***
ሀብት ንብረት ብቻ አይደለም የወደመው
ብዙ ወንድሞቻችን ሆስፒታል ናቸው
ዛሬ ሆስፒታል ሄደን በህክምና ያሉ ወንድሞችን ጠይቀናል።
መውጫ አጥተው ህይወታቸው ያለፈም አሉ።
በተቻለ መጠን ከነዚህ ወገኖቻችን ጎን መቆም አለብን
***
በአካልም፣ በስልክም ያገኘናቸው ተጎጂዎች በዚህ ሁሉ መከራ ውስጥም ሆነው ከአንደበታቸው የሚወጣው አልሀምዱሊላህ ብቻ ነው።
ለፈተና በማይገበሩ፣
ሁሉም ነገር ለበጎ ነው በሚሉ ብርቱ ሰዎች ላይ የአላህ እዝነትና ራህመት ይስፈን።
***
ለሞተባችሁ ሶብርን
ህክምና ላላችሁ አፊያን
ንብረት ለጠፋባችሁ የተሻለውን ፈጣሪ ይወፍቃችሁ🤲
***