ማዕዶት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ @maedotzeorthodox Channel on Telegram

ማዕዶት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

ማዕዶት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
ይህ ማዕዶት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የተሰኘ የቴሌግራም ስብስባችን ነው::
• በእርጅናና በተለያየ ምክንያት ጤናቸው የተጓደለና በየመቃብር ቤቱ የወደቁ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያንን ለመንከባከብ
• የአብነት ትምህርት መምህራንን: ተማሪዎችን ለመርዳት እንዲሁም የትናንቱን ለነገ ለማስቀጠል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ልጆች የሚመክሩበት የቻናል ገፅ ነው::
31,278 Subscribers
493 Photos
5 Videos
Last Updated 12.02.2025 03:00

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ማዕዶት በኢትዮጵያ

በዚህ ዘመን የሚሰጥ የጥናት ጥናትን አድርገዋል የግንዛቤና የአስተዳደር ዕድገት። በኢትዮጵያ ውስጥ "የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ" ማዕዶት መሆን በተለይ በመጠቀም የነገ እና የታሪክ መረጃ የሚያቀርበው ጠቃሚ ዝርዝር አዝማሪ፣ በነዚህ መሠረት የታወቀው የቤተክርስቲያን ሥርዓት እና የዚህ ዓይነት ማዕዶት የታሰበ ነው። ይህ ማዕዶት የውድድር ምክንያት እና በአዳዲስ ዕድገት ተማሪዎች ለማዕድና የተመለከተ ምክንያት ነው።

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ማዕዶት ምንድነው?

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ማዕዶት አንድ ከብዙ ቡድን የሚያንቀባ ማዕድ ማለት እና የዕውቀትን የተቀንበር ትምህርት ለማቅረብ ፌዴሬሽን ይኖራል በዚህ እንዲሁ የሙዚቃ እና የመድኃኒታት ደረጃ ይኖራል።

ማሕበረ ወንበር መነሻ እና ያማሪም ወይነኛ ይዛቢ ጥንቃቄይ በመምህራን የተወከለ ይዤን ይኖራል እና ይህ ዓይነት ማዕዶት ይወድዱት እንደሞኝ ይመለከት።

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ማዕዶት እንዴት ይሰራል?

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ማዕዶት በየተለያዩ የመምህራን ቦታ የሚያርቀውን ጥናትና የዕውቀት መረጃ አካባቢ። ይኖራል ምንድነው ይለይው መድሃኒታት ይምረታት።

በማዕዶት የሚገኛ የመምህራን ትምህርት እና የማዕበል ተዋሕዶ ነው በምንድነው ስም ሕንግሬ ይቀርበዋል እና ይህ ዕወቃታት የሙዚቃ ተዋሕዶ ይምረታትና ያነድብነው ነው።

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ማዕዶት ለምን አስፈላጊ ነው?

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ማዕዶት ይቀርባው ማንአሪያቸው የእንደሞኝ አስፈላጊ ስም ምዕድነ ነው። ሌላ ጉዳይ ይኖራል የእውቀት ስም ነው።

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ማዕዶት የብዙ ተማሪዎች መረጃ ይወቀ ይኖራል ፈጠራ እንዲሁ ይገኛ ወይን ጥይት ይኖራል።

ይህ ማዕዶት ስለ ማሳሰቢያ አንድ ነው?

ማዕዶት የማሳሰቢያ ከፍተኛ ዝርዝር ይሳቀው ዘንድን ይስማር። ይህ ማዕዶት ይገናኛ ሁለት እንዲሁ ለተለይ ይወዱ ይሉይ ይኖራል።

ጥይት ምንጮች፣ ለወደሮዕ ማሳሰቢያ በግንዛቤ መነሻ የሚወደው ይህ ዓይነት ማዕዶት ይምዕደን ነው።

ማዕዶት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ Telegram Channel

ማዕዶት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የተሰኘ የቴሌግራም ስብስባችን ነው:: ይህ ማዕዶት በእርጅናና በተለያየ ምክንያት ጤናቸው የተጓደለና በየመቃብር ቤቱ የወደቁ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያንን ለመንከባከብ ይሆናል። ማዕዶት ምንድን ነው? የቴሌግራም ስብስባችንን በመጠቀም በአብነት ትምህርት መምህራንን ለመርዳት የሚባለው ምንድን ነው? የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች በየመቃብር ቤተክርስቲያንን የቼናል ገፅ ተቀብሏል።

ማዕዶት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ Latest Posts

Post image

✍️✍️✍️

❝አትገረምም!❞
*********

አየህ አገልግሎት ገደብ የለውም! ዕድሜ፣ ቦታ፣ ስራ፣ ትዳር፣ ሁኔታ፣ ሌላውም ምክንያት አይገድበውም። ይህን መልዕክት የምትመለከተው ወንድሜ ሆይ ያኔ በልጅነት ሰንበት ትምህርት ቤት ያሳለፍከውን ጊዜ አስብ፤ መልዕክቱን የምታነቢውም እህቴ፣ ያን የማይረሳ የአገልግሎት ዘመን አስቢው! ዝማሬ ለመቆም፣ መዝሙር ለማጥናት፣ ያሬዳዊ ዝማሬን አጥንቶ ለማቅረብ፣ ድራማ እና ጭውውት ለመስራት፣ አልባሳት ለብሶ ለመዘመር፣ በየበዓላቱ በአልባሳት ደምቆ ቄጤማ እና ዘንባባ ይዞ በየከተማው እየዘመሩ ለመሄድ፣ በየወርሃዊ የዝክር መርሐግብሮች ላይ ጸበል ጸድቅ ለመቃመስ፣ በየልቅሶው ቤት አጽናኝኝ እመአምላክ እያሉ እየዘመሩ ሐዘንተኞችን ለማጽናናት፣ የታመሙትን ድውይ ነኝ አንተ አድነኝ እያሉ እየዘመሩ በሽተኞች በሽታቸውን እንዲረሱ ለማድረግ፣ በየሰርጉ ላይ መርአዊ ሰማያዊ እያሉ ለማጀብ፣ በየንግሱ ታቦታቱን በአልባሳት አሸብርቆ ለማጀብ ያለህን ፍቅር እና ፍላት ቅናት እና መነሳሳት አስበው ወንድሜ። እስኪ ትዝ ይበልሽ እህቴ!

ዛሬስ? ዛሬማ ትልቅ ሆንና! መንግስት ሰራተኞች ደመወዝተኞ ሆንና! ዛሬማ ጊዜ የለንማ፣ ትላልቆች ሆነን አግብተን ወልደን ከበድና፣ ዛሬማ ዕድሜያችን ገፍቶ አልባሳት ለብሶ ማገልገል ያሳፍረናላ፣ ጡረታ ወጣና! ያሳዝናል።

ግን የቤተክርስቲያን ፍቅር እና አገልግሎት በእውቀት ለገባው ምንም ነገር ላለማገልገል ምክንያት አይሆነውም። ብዙዎች መንፈሳዊው እውቀት ላይ ደካሞች ስለሆኑ ተበተኑ። የገባቸው ግን ምንም አይገድባቸውም። ልክ እንደኚህ አባት! ለአባታችን ረዥም እድሜ ከጤና ጋር ያድልልን!

ንሽኩር ረቢና!
24/11/2013 ዓ.ም (ቅዳሜ)

01 Aug, 00:34
164,274
Post image

ተወዳጆች ሆይ !!

… ለሁላችሁ ይድረስ ዘንድ ከዋልድባ አባቶች የመጣውን መልእክት እና የጻፉትን ደብዳቤም እነሆ ለጥፌላችኋለሁ። የዋልድባ አባቶች የችግራቸውን ዝርዝር ሁኔታ አንድ ሁለት ብለው ገልጸውላችኋል። የባንክ ደብተራቸውንም ልከዋል። እናም በተጠቀሰው የባንክ አካውንት በሃገር ውስጥም ከሃገር ውጪም ያላችሁ እስከ ነገ ረቡዕ ድረስ እያስገባችሁ ጠብቁኝ። ገንዘቡ በሦሥተኛም በሁለተኛም ሰው እጅ አይነካካም። በዚያ በኩል ስጋት አይግባችሁ።

… እናንተ ከያላችሁበት ሆናችሁ የተቻላችሁን አስገቡላቸው። አስገቡና ያስገባችሁበትን ሪሲቱን የክርስትና ስማችሁን እየጻፋችሁበት በውስጥ መስመር ላኩልኝ። ነገ ረቡዕ በመረጃ ቲቪ፣ በኢትዮ ቤተሰብ፣ በዘወንጌል እና ( አግኝቼ አላስፈቀድኩትም ነገር ግን በኋላ ደውዬ እነግረዋለሁ) በወንድሜ በዲን ዓባይነህ ካሤ የፅዋዕ የዩቱዩብ ቻናሎች ላይ ለታላቁ ገዳማችን ለዋልድባ አብረንታንት ገዳም የገቢ ማሰባሰቢያ እናደርግላቸዋለን።

… እግዚአብሔር የፈቀደልን አሁኑኑ መስጠት እንጀምር። ከበረከቱም ለመሳተፍ እንሽቀዳደም። ጀምሩ … እንጀምር።

… ማነው?  የዋልድባ ወዳጅ የመጀመሪያው ፈር ቀዳጅ? እኔ ነኝ በልማ። ፍጠን፣ ፍጠኚ።

ጎንደር ዐቢይ ቅርንጫፍ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
የሂሳብ ቁጥር 1000018796779
SWIFT = CBETETAA
ዋልድባ አብረንታንት ገዳም ዘቤተ ሚናስ ማኅበር

18 May, 09:08
110,245
Post image

“አሁንም፦ አይዞአችሁ ብዬ እመክራችኋለሁ፤ ይህ መርከብ እንጂ ከእናንተ አንድ ነፍስ እንኳ አይጠፋምና።” ሐዋ 27፥22

18 Apr, 08:40
101,944
Post image

+ ለምን ትቀናለህ? +

በዜና አበው ላይ አጋንንት አንድን መነኩሴ ለማሰናከል ሲማከሩ የሚያሳይ ታሪክ ተጽፎአል፡፡ መነኩሴው ለብዙ ዘመናት በተጋድሎ አሳልፎ ከብቃት የደረሰ መናኝ ነበር፡፡ የአጋንንቱ ጭፍራ በአለቃቸው ተመርተው ይህንን መነኩሴ ለማሳት ዘመቱ፡፡ ተራ በተራ ወደ እርሱ እየሔዱ የፈተና ወጥመዳቸውን ዘረጉበት፡፡ በዝሙት ሊፈትኑት ሞከሩ፡፡ አልተሳካም፡፡ በምግብም ሞከሩ ድል ነሣቸው፡፡ የሚያውቁትን የፈተና ስልት በተለያየ መንገድ እየተገለጹ አንዴ ሰው አንዴ መልአክ እየመሰሉ ሊጥሉት ቢሞክሩም አልቻሉም፡፡

አለቃቸው ይኼን ጊዜ በሉ እኔ የማደርገውን ተመልከቱ አላቸውና መንገደኛ መስሎ ወደ መነኩሴው ቀረበ፡፡ በጆሮው የሆነ ነግሮት ወዲያው ተሰናብቶት ወጣ፡፡ ይህንን ጊዜ አጋንንቱ እያዩት መነኩሴው መንፈሳዊ ገጽታው ተገፍፎ ፊቱ በቁጣና በንዴት ሲለዋወጥ ተመለከቱት፡፡ በዚህም ተደንቀው ምን ብለህ ነው ያሸነፍከው? ብለው አለቃቸውን ጠየቁት፡፡ እርሱም እንዲህ አላቸው፦ ‘ከአንተ ጋር ያደገውና ከአንተ ጋር የተማረው ጓደኛህ እኮ የእስክንድርያ ፓትርያርክ ሆኖ ተሾመ’ ብዬ ነገርኩትና ወጣሁ፡፡ አሁን ልቡ በቅናት እየነደደ ነው አላቸው፡፡ አጋንንቱ በደስታ ጨፈሩ፡፡

ሰይጣን የቅናትን ኃይል ጠንቅቆ ያውቃል፡፡ መጽሐፈ ቅዳሴ ሞትን ሲገልጸው ‘በሰይጣን ቅናት ወደ ዓለም የገባ’ ይለዋል፡፡ ሰይጣን በሰው ልጅ ጸጋ ቀንቶ አዳምና ሔዋንን በፈጣሪያቸው እንዲቀኑና አምላክ መሆን እንዲመኙ አድርጎ ዓለምን ያመሰቃቀለ ነውና ይህንን መነኩሴ ለመጣል ለሺህ ዓመታት ብዙዎችን ወግቶ የጣለባትን ሰይፉን መዘዘበት፡፡ መነኩሴው የእኩያውን መሾም ሲሰማ ቅናቱን መቋቋም አቃተው::

ቅናት እጅግ ክፉ ኃጢአት ነው፡፡ ሰው ቢዘሙት ቢሰክር በሥጋው ነው:: ቅናት ግን በምታስተውል ነፍሱ ውስጥ የሚበቅል መርዝ ነው፡፡ ቃየልን በየዋህ ወንድሙ ላይ ያስጨከነው ቅናት ነበር፡፡ የአቤል ስኬት ለቃየል ውድቀት መስሎ ስለተሰማው በግፍ ሊገድለው በቃ፡፡

ዮሴፍ የለበሳት ቀለምዋ ብዙ የሆነ ጌጠኛ ቀሚስ በወንድሞቹ ዘንድ የመረረ ጥላቻን አትርፋለት ነበር፡፡ አንዱ አጊጦ አምሮ ሲታይ ቢሞትና ቢገላገሉት ደስ የሚላቸው የዮሴፍ ወንድሞች በየዘመኑ አሉ፡፡

ዮሴፍም አርፎ አልተቀመጠም፡፡ እየሔደ ሕልሙን ይነግራቸው ነበር፡፡ ስለ ሕልሙም የበለጠ ጠሉት ይላል፡፡ ወዳጄ ሕልምህን ዝም ብለህ ለሰዎች አትዝራ፡፡ ሕልም ስልህ ተኝተህ የምታየውን ብቻ ማለቴ አይደለም፡፡ ራእይህን ፣ ተስፋህን ዕቅድህን ሲያውቁ የሚንገበገቡ የዮሴፍ ወንድሞች በየዘመኑ አሉ፡፡ ፍቺው ባይገባቸውም ባልተፈታ ሕልም ይጠሉሃል፡፡ ምንም ነገር ሳታደርግ እንኳን "ለምን አለምከው?" ብለው ጥርስ ይነክሱብሃል፡፡ ዮሴፍ ግን ይኼ ስላልገባው ነገራቸው፡፡ ወዳጄ አንተም ሕልምህን እንደ ዮሴፍ በየዋህነት የምትዘራ ከሆንህ እንግዲህ የዮሴፍ አምላክ ይጠብቅህ፡፡

ቅናት እጅግ ከባድ ነው፡፡ እረኛው ዳዊት ጎልያድን የገደለ ዕለት የተዘፈነለት መዘዘኛ ዘፈንም ነበረ፡፡ ‘ሳኦል ሺህ ገደለ ዳዊት እልፍ ገደለ’ ብለው ዘፈኑለት፡፡ ይህች ዘፈን በሳኦል ጆሮ ስትደርስ ዳዊት ላይ ብዙ ጦር አስወረወረች፡፡ ሳኦሎች ሌላ ሰው ከእነርሱ በላይ ሲመሰገን የሰሙ ዕለት በቅናት ታውረው ገበታ ላይ ሳይቀር ሰይፍ ይመዛሉ፡፡

የጠፋው ልጅ ወንድምን አስበው፡፡ (ሉቃ 15:20) ወንድሙ ከጠፋበት ተመልሶ ደስታ ሲደረግ እርሱ ግን ከፍቶት ውጪ ቁጭ አለ፡፡ ወዳጄ ቅናት ከቤተ ክርስቲያንና ከእግዚአብሔር መንግሥት ያስወጣል፡፡ የሌላው ስኬት ካበሳጨህ እንደጠፋው ልጅ ወንድም ውጪ ቁጭ ብለህ አፈር እየጫርክ ‘እምቢየው አልገባም’ እያልክ እያልጎመጎምክ ትቀራለህ፡፡

ክርስቶስ ላይ አይሁድ ያቀረቡት ትችት ሁሉ ለሕግ ከመቆርቆር ሳይሆን ከቅናት ነበር፡፡ ጲላጦስ እንኳን ‘በቅናት አሳልፈው እንደሠጡት ያውቅ ነበር’ ይላል፡፡ አንዳንዴ ሰዎች ቅናታቸውን በሌላ ነገር እንደ አይሁድ ሸፍነው ትችት ያቀርባሉ፡፡ ለእግዚአብሔር ሕግ እንደተቆረቆሩ ፣ ለሥርዓቱ እንዳዘኑ መስለው ውስጣቸው ያለውን ቅናትና ጥላቻ ያንጸባርቃሉ፡፡

የሰንበት መሻር ፣ ለቄሣር ግብር መከፈል ፣ የመቅደሱ በሦስት ቀን ፈርሶ መሠራት እንዳንገበገባቸው እርር እያሉ ቢናገሩም እውነታው ግን ቅናት ነው፡፡ ‘የቤትህ ቅናት በላኝ’ እንዳለው ጌታ በየዘመኑ የሰዎች ቅናት ብዙ ንጹሐንን ትበላለች፡፡

ወዳጄ በሌላው ትቀና እንደሆን አሁኑኑ ከዚህ ውስጥን በልቶ ከሚጨርስ ካንሰር ራስህን አድን፡፡

ራስህን ከሌሎች ጋር አታወዳድር፡፡ በምድር ላይ እግዚአብሔር የፈጠረው አንተን የሚመስል ሌላ ሰው የለም፡፡ ካንተ ቀድሞም በትክክል አንተን የሆነ ሰው አልተፈጠረም ለወደፊትም አይፈጠርም፡፡ እግዚአብሔር ቀድሞ ያልሠራው ደግሞም የማይሠራው ምርጥ ዕቃው ነህና ራስህን ከሌላ ጋር አታወዳድር፡፡

ለአንተ ብቻ የሠጠው ጸጋ አለና ሌሎችን መመልከት ትተህ ውስጥህ ያለውን ውድ ማንነት ቆፍረህ አውጣ፡፡ ያንተ ሕይወት ቁልፍ የተቀበረው አንተው ውስጥ ነው፡፡ ሌሎችን ረስተህ ወደ ራስህ ጠልቀህ ግባ፡፡ መብለጥ ከፈለግህም አሁን ያለውን ራስህን ብለጠውና ሌላ ትልቅ አንተን ሁን፡፡

በቅናት እንዳትቃጠል ሌሎችን ሰዎችንም ውደዳቸው፡፡ ከወደድሃቸው ‘ፍቅር አይቀናም’ና የእነርሱ ስኬት የደስታህ ምንጭ ይሆናል፡፡ የቅናት ስሜት ሲሰማህም ‘ቀናተኛ ልቤን ፈውስልኝ’ ብለህ ለምነው፡፡

‘በአገባብ እንመላለስ፤ በዘፈንና በስካር አይሁን፥ በዝሙትና በመዳራት አይሁን፥ በክርክርና በቅናት አይሁን’ ሮሜ 13፡13

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
አለታ ወንዶ ኢትዮጵያ
ጥር 5 2013 ዓ.ም.

መነሻ ሃሳብ:- የአንድ በቅናት ጦስ ሊያበሩ ሲችሉ ብዙ ዋጋ የከፈሉ ቤተሰቦች ታሪክ

13 Jan, 03:03
138,328