Dernières publications de ሞዐ ተዋሕዶ ልጆች ፔጅ (@moaetewahedob) sur Telegram

Publications du canal ሞዐ ተዋሕዶ ልጆች ፔጅ

ሞዐ ተዋሕዶ ልጆች ፔጅ
"ነፍሳችን በስጋ ስንኖር ብዙ መከራ አለባት።
እንዲሁም ከስጋችን ከተለየች በኋላ እንደሰራነው ስራ ጥሩ ወይም መጥፎ እጣፈንታዎች ይገጥሟታል።
ታዲያ በህይወት ስንኖር ነፍሳችንን የምታሻግር አንድ መንገድ አለች ይህችም ቀጥተኛዋ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ናት። "
https://t.me/MoaeTewahedoB

አስተያየት ና ጥያቄ ያለው ብቻ‼️
@sosi5555
ይህ ፔጅ ታህሳስ 30/4/2014
11,268 abonnés
3,538 photos
199 vidéos
Dernière mise à jour 06.03.2025 12:42

Le dernier contenu partagé par ሞዐ ተዋሕዶ ልጆች ፔጅ sur Telegram

ሞዐ ተዋሕዶ ልጆች ፔጅ

05 Mar, 09:42

783

‹‹ጌታዬ ሆይ! በሰው ፊት ክብሬን አትግለጥብኝ››

አቡነ ሀብተ ማርያም የዘውትር ጠባቂያቸው ቅዱስ ሚካኤል ካዘዛቸው በቀር ምንም አይሠሩም ነበር፡፡ ቅዱሳት መጻሕፍትንም ባነበቡ ጊዜ ኃይለ ቃሉን እየተረጎመ ምሥጢራትን ይነግራቸዋል፤ የተሰወረውንም ይገልጥላቸዋል፡፡ ከእንስሳት ጩኸት ጀምሮ ከዱር አራዊት ድምፅና እስከ አእዋፍ ቋንቋ ያለውን ያስረዳቸው ነበር፡፡

ይኸውም ቅዱስ መልአክ አንድ ቀን አቡነ ሀብተ ማርያምን ወደ ቤተ ክርስቲያን አስገብቷቸው ሥጋ ወደሙን ለመቀበል ተዘጋጅተው ሳለ ወንጌል የሚነበብበት ሰዓት ሲደርስ ያልተማረ ቄስ የክርስቶስ ጌትነቱን የምትናገር ወንጌልን ሲያነብ ‹‹ወዮሴፍ ብእሲሃ ለማርያም ጻድቅ ውእቱ›› የሚል ከቄሱ አፍ ይህን ንባብ አባታችን ሲሰሙ እጅግ ደንግጠው ወንጌል ወደሚነበብበት ስፍራ ሄደው የሚያነበውን ቄስ ገሠጹት፡፡ ‹‹ወዮሴፍሰ ፈሃሪሃ ለማርያም ጻድቅ ውእቱ በል እንጂ ብእሲሃ አትበል›› ብለው መከሩት፡፡ ቄሱም አቡነ ሀብተ ማርያም እንዳዘዙት ከስህተቱ ወደ ቀና ንባቡ ተመለሰ፡፡ ይህን ጊዜ ጌታችን ለአባታችን ድጋሚ ተገልጦላቸው ‹‹ሀብተ ማርያም ሆይ ይህን ትምህርትህን ወድጄ አመሰገንኩህ፣ የእናቴን የድንግል ማርያምን የድንግልናዋን ንጽሕና ስለ አከበርክ እኔም በመንግስተ ሰማያት ፈጽሜ አከብርሃለሁ›› አላቸው፡፡ ዳግመኛም ጌታችን ‹‹አሁንም ዮሴፍ ብእሲሃ ለማርያም የሚሉትን ሁሉ ለያቸው እንጂ አትተዋቸው፤ እንዲህ የሚል ጽሑፍም ብታገኝ እንዳይኖር እርሱን ፍቀህ ፈሃሪሃ ለማርያም የሚለውን ጻፍ›› ብሎ አባታችንን ካዘዛቸው በኋላ ሰላምታ ሰጥቷቸው ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡

አባታችንም በዚህ ጊዜ ፊታቸው ላይ ብርሃን ስለተሳለባቸውና እንደ ፀሐይ ስላበራ ሰዎችም አይተው ባደነቁ ጊዜ ወደ በዓታቸው ገቡና ጌታችንን ‹‹አቤቱ ጌታዬ ሆይ በሰው ፊት ክብሬን አትግለጥብኝ ሰውርልኝ፣ በቸርነትህም አድነኝ›› ብለው ጸለዩ፡፡እንዲህም ብለው በጸለዩ ጊዜ ፊታቸው መልኩ ተለውጦ እንደ ቀድሞው ሆነ፡፡

የአቡነ ሀብተ ማርያም የከበረች በረከታቸው ትደርብን አሜን።

https://t.me/MoaeTewahedoB
ሞዐ ተዋሕዶ ልጆች ፔጅ

05 Mar, 09:02

740

🕰🔔

6:00
ተንስኡ ለጸሎት

በዚህ ሰዓት ይህንን የምታይ ሰው የምታደርገውን ለ2 ደቂቃም ብትሆን ተውና ልዑል እግዚአብሔር እያሰብን ቢያንስ አንድ አባታችን ሆይ እንጸልይ

እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥

አገር ውስጥ ያላቹሁ  በስደትም በስራም እንኳን ቢሆን አንድ አባታችን ሆይ እንበል🥰
    

     @MoaeTewahedoB
ሞዐ ተዋሕዶ ልጆች ፔጅ

05 Mar, 04:16

897

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
የካቲት 26-ቅዱስ ሳዶቅ ማኅበርተኞቹ ከሆኑ ሁለት ሺህ ስምንት ሰዎች ጋር በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡
+ የእግዚአብሔር ነቢይ ቅዱስ ሆሴዕ ዕረፍቱ ነው፡፡
ሰማዕቱ ቅዱስ ሳዶቅ፡- ይኽም ቅዱስ ምግባር ሃይማኖቱ ያማረ ደገኛ ክርስቲያን ነው፡፡ የከበረ ሳዶቅን ለፀሐይ ይሰግድ ዘንድ ብርህም የተባለው የፋርስ ንጉሥ አዘዘው፡፡ ቅዱስ ሳዶቅም ‹‹ፀሐይን ለፈጠራት ለዕውነተኛው አምላክ እንጂ ለዚህች ለምትታይ ፍጥረት ለሆነች ፀሐይ ልሰግድ ከእናቴ ማኅፀን አልወጣሁም›› አለው፡፡ ንጉሡም መልሶ ‹‹ለዚህች ፀሐይ አምላክ አላት እንዴ?›› ብሎ የጠቀው፡፡ ቅዱስ ሳዶቅም ‹‹ዓለምን ሁሉ የፈጠረ ዕውነተኛው አምላክ ክርስቶስ ነው›› አለው፡፡ ንጉሡም ይህን ሲሰማ እጅግ ተናዶ የቅዱስ ሳዶቅን ራስ በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ፡፡ የከበረ ቅዱስ ሳዶቅም ቆሞ ወደ እግዚአብሔር ከጸለየ በኋላ በሰይፍ ይቆርጡት ዘንድ ራሱን ዘንበል አድርጎ ሰጣቸው፡፡ እነርሱም ራሱን በሰይፍ ቆረጡትና ሰማዕትነቱን በድል ፈጸመ፡፡ ያን ጊዜም ከሰማይ ብሩህ ብርሃን በላዩ ወረደ፡፡ በዚያ ያሉ ሰዎችም ሁሉ ይህንን ለቅዱስ ሳዶቅ ከሰማይ የወረደለትን ብርሃን አይተው ‹‹እኛ ሁላችንም በቅዱስ ሳዶቅ አምላክ አምነናል፣ ክርስቲያን ነን›› ብለው ጮኸው መሰከሩ፡፡ ንጉሡም በዚህ ይበልጥ ተናዶ ሁሉንም በሰይፍ ራስ ራሶቻቸውን ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ፡፡ ያመኑትና የመሰከሩትም ሁሉም ተሰይፈው የሰማዕትነት አክሊልን በመንግሥተ ሰማያት ተቀበሉ፡፡ ቁጥራቸውም ሁለት ሺህ ስምንት ነፍሳት ናቸው፡፡ የቅዱስ ሳዶቅ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!
+ + +
ነቢዩ ቅዱስ ሆሴዕ፡- ይኽም ቅዱስ ነቢይ በአራቱ የይሁዳ ነገሥታት ዘመን በዖዝያን፣ በኢዮአታም፣ በአካዝና በሕዝቅያስ ዘመን ትንቢትን ሲናገር የኖረ ነው፡፡ በትንቢቱም ድንቆች ሥራዎችን ተናገረ፡፡ የእስራኤል ልጆችንም በክፋታቸው ገሠጻቸው፡፡ ‹‹የአመንዝራ ልጆች›› ብሎም ጠራቸው፡፡ እግዚአብሔርም ቁጣውን ከእነርሱ እንደማይመልስ ነገራቸው፡፡ ዳግመኛም ‹‹የእስራኤል ልጆች ቁጥራቸው እንደማይሰፈርና እንደማይቆጠር የባሕር አሸዋ ቢሆን ከጥቂት በቀር አይተርፉም›› አለ፡፡
ዳግመኛም አሕዛብ የሆኑ በእግዚአብሔር እንደሚያምኑ ትንቢትን ሲናገር ‹‹እኔ ወገኖቼ ያልሆኑትን እጠራቸዋለሁ፣ እነርሱም ይሰሙኛል›› አለ፡፡ ነቢዩ ሆሴዕ ዳግመኛም ስለ ጌታችን መከራ መስቀልና በከበረ ደሙ ስለመዳናችን ስለ ትንሣኤውም እንዲህ ብሎ ትንቢት ተናገረ፡- ‹‹እርሱ በመከራው ተገርፎ ያድነናል፣ ሲያድነንም በሁለተኛ ቀን ነው፡፡ በሦስተኛውም ቀን ድነን በእርሱ ፊት እንነሣለን፡፡›› ዳግመኛም እግዚአብሔርን ዐውቀን እንከተለው ዘንድ ስለሞት ሥልጣን መሻር ስለ መቃብርም መሸነፍ ትንቢትን ሲናገር ‹‹ሞት ሆይ! ይዘህ ማስቀረትህ መቃብርስ ድል መንሣትህ ወዴት ነው?›› አለው፡፡ ቅዱስ ሆሴዕ ትንቢትን እየተናገረ 70 ዓመት ኖሮ በበጎ የሽምግልናው ወቅት በሰላም ዐረፈ፡፡  ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን አሜን።
https://t.me/MoaeTewahedoB
ሞዐ ተዋሕዶ ልጆች ፔጅ

04 Mar, 14:03

1,417

🕰🔔

11:00
ተንስኡ ለጸሎት

በዚህ ሰዓት ይህንን የምታይ ሰው የምታደርገውን ለ2 ደቂቃም ብትሆን ተውና ልዑል እግዚአብሔር እያሰብን ቢያንስ አንድ አባታችን ሆይ እንጸልይ

እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥

አገር ውስጥ ያላቹሁ  በስደትም በስራም እንኳን ቢሆን አንድ አባታችን ሆይ እንበል🥰
    

     @MoaeTewahedoB
ሞዐ ተዋሕዶ ልጆች ፔጅ

04 Mar, 12:04

1,018

🕰🔔

9:00
ተንስኡ ለጸሎት

በዚህ ሰዓት ይህንን የምታይ ሰው የምታደርገውን ለ2 ደቂቃም ብትሆን ተውና ልዑል እግዚአብሔር እያሰብን ቢያንስ አንድ አባታችን ሆይ እንጸልይ

እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥

አገር ውስጥ ያላቹሁ  በስደትም በስራም እንኳን ቢሆን አንድ አባታችን ሆይ እንበል🥰
    

     @MoaeTewahedoB
ሞዐ ተዋሕዶ ልጆች ፔጅ

04 Mar, 09:01

984

የጴጥሮስን እንባ ስጠኝ እልሀለሁ
  ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ

የጴጥሮስን እንባ ስጠኝ እልሀለው
ሀጢአቴን ልናዘዝ ፍቅርህን እያሰብኩ
በሞት ጥላ ውስጥ እንኳን ብሄድ ጌታ ሆይ/2/
ልቤን በፍቅር ውሃ እጠበው እባክህን



ቸርነትህ በዝቶ ምህረት ቢያሰጠኝ
እጆቼን ዘርግቼ እማጸናለውኝ
ደምህ የፈሰሰው ለኔ ስለሆነ/2/
በሀጢአት ልትተወኝ ልብህ አልወሰነ

አዝ___

አለማዊ ምግባር ልቤ ቢከተልም
ከዚህ ሁሉ ማዳን ጌታ አይሳንህም
ሀጢአት እየሰራው ባስቀይምህም/2/
በሂሶጵ እርጨኝ ጌታ አንጻኝ እባክህ

አዝ___

ዳቢሎስ ያመጣው ጸጸት የውድቀት ነው
የይሁዳ ምሬት መሞት ነው ፍፃሜው
ይህንን መማረር እኔ አልፈልግም/2/
የውድቀት ጉዞ እንጂ ፍፃሜ የለውም

አዝ__

ጴጥሮስ አባብሎ የተማጸነበት
ፍቅሩን በንስሀ ስቦ ያመጣበት
ፍፃሜው የሚያምር ንስሀ ስጠኝ/2/
የለቅሶ አምሀ የእንባ ሕይወት ስጠኝ


ተዋሕዶ ልጆች👇
                •➢ ሼር // SHARE
https://t.me/MoaeTewahedoB
    
ሞዐ ተዋሕዶ ልጆች ፔጅ

04 Mar, 08:59

1,146

🕰🔔

6:00
ተንስኡ ለጸሎት

በዚህ ሰዓት ይህንን የምታይ ሰው የምታደርገውን ለ2 ደቂቃም ብትሆን ተውና ልዑል እግዚአብሔር እያሰብን ቢያንስ አንድ አባታችን ሆይ እንጸልይ

እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥

አገር ውስጥ ያላቹሁ  በስደትም በስራም እንኳን ቢሆን አንድ አባታችን ሆይ እንበል🥰
    

     @MoaeTewahedoB
ሞዐ ተዋሕዶ ልጆች ፔጅ

04 Mar, 06:02

997

🕰🔔

3:00
ተንስኡ ለጸሎት

በዚህ ሰዓት ይህንን የምታይ ሰው የምታደርገውን ለ2 ደቂቃም ብትሆን ተውና ልዑል እግዚአብሔር እያሰብን ቢያንስ አንድ አባታችን ሆይ እንጸልይ

እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥

አገር ውስጥ ያላቹሁ  በስደትም በስራም እንኳን ቢሆን አንድ አባታችን ሆይ እንበል🥰
    

     @MoaeTewahedoB
ሞዐ ተዋሕዶ ልጆች ፔጅ

03 Mar, 20:48

966

🥰
ሞዐ ተዋሕዶ ልጆች ፔጅ

03 Mar, 20:48

881

ተንሳፈፈ፡፡ አባ አቡናፋ የተለያዩ ተአምራትን እያደረገ ድውያንን እየፈወሰ ሲያገለግል ከዕለታት በአንደኛው ቀን ‹‹አባ አቡናፋ ሆይ! ዓሥራ ስምንት ቀረህ›› የሚል ድምጽ ከሰማይ ወደ እርሱ መጣ፡፡ እርሱም 18 ቀናት እንደሆኑ አስቦ ‹‹እነዚህ ዕለታት የሱባኤ ቀናት ናቸው›› ብሎ ሳይቀመጥ 18 ቀን ቆሞ ጸለየ፡፡ ዳግመኛም ‹‹18 ወሮች ይሆናሉ›› ብሎ ሳይቀመጥ 18 ወራት ቆሞ ጸለየ፡፡ ከዚህም በኋላ እንደገና ‹‹አባ አቡናፋ ሆይ! 18 ዓመት ናትና ጽና በርታ›› የሚል ድምጽ ከሰማይ ወደ እርሱ መጣ፡፡ በዚያንም ጊዜ ፈጽሞ በመጽናት ዓሥራ ስምንቱን ዓመት ቆሞ በጸሎት አሳለፈ፡፡ ሲመገብም ሆነ ሲያንቀላፋ ግድግዳ ተጠግቶ ነው እንጂ ጎኑን መሬት ላይ አያሳርፍም ነበር፡፡ እግሮቹም እንደዝሆን እግር እስከሚሆኑ ድረስ በእንዲህ ዓይነቱ ተጋድሎ ጸንቶ ኖረ፡፡  አባ አቡናፋ በታላቅ ጽናት ዓሥራ ስምንቱን ዓመት ቆሞ በጸሎት ካሳለፈ በኋላ ወዲያው ቅዱስ ቁርባንን ተቀበለ፡፡ የዕረፍቱንም ቀን ዐውቆ ወደ ማረፊያው ገብቶ ራሱን ዘንበል አድርጎ ቅድስት ነፍሱን በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ፡፡ የአባ አቡናፋ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን አሜን።
https://t.me/MoaeTewahedoB