ቀን 08/02/2017 ዓ.ም
ማስታወቂያ
ለሚሊነየም አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት መምህራን ተማሪዎች በሙሉ
የእንግሊዘኛንና ሂሳብ ትምህርቶችን ውጤት ከማሻሻልና ሁለቱ የት/ርት ዓይነቶች ለሌሎች የትምህርት ዓይነቶች መሰረታዊ መሆናቸውን ታሳቢ በማድረግ ከአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የወረደውን የአፈፃፀም ስትራቴጂ ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር ከስትራቴጂዎቹ አንዱ ተግባር የሆነው በየሳምንቱ ሰኞ፣ ሰኞ የእንግሊዘኛ ቀን መሆኑን እንደ ተቋም የተግባባንበት ጉዳይ መሆኑ ይታወቃል፡፡
ስለሆነም ሰኞ በ11/02/2017 ዓ.ም ዕለት ሁሉም የት/ቤታችን ማህበረሰብ በእንግሊዘኛ ቋንቋ በመግባባት፣ መልዕክት በማስተላለፍ፣ ቀኑን ሙሉ የሚኒሚዲያ አገልግሎት በእንግሊዘኛ ቋንቋ እንዲሆንና የመማር ማስተማሪያ ቋንቋ ካለምንም አቻ ትርጉም በእንግሊዘኛ ሆኖ ዕለቱ እንዲከበር የበኩላችሁን አስተዋፅኦ እና በትግበራ ሂደቱ ላይ ተሳትፎ እንድታደርጉ እያሳሰብን የእንግሊዘኛ መምህራን በባለቤትነት አተገባበሩን እንድታስተባብሩ ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡
ት/ቤቱ