅናት ልባቸው ነደደ፡፡ ፈጥነውም ወጥተው ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ጌታችንን ስሙን እየጠሩ እየሰገዱለት አመሰገኑት፡፡ ከዚያ ካሉት ውስጥ አንደኛው ሰው በሰማቸው ጊዜ በጣዖታቸው ላይ እንደዘበቱ የተናገሩትን አስታውሶ በከሃዲው መኮንን ዘንድ ወነጀላቸው፡፡
መኮንኑም ከወታደሮቹ ጋር ፈጥኖ ሄዶ እነዚህ ሦስቱ ክርስቲያኖች ያሉባትን ቤተ ክርስቲያን ከበባት፡፡ በዚህም ጊዜ ከምእመናን ሸሽተው ያመለጡ አሉ፡፡ ቅዱስ አውሳንዮስ፣ ቅዱስ ፊልሞና እና ቅድስት ሉቅያ ግን ክርስቲያን መሆናቸውን በመመስከር ለሰማዕትነት የተዘጋጁ ሆነው ራሳቸውን ለመኮንኑ አሳልፈው ሰጡ፡፡ መኮንኑም እነዚህን ሦስት ቅዱሳን ይዞ አሠቃያቸው፡፡ የብረት ዘንጎችን በእሳት አግሎ ጎኖቻቸውን ወግቶ አቃጠላቸው፡፡ ቀጥሎም የከበረ አውሳንዮስን ወደ ጉድጓድ ውስጥ ወረወሩትና ነፍሱን እስከሰጠ ድረስ በድንጋይ ወገሩት፡፡ የከበረ ፊልሞናን እና የከበረች ቅድስት ሉቅያን ግን ብዙ ጊዜ ጽኑ በሆኑ ሥቃዮች አሠቃዩአቸው፡፡ እነርሱም ነፍሳቸውን ይወስድ ዘንድ እግዚአብሔርን ለመኑት፡፡ እርሱም ልመናቸውን ተቀብሎ ነፍሳቸውን ወሰደ፡፡ ሦስቱም ቅዱሳን ሰማዕትነታቸውን በድል ፈጽመው የድል አክሊልን በመንግሥተ ሰማያት ተቀበሉ፡፡ የሰማዕታቱ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!
+ + +
አባ አቡፋና፡- ይኽም ቅዱስ አባት ብርሃን በሌለበት ዋሻ ውስጥ የሚኖር ሆኖ በሁለት ቀን አንድ ጊዜ ብቻ ይመገብ ነበር፡፡ የሚመገበውም ሆነ የሚጠጣው በመለኪያ ለክቶ ነው፡፡ በመዓልትም በሌሊትም 500 ጊዜ ይጸልያል፡፡ የከበረች የአርባ ቀንን ጾም ከሦስት ቀኖች በቀር ሳይበላ ይፈጽማል፡፡ በአንዲት ዕለትም ቁጥራቸው 20 የሆኑ ወንድሞች ሊጎበኙትና ከእርሱ ሊባረኩ መጡ፡፡ አባ አቡናፋም በበዓቱ የሚበላ የለም ነበርና ሦስት እንጀራን ፈልጎ አመጣ፡፡ እነዚህንም ሦስት እንጀራዎች ባርኮ ቢሰጣቸው ሃያውም ሰዎች ጠግበው እስኪተርፋቸው ድረስ ተመገቡ፡፡
በአንዲትም ዕለት አባ አቡናፋ ለደቀ መዛሙርቱ ‹‹እነሆ ዓለም አለፈ›› አላቸው፡፡ በጠየቁትም ጊዜ ‹‹እነሆ ንጉሥ ቴዎዶስዮስ ሞተ›› አላቸው፡፡ ከዕለታትም በአንደኛው ቀን ሦስት መቶ የወርቅ ዲናር የያዘ እንግዳ በአንድ ቄስ ቤት አደረ፡፡ ቄሱም ስለ ገንዘብ ፍቅር እንግዳውን ገደለውና ወርቁን ወሰደ፡፡ ሬሳውንም ከአንድ መነኩሴ ደጅ ወስዶ ጣለው፡፡ ይህንንም ለአባ አቡናፋ በነገሩት ጊዜ ከሟቹ ላይ እንዲጥሉት ቆቡን ሰጣቸው፡፡ ወስደውም የአባ አቡናፋን ቆብ በላዩ ላይ በጣሉበት ጊዜ የሞተው ሰው ፈጥኖ ተነሣ፡፡ ስለ ገንዘብ ፍቅር ቄሱ እንገደለውም ሲነገራቸው እነርሱም እጅግ አደነቁ፡፡ ከዕለታትም በአንደኛው ቀን አንድ ሰው ከአባ አቡናፋ ቡራኬ ሊቀበል ወደ እርሱ ሲመጣ ልጁ በጉዞ ላይ ሞተ፡፡ ሰውየውም የሞተ ልጁን ተሸክሞ ወደ ቅዱስ አቡናፋ በመሄድ በፊቱ ሰግዶ የልጁን አስክሬን አስቀምጦ ተመለሰ፡፡ ያንጊዜም ልጁ ከሞት ተነሥቶ አባቱን ተከተለው፡፡በአባ አቡናፋ ዋሻ ደጃፍ የውኃ ምንጭ ነበረ፡፡ እርሱም ምሳርን በወረወረ ጊዜ ምሳሩ ነቢዩ አልሳዕ እንዳደረገው በውኃው ላይ
ሞዐ ተዋሕዶ ልጆች ፔጅ

03 Mar, 17:58

341

🕰🔔

3:00
ተንስኡ ለጸሎት

በዚህ ሰዓት ይህንን የምታይ ሰው የምታደርገውን ለ2 ደቂቃም ብትሆን ተውና ልዑል እግዚአብሔር እያሰብን ቢያንስ አንድ አባታችን ሆይ እንጸልይ

እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥

አገር ውስጥ ያላቹሁ  በስደትም በስራም እንኳን ቢሆን አንድ አባታችን ሆይ እንበል🥰
    

     @MoaeTewahedoB
ሞዐ ተዋሕዶ ልጆች ፔጅ

03 Mar, 16:06

499

🥰
ሞዐ ተዋሕዶ ልጆች ፔጅ

03 Mar, 12:01

640

🕰🔔

9:00
ተንስኡ ለጸሎት

በዚህ ሰዓት ይህንን የምታይ ሰው የምታደርገውን ለ2 ደቂቃም ብትሆን ተውና ልዑል እግዚአብሔር እያሰብን ቢያንስ አንድ አባታችን ሆይ እንጸልይ

እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥

አገር ውስጥ ያላቹሁ  በስደትም በስራም እንኳን ቢሆን አንድ አባታችን ሆይ እንበል🥰
    

     @MoaeTewahedoB
ሞዐ ተዋሕዶ ልጆች ፔጅ

03 Mar, 08:59

742

#እውነተኛውን_ጥበብ_እንዴት_እንቀበል?

ማክሲመስ መስካሪው እንዲህ ይላል፦ "አንድ ክርስቲያን አምላካዊውን ጥበብ የሚቀበለው በሦስት መንገድ ነው። በትእዛዝ፣ በትምህርትና በእምነት ነው። ትእዛዝ ሐሳብን ከክፉ ስሜት ያነጻል፤ ትምህርት ወደ ርቱዕ የተፈጥሮ ዕውቀት ይመራል፤ እምነት በተቀደሰ ሦስትነት ወደ መመሰጥ ይመራል።" St. Maximus the Confessor, Chapters on Love, 4.47)።

የእግዚአብሔርን ትእዛዝ የሚያውቅና በዚያም  ለመጓዝ የሚፈቅድ ሰው ሐሳቡን በርቱዕ መሠረት ላይ ያንጻል። የሐሳብ ጥራት መነሻው በእግዚአብሔር ትእዛዝ ውስጥ ባለችው በእግዚአብሔር ፈቃድ ነውና። ሐሳባችን የሚበከለው በማንኛውም መንገድ ከእግዚአብሔር ፈቃድ አፈንግጠን ስንወጣ ነው። ጥበብ ማለት በእግዚአብሔር ትእዛዝ ውስጥ የመኖር ጉዳይ ነው። ከዚያ ውጭ ስንኾን ርቱዕ ከኾነው ጥበብ ውጭ እንኾናለን፤ ያን ጊዜ ድንቍርናው በራሱ ጥበብ መስሎ ሐሳባችንን ይረብሸዋል፡ ወደ ርኲሰትም ይመራዋል!

ትምህርተ ቤተ ክርስቲያን ደግሞ ወደ እውነተኛው ዕውቀት መግቢያ በር ነው። በዓለም ከሚወረወረው የስሕተት ቀስት የምንጠበቀው በኦርቶዶክሳዊ ትምህርት ነው። ኦርቶዶክሳዊ ትምህርትን መውደድ ማለት እውነተኛ ዕውቀትን መውደድ ማለት ነው። ስለ ዓለም ያለን ዕውቀት ትክክለኛ ቅርጹን የሚዪዘው በቤተ ክርስቲያን ትምህርት በኩል ነው። ቤተ ክርስቲያን በዋናነት እውነትን ትገልጣለች፡ በትምህርት በኩልም በልጆቿ ልብ ውስጥ እውነትን ትዘራለች፡ በዘራችው እውነትም ወደ ርቱዕ ዕውቀት የልጆቿን ልብ ትመራለች። እንግዲህ በዚህ ደግሞ ጥበብ ራሱ ርቱዕ ዕውቀት መኾኑን ርቱዐዊነት ባለው ዕውቀት በኩል መቅመስ እንችላለን።

እምነት ደግሞ የማይመረመረውን ምሥጢረ ሥላሴ በምንችለው ልክ ቀምሰን እንድንመሰጥበት ወደዚያ የሚመራ ረቂቅ መሣሪያ ነው። እምነት የምእመናንን ልብ ከምድር ወደ ሰማይ የሚያስገባ ታላቅ ኃይል ነው። የማይታየውን የሚያሳይ፣ ልቡናን በጽኑዕ መሠረት ላይ የሚያንጽ መንፈሳዊ ኃይል ነው። በእምነት ከእግዚአብሔር ጋር እንገናኛለን። እርሱ ደግሞ የጥበብ ቤቷ ነው። እንግዲያውስ ከእርሱ ንጹሕ ጥበብን በእምነት ቀድተን ለዓለም እናፈሳለን። ዓለምንም ወደ ርቱዕ እምነትና ጥበብ እናስገባ ዘንድ አደራ አለብን። ምክንያቱም የጥበብ ምንጭ የኾነው ክርስቶስ አምላካችን ራስ ኾኖን ክርስቲያን ተሰኝተናልና። እርሱ ደግሞ ኹሉን ወደ እርሱ እንድንማርክ ይፈልጋል። ይህም የሚኾነው ከንግግር ባለፈ እርሱ ክርስቶስን በእውነተኛ ሕይወት ስንገልጠው ነው። የእርሱን ፈቃድ ትተን የየግላችንን አጽድቀን የምንኖር ከኾነ ክርስቲያን የሚለው ስሙ እንጅ ትክክለኛ ትርጒሙ በእኛ ገቢራዊ ሕይወት አይገለጥምና ሌሎች ከሕይወት ድንቍርና ይላቀቁ ዘንድ ቀርቶ እኛው ራሳችን በራሳችን የፈቃድ ጥመት ድንቍርና ውስጥ ተቀብረን ያለን አሳዛኞች እንኾናለን።

ትእዛዛተ እግዚአብሔር ሕይወታችንን የሚያጣፍጥ ኾኖ ሳለ ከዚያ አፈንግጠን ምሬትን ገንዘብ በማድርግ ትእዛዙን ከመፈጸም ደንቍረናል። በዚህም ላይ እንደ ገና ትምህርተ ቤተ ክርስቲያንንም ጠልተን ወይም ከልብ ለመማር ወይም ለመረዳት ባለመፈለጋችንም ሌላ ድንቍርናን ጨምረናል። ስለዚህ በንጽሕት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ እምነት ምሥጢር ከመመሰጥ እና ከመደነቅ ይልቅ የጥርጣሬን ብርድልብስ ለራሳችንን ደራርበናል። እንግዲያውስ ጥበብ ከወዴት ይደርብን? ሕይወታችንስ እንዴት አይምረር? ፍሬ ምግባርስ እንዴት አይጉደልብን? ጸጋስ እንዴት አይራቀን? ሕማመ ነፍስስ እንዴት አይጽናብን? ሌሎችስ እውነት የሌለን እንዴት አይምሰላቸው? ወዳጆች ሆይ ትእዛዘ እግዚአብሔርን በመፈጸም፤ ትምህርቱንም (እውነተኛ ዕውቀት የሚቀዳበትን መንገድ) በመጠጣት፣ በርቱዕ እምነት ሰውነታችንን አጽንተን የጠቢባንን አኗኗር አሐዱ ብለን እስኪ እንጀምረው።

https://t.me/MoaeTewahedoB
ሞዐ ተዋሕዶ ልጆች ፔጅ

03 Mar, 08:58

888

🕰🔔

6:00
ተንስኡ ለጸሎት

በዚህ ሰዓት ይህንን የምታይ ሰው የምታደርገውን ለ2 ደቂቃም ብትሆን ተውና ልዑል እግዚአብሔር እያሰብን ቢያንስ አንድ አባታችን ሆይ እንጸልይ

እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥

አገር ውስጥ ያላቹሁ  በስደትም በስራም እንኳን ቢሆን አንድ አባታችን ሆይ እንበል🥰
    

     @MoaeTewahedoB
ሞዐ ተዋሕዶ ልጆች ፔጅ

03 Mar, 05:59

726

🕰🔔

3:00
ተንስኡ ለጸሎት

በዚህ ሰዓት ይህንን የምታይ ሰው የምታደርገውን ለ2 ደቂቃም ብትሆን ተውና ልዑል እግዚአብሔር እያሰብን ቢያንስ አንድ አባታችን ሆይ እንጸልይ

እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥

አገር ውስጥ ያላቹሁ  በስደትም በስራም እንኳን ቢሆን አንድ አባታችን ሆይ እንበል🥰
    

     @MoaeTewahedoB
ሞዐ ተዋሕዶ ልጆች ፔጅ

03 Mar, 04:52

697

🥰
ሞዐ ተዋሕዶ ልጆች ፔጅ

03 Mar, 04:51

679

ቅድስት (የዐቢይ ጾም ሁለተኛ ሳምንት)
#እንኳን_አደረሳቹሁ🥰

🥀«ቅድስት» ማለት የዘይቤ ፍችው « የተቀደሰች የተለየች » ማለት ነው። ምስጢራዊ መልእክቱ ግን የምስጢረ አድኅኖት ታላላቅ ሥራውን ለመጀመር መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶሰ በገዳመ ቆሮንቶስ ገብቶ ከቆመ ሳያርፍ፣ ከዘረጋ ሳያጥፍ የጾማት የአርብዓው ቀንና ሌሊት ልዩ የሆነችና ክብርት ጾም የምትጀመርበትን ሁለተኛ ሳምንት ከልብ ያሳስበናል፡፡ ማቴ. 4-2

🥀ቅድስት የዐቢይ ጾም ሁለተኛ ሰንበት ስያሜ ነው፡፡ ስያሜውም ከኢትዮያዊው የዜማ ሊቅ ከቅዱስ ያሬድ የተገኘ ነው። ከዚህ ሰንበት ዋዜማ ጀምሮ ስለ ዕለተ ሰንበት ቅድስና ይዘመራል፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንም ሰንበቱን ስለ ቅድስና ልጆቿን ታስተምርበታለች ፡፡

🥀በቅዳሴ ጊዜ የሚሰበከው ምስባክ ፤ የሚነበቡ መልዕክታት ፤የሐዋርያት ሥራ ና ወንጌል ስለ ቅድስት የሚያስተምሩ ናቸው፡፡

🥀‹‹ቅዱስ›› ማለት ልዩ፤ ክቡር ማለት ነው፡፡እግዚአብሔር አምላካችን በባሕርዩ ቅዱስ ነው፡፡ ይህም ቅድስና ከማንም ያላገኘው የባሕርይ ገንዘቡ ነው። መጻሕፍትም የባሕርይ ቅድስናውን ተባብረው መስክረዋል፡፡ ባባሕርዩ ቅዱስ ስለሆነ ‹‹ቅዱስ፡ቅዱስ፡ቅዱስ›› እየተባለ ይመሰገናል፡፡ ( ኢሳ 6፡1-3፤40፡25 ራዕ 15፡4 ፤ 1ሳሙ2፡2-3፡፡) እኛም ቅዱስ ልጁ በሥጋ ተገልጦ እንዳስተማረን በየዕለት ጸሎታችን ‹‹ስምህ ይቀደስ›› እንለዋለን፡፡

🥀የቅድስና ምንጭ ፡ ቅድስናን የሚሰጥ እርሱ ብቻ ነው፡፡ ‹‹ ቅዱስ ›› የሚለው ቃል ለሰዎች ፡ለመላእክት ፡ ለቦታ ፡ለዕቃ: ለዕለታት … ቢቀጸልም ቅድስናቸው በባሕርይው ቅዱስ ከሆነው ከእግዚአብሔር የተገኘ ነው፡፡ ይህም የጸጋ ቅድስና ይባላል፡፡

🥀እግዚአብሔር ቅዱስ ስለሆነ በመልኩና በምሳሌው አክብሮ የፈጠረንን እኛም ቅዱሳን እንድንሆን ይፈለጋል፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ‹‹ዳሩ ግን እኔ ቅዱስ ነኝና ቅዱሳን ሁን›› ተብሎ ስለተጻፈ የጠራቸው ቅዱስ እንደሆነ እናንተ ደግሞ በኑሮአችሁ ሁሉ ቅዱሳን ሁኑ ›› ያለንም
ይህንን ሲያስተምረን ነው። ከመፈጠራችን አስቀድሞ መጠን በሌለው ፍቅር የወደደን እግዚአብሔር ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣን ፤ ለውርደት ሳይሆን ለክብር፤ ለርኩሰት ሳይሆን ለቅድስና፤ ለሞት ሳይሆን ለሕይወት ነው፡፡ የመፈጠራችንም ዓላማ በፊቱ በፍጹም ምግባርና ሃይማኖት በመመላለስ ከእርሱ ጋር እንድንኖር ነው፡፡ ብርሃን ከጨለማ፡ ጽድቅ ከኃጢአት፡ ጋር ኅብረት የለውምና ከእርሱ ጋር ለዘላለም ነግሰን ለመኖር በቅድስና መኖር ይጠበቅብናል፡፡

🥀ቅድስናችን በኑሮአችን ሁሉ እንዲሆን ታዘናል (1ጴጥ1፡15)፡፡ ስለዚህ በተሰማራንበት የሥራ መስክ ፣ በማኅበራዊ ኑራአችን ፣በምንበላው ምግብ ፣በምንለብሰው ልብስ ፣ በንግግራችንና በመሳሰለው ሁሉ ለእግዚአብሔር ደስ የሚያሰኘውን በማድረግ እግዚአብሔርን በሚሞት ሥጋችን እናክብረው፡፡ ‹‹እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ የኃጢአትንም ጭንቀት ከእኛ አስወግደን በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግስት እንሩጥ፡፡

🥀የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን እንከተለው፤ እርሱ ነውርን ንቆ ፣ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጧል ›› ተብሎ እንደተጻፈ ደምን እስከ ማፍሰስ ድረስ ተጋድሎ አድርገን ከኃጢአት ርቀት በቅድስና እንድንኖር ይገባናል (ዕብ 12፡1)።

🥀ሥጋዊ ምኞታችንንና መሻታችንን ሰቅለን አሮጌው ሰዋችንን አስወግደን ንስሐ ገብተን ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ተቀብለን በቅድስና እንድናኖር ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን፡፡ ( የሞዐ ተዋህዶ

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክብር አሜን ይቆየን🥰
ተቀላቀሉ ቴሌግራም
https://t.me/MoaeTewahedoB
https://t.me/MoaeTewahedoB
https://t.me/MoaeTewahedoB
ሞዐ ተዋሕዶ ልጆች ፔጅ

02 Mar, 21:57

580

🥰