የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኅብረተሠብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትን በማጠቃለል የ2017 ዓ.ም የበጋ በጎ ፈቃድ ፕሮግራምን በነገው ዕለት በይፋ ያስጀምራል።
በመርሃ ግብሩ ላይ ከ1000 በላይ በጎ ፈቃደኞችና ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉ ሲሆን ፕሮግራሙ "በጎ ፈቃደኝነት ለማኅበረሰብ ለውጥ!" በሚል መሪ ቃል ተግባራዊ ይሆናል።
አስር ዐበይት መርሃ ግብሮችንና 13 ንዑሳን ተግባራትን ያካተተው ይህ ፕሮግራም ከአንድ ሚሊዮን በላይ በጎ ፈቃደኞች ይሳተፉበታል ተብሎ ይጠበቃል!