Artios Media @artios_media Channel on Telegram

Artios Media

@artios_media


We Are Artios! We are complete!

#Artios spiritual journey towards #completeness !

"So that the man of God may be complete and equipped for every good work." 2 Tim 3:17

Join the complete journey @artios_media

Artios Media (English)

Are you on a spiritual journey towards completeness? Look no further than Artios Media! Our channel, @artios_media, is dedicated to guiding individuals on their path towards completeness in every aspect of their lives. The name Artios comes from the Bible verse 2 Timothy 3:17, which states, 'So that the man of God may be complete and equipped for every good work.' This verse serves as the foundation of our mission to help individuals become whole and prepared for all the good works they are meant to do. Whether you are seeking spiritual guidance, personal development tips, or simply looking for a supportive community, Artios Media is the place for you. Join us on this complete journey and let us help you become the best version of yourself. Follow us on @artios_media today and begin your transformation towards completeness!

Artios Media

20 Feb, 21:22


የሚቆረስ ሕይወት

35ኛ ሳምንት
5ኛ ቀን


ባለጠጋ ለመሆን የሚፈልጉ ግን ወደ ፈተናና ወደ ወጥመድ፣ እንዲሁም ሰዎችን ወደ መፍረስና ወደ ጥፋት ወደሚያዘቅጠው ወደ ብዙ ከንቱና ክፉ ምኞት ይወድቃሉ። ምክንያቱም የገንዘብ ፍቅር የክፋት ሁሉ ሥር ነው። አንዳንዶች ባለጠጋ ለመሆን ካላቸው ጕጕት የተነሣ ከእምነት መንገድ ስተው ሄደዋል፤ ራሳቸውንም በብዙ ሥቃይ ወግተዋል።
1 ጢሞቴዎስ 6፥9-10

ይህ ቃል በሕይወት መንገድ ላይ እየከነፉ በብልጽግና አውራ ጎዳና ላይ ወጥተው እየፈረጠጡ ላሉት ሰዎች በትልቅ ፊደላት ጎልቶ ተጽፎ ከመንገዳቸው ዳር ተተክሎ የምትሄዱበት መንገድ ወደ ድሎት ሳይሆን ወደ ጥፋትና ስቃይ የሚወስድ ነው የሚል ማስጠንቀቂያ ነው።

ሐዋርያው ጳውሎስ በኤፌሶን ያሉት አማኞች በብልፅግና ምኞት ተወግተው ከእምነት ስተው መዳረሻው ጥፋት እንዳይሆን ጢሞቴዎስን አስጠንቅቃቸው በማለት ያዘዋል። 

የብልፅግና ትምህርት በቤተክርስቲያን ውስጥ መሰበክ ከተጀመረ ሰዎች ተስፋቸውን በክርስቶስ ላይ ሳይሆን በሚጠፋ ምድራዊ ሃብት ላይ እንዲያደርጉ ያስታቸዋል።

ዓለማዊ ምኞትን እንዲክዱ ሳይሆን ይባሱኑ ስስትና መጎምጀት እንዲያይልባቸው ያደርጋል። ነፍሳቸውን በምኞት ባህር ውስጥ በማስጠም ኑሮዬ በቃኝ ከሚለው የአመስጋኝነትን ሕይወት ነቅሎ በማጉረምረም ጥላ ሥር ያኖራቸዋል።

በቤተክርስቲያን አዳራሽ ውስጥ የሚሰብኩት የብልፅግና ዲስኩሮች በክርስቶስ ስምና አውዱን በሳተ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ ስለሚሸፈኑ እጅግ አደገኛና አሳች ናቸው። 

እነዚህ የገንዘብ ሰባኪዎች ተከታዮቻቸውን ቀስ በቀስ በመስቀል ላይ የሞተላቸውንና ነፍሳቸውን ያዳናቸውን ኢየሱስን ከልባቸው ላይ ፍቆ የሚፈልጉትን በመስጠት የሚባርካቸውንና ምኞታቸውን ለሟሟለት እንደ ካፌ አስተናጋጅ ጎንበስ ብሎ የሚታዘዝላቸውን ሌላ ኢየሱስ በራሳቸው አእምሮ ውስጥ ፈጥረው እንዲያመልኩ ያደርጓቸዋል።

በዚህ የብልፅግና ምኞት የተጠቁት አማኞች አመስጋኞች መሆን አይችሉም፣ እርካታ የላቸውም፣ የትም ፍጪው ዱቄቱን አምጪው አይነት መርህ የሚከተሉ ናቸው። አምጣ እንጂ እንካ ጨርሶ አያውቃቸውም።

በተለይ በዚህ ዘመን ያሉት ሰዎች ይህ የስስት ካንሰር እንደ ወረርሽኝ ስለገባባቸው ሃብት እናገኝበታለን ብለው ያሰቡትን ማንኛውንም ነገር ለማድረግ ወደ ኋላ አይሉም።

የዛሬው ንብረት ማከማቸት እንጂ የነገው ተጠያቂነት ግድ አይሰጣቸውም። ሁሉን ነገር የሚያደርጉት እራሳቸውን ማዕከል አድርገው ነው። የሌሎች ሕይወት ይጎዳ ይሆን፣ እግዚአብሔር ምን ይለኛል፣ ቅድስናዬን ያጎድፋል ወይ ብለው በጭራሽ አያስቡትም።

አንድ ሰው በሕይወት ዘመኑ ያከማቸውን ንብረት አንዱንም ከሞት ወንዝ ማሻገር አይችልም። እራቁታችንን እንደ ተወለድን ራቁታችንን እንቀበራለን። ከሞት በስቲያ የሚጠብቀን ሃብት ለድሆች ያካፈልነውና ለወንጌል አገልግሎት የሰጠነው ንብረት ብቻ ነው።

ወገኖቼ! የልግስና እንቅፋት የብልፅግና ምኞት ነው። መሰብሰብን ብቸኛው የሕይወታቸው መርህ አድርገው ለሚኖሩ ሰዎች መቆረስ እንግዳ ቋንቋ ነው። ሆኖም ግን ገዳይ ከሆነው የስስትና የመሰብሰብ በሽታ የሚያድነን ብቸኛው መድኃኒት በልግስና መስጠት ነው።

ሕይወትን ትርጉም ያለውና ጣፋጭ የሚያደርገው መቀበልና መሰብሰብ ሳይሆን መስጠትና ማካፈል ነው። ውስጣችን የሚረካው ለተቸገሩት ስናካፍል ነው።

የብልፅና ምኞትና የገንዘብ ፍቅር ነድፎን ከሕይወት መስመር እንዳያስተን የልግስና መጠናችንን ከፍ በማድረግ ነፍሳችን እንድናተርፍ ጌታ ማስተዋሉን ያብዛልን።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት፦ ከባለጠግነት ምኞትና ከገንዘብ ፍቅር የመጠበቅ ጥሪ ከሞት የመጠበቅ ያህል አንገብጋቢ ጥሪ ነው።

የዛሬው ፀሎት፦ እግዚአብሔር ሆይ ልቤን ከሚመርዘው አፍቅሮተ ንዋይና የብልፅግና ምኞት በቃልህ ልቤን መጠበቅ እንድችል እንድትረዳኝ እለምንሃለሁ። አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

19 Feb, 21:03


የሚቆረስ ሕይወት

35ኛ ሳምንት
4ኛ ቀን


እያንዳንዱ ሰው በቅሬታ ወይም በግዴታ ሳይሆን፣ በልቡ ያሰበውን ያህል ይስጥ፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ሰው ይወድዳል። 2ቆሮ 9፥7

ጳውሎስ በኢየሩሳሌም ያለችው ቤተክርስቲያን በችግር ውስጥ ስትገባ በግሪክ ሀገር ካሉት አብያተክርስቲያናት እርዳታ አሰበሳስቦ ለመደጎም ቅዱሳንን እያስተባበረ ነበር።

በሁለተኛው የቆሮንቶስ መልዕክት ውስጥም እንዴት መስጠት እንዳለባቸው መመሪያ ሰጣቸው። ይህም ትዕዛዝ ለየትኛውም ቤተክርስቲያን የሚጠቅም የልግስና መርህ ሊሆን ይችላል። በተለይ በመቄዶንያ ያሉትን አብያተክርስቲያናት እንደ ምሳሌ በመጠቀም የቆሮንቶስ አማኞችን ያነሳሳቸዋል።

የመቄዶንያ ሰዎች "የደረሰባቸው መከራ ጽኑ ቢሆንም ደስታቸው ግን የላቀ ነበር፤ ድኽነታቸው ብርቱ ቢሆንም ልግስናቸው ግን የበዛ ነበር" (2ቆሮ 8፥2) በማለት ያደንቃቸዋል።

ይህም ብቻ ሳይሆን "እነርሱም ቅዱሳንን ለመርዳት በሚደረገው አገልግሎት ለመሳተፍ ዕድል ያገኙ ዘንድ አጥብቀው ይለምኑን ነበር።"
(2ቆሮ 8፥4) ይላል።

የመቄዶንያ ሰዎች የተሰጣቸውን የልግስና ፀጋ በሚገባ አስተናግደዋል። ስስት እንጂ ድህነት ከልግስና እንደማይከለክል የመቄዶንያ ሰዎች ምስክር ናቸው።

ደግሞም በልግስና ሥራ ውስጥ ለመሳተፍ ተጋብዘው ወይም ተጎትጉተው ሳይሆን እራሳቸው ዕድሉ እንዲመቻችላቸው አጥብቀው ለምነው መሆኑን ሐዋርያው ጳውሎስ ይመሰክርላቸዋል።

ልግስና የሌሎችን ችግር ከራሳችን ችግር አስበልጠን በማየት ለእነርሱ ፍላጎት ቅድሚያ የመስጠት ጉዳይ እንጂ ስለ ተረፈን ብቻ በዘፈቀደ የምናደርገው አገልግሎት አይደለም። የመቄዶንያ ሰዎች ለኢየሩሳሌም አማኞች እርዳታ የላኩት ካላቸው ትርፍ ሳይሆን ከብርቱ ድኽነት ውስጥ ነው።

ሐዋርያው ጳውሎስ የቆሮንቶስ ቤተክርስቲያን የመቄዶንያን አብያተክርስቲያናት አርዓያነት በመከተል የኢየሩሳሌምን ቅዱሳን እንዲረዱ ያሳስባቸዋል።

በመመሪያውም መሰረት ልግስና በቅሬታ ወይም በግዴታ የሚፈጸም ሳይሆን በልብ ውስጥ የታሰበው ያህል ብቻ ቢሰጥ ነው አግባብነት የሚኖረው ይላል። ቅሬታና ግዴታ ከውጪ የሚመጣ ግፊትን የሚያመለክት ነው። ደስተኛ የሚያደርግ ልገሳ ያመንበትን፣ በአቅማችን ልክ፣ ፈቃደኛ ሆነን፣ ያለ ተጽዕኖ የምንሰጠው ሲሆን ይህም እግዚአብሔርን ያስደስታል።

ወገኞቼ! ተካፍሎ መኖርና የተቸገሩትን መርዳት እግዚአብሔር በሁለቱም ኪዳናት ውስጥ እርሱን ለሚያመልኩ ሕዝቦቹ የሰጣቸው ትዕዛዝ ነው።

በመጀመሪያይቱ ቤተክርስቲያን ውስጥ የነበሩት ቅዱሳን ስስት ያልነካካቸው፣ ያላቸውን ተካፍለው ለመኖር በጭራሽ የማይከብዳቸው ነበሩ። በመካከላቸው ችግረኛ እስከማይኖር ድረስ ያላቸውን በጋራ በማድረግ መንፈሳዊ የጋርዮሽ ስርዓት የገነቡ ነበሩ።

በኢየሩሳሌም የተጀመረችው ቤተክርስቲያን በትንሿ ኤስያና በአውሮፓ እንዲሁም በሜዲትራኒያንን ባህር አካባቢ ወዳሉት ሀገራት ስትስፋፋ ይህንኑ ባህል ይዛ ነው።

በአንድ አከባቢ ያለች ቤተክርስቲያን በሌላ አገር ያለች ቤተክርስቲያን በችግር ውስጥ ስትገባ በገንዘብ፣ በቁስ፣ በፀሎት መደገፍ በየትኛውም ዘመን በማንኛውም ጊዜ መጣል የሌለበት ቋሚ እሴት ነው።

እኛም ያለንን ንብረት ለወገኖቻችን በመለገስ ከክርስቶስ የተካፈልነውን የመቆረስ ሕይወት እንድንለማመድ ጌታ በነገር ሁሉ ፀጋውን አትረፍርፎ ይስጠን።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት፦ በቤተክርስቲያናት መካከል መረዳዳት ከጥንት የነበረ አሁንም መቀጠል ያለበት ቋሚ የቤተክርስቲያን እሴት ነው።

የዛሬው ፀሎት፦ እግዚአብሔር ሆይ በአባልነት የታቀፍኩበት አጥቢያ ቤተክርስቲያን በችግር ውስጥ ላሉት ሌሎች አብያተክርስቲያናት በልግስና መስጠት እንድትችል ማስተዋልን አብዛላት። አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

18 Feb, 21:34


የሚቆረስ ሕይወት

35ኛ ሳምንት
3ኛ ቀን


“የምድራችሁን መከር በምትሰበስቡበት ጊዜ፣ የዕርሻችሁን ዳርና ዳር አትጨዱ፤ ቃርሚያውን አትልቀሙ፤ እነዚህንም ለድኾችና ለእንግዶች ተዉላቸው፤ እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ነኝ። ” ዘሌ 23፥22

"ልግስና ለእግዚአብሔርና ለሕዝቡ ጥልቅ የሆነ ፍቅር ከሌለን በጭራሽ የማይታሰብ ነገር ነው። ነገር ግን ሰውና እግዚአብሔርን መውደድ ከቻልን ልግስና የሚቻል ነገር ብቻ ሳይሆን አይቀሬ የሕይወታችን ልምምድ ይሆናል።" ጆን ማክአርተር
 
በዘሌዋውያን መጽሐፍ ውስጥ የተሰጠው መመሪያ እስራኤላውያን ወደ ተስፋይቱ ምድር ሲገቡ ሊከተሉት የሚገባ የልግስና ሕግ ነው።

ከራሳቸው አልፈው ለተቸገሩት ወገኖቻቸውና ለእንግዶች እንዲሰጡ እግዚአብሔር የመስጠትን መርህ ሰጣቸው።

የዚህ ሕግ ዋናው መልዕክት በሰው ልጆች መካከል መተሳሰብ እንዲዳብር፣ ከራስ አልፎ ለተቸገሩት መቆረስን እንዲያውቁ፣ የእግዚአብሔርን ባህሪይ እንዲለማመዱ፣ የሚኖሩትም በሰበሰቡት ሰብል ሳይሆን በእግዚአብሔር ቸርነት መሆኑን እንዲያውቁ ለማስተማር ነው።

የእግዚአብሔር ሕግ ድሆችን የሚገፋና የሚያገል ሳይሆን የሚያቅፍ ነው። አምላካች አቅመ ደካሞችን፣ አካል ጉዳተኞችን፣ መበለቶችንና ወላጅ አልባ የሆኑትን ታሳቢ ያደረገ የኢኮኖሚ ስርዓት ነው የዘረጋው።

የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅድመ አያቶች ሩትና ቦዔዝ የተገናኙት የዘሌዋውያኑ ሕግ ተግባራዊ ሲያደርጉ ነው። በመጽሐፈ ሩት ውስጥ በዝርዝር የተጻፈው ውብ ታሪክ የቦዔዝ ቸርነት አንዲትን ደሃ መበለት ከመርዳት ባለፈ የእግዚአብሔር የትድግና ፕሮግራም አካል ሆኖ እናገኛለን።

በብሉይ ኪዳን ውስጥ የተሰጠው መመሪያ ለእስራኤላውያን ብቻ ሳይሆን በየትኛውም ዘመን ለየትኛውም ሕዝብ የሚጠቅም መርህ ነው።

እግዚአብሔር የሰጠንን ንብረት ለአቅመ ደካሞችና ለድሆች በማካፈል በስስትና መጎምጀት ከሚመጣብን ዘርፈ ብዙ የኃጢአት መዘዞች እራሳችንን እንድንጠብቅ እግዚአብሔር ማስተዋሉን ይስጠን።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት፦ ለድሃ መስጠት በዘፈቀደ እንደ ተመቸን የምናደርገው ሳይሆን መለኮታዊ ትዕዛዝን የመፈጸም ጉዳይ ነው።  

የዛሬው ፀሎት፦ እግዚአብሔር ሆይ የማካፈልን ትዕዛዝ በመፈጸም በሰጠኸኝ ንብረት ሁሉ እንዳከብርህ እርዳኝ። አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

18 Feb, 03:34


የሚቆረስ ሕይወት

35ኛ ሳምንት
2ኛ ቀን


“እግዚአብሔርም ለድሆች መጠጊያ ሆናቸው፥ እርሱም በመከራቸው ጊዜ ረዳታቸው ነው።” መዝ 9፥9

መዝሙረኛው ዳዊት እግዚአብሔር ምን ያህል ለድሆች ስፍራ እንዳለው በማሰብ እየተቀኘ ነው። ድሆች ሳይሸማቀቁ የሚጠጉበትና በመከራቸውም ጊዜ ረዳታቸው የሚያደርጉት እግዚአብሔርን ነው።

በጣም የሚገርመኝ እግዚአብሔር ድሆችን ለማስጠጋት ፈቃደኛና ደስተኛ መሆኑ ነው። የሰው ትኩረት በሃብታሞች ላይ ሲሆን የእግዚአብሔር ግን በድሆች ላይ ነው።

በሌላ መዝሙር ላይ ዳዊት እንዲህ በማለት ተቀኝቶአል "እግዚአብሔር በተቀደሰ ማደሪያው፣
ለድኻ ዐደጉ አባት፣ ለባልቴቲቱም ተሟጋች ነው። (መዝ 68፥5)

በየትኛውም የመጽሐፍ ቅዱስ ላይ እግዚአብሔር ድሆችን ሲገፋና ሲያስጨንቅ አይታይም። እንዲያውም እራሱን ከድሆች ጋር በማነጻጸር ለእነርሱ ከሰጣችሁ ለእኔ እንዳደረጋችሁት ነው የማስበው ብሎናል።

በመጨረሻው የፍርድ ቀን በአመጸኞች ላይ ከሚፈረድባቸው ምክንያቶች አንዱ ድሆችን መርዳት ለእግዚአብሔር መስጠት መሆኑን ባለመረዳት በስስት በመኖራቸው ነው።

እነርሱም መልሰው፣ ‘ጌታ ሆይ፤ ተርበህ ወይም ተጠምተህ፣ እንግዳ ሆነህ ወይም ታርዘህ፣ ታመህ ወይም ታስረህ አይተን መቼ አልደረስንልህም’ ይሉታል። “በዚያን ጊዜ እርሱም መልሶ፣ ‘እውነት እላችኋለሁ፣ ከእነዚህ አነስተኛ ከሆኑት ወንድሞቼ ለአንዱ አለማድረጋችሁ፣ ለእኔ እንዳላደረጋችሁት ነው’ ይላቸዋል። (ማቴ 25፥44-45)

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋ ለብሶ ወደዚህ ምድር ሲመጣ የሐብታሞችን መልክ ይዞ ሳይሆን የድሃን መልክ ወስዶ ነው። እንደ አሰሪ ገዢ ሳይሆን እንደ ባሪያ ሆኖ ነው። በምድር ላይ ኀብት በማከማቸት ሳይሆን እራሱን የሚያስጠጋበት ቦታ የሌለው ተንከራታች ሆኖ ነው።

ለድሃ ማሰብ ከእግዚአብሔር የተካፈልነው መለኮታዊ ባህሪይ ነው። በድሃ ጫማ ውስጥ ሆነን እነርሱን መረዳት፣ ሃፍረታቸውን መካፈል፣ ረሃባቸውን መራብና እርዛታቸውን ታርዘን  ከእነርሱ ጋር ሆነን በምንችለው ሁሉና በሚያስፈልጋቸው ነገር አብረናቸው እንድንሆን ያስፈልገናል።

ወገኞቼ ድሃን የተቀበለ ለእነርሱ ደግሞ የሚራራ አምላክ እያመለክን ድሆችን የምንንቅና የማንረዳ ከሆነ የማን ልጆች እንደሆንን ሳይረፍድ በጊዜ እራሳችንን ብንጠይቅ መልካም ነው።

በመጽሐፍ ቅዱሳችን ውስጥ ለንብረት ሳይሆን ለሰው ቅድሚያ የሚሰጥ አምላክ ነው ያለን። ከሰው ይልቅ ገንዘብ የሚወድ ከእግዚአብሔር አይደለም። ደሃ ጠል የሆነ የክርስትና የእምነት የለም።

ስለዚህ ለድሆች መቆረስ፣ ያለንን ማካፈል፣ በብዙ አይነት የሕይወት ትግል ውስጥ የሚያልፉትን ሰዎች ማገዝ የጌታ ልጆች መገለጫ ነው። ከአባታችን የወረስነውን እሴት በተሰጠችን ዘመን በመተግበር በመጨረሻው ቀን ተሸላሚ ከሚሆኑት ቅዱሳን መካከል እንድንገኝ ጌታ ይርዳን።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት፦ እግዚአብሔር ደሃ ጠል አምላክ አይደለም። እንዲያውም ለድሃው አባት፣ ተሟጋች፣ መጠለያ፣ ዳኛ፣ ተስፋና ታዳጊ ነው።

የዛሬው ፀሎት፦ጌታ ሆይ በቻልኩት አቅም ሁሉ ድሆችን እንድረዳ ያንተን ባህሪይ እንዳንፀባርቅ እርዳኝ። አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

16 Feb, 21:13


የሚቆረስ ሕይወት

35ኛ ሳምንት
1ኛ ቀን


"ደግሞም መልካም ማድረግንና ያላችሁንም ከሌሎች ጋር መካፈልን አትርሱ፤ እግዚአብሔር ደስ የሚሰኘው እንደዚህ ባለው መሥዋዕት ነውና።" ዕብ 13፥16

"እግዚአብሔር ሁለት እጆችን የሰጠን ባንዱ እንድንቀበል በሌላኛው ደግሞ እንድንሰጥ ነው" - ቢሊ ግርሃም

በዚህ ሳምንት ጌታ ቢፈቅድና ብንኖር እግዚአብሔር በአደራ የሰጠንን ማንኛውንም ነገር መስዋዕት በማድረግ በመቆረስ የመስጠትን ጣፋጭ ሕይወት እንነጋገራለን።

በመግቢያው ላይ ባለው ክፍል የዕብራውያን መልዕክት ጸሐፊ በመጨረሻው ምዕራፍ ውስጥ ካስቀመጣቸው አጫጭር መልዕክቶች መካከል አንዱ መልካም ማድረግና ከሌሎች ጋር ያለንን መካፈል እንዳለብን ነው።

ይህንንም ማድረግ በብሉይ ኪዳን ዘመን ለእግዚአብሔር ከሚቀርብ የአምልኮና የምስጋና መስዋዕት ጋር በማነጻጸር ያስቀምጣል።

ከእግዚአብሔር የተካፈልነው ሕይወት እንደ እቋሪ ውሃ ታጉሮ ደርቆ በስስት ባክኖ የሚቆም ሳይሆን እንደ ወራጅ ውሃ የሚያልፍበትን ሁሉ እያለመለመ የሚሄድ በልግስና ለሌሎች እየተቆረሰ የሚሄድ ሕይወት ነው።

አጠገባችን ላሉት ችግረኞች እንዲሁም በወንጌል አገልግሎት ላይ ለተሰማሩት የመንግሥቱ ሰራተኞች በልግስና መስጠት ከአባታችን የወረስነው በደማችን ውስጥ ያለ የማንነታችን መሰረት ነው። አንድ ልጁን የሰጠን አባት የወለደን፣ አንድ ነፍሱን የሰጠን ጌታ ያዳነን የፍቅር ልጆች ነን።

እግዚአብሔር የፈጠራቸው ፍጥረታት በሙሉ እንዲሰጡ አድርጎ ነው። ፀሐይ ሙቀትን እንድትሰጥ፣ ምድር ምርትን እንድታበቅል፣ ተክሎች ፍሬ እንዲያፈሩ፣ ላሞች ወተትን ንቦች ማርን እንዲሰጡ ተደርጎ ነው የተፈጠሩት። ነገር ግን ከሁሉ በላይ በእግዚአብሔር መልክና አምሳል እንደተፈጠረው የሰው ልጅ ስስታም ግን የለም።

በዳግም ልደት የመታደስ እድል ያገኘን ቅዱሳን በሙሉ በአስተሳሰባችን መለወጥ አለብን። ስስት የአሮጌው ሰው ባህሪይ ስለሆነ ጨክነን ማስወገድ አለብን።

የምንሰጠው የራሳችን የምንለው አንዳች የለንም። ሁሉን የተቀበልነው  ከእግዚአብሔር ነው። በእጃችን ላይ ላሉት ንብረቶች ባላደራዎች ነን። ይህም የንብረቱ ባለቤት ለፈለገው ዓላማ በሚፈልግበት ጊዜ ሁሉ የማዋል መብት አለው።

እግዚአብሔር በቅዱስ ቃሉ በተደጋጋሚ ካሳሰበን አንዱ የሰጠንን ንብረት ለተቸገሩት በልግስና እንድንሰጥ ነው።

ስጥ የሚለው ቃል ምክረ ሃሳብ ሳይሆን ግልፅ የሆነ ትዕዛዝ ነው "ለሚለምንህ ስጥ፥ ከአንተም ይበደር ዘንድ ከሚወደው ፈቀቅ አትበል።" ማቴ 5: 42

አውግስጢኖስ የተባለ ሰው የፍቅርን ምንነት ለማወቅ አንዱ ሰው ጓደኛውን ስለ ፍቅር ምንነት ጠይቆ ጓደኛው የመለሰለትን ነገር እንዲህ ብሎ ይነግረናል። "ፍቅር ለሌሎች የሚያካፍል እጅ፣ ድሆችና ችግረኞችን የሚጎበኝ እግር፣ በሰቆቃ ውስጥ ያሉት የሚያይ አይን፣ የሰዎችን የሰቆቃ ጩኸት የሚያዳምጥ ጆሮ ነው። ፍቅር እርሱን ይመስላል።"

ያለንን ነገር ማካፈል የክርስቶስን ፍቅር ለሰዉ ልጆች ሁሉ ከምናሳይበት አንዱና ዋነኛው ተግባር ነው። እግዚአብሔር ሲያበለጽገን የኑሮ ደረጃችንን ከፍ እንድናደርግ ሳይሆን የመስጠት መጠን እንድንጨምር ነው።

ስለዚህ ያለችንን ምድራዊ ሃብት ለሌሎች በማካፈል የሚጠፋውን ጊዜያዊ ንብረት ወደ ዘላለማዊ ጥሪት እንድንለውጥ እግዚአብሔር ማስተዋሉን ያብዛልን።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት፦ የንብረቴ ሁሉ ባለቤት እግዚአብሔር ነው። እኔ ባላደራ ብቻ ነኝ።

የዛሬው ፀሎት፦ጌታ ሆይ ከቸርነትህ የተካፈልኩትን ጠፊ ሃብት በማካፈል በሰማይ ዘላለማዊ ጥሪት ማከማቸት እንድችል ማስተዋል ስጠኝ" አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

15 Feb, 21:04


መንፈሳዊ ዕድገት

34ኛ ሳምንት
7ኛ ቀን


"በድነታችሁ እንድታድጉ፣ አዲስ እንደ ተወለዱ ሕፃናት ንጹሑን መንፈሳዊ ወተት ተመኙ፤" 1ኛ ጴጥ 2: 2

ሐዋርያው ጴጥሮስ በዚህ ደብዳቤ ውስጥ በስደት ላይ ያሉ አማኞች በመንፈሳዊ ሕይወታቸው እንዲያድጉና በመከራቸው ጸንተው በመቆም የተዘጋጀላቸውን ተስፋ እንዲቀበሉ እያበረታታቸው ነው።

በዋናነትም ዳግም የተወለዱበትን የማይጠፋውን የእግዚአብሔርን ቃል በማስታወስ ያንኑ ቃል እንደ መንፈሳዊ ምግብ እየተመገቡት በድነታቸው እንዲያድጉ እያዘዛቸው፤ በመጨረሻም ዳግም ልደት የሰጣቸውና ተመግበው ያደጉበት ቃል የሚሰጠውን እረፍት ለመውረስ ተስፋ እያደረጉ እንዲኖሩ ይመክራቸዋል።

የእግዚአብሔር ቃል ለአማኞች የዳግም ልደት ዘራቸው እንዲሁም በአዲስ ልደት ላገኙትም ሕይወት ምግባቸው መሆኑን በአጽንኦት ይነግራቸዋል። አማኝ ከጌታ ቃል ወጪ ሕይወትም፣ ዕድገትም ፍጻሜም የለውም።

ወንድማችን ጴጥሮስ እንደ ጥሩ የሕጻናት ሃኪም በክርስቶስ ኢየሱስ በማመን ዳግም የተወለዱት አማኞች ምን መመገብና ምን መተው እንዳለባቸው በጥንቃቄ ይመክራቸወል።

ለማደግ መመገብ ብቻ ሳይሆን መንፈሳዊ ዕድገትን የሚያቀጭጩ ነፍስን የሚያረክሱ መርዛማ ምግቦችን ያለመመገብም እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ይገልጻል።

እነርሱም እንዲህ ይዘረዝራቸዋል "ክፋትን ሁሉ፣ ማታለልን ሁሉ፣ ግብዝነትን፣ ቅናትንና ሐሜትን ሁሉ አስወግዱ።" (1ጴጥ 2፥1)

እነዚህ ርዝራዥ ባህሪያት ባልተለወጠው አዳማዊ ማንነታቸው ውስጥ ተሰግስገው ሊኖሩ ስለሚችሉ ጨክነው እንዲያስወግዱ ያዛቸዋል። ካልሆነ ግን በጭራሽ ማደግ አንደማይችሉ ያሳስባቸዋል።

አንዳንድ ጊዜ ያገኙትን እያግበሰበሱ የመመገብ አመል ያለባቸው ከብቶች ድንገት ፌስታል አልያም ልብስ ይውጣሉ ያው ባዕድ ነገር በሆዳቸው ውስጥ ሳይፈጭ ዘቅጦ ይቀራል አልያም በጨጓራቸው ውስጥ ተወትፎ የአመጋገብ ስርዓታቸውን ያዛባል።

ብዙ ጊዜ ያልተገባ ነገር የዋጡ ከብቶች አይወፍሩም መልካቸውም ይቀየራል አንዳንዴም ይፈዛሉ ባጠቃላይ ጤናማ አይሆኑም።

እንደዚህ አይነት የጤና መቃወስ የጀመራቸው ከብቶች ወደ ባሰ ችግር ሳይገቡ ቶሎ ይታረዳሉ ከዚያ በጨጓራቸው ውስጥ ጨርቅ፣ ፌስታል ተወትፎ ይገኛል። ይህንን ብዙ ጊዜ አይቻለሁ።

ይህ ክስተት በአማኞችም መንፈሳዊ ሕይወት ላይ በጉልህ የሚታይ እውነት ነው። የኃጢአት ልምምድ ያላቸው፣ እግዚአብሔር የማይፈልገውን ሸሽገው በውስጣቸው የሚያቆዩ፣ በየቀኑ ልክ ያልሆነ የተመረዘ ምግብ የሚመገቡ አማኞች በክርስትናቸው ማደግ አይችሉም።

ሐዋርያው ጴጥሮስ ለሁላችንም የሚጠቅም ግልጽ የሆነ ምክር አስቀምጦልናል። ለማደግ የማይገባውን ባህሪይ አስወግደን መንፈሳዊ ምግብ የተባለውን የእግዚአብሔርን ቃል በስርዓት መመገብ እንዳለብን አሳስቦናል።

የዚህን ሳምንት ጥናት ዛሬ እየቋጨን ነው። በእግዚአብሔር መንግስት ውስጥ ዳግም ለተወለደ አማኝ ሁሉ ማደግ ግዴታው  መሆኑን በሚገባ መገንዘብ አለበት። የማያድግ አማኝ ወይ ጭራሹኑ ዳግም አልተወለደም አልያም ከሞተ ሰንብቷል ማለት ነው።

ወዳጆቼ! ክርስትናን የመሰለ ከእግዚአብሔር ቃል የተገኘ ሕይወት ያለበት፣ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል የሚመራ፣ በክርስቶስ ፀጋ የታጀበ ኃይማኖት ይዘን የቀጨጨ፣ ልፍስፍስና ድንክዬ ማንነት ይዞ መኖር እጅግ የሚያሳፍር ነው።

ፈጥነን መንቃት ይሁንልን። በልባችን ውስጥ ተሰንቅሮ እንዳናድግ ያደረገንን ኃጢአት በቃሉ ብርሃን ፈትሸን ጠርገን ማስወገድ እንድንችል ጌታ ይርዳን።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት፦ በመንፈሳዊ ሕይወት ለማደግ የማይገባውን ባህሪያት ማስወገድና የቃሉን ወተት እየተመገቡ መኖር ግድ ነው።

የዛሬው ፀሎት፦ እግዚአብሔር ሆይ በተወለድኩበት ሕይወት ውስጥ የማድግበት ግብዐት ሁሉ ቀርቦልኝ ያንን ሳልጠቀም ቀርቼ በሕጻንነት እንዳልኖር እባክህ አንቃኝ። ቃልህን እንድመገብ እርዳኝ። አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

14 Feb, 21:12


መንፈሳዊ ዕድገት

34ኛ ሳምንት
6ኛ ቀን


"ወንድሞች ሆይ፤ በአስተሳሰባችሁ ሕፃናት አትሁኑ፤ ለክፉ ነገር ሕፃናት ሁኑ፤ በአስተሳሰባችሁ ግን ጐልማሶች ሁኑ።" 1ቆሮ 14: 20

የቆሮንቶስ ቤተክርስቲያን በፀጋ ስጦታ የተንበሸበሸች ሕብረት ብትሆንም በመንፈሳዊ ብስለት ረገድ ግን ብዙ የሚቀራት መሆኑን ሐዋርያው ጳውሎስ በተደጋጋሚ ከሚገስጻቸው ንግግሮች መረዳት ይቻላል።

በተለይ በቆሮንቶስ ከተማ በሚኖሩት አማኞች መካከል የተገለጠው የመንፈስ ቅዱስ ስጦታ እጅግ የሚገርም ነበር። ሆኖም ግን ፀጋው የተገለጠባቸው አማኞች የስጦታውን ዓላማና አጠቃቀም የተገነዘቡ አይመስልም።

ሐዋርያው ጳውሎስ ከፀጋ ስጦታ አጠቃቀም ጋር በተገናኘ ብዙ  አገልጋዮች ብስለትና ማስተዋል ሲጎድላቸው በማየቱ ሕጻናት አትሀኑ በማለት ይመክራቸዋል።

እግዚአብሔር የፀጋ ስጦታን የሚሰጠው ለበሰሉት አማኞች መርጦ ሳይሆን ሥጦታውን ለመቀበል ፈቃደኛ ለሆኑት ልጆቹ ሁሉ ነው። ሥጦታውን ከተቀበሉ በኋላ ሕጻናት ሆኖ በመቆየት ፀጋውን ያላግባብ መጠቀም ወይም እየበሰሉ በማደግ ለብዙዎች በረከት መሆን ግን የአገልጋዩ ምርጫ ነው።

የሕጻናት መገለጫ የተቀበሉትን የመንፈስ ቅዱስ ስጦታ ምንነት፣ ዓላማና አጠቃቀም ያለ ማወቅ ነው። ይህ በራሱ ችግር አይደለም። ችግሩ ከስህተት ላለ መታረም፣ ላለመማር፣ ላለመሰልጠንና ላለማደግ ያለ መፈለግ ነው።

ያልበሰሉና ሕጻናት የሆኑ አገልጋዮች ሥጦታቸውን ኃላፊነት በጎደለው ሁኔታ ሲጠቀሙ ጉባዔውን ከማነጽ ይልቅ የሚጎዳ ይሆናል። በምድራችንም ባለች ቤተክርስቲያን ውስጥ ለምናየቸው ውጥንቅጦች አንዱ ምክንያት ሕጻናት ሆነው በመቆየት የፀጋ ስጦታቸውን ያለ አግባብ በሚጠቀሙ ሰዎች ነው።

የበሰሉ አገልጋዮች የተሰጣቸውን የፀጋ ሶጦታ ምንነት፣ አጠቃቀምና እንዴት በሥራ ላይ ማዋል እንዳለባቸው በሚገባ ያውቁታል። የአገልግሎታቸው መሪ እሴት ፍቅር በማድረግ ከራሳቸው ይልቅ ለመንጋው ቅድሚያ በመስጠት በትህትና ያገለግላሉ።

ለራሳቸው ክብር፣ ዝና ታዋቂነትና ጥቅም በጭራሽ የማያስቡ ናቸው። ከዚያ ይልቅ ለክርስቶስ አካል ግንባታ ማንኛውንም መስዋዕት በመክፈል የሚያገለግሉ ናቸው።

የበሰሉ ሰዎች ሌላኛው መገለጫ አገልግሎታቸው የወንጌል መልዕክት ባላመኑ ሰዎች ዘንድ ብዥታ በማይፈጥር መንገድ ኩልል ቡሎ እንዲደርስ ማድረግና ደካሞችን በማያሰናክል መልክ በትልቅ ጥበብ ማቅረባቸው ነው።

ወገኖቼ ከሁሉ በላይ መታሰብ ያለበት የመንፈሳዊ ሕይወት ዕድገት መለኪያው በሕይወታችን በተገለጠው የፀጋ ስጦታ መጠን ሳይሆን ለቃሉ ባለን የመታዘዝ ልክ መሆኑ ነው።

ስለዚህ የመንፈሳዊ ሕይወት ዕድገት ከፀጋ ሥጦታችን አጠቃቀም ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ስላለው እግዚአብሔር ለእድገት የሰጠንን ማንኛውንም ዕድል ተጠቀመን ወደ ብስለት እንድናድግ ጌታ ይርዳን።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት፦ የፀጋ ስጦታን በአግባቡ ለመጠቀም በመንፈሳዊ ሕይወት ማደግ በጣም አስፈላጊ ነው።

የዛሬው ፀሎት፦ እግዚአብሔር ሆይ ልጅህ በመሆኔ ምክንያት ደግሞም ለቤተክርስቲያን መታነጽ የተሰጠኝን የፀጋ ስጦታ ሕጻን ሆኜ በመቆየት እንዳላበላሸው እርዳኝ። አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

13 Feb, 21:23


መንፈሳዊ ዕድገት

34ኛ ሳምንት
5ኛ ቀን


በውስጥ ሰውነታችሁ እንድትጠነክሩ፣ ከክብሩ ባለጠግነት በመንፈሱ በኩል ኀይል እንዲሰጣችሁ እጸልያለሁ፤  ኤፌሶን 3፥16

ሐዋርያው ጳውሎስ ለኤፌሶን አማኞች በአብ ፊት በመንከርከክ በብርቱ እንደሚጸልይላቸው ይነገርላቸዋል። ከሚጸልይላቸው ጉዳዮች አንዱ በውስጥ ሰውነታቸው እንዲጠነክሩ ነው።

የውስጥ ሰውነት የሚለው በዳግም ልደት ያገኘነውን ማንነታችንን የሚያሳይ ነው። ይህ የውስጥ ሰውነት ልክ እንደ ሕጻን ልጅ ለማደግ ትኩረትና እንክብካቤ የሚፈልግ ነው።

የውስጥ ሰውነታችንን እንዲያድግ ከሚያደርገው ተግባር መካከል አንዱ ፀሎት ነው። ፀሎት ከመንፈስ ቅዱስ ዘንድ ለመንፈሳዊ ሕይወት ግንባታ የሚጠቅመውን ኃይል የምንቀበልበት ትልቁ መስመር ነው።

መንፈሳዊ እድገት ከእግዚአብሔር ዘንድ የሚሰጥ እንጂ በራሳችን ጥረት የምናመጣው ጉዳይ አይደለም። ፀሎት ደካማ መሆናችንን በማመን በእግዚአብሔር ጥንካሬ ላይ ለመደገፍ ፈቃደኝነታችንን የምናሳይበት ጥበብ ነው

ደካማ መሆናችንን በተረዳን ልክ በእግዚአብሔር ላይ መደገፋችን ይጨምራል። በእግዚአብሔር ላይ መደገፋችን በበዛ ልክ የውጭ ሰውነታችን እያረጀ ቢመጣም እንኳ በመንፈሳዊ ሕይወታችን እያደግን እንዲሁም እየታደስን እንሄዳለን።

ስለዚህ ጸሎት ያለ መንፈስ ቅዱስ እገዛ ምንም ማድረግ እንደማንችል በማመን ለእግዚአብሔር ፈቃድ እራችንን የምናስረክብበት መሰዊያ ነው።

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ወደ አባቱ ሊመለስ ሲል ለደቀመዛሙርቱ የጸለየው አባቱ የኃልይ ምንጭ የሚሆናቸውን መንፈስ ቅዱስን እንዲሰጣቸው ነበር።

ዛሬም ላለን አማኞች ውስጣችን በኃይል እንዲጠነክር ሌላ አማራጭ የለንም። በጸሎት አማካኝነት ከመንፈስ ቅዱስ ኃይልን መቀበል ብቻ ነው።

ወዳጆቼ ! እድገትም ኃይልም ያለው ከመንፈስ ቅዱስ ዘንድ ብቻ ነው። መንፈስ ቅዱስን የተሞላ ሰው ልፍስፍስ መሆን አይችልም። ይህንን እርግጠኛ ልንሆን ይገባናል።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት፦ ለመንፈሳዊ ሕይወት እድገት የሚሆን ብቸኛው የኃይል ምንጭ መንፈስ ቅዱስ ነው።

የዛሬው ፀሎት፦ እግዚአብሔር አባት ሆይ በውስጥ ሰውነቴ እንድጠነክር፣ ከክብርህ ባለጠግነት በመንፈስህ በኩል ኀይል እንዲሰጠኝ እለምንሃለሁ። አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

12 Feb, 21:53


መንፈሳዊ ዕድገት

34ኛ ሳምንት
4ኛ ቀን


በእርሱ ሕንጻ ሁሉ አንድ ላይ ተገጣጥሞ በጌታ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንዲሆን ያድጋል። እናንተም ደግሞ እግዚአብሔር በመንፈሱ የሚኖርበት ማደሪያ ትሆኑ ዘንድ አብራችሁ እየተገነባችሁ ነው። ኤፌ 2፥21-22

ሐዋርያው ጳውሎስ ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ኢየሱስ ላይ የምትገነባ እግዚአብሔር በመንፈሱ የሚኖርበት መንፈሳዊ ቤተመቅደስ አድርጎ በሕንፃ ግንባታ አስመስሎ ይናገራል።

ይህ ክፍል አህዛብና አይሁድ በክርስቶስ ውስጥ አንድ በመሆን የተጠሩበትን እውነትና እንደ አንድ ሕንፃ በጋራ እየተገነቡ መሆናቸውን የሚናገር ነው።

አማኞች በግላችን የማደግ ጥሪና ኃላፊነት ቢኖርብንም የቤተክርስቲያን አካል እንደ መሆናችን መጠን ደግሞ ከሌሎች ቅዱሳን ጋር በአብሮነት ማደግ እንዳለብን ተነግሮናል።

ቤተክርስቲያን የግለሰቦች ልዩ ችሎታ፣ ፀጋ፣ ብቃት በተለየ ሁኔታ የሚታይበት የመደናነቂያ መድረክ ሳትሆን አማኞች በሙሉ በሕብረት በመገንባት የክርስቶስ ማደርያ ለመሆን የሚያድጉበት ቤት ነች።

እንደ ቤተክርስቲያን በጋራ መገንባት እጅግ አስፈላጊ ጉዳይ ነው። ቅዱሳን በየጊዜው እየተገናኘን ፀጋን በመከፋፈል፣ በመተናነጽ፣ አንዳችን ለሌላችን በመጸለይ አብረን ማደግ አለብን።

ከሕንፃ አጠቃላይ ንድፍ ውጪ ያለ ድንጋይ ለቤቱ እንደማያስፈልግ ሁሉ ከቤተክርስቲያን አካል ውጪ መሆን የሚፈልግ ሰውም ብቻውን በመንፈሳዊ ሕይወቱ በጭራሽ ጤናማ ዕድገት ሊኖረው አይችልም።

የተጠራነው ወደ ሕብረት እንጂ ወደ ግለኝነት አይደለም። የሀገራችን ሰዎች "ቀድማ የወጣች እሸት አንድም ለወፍ አንድም ለወንጭፍ እንደሚሉት ነው። "ከቅዱሳን ሕብረት ያፈነገጡ ሰዎች ለብዙ አደጋ ይጋለጣሉ።

መንፈሳዊ ሕይወት የሕብረት ሕይወት ነው። መንፈሳዊ ዕድገትም የጋራ እድገት ነው። በዚህ ዘመን ብዙ አማኞች ታማሚዎች፣ እንክብካቤ የሚፈልጉ፣ ሕጻናት ከመሆናቸው የተነሣ ቤተክርስቲያንን ከተዋጊ ሰራዊትነት በሆስፒታል ውስጥ ወዳሉ ታካሚዎች ቀይረውታል።

እንደ ቤተክርስቲያን በጋራ በማደግ ላይ ተግተን በመስራት ፣ የደቀመዛሙርነት ሕይወት በመገንባት፣ የፀሎት ባህል እያዳበርን፣ የቅዱስ ቃሉ ቋሚ ቀለብተኞች እየሆንን፣ የምጻቱ ናፋቂዎች በመሆን ዘመናችንን እንድንጨርስ ጌታ ይርዳን።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት፦  መንፈሳዊ ሕይወት የሕብረት ሕይወት ነው። መንፈሳዊ ዕድገትም የጋራ እድገት ነው።

የዛሬው ፀሎት፦ እግዚአብሔር ሆይ በመንፈስህ በኩል በመካከላችን እንድታድር መንፈሳዊ ቤት ለመሆን ከቅዱሳን ጋር በሕብረት እንድንገነባ እርዳን። አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

11 Feb, 21:13


መንፈሳዊ ዕድገት

34ኛ ሳምንት
3ኛ ቀን


ነገር ግን በጌታችንና በአዳኛችን በኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ዕውቀት እደጉ፤ ለእርሱ አሁንም፣ ለዘላለምም ክብር ይሁን፤ አሜን።" —2ኛ ጴጥሮስ 3: 18

ሐዋርያው ጴጥሮስ ለተቀበለው የወንጌል አደራ ሰማዕት ሆኖ የሚሄድበት ጊዜ መቅረቡን በመረዳት የመጨረሻ መልዕቱን በትንሿ ኤስያ ውስጥ ተበታትነው ላሉት ቅዱሳን ይልካል።

በጎቼን ጠብቅ ያለውን የጌታን ትዕዛዝ በማሰብ የእረኝነቱን አደራ ለመወጣት አማኞች ከሐሰተኛ አስተማሪዎችና ነቢያት እንዲጠነቀቁ ያሳስባቸዋል።

በስህተት ውስጥ ላለ መውደቅ ትልቁና ዋነኛው መፍትሔ በኢየሱስ ክርስቶስ አማካኝነት ባገኙት ፀጋና እውነት ማደግ መሆኑን አበክሮ ይነግራቸዋል።

ፀጋ ድነትን ያገኘንበት ብቻ ሳይሆን ባገኘነው አዲስ ሕይወት ውስጥ ለማደግ የሚረዳ ግብዐት ነው። በፀጋ ማደግ ማለት ከእግዚአብሔር ዘንድ በሚመጣ ኃይል፣ ሞገስ፣ ሕይወት፣ ብስለት ውስጥ ዕለት ዕለት መጨመር ማለት ነው።

በኢየሱስ ክርስቶስ እውቀት ማደግ ማለት በመገለጥ የበራልንን ኢየሱስን በቃሉ አማካኝነት በመንፈስ ቅዱስ አስተማሪነት ዕለት ዕለት እየተረዳነው መሄድ ማለት ነው።

ኢየሱስን ማወቅ በአእምሮ የመበልፀግ ጉዳይ ሳይሆን እንደ ልጅና አባት በፀሎት የመነጋገር ለቃሉ በመገዛት እየታዘዝን የመኖር ጉዳይ ነው።

ስቴፈን ካርኖክ የተባለ አገልጋይ እንዲህ ይላል "አንድ ሰው በሥነ መለኮታዊ ትምህርት ምሁር ሆኖ በመንፈሳዊ ሕይወቱ ዝንጉ ሊሆን ይችላል"

ሐዋርያው ጴጥሮስ አማኞች በክርስትና ሕይወታቸው በማደግ በዘመናቸው ከተነሱት የሐሰት አስተማሪዎችና ነቢያት እንዲጠበቁ ያሳስባቸዋል።

በአጠቃላይ በመንፈሳዊ ሕይወቱ ሕጻን ሆኖ የሚቆይ ሰው ጳውሎስ እንደ ተናገረው በማዕበል ወደ ፊትና ወደ ኋላ እየተነዳ፣ በልዩ ልዩ ዐይነት የትምህርት ነፋስ፣ በሰዎችም ረቂቅ ተንኰልና ማታለል ወዲያና ወዲህ እየተንገዋለለ ለመኖር ይገደዳል። (ኤፌ 4፥14)

ወገኖቼ እግዚአብሔር አምላካችን በምድር ላይ ያለችንን ቀሪ ዕድሜ የማደጊያ ጊዜ ያድርግልን።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት፦ በፀጋና በእውቀት ማደግ ከስህተት ትምህርትና ትንቢት የምንጠብቅበት መንገድ ነው። 

የዛሬው ፀሎት፦ እግዚአብሔር ሆይ በልጅህ በክርስቶስ ኢየሱስ አማካኝነት ባገኘሁት ፀጋና እውነት ውስጥ ዕለት ዕለት እንዳድግ እርዳኝ። አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

10 Feb, 21:18


መንፈሳዊ ዕድገት

34ኛ ሳምንት
2ኛ ቀን


"በዚህ ጊዜ አስተማሪዎች ልትሆኑ ሲገባችሁ፣ ገና የእግዚአብሔርን ቃል የመጀመሪያ ትምህርት የሚያስተምራችሁ ሰው ያስፈልጋችኋል፤ የሚያስፈልጋችሁም ጠንካራ ምግብ ሳይሆን ወተት ነው።"—ዕብ 5: 12

ለዕብራውያን ሰዎች የተላከው ደብዳቤ የክርስቶስ ብልጫና በቂነት ደብዝዘውባቸው ወደ ቀድሞ የብሉይ ኪዳን ስርዓት ለመመለስ ወደ ኋላ እየተንሸራተቱ ያሉትን አማኞች የሚሸነቁጥ የግሳ ጼ መልዕክት ነው።

የዕብራውያን አማኞች በጌታ ቤት ውስጥ ያሳለፉት ዘመንና የመንፈሳዊ ሕይወት ዕድገታቸው የማይመጣጠን ነበር። በጌታ ካመኑ በኋላ የነበራቸው ቆይታ አስተማሪ መሆን እንዳለባቸው ሲናገር ሕይወታቸው ግን ገና መሰረታዊ ትምህርት እንኳን በአግባቡ መማር የማይችሉ መሆናቸውን ያሳያል።

አማኞች በምድር ላይ የተሰጣቸውን የለውጥ ዘመን የማባከን መጥፎ ልምድ ካዳበሩ ፣ እግዚአብሔር ባህሪያቸውን ለመስራት በችግር ውስጥ ሲያሳልፊን በማጉረምረም ሲያበላሹት፣ እውነትን የሚነግሯቸውን አገልጋዮች በመግፋት የልባቸውን ምኞት የሚያወሯቸውን እኩይ አገልጋዮች መስማት ሲመርጡ መንፈሳዊ ሕጻናት ሆነው ለመሰንበት ይገደዳሉ።

በመንፈሳዊ ሕይወት ሕጻን ሆኖ መቆየት እውነትን ከመረዳት ያጎድላል፣ በተለያዩ የስህተት ትምህርቶች ለመወሰድ ይዳርጋል፣ ወደ ኋላ ለማፈግፈግ ያጋልጣል፣ አልፎም የነፍሳቸው መዳረሻዎችን ሊያስቀይር ይችላል።

ወገኖቼ የማደግ ተቃራኒ አለማደግ ሳይሆን መበስበስና መሞት ነው። ሕይወት ያለው ፍጥረት ያድጋል እድገት አከተመ ማለት ሞት ተጀመረ ማለት ነው። ግሪጎሪ ማክዶናልድ "ወደ እግዚአብሔር የማያድግ ወደ መበስበስ ያድጋል" ብሏል።

የእግዚአብሔር ልጆች ተደርገን፣ የኢየሱስ ክርስቶስን ፀጋ ተቀብለን፣ የመንፈስን ቅዱስን ኃይል ተሞልተን፣ ሕይወት ለዋጭ የሆነውን ቅዱስ መጽሐፍ እያነበብን በመንፈሳዊ ሕይወታችን ያለ ማደግ በምድር ላይ ትልቁ አሳዛኝ ነገር ነው።

ስለዚህ ከገባንበት ከመቀጨጭና ከመቀንጨር ሕይወት በመውጣት ወደ ዕድገት ጎዳና ፈጥነን እንድንመለስ እግዚአብሔር ያንቃን፣ ፀጋው ይብዛልን።

እግዚአብሔር ያየልንን ክርስቶስን የመምሰል የመንፈሳዊ ሕይወት ዕድገት ጥግ ጋር ለመድረስ ቆራጥ ውሳኔ በማድረግ አሁን እንድንነሳ ጌታ ይርዳን።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት፦ የማደግ ተቃራኒ አለማደግ ሳይሆን መበስበስና መሞት ነው።

የዛሬው ፀሎት፦ እግዚአብሔር ሆይ ለመንፈሳዊ ሕይወት ዕድገት እንዲሆን የሰጠኸን ዕድል ነቅቼ እንድጠቀምበት እርዳኝ። አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

09 Feb, 21:07


መንፈሳዊ ዕድገት

34ኛ ሳምንት
1ኛ ቀን


"ማደግህ በነገር ሁሉ እንዲገለጥ ይህን አስብ፥ ይህንም አዘውትር።" 1ኛ ጢሞ 4:15

"የእግዚአብሔር ፍቃድ በሕይወታችሁ ምን እንደሆነ ማወቅ ትፈልጋላችሁ? ክርስቶስን ወደ መምሰል እንድታድጉ ነው!!! የመንፈሳዊ ሕይወት ብስለት ጥጉ እርሱ ነው" ቢሊ ግርሀም

በዚህ ሳምንት ጌታ ቢፈቅድና ብንኖር ስለ መንፈሳዊ ሕይወት ዕድገት እናጠናለን። መንፈሳዊ ዕድገት የሚለው ሃሳብ በአዲስ ኪዳን ውስጥ በውስጠኛው ማንነት መጠንከር፣ ክርስቶስን ወደ መምሰል መለወጥ፣ መብሰል፣ ወደ ፍጹምነት መጠጋት፣ በመረዳት ባለጠጋ መሆንና በመሳሰሉት ቃላት ተገልጿል።

መንፈሳዊ ዕድገት ከዳግም ልደት በኋላ የሚመጣ ጉዳይ ነው። ያልተወለደ ስለማያድግ አማኝ ነኝ የሚል ማንኛውም ሰው ስለ መንፈሳዊ ዕድገት ከማሰቡ በፊት ስለ ዳግም ልደቱ እርግጠኛ መሆን መቻል አለበት።

በተለይ ብዙ ነገሮች በተደበላለቁበት በዚህ ዘመን ለዘመናት በቤተክርስቲያን ውስጥ እየኖሩ የመንፈሳዊ ሕይወት ዕድገት መገለጫ የሆነው የመንፈስ ፍሬ የማይታይባቸው አማኞች በበረከቱበት ጊዜ ስለ መንፈሳዊ ሕይወት ዕድገት በግልጽ መነጋገር አንገብጋቢ ጉዳይ ነው ብዬ አምናለሁ።

ከቤተክርስቲያን አባቶች የአርዮስን የስህተት ትምህርት በመመከት የሚታወቀው አትናቴዎስ ስለ መንፈሳዊ ዕድገት ከተማሪዎቹ አንዱ ለሆነው ለአንቶኒ እንዲህ ብሎ ነው ያስተማረው "መንፈሳዊ ዕድገት ከእግዚአብሔር ሕይወትን ከመካፈል የሚጀምር ጉዞ ሆኖ ሙሉ ለሙሉ ማንነታችንን ለእርሱ በማስገዛትና በቅድስና መኖር የሚያጠቃልል ነው" ይላል።

መንፈሳዊ እድገት በምኞት የሚመጣ ነገር አይደለም። ማደግ ከተፈለገ ማንኛውንም ዋጋ ከፍለን መንፈሳዊ ሕይወታችንን ከከፋ አደጋና ሞት መታደግ አለብን።

መንፈሳዊ እድገት የእግዚአብሔርን ፈቃድ ሳናመቻምች እየታዘዝን በመኖር እንጂ በአገልግሎት ቆይታና በቤተክርስቲያን ውስጥ ባለን ኃላፊነት የሚመጣ ስላይደለ እንዳንታለል መጠንቀቅ አለብን።

ወዳጆቼ! በመንፈሳዊ ሕይወታችን ሳናድግ እንዳናረጅ እግዚአብሔር ፀጋውን ያብዛልን በምህረቱም ከመቀንጨርና ከመቀጨጭ ሕይወት ያውጣን።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት፦እድገት ከዳግም ልደት ቀጥሎ የሚመጣና የመንፈሳዊ ሕይወታችን ሕያውነትና ጤናማነት ዋነኛው ማረጋገጫ ነው።

የዛሬው ፀሎት፦እግዚአብሔር ሆይ በመንፈሳዊ ሕይወቴ የሚያሳድገኝን ሙሉ ግብዐት ስለ ሰጠኸኝ አመሰግንሃለሁ። እነዚህን በአግባቡ ተጠቅሜ ዕለት ዕለት ክርስቶስን ወደ መምሰል እንድለወጥ አግዘኝ" አሜን!   

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

09 Feb, 00:03


ሙያህ ጥሪህ ነው

33ኛ ሳምንት
7ኛ ቀን


"ስድስት ቀን ሥራ፤ በሰባተኛው ቀን ግን ዕረፍ፤ በዕርሻና በመከር ወቅት እንኳ ቢሆን ማረፍ አለብህ።" ዘፀ 34፥21

"ማረፍ ስራ መፍታት አይደለም። ነገር ግን የሚያኖረን ሥራችን ሳይሆን እግዚአብሔር መሆኑን የምናስብበት የተቀደሰ የጥሞና ጊዜ ነው እንጂ" ጆን ማርከ ኮመር

አንድ አዲስ ማሽን ሲሰራ የፈጠራው ባለቤት እቃው ሳያቋርጥ ምን ያህል መስራት እንደሚችልና ምን ያህል ሰዓት ማረፍ እንዳለበት በአጠቃቀም መመሪያው ላይ ይጽፋል።

እግዚአብሔርም ሰውን ሲፈጥረው በቀንና በሳምንት ውስጥ ምን ያህል ጊዜ መስራትና ማረፍ እንዳለበት ግልጽ አድርጎልናል።

ቀናችንን በፀሐይ ብርሃን መርቆ ሲከፍትልን አሁን ወደ ሥራ ተሰማሩ እያለን ማታ ደግሞ ጨለማው በተራው ሲነግስ አሁን የአራዊቶች ተራ ስለ ሆነ እናንተ ወደ ቤታችሁ ገብታችሁ እረፉ ማለቱ ነው።

የሰው ልጅ ፍላጎቱን መግታት ተስኖት በቀን ሰርቶ ከማረፍ ይልቅ የሌሊቱንም ሰዓት ሲባትልበት ያሰበውን ያህል ወጤታማ ከመሆን ይልቅ እራሱን በብዙ ስቃይ ወግቶ እያቃሰተ ሲኖር በገሃድ እያየን ነው።

እንኳን ሰው ይቅርና ትደክማለች ብለን የማናስባት ምድር እንኳን ፈጣሪዋ ማረፍ እንዳለባት እንዲህ በማለት ተናግሯል።

ለእስራኤላውያን እንዲህ ብለህ ተናገር፤ ‘ወደምሰጣችሁ ምድር በምትገቡበት ጊዜ ምድሪቱ ራሷ የእግዚአብሔርን ሰንበት ታክብር። ስድስት ዓመት በዕርሻህ ላይ ዝራ፤ ስድስት ዓመት ወይንህን ግረዝ፤ ፍሬውንም ሰብስብ። በሰባተኛው ዓመት ግን ምድሪቱ የዕረፍት ሰንበት ታድርግ፤ ይህም የእግዚአብሔር ሰንበት ነው። በዕርሻህ ላይ አትዝራ፤ ወይንህንም አትግረዝ።
ዘሌ 25፥2-4

እግዚአብሔር ብታርፉ ይሻላል የሚል አማራጭ ሃሳብ ሳይሆን እረፉ የሚል ግልጽ ትዕዛዝ ነው የሰጠን። ለመሆኑ ለምንድነው እግዚአብሔር ማረፋችንን የፈለገው ያልን እንደሆነ፦

አንደኛና ዋነኛው ምክንያት እግዚአብሔር እረፉ ብሎ ስላዘዘን። እግዚአብሔር አድርጉ ያለንን ነገር የምንፈጽመው በገባን፣ ባመንበትና ደስ ባለን ልክ ሳይሆን የእግዚአብሔር ትዕዛዝ በመሆኑ ብቻ መሆን አለበት።

ሁለተኛው ምክንያት ሰንበት አካላዊ እረፍት ብቻ ሳይሆን መንፈሳዊ ተሃድሶ የምናደርግበት ውድ ጊዜ በመሆኑ ነው። በተጨማሪ የማያልፍ የዘላለም ሰንበት በሰማይ እንደ ቀረልን የምናስብበት ቀን ነው።

ሌላኛው ምክንያት የምንኖረው በጥረታችን ልክ ሳይሆን በእግዚአብሔር አቅርቦት ልክ መሆኑን ለመረዳት ስለሚያስችለን።

ሰንበት የተወደደ ቀን ነው። መለኮት ከስራው ያረፈበትና ልጆቹም የእርሱን ፈለግ በመከተል እንዲያርፉ ያዘዘበት ውድ ጊዜ ነው።

ስለዚህ ያረፈና የሚያሳርፍ አምላክ እያመለክን በመቅበዝበዝ ዘመናችን እንዳያልፍ ጌታ ይርዳን።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት፦ እረፍት የግምገማ፣ የኃይል ማደሻ፣ ከሌሎች ልምድ የመቅሰሚያ፣ መመሪያ የመቀበያ፣ የሞራል የማደሻ ጊዜ ነው።

የዛሬው ፀሎት፦ እግዚአብሔር ሆይ ያረፍከውን አባት አንተን እያመለኩ እየተቅበዘበዝኩ የምኖር ልጅህ እንዳልሆን እርዳኝ። አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

08 Feb, 00:12


ሙያህ ጥሪህ ነው

33ኛ ሳምንት
6ኛ ቀን


እናንተ ግን ወንድሞች ሆይ፤ መልካም ሥራን ከመሥራት ከቶ አትታክቱ። 2ተሰ 3፥13

ለተሰሎንቄ ሰዎች በተጻፉት ደብዳቤዎች ውስጥ አማኞችን ለክርስቶስ ዳግም ምጻት የማዘጋጀት መልዕክቶች ይገኛል።

ሐዋርያው ጳውሎስ በመጀመሪያው መልዕክቱ አማኞች ለንጥቀት መዘጋጀት እንዳለባቸው ሲያሳስባቸው የተሰሎንቄ ሰዎች በተሳሳተ ሁኔታ በመረዳት ጌታ በቅርቡ የሚመጣ ከሆነ ለምንድነው የምንሰራው የሚል ጠማማ አስተሳሰብ ውስጥ ገቡ።

ይህ መረጃ እንደ ደረሰው ጳውሎስ ሁለተኛውን መልዕክት በመላክ አማኞች ለንጥቀት የሚዘጋጁት ሥራ ፈት ሆነው በስንፍና በመያዝ ሳይሆን በትጋት በመስራት እንደሆነ አስጠነቀቃቸው።

አንዳንዶች ሥራ በመፍታታቸው ምክንያት ስንፍና የነገሰባቸው፣ በሰው ጉዳይ ውስጥ ጣልቃ የሚገቡ፣ የስንፍናን እንጀራ የሚበሉ፣ በሌሎች ሰዎች ላይ ሸክም የሚሆኑ፣ ለስህተት ትምህርት የተጋለጡ ሆነዋል።

ጳውሎስ እነዚህን ሰዎች በመገሰጽ በፍጥነት ወደ ሥራ መመለስ እንዳለባቸው እያሳሰበ ሌሎች ቅዱሳን እነዚህን የሳቱትን ወደ መስመር እንዲያስገቧቸው ያሳስባል።

ይህ ስህተት በየዘመኑ መልኩን ቀይሮ ይታያል። የተለያዩ ቀመሮችን በመጠቀም ለክርስቶስ ዳግም መምጣት ቀን እየቆረጡ ጌታ የሚመጣው በዚህ ቀን ነው የሚሉ ደፋሮች በየጊዜው ይታያል።

የዚህ ስህተት አንዱ ችግሩ ብዙዎችን ሥራ ፈት በማድረግ በውሃ ላይ እንዳለ ኩበት ሰዎችን በከንቱ ተስፋ ላይ የሚዋልሉ ማድረጉ ነው።

ጌታችን ሲመለስ ሥራ ፈታ የምታውደለድል ቤተክርስቲያንን ሳይሆን የተሰጣትን ሁለንተናዊ ተልዕኮ በትጋት በመፈጸም ላይ ያለችውን ቤተክርስቲያንን ማየት ይፈልጋል።

የክርስቶስን ዳግም ምጻት የሚናፍቅ ሰው
ጌታ ሲመጣ ሊያገኘን የሚፈልገው በሥራ ገበታችን ላይ መሆኑን በማወቅ ከሥራ ፈትነት ሊጠበቅ ይገባዋል። ከሥራ የራቀ ሰው ከንጥቀትም የራቀ ሊሆን ስለሚችል መጠንቀቅ አስፈላጊ ነው።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት፦ የክርስቶስ ምጻት ናፋቂዎች ሰራተኞቸ ናቸው።

የዛሬው ፀሎት፦ ጌታ ሆይ ስትመጣ በሰጠኸኝ የሥራ ገበታ ላይ ሆኜ በትጋት እየሰራሁ እንድታኘኝ እለምንሃለሁ። አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

06 Feb, 23:31


ሙያህ ጥሪህ ነው

33ኛ ሳምንት
5ኛ ቀን


ምንም እንኳ ክፉ እንደምትሠሩ አድርገው ቢያሟችሁም፣ ለፍርድ በሚመጣበት ጊዜ መልካሙን ሥራችሁን አይተው እግዚአብሔርን እንዲያከብሩ፣ በአሕዛብ መካከል በመልካም ሕይወት ኑሩ። 1ጴጥ 2፥12

የሐዋርያው ጴጥሮስ መልዕክቶት ክርስቲያኖች በሮም መንግስት ውስጥ ተጠልተው በብዙ ስደትና መከራ ውስጥ በሚያልፉበት ጊዜ ለማጽናናትና ለማበረታታት የተጻፉ መልዕክቶች ናቸው።

በክርስቶስ ኢየሱስ በማመናቸው ቢቻ መሰረተ ቢስ ክሶች፣ የሥም ማጥፋት ዘመቻዎች፣ መድሎና መገለል ይደርስባቸው ነበር።

ጴጥርስ ይህንን መሠረተ ቢስ ውንጀላ ለመመከት እምነታቸውን በመልካም አኗኗር በመግለጽ በከንቱ የሚጠሏቸውን ሰዎች ማሳፈር እንዳለባቸው ይነግራቸዋል።

አኗኗራችሁን ባላመኑት ሰዎች ዘንድ ለምሳሌነት የሚበቃና ነቀፋ የሌለበት አድርጋችሁ አቅርቡት ይላል። በታማኝነት፣ ጠላቶቻችሁን በመውደድ፣ በመልካምነትና የተቸገሩትን በመርዳት እምነታችሁ እውነተኛ መሆኑን አሳዩ በማለት ይመክራቸዋል።

ምላስን በምላስ ሳይሆን ምላስን በተግባር መልሱ ይላቸዋል። ምክንያቱም ተግባር ከምላስ ይልቅ ጮኾ ስለሚናገር። መልካም ሥራችሁን ለሰው ሁሉ የሚታይ አድርጋችሁ ስታቀርቡ መሰረት ቢስ ውንጀላዎችንና የሥም ማጥፋት ዘመቻቸውን በቀላሉ ማክሸፍ እንደሚችሉ ያሳስባቸዋል።

ሐዋርያው ጴጥሮስ መልካም ስራን የእቅበተ እምነት መሣሪያ አድርጋችሁ ተጠቀሙበት የሚል ይመስላል። 

የሰርምነሱ የእምነት አባት ፖሊካርፕ (69-155 ዓ.ም ) በውሸት በሚከሷቸውና ስማቸውን በሚያጠፉት ሰዎች ዘንድ ክፉውን በመልካም በመመለስ የሚታወቅ ሰው ነበር።

ሰማዕት ሆኖ ከማለፉ በመጨረሻዎቹ የሕይወቱ ምዕራፍ ላይ የሮማውያን ወታደሮች ባለቤት ቤት ውስጥ ለመግደል ይዟቸው ለመሄድ ሲመጡ የሚገርም ቸርነት በማሳየት መግቧቸው የመጸለያ ጊዜ እንዲሰጡት ጠየቋቸው ነበር።

ወዳጆቼ በትጋት መስራት ወንጌልን ላልሰሙት የምናሰማበት ጥሩ በር ብቻ ሳይሆን በወንጌልና በአማኞች ላይ ክፉ የሚያስወሩትንም የምናሳርፍበት መሳሪያ ነው።

ሐዋርያው ጳውሎስ ለተሰሎንቄ ሰዎች "ወንድሞች ሆይ፤ ሥራ ፈት ከሆነና ከእኛ በተቀበላችሁት ትምህርት መሠረት ከማይኖር ወንድም እንድትርቁ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እናዝዛችኋለን፤" (2ተሰ 3፥6)

ሥራ ፈትነት የክርስትናን እምነት መርህ የሚጣረስ፣ የወንጌል እንቅፋትና የስህተት ትምህርት መባዣ ስልት ስለሆነ ከሥራ ፈትነት ልንጠነቀቅ ይገባናል።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት፦ ሥራን እንደ እቅበተ እምነት መሳሪያ የመጠቀም አስፈላጊነት።

የዛሬው ፀሎት፦ ጌታ ሆይ ሥራን እንደ ቀንበር ሳይሆን እንደ እድልና የወንጌል መመከቻ መሳሪያ አድርጌ በደስታ እንድሰራ እርዳኝ። አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

06 Feb, 00:41


ሙያህ ጥሪህ ነው

33ኛ ሳምንት
4ኛ ቀን


ከእኛ ወገን የሆኑት ለዕለት የሚያስፈልጋቸውን እንዲያገኙና ኑሯቸውም ፍሬ የሌለው እንዳይሆን ለመልካም ሥራ መትጋትን ይማሩ ዘንድ ይገባቸዋል። ቲቶ 3፥14

ሐዋርያው ጳውሎስ ለቲቶ ከእኛ ወገን የሆኑት ሲል በቀጥታ በቀርጤስ ደሴት ላይ የሚኖሩትን ቅዱሳን ለማመልከት እንደሆነ ከንባቡ መረዳት ይቻላል።

በዚህ ደሴት ላይ የሚኖሩ ሰዎች በኃጢአት ምክንያት የሥራ ባህላቸውና ሥነ ምግባራቸው
የተዛባ ነው። ጳውሎስ የቀድሞ ሕይወታቸውን እንዲህ በማለት ይገልጻል።

"ቀደም ሲል እኛ ራሳችን ማስተዋል የጐደለን፣ የማንታዘዝ፣ የተታለልን፣ ለተለያየ ምኞትና ምቾት ባሪያ ሆነን የተገዛን ነበርን፤ እየተጣላንና እርስ በርስ እየተጠላላን በክፋትና በምቀኝነት እንኖር ነበር። (ቲቶ 3፥3)

ስለዚህ አማኞች ከዚህ አይነት አመለካከት ወጥተው ለመልካም ሥራ መትጋት መማር ግድ ነው። ለመልካም ስራ መትጋትን ሲማሩ ሁለት ዋና ዋና ጥቅሞች እንዳሉት ያስምጣል።

የመጀመሪያው ላባቸውን ጠብ አድርገው የሚያስፈልጋቸውን መሰረታዊ ፍላጎት እንዲያገኙ ነው። ይህም እግዚአብሔር ገና በዘፍጥረት ላይ አዳምን በሕይወትህ ዘመን ሁሉ ምግብህን ጥረህ ግረህ ከእርሷ ታገኛለህ ባለው መሰረት ነው።

ይህ ለሰው ልጆች ሁሉ የሚሆን መለኮታዊ መመሪያ ነው። በምድር ላይ ያለ ሰው ለመኖር የሚያስፈልገውን ነገር የሚያገኘው መንገድ ጥሮ ግሮ በመስራቱ ብቻ ነው። ይህ ሥርዓት በክርስቶስ ስላመንን ለኛም ለቅዱሳን አልተሻራለንም።

ሁለተኛው ምክንያት ኑሯቸው ፍሬ የሌለው እንዳይሆን ነው። በኑሩአችን ፍሬያማና ምርታማ ለመሆን ሌላ አቋራጭ መንገድ የለም። ብቸኛው አማራጭ በትጋት መስራት ነው።

ሐዋርያው ጳውሎስ ምንም እንኳ እንደ ሐዋርያነቱ ከቤተክርስቲያን ለኑሮው የሚያስፈልገውን ነገር የማግኘት መብት ቢኖረውም ለሌሎች ምሳሌ ለመሆን ይሰራ ነበር።

ከእናንተ ጋር በነበርንበት ጊዜ ሥራ ፈቶች አልነበርንም፤ ደግሞም የማንንም እንጀራ በነጻ አልበላንም፤ ነገር ግን ከእናንተ በአንዳችሁም ላይ ሸክም እንዳንሆን ሌሊትና ቀን እንደክምና እንሠራ ነበር፤ ይህን ያደረግነው ምሳሌነታችንን እንድትከተሉ ብለን እንጂ የሚያስፈልገንን ነገር ከእናንተ ለማግኘት ሥልጣን ሳይኖረን ቀርቶ አይደለም። (2 ተሰ 3፥7-9)

ወገኖቼ ክርስትና የሥራ ፈቶች አልያም የሰነፎች እምነት አይደለም። ክርስቶስ ከኃጢአትና ከሞት እንጂ ከሥራ አልዋጀንም። እንዲያውም ማንኛውም ሥራ በላቀ የሥነ ምግባር መርሆ እየደከመን የተቸገሩትን በመርዳት ምሳሌ መሆን ይኖርብናል።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት፦ አማኞች በሥራ የመትጋትን ስልጠና ከመሰረታዊ የክርስትና ትምህርት እንደ አንዱ ርዕሰ አድርገው መማር ያስፈልጋል።

የዛሬው ፀሎት፦ ጌታ ሆይ አንተ በሰነፍና ሥራ ፈት ሰው ደስ ስለማትሰኝ ሥራዬን በትጋት እንዳከናውን እርዳኝ። አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

05 Feb, 00:08


ሙያህ ጥሪህ ነው

33ኛ ሳምንት
3ኛ ቀን


የምታደርጉትን ሁሉ ለሰው ሳይሆን ለጌታ እንደምታደርጉት ቈጥራችሁ በሙሉ ልባችሁ አድርጉት፤ ከጌታ ዘንድ እንደ ብድራት የምትቀበሉት ርስት እንዳለ ታውቃላችሁና፤ የምታገለግሉት ጌታ ክርስቶስን ነው። ቈላ 3፥23-24

ሐዋርያው ጳውሎስ ክርስቲያናዊ ቤተሰብ በምን አይነት መኖር እንዳለባቸው ለቆላስይስ ሰዎች በጻፈላቸው ደብዳቤ ምዕራፍ 3 ከቁጥር 18 እስከ 25 ባለው ክፍል ላይ በዝርዝር አስቀምጧል።

ከእነዚህ የቤተሰብ መዋቅሮች ውስጥ በአሰሪና በሰራተኛው መካከል ሊኖር ስለሚገባው ግንኙነት መለኮታዊ ድንጋጌ ያስቀምጣል። የአንድ ማህበረሰብና ቤተሰብ አኗኗር በየዘመናቱ ቢቀየሩም የእግዚአብሔር ቃል መመሪያ ግን አይለወጥም።

ሐዋርያው ጳውሎስ ሰራተኞችን ሲመክር የሥራ ዝርዝር አልያም የመስሪያ ሰዓታቸውን በመደንገግ አይደለም። ይህ በአሰሪዎቻቸውና በእነርሱ መካከል በሚኖረው ውል የሚወሰን ነው።

ትልቁ ትኩረቱ ሰራተኞች የሚያገለግሉበት ልብ የተለወጠና ከክርስቶስን የተካፈልነውን ባህሪይ በሚገልጽ መሆን እንዳለበት በማሳሰብ ላይ ነው።

ስለዚህ ባሮች (ሰራተኞች - በዘመናዊው አጠራር) ሆይ፤ ሰውን ለማስደሰትና ለታይታ ብላችሁ ሳይሆን፣ በቅን ልብ ጌታን በመፍራት ለምድራዊ ጌቶቻችሁ በሁሉ ነገር ታዘዙ " (ቈላ 3፥22)

ሰራተኞች አሰሪዎቻቸው ዘንድ ለመሞገስ ብለው ለታይታ ሳይሆን አሰሪያቸው ቢኖር ባይኖርም ሁል ጊዜ በሚመለከታቸው በእግዚአብሔር ፊት እንዳሉ በማሰብ በትጋትና በፍጹም መገዛት እንዲሰሩ ይመክራቸዋል።

እንደዛሁም እናንተም ጌቶች (አሰሪዎች) ሆይ፤ ለባሮቻችሁ እንዲሁ አድርጉላቸው፤ የእነርሱም፣ የእናንተም ጌታ የሆነው በሰማይ እንዳለ፣ የሰውንም ፊት አይቶ እንደማያደላ ታውቃላችሁና አታስፈራሯቸው።(ኤፌ 6፥9)

አሰሪዎች ወይም ቀጣሪዎች በቀጠሩት ሰው ላይ የበላይነት ስለሚሰማቸው የማስፈራራትና የመጨቆን ዝንባሌ ይታይባቸዋል። ሐዋርያው ጳውሎስ ለአሰሪዎች አንድ ቀን በጌታ ፊት ስለምትጠየቁ በኃላፊነትና በአደራ አስተዳድሯቸው እያለ ግልጽ መመሪያ ይነግራቸዋል።

በማንኛውም መስክ ተቀጥረን የምንሰራ ሰዎች
የቀጠረን ሰው/ድርጅት በሰጠን የሥራ ድርሻ መሰረት ደመወዝ ሲከፍሉን እግዚአብሔር ግን የምንሰራበት ልብና አመለካከት መዝኖ ነው የሚከፍለን።

በጣም ብዙ አማኞች በተቀጠሩበት በምድራዊ ድርጅቶች ብቻ ሳይሆን በቤተክርስቲያንም ጭምር ለታይታ ሲሯሯጡ፣ በሰው ዘንድ ለመሞገስ ሲሰሩ ማየት በጣም ያሳዝናል።

ወዳጆቼ የሁለት ጌቶች ሰራተኞች መሆናችንን ሁል ጊዜ ልብ ልንል ይገባናል። አንዱ ጌታ የሚታይ፣ በምድር የሚከፍል፣ ሊታለል የሚችል፣ ከሰራነው አብልጦ አልያም ቀንሶ ሊከፍል የሚችል ነው።

በሰማይ ያለው ጌታችን ግን ዋጋችንን በምድርም በሰማይም የሚከፍል፣ በጭራሽ የማይሳሳትና ሁል ጊዜም ለእያንዳንዱ ሰው እንደ ስራው የሚከፍል አምላክ ነው።


ዛሬ የማሰላስለው እውነት፦ በሰው ፊት ለመታየት ሳይሆን እግዚአብሔር እንደሚያየን እያሰብን የመስራት አስፈላጊነት።

የዛሬው ፀሎት፦ እግዚአብሔር ሆይ ለቀጠረኝ ሰው ሳይሆን ዋጋዬን የምትከፍለኝን እያየሁ በሙሉ ልብና በታማኝነት  እንድሰራ እርዳኝ። አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

03 Feb, 21:18


ሙያህ ጥሪህ ነው

33ኛ ሳምንት
2ኛ ቀን


በሙያው ሥልጡን የሆነውን ሰው አይተሃልን?
በነገሥታት ዘንድ ባለሟል ይሆናል፤
አልባሌ ሰዎችን አያገለግልም። ምሳሌ 22፥29

ጠቢቡ ሰለሞን በምሳሌ መጽሐፍ ውስጥ የሕይወትን ገጽታ በተለያየ መንገድ በመግለጽ ጽፎአል።

ከመከረን ነገሮች አንዱ የሥራ ትጋት አስላጊነትንና የሚሰጠውን ጠቀሜታ ነው። ሙያውን አክብሮ በትጋት የሚተገብርና በየዕለቱ ክህሎቱን የሚያሳድግ ሰው እውቅና እንደሚይገኝ፣ በታላላቅ ሰዎች ዘንድ ተፈላጊ እንደሚሆን ይናገራል።

ትጋትና በአግባቡ መሰልጠን የስኬት ቁልፍ እንደሆኑ ያስተምረናል።

በሙያው የተሻለ ብቃት ያለው ሰው በታላላቅ ሰዎችና ነገሥታት ሁሉ ሳይቀሩ ይፈልጉታል። ሙያችንን ባጎለበትን መጠን የዕድገት መስላላችንን እያስረዘምን እንሄዳለን።

ለምሳሌ የዮሴፍን ታሪክ ስናይ በመጀመሪያ በጲጥፋራ ቤት ሲቀጠር ምናልባት በአነስተኛ የሙያ መስክና በትንሽ ክፍያ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን እየቆየ ሲመጣ ሙያውን በታማኝነት ሲከውን ስለዚህ ጲጥፋራ ባለው ሁሉ ላይ ሥልጣን ሰጠው፤ የቀረበለትንም ከመመገብ በስተቀር፣ ማናቸውንም ጕዳይ በዮሴፍ ላይ ጥሎ እንደ እንደ ነበር እናያለን። (ዘፍ 39፥6)

ይህ ታማኝነቱና በታታሪነት ማገልገሉ በእስር ቤት ውስጥም በሚገባ ታዬ። ስለዚህ የወህኒው አዛዥ ዮሴፍን የእስረኞች ሁሉ አለቃ አደረገው፤ በእስር ቤቱ ላለውም ነገር ሁሉ ኀላፊ ሆነ። ( ዘፍ 39፥22)

ይህ ስኬቱ በዚያ ብቻ አላበቃም በዚያን ዘመን በነበረው ዓለም ሁሉ ላይ ታዋቂ የሥነ ምጣኔ ምሁር እስኪሆን ድረስ አልፎም በግብፅ አገር ምክትል ጠቅላይ ሚንስቴር ሆኖ አገርን የመመራት ብቃት ያካበተ ሰው ሆነ።

ከዚያም፣ ፈርዖን ዮሴፍን፣ “በመላዪቱ የግብፅ ምድር ላይ ኀላፊ አድርጌሃለሁ” አለው። ፈርዖንም ባለ ማኅተሙን ቀለበት ከጣቱ አውልቆ በዮሴፍ ጣት ላይ አደረገው፤ እንዲሁም ከጥሩ የተልባ እግር የተሠራ ልብስ አለበሰው፤ በዐንገቱም የወርቅ ሐብል አጠለቀለት። (ዘፍ 41፥41-42)

ዮሴፍ ሳይታክት የአመራር ክህሎቱን ከጲጥፋራ ቤት እስከ ቤተመንግሥት ድረስ ባጋጠመው ዕድል ሁሉ እያሳደገ የነበረ ታታሪ ሰራተኛ ነበር።

ዮሴፍ በአንድ ሰው ቤት ውስጥ እንደ ባሪያ ተሽጦ በዝቅተኛ የስራ እርከን ላይ ከመስራት ተነስቶ የአንድ አገር መሪ እስከ መሆን የደረሰበት ሚስጥር እግዚአብሔር በሕይወቱ ሊሰራ ያሰበውን ዓላማ በመቀበል ከእርሱ የሚጠበቀውን በታማኝነትና ታታሪነት በማገልገሉ ነው።

በአጠቃላይ ጠቢብ ሰለሞን የሚመክረን ከዮሴፍም ሕይወት የምንማረው ማንኛችንም የተሰጠውንን ሙያ፣ ትምህርት፣ ችሎታ፣ ልዩ ተስጦ ወደ ላቀ ደረጃ በማሳደግ እግዚአብሔርን በሙያችን እንድናከብረው  ነው።

ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደ ተሰጠው አድርጎ የሚያስብ ሰው ክህሎቱን ለማሳደግ አይታክትም።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት፦ የትክክለኛው እድገትና ተፈላጊነት መሰላል ትጋት ይባላል።

የዛሬው ፀሎት፦ እግዚአብሔር ሆይ በተሰጠኝ ሙያ ሁሉ ትጉ ሰራተኛና ሱልጡን እንድሆን እርዳኝ። አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

02 Feb, 21:48


ሙያህ ጥሪህ ነው

33ኛ ሳምንት
1ኛ ቀን


"እግዚአብሔር አምላክ ሰውን ወስዶ እንዲያለማትና እየተንከባከበ እንዲጠብቃት በኤደን የአትክልት ስፍራ አስቀመጠው።" ዘፍ 2:15

ከዘፍጥረት 1፡1-2:2 ባለው ክፍል ውስጥ እግዚአብሔርን ብርቱ ሰራተኛ ሆኖ እናገኘዋለን። የፍጥረቱ በኩር አድርጎ የስራውንም ሰው የራሱን መልክና አምሳል አካፍሎት ፈጠረው ማለት ሰው ከመፈጠሩ ጀምሮ ሰራተኛ ተደርጎ ነው የተፈጠረው ማለት ነው።

ሥራን የምንከውንበት መንገድም የእግዚአብሔር መልክ በእኛ ውስጥ እንዲንጸባረቅ ምን ያህል እንደ ፈቀድንለት ያሳያል።

አንድ መሥሪያ ቤት ሰራተኛ ከመቅጠሩ በፊት የሥራ ዝርዝር ቀድሞ እንደሚያዘጋጅ ሁሉ እግዚአብሔርም አዳምን ከመፍጠሩ በፊት የሥራ ድርሻውን ተናግሮ ነበር።

ስለዚህ ሥራ ከውድቀት በፊትም የነበረ ስለሆነ የውድቀት ውጤት ነው ማለት ስህተት ነው። በኀጢአት መውደቅ ያመጣብን ጣጣ በተረገመች መሬት ላይ ከእሾህና አሜኬላ ጋር እየታገልን በፊታችን ወዝ እንድንኖር ማድረጉ ነው።

ኃጢአት በሥራ ባህል ላይ ያጠላው ክፉ ድባብ በየዘመናቱ የጉስቅልና ምክንያት ሲሆን ታይቷል። በዚህም ዘመን በብዙ መሥሪያ ቤቶች፣ የንግድ መረብ ውስጥ፣ የሕዝብ አገልግሎት መስጫ ተቋማት አካባቢ ሙስና፣ አድሎ፣ በጥቅም ፍትሕን ማዛነፍ ተንሰራፍቶ ዜጎችን ሲያማርር ይታያል።

አብርሃም ኩክ የተባለ ደራሲ የእግዚአብሔርን መንግስት ተሸክመው በብዙ መስዋእትነት በረከሰችው አለም ውስጥ ለእውነት የሚታገሉትን እንደዚህ ብሎ ይመክራል።

"ቅዱሳን ብርሃናቸውን ይጨምራሉ እንጂ በጨለማው ብርታት አያጉረመርሙም፣ ለፍትሕ ይታገላሉ እንጂ ስለ በዛው ግፍ አያማርሩም፣ ፈረሃ እግዚአብሔርን ይጨምራሉ እንጂ እየተበራከተ በመጣው የሙስና ማዕበል አይናወጡም"

አንተ መዶሻህን አዘጋጅተህ ጠብቀው እንጂ እግዚአብሔር ሥራውን ያገናኝሃል እንደሚባለው ሥራን ደሞዝ ለማግኘት ብቻ ሣይሆን እንደ አገልግሎትና የወንጌል በር እያሰብን ክፍያ ያለው ጌታ ዘንድ መሆኑን በጽኑ በማመን መትጋት አለብን። አንተ ሥራውን በትክክል ከውን እንጂ እንዴት እንደሚከፍልህ እግዚአብሔር ያውቅበታል።

ወዳጆቼ እግዚአብሔር በስራው የሚተጋን ሰው ሲያገኝ በሞገስና በበረከት ሲጎበኝ ሰይጣን ደግሞ ሥራ ፈት የሆነውን ሰው ሲያገኝ የተለያዩ ፈተናዎችን በአእምሮው ላይ በመዝራት በኃጢአት ወጥመድ ውስጥ ይከተዋል።

ቶማስ ካርልየል የተባለ ሰው እንዲህ ብሏል "ሥራ ያገኘ ሰው እርሱ ብሩክ ስለሆነ እግዚአብሔርን ባርከኝ ብሎ ባይወተውት ጥሩ ነው። እግዚአብሔር ሥራ ከመስጠት በላይ በምንም አይባርክምና"

ዛሬ የማሰላስለው እውነት፦ ሥራ ሁነኛ የወንጌል በር ስለሆነ እጠቀምበታለሁ!

የዛሬው ፀሎት፦ "ሰው ሳይፈጠር ሥራን የፈጠርክለት እግዚአብሔር ሆይ ስለ እንከን አልባው ዓላማህ ተመስገን። ሥራዬን የወንጌል በር እንደሆነ አምኜ፣ ደሞዜን አንተ እንደምትከፍለኝ እያሰብኩ በክርስቲያናዊ ሥነ ምግባርና በደስታ እንድሰራ እርዳኝ። አሜን!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

29 Oct, 17:01


እንባን ሁሉ ከዐይናቸው ያብሳል፤ ከእንግዲህ ወዲህ ሞት ወይም ሐዘን ወይም ልቅሶ ወይም ሥቃይ አይኖርም፤ የቀድሞው ሥርዐት ዐልፏልና።
ራእይ 21፥4

Artios Media

02 Jul, 05:05


በቤተክርስትያን ውስጥ ማገልገል

32ኛ ሳምንት
7ኛ ቀን

ለአክሪጳም፣ “በጌታ የተቀበልኸውን አገልግሎት ከፍጻሜ ለማድረስ ተጠንቀቅ” በሉልኝ። ቈላ 4፥17

"አገልግሎታችንን አደጋ ላይ ከሚጥሉት ነገሮች ዋነኛው ከእግዚአብሔር ጋር  ሕብረት በማድረግ ከእርሱ ኃይል፣ መልዕክትና ምሪት መቀበል ያለብንን ጊዜ ውጤት በሌለው በብዙ ጉዳዮች አባክነን እንዝላል ኑሮ መግፋት ነው" አንድሪው ቦናር

በቤተክርስቲያን ውስጥ ማገልገል ከእግዚአብሔር ዘንድ ጥሪ በመቀበልና የመንፈስ ቅዱስን ስጦታ ከማግኘት የሚጀምር ክቡር ተግባር ነው።

አገልግሎት ሰው ሲፈልግ ጀምሮት ባልተመቸው ጊዜ ደግሞ ጥሎት የሚሄደው በዘፈቀደ የሚተገበር ነገር ሳይሆን በእግዚአብሔር ምሪት ውስጥ ብቻ ተከውኖ እርሱ ከማሳው ውስጥ ሲጠራን ወደ እርሱ የምንሄድበት አደራ ነው።

ብዙ አገልጋዮች ወደ አገልግሎት ተንደርድረው የገቡትን ያህል በጽናት ቆመው ሩጫቸውን ሲጨርሱ አይታይም። ሐዋርያው ጳውሎስ በቆላስይስ ቤተክርስቲያን ውስጥ የሚያገለግለውን አክሪጳን የሚያስጠነቅቀውም ለዚሁ ይመስለኛል።

በአዲስ ኪዳን ውስጥ የአገልግሎትን ጥሪ ተቀብለው በገንዘብ ፍቅርና በዓለም ፍቅር ተደናቅፈው ከቀሩት የአስቆሮቱ ይሁዳና ዴማስ በጉልህ ይጠቀሳሉ።

በቤተክርስቲያን ታሪክ የተሰጣቸውን አገልግሎት በጽናት በመጨረስ ምሳሌ የሆኑን እንደ እነ እስጢፋኖስና ጳውሎስ ደግሞ በሌላ ጎን ይጠቀሳሉ።

ስለዚህ እኛም እግዚአብሔር በረዳን መጠን ከገንዘብ ፍቅርና ከዓለማዊ ምኞት እራሳችንን ጠብቀን የተሰጠንን መክሊት በአግባቡ ነግደንበት ለሽልማት በጌታ ፊት እንድንቆም ጌታ ይርዳን።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት
አገልግሎት የሚጀመር ብቻ ሳይሆን የሚጨረስም ነው።

የዛሬው ፀሎት
እግዚአብሔር ሆይ አገልግሎቴን እስከ ፍጻሜው እንድጨርስ ፀጋህን አብዛልኝ። አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

25 Jun, 07:49


በቤተክርስቲያን ውስጥ ማገልገል

32ኛ ሳምንት
6ኛ ቀን

እነርሱም ቅዱሳንን ለመርዳት በሚደረገው አገልግሎት ለመሳተፍ ዕድል ያገኙ ዘንድ አጥብቀው ይለምኑን ነበር። 2ቆሮ 8፥4

በቤተክርስትያን ውስጥ ከሚደረጉት አገልግሎቶች አንዱ እግዚአብሔር ከሰጠን ነገር ለሌሎች በልግስና የማካፈል ሥራ ነው። የክርስቶስ ቤተክርስትያን ለጋስ ናትና።

እራሷም እግዚአብሔር አብ ልጁን ለግሷት ልጁም ደግሞ ሕይወቱን ሰጥቷት የመሰረታት ሕያው ተቋም ስለሆነች መስጠት አይከብዳትም።

በቤተክርስትያን ውስጥ ለምናደርገው ለማንኛውም አይነት ስጦታ መሰረቱ እራሳችንን ሕያውና ቅዱስ መስዋዕት አድርገን በእግዚአብሔር ፊት ከማቅረብ ነው የሚጀምረው።

እራሱን የሰጠ ሰው ያለውን መስጠት በጭራሽ አይከብደውም። የክርስትና የልግስና ፍልስፍና መነሻው በነጻ የተለገሰንን የዘላለም ሕይወት በማወቅና ለሌሎች መቆረስ የተጠራንበት የኑሮ ዘይቤ መሆኑን በመገንዘብ ላይ ነው።

ስጦታችን የተቀባዮችን መንፈሳዊና አካላዊ ፍላጎት ከሟሟላት ባለፈ ለእግዚአብሔር መመስገን ትልቅ ምክንያት ይሆናል።

ሐዋርያው ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ሰዎች ይህ የምትሰጡት አገልግሎት የቅዱሳንን ጕድለት የሚያሟላ ብቻ ሳይሆን፣ ብዙ ምስጋና ለእግዚአብሔር የሚቀርብበት ነው። (2ቆሮ 9፥12) ይላቸዋል።

ቅዱሳን ወዳጆቼ! በተለያዩ ብልሹ አሰራሮችና በግለሰቦች ስግብግብነት በቤተክርስትያን ውስጥ ለዘመናት የነበረው የልግስና መንፈሳዊ እሴትና ልምምድ ቢደበዝዝም በስጦቻን እግዚአብሔር የማገልገል ትዕዛዝ ግን ሳይሸራረፍ አሁንም አለ።

የእኛ ልምምድ ቢዋዥቅም የእግዚአብሔር ቃል ግን በዘመናት ሁሉ ሕያው እንደሆነ ይኖራል። ይህ እውነት የገባቸው የመቄዶንያ ቅዱሳን እንዲሰጡ ተለምነው ሳይሆን እንደ ዐቅማቸው ብቻ ሳይሆን፣ ከዐቅማቸው በላይ በፈቃዳቸው የሚሰጡና ቅዱሳንን ለመርዳት በሚደረገው አገልግሎት ለመሳተፍ ዕድል ያገኙ ዘንድ አጥብቀው ይለምኑ ነበር (2ቆሮ 8፥4)።

እኛም ባለችን አጭር ዘመን እግዚአብሔር ለሌሎች እንድናካፍልና ለወንጌል አገልግሎት የሰጠን ንብረት በስስት ሳንሰጥ ቀርተን የዘላለም መዝገባችን ባዶ እንዳይሆን ጌታ ማስተዋሉን ያብዛልን።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት
የክርስቶስ ቤተክርስትያን ለጋሽ ናት

የዛሬው ፀሎት
እግዚአብሔር ሆይ ለመቄዶንያ ሰዎች የሰጠኻቸውን የልግስና ፀጋ ለእኔም እንድትሰጠኝ እጠይቅሃለሁ።  አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

24 Jun, 06:30


በቤተክርስትያን ውስጥ ማገልገል

32ኛ ሳምንት
5ኛ ቀን

ስጦታዎች ልዩ ልዩ ሲሆኑ፣ መንፈስ ግን አንድ ነው፤ አገልግሎትም ልዩ ልዩ ሲሆን፣ ጌታ ግን አንድ ነው፤ አሠራርም ልዩ ልዩ ሲሆን፣ ሁሉን በሁሉ የሚሠራው ግን ያው አንዱ እግዚአብሔር ነው።  1ቆሮ 12፥4-6

ቤተክርስትያን ጉራማይሌ ነች። በሕብረ ቀለማት ያሸበረቀች ውብ ጎጆ። በልዩ ልዩ የከበሩ ድንጋዮች የተሸለመች የንጉሥ ማደሪያ እልፍኝ ናት።

ቤተክርስትያን ግንባታዋ ቀን ከሌት የማይቋረጥ ባተሌና ትጉ አገልጋዮቿ  የሚርመሰመሱባት ቦታ ነች። የቤቱ ንድፈ ሃሳብ አዘጋጅ በሆነው በእግዚአብሔር ምህንድስና በመመራት ሁሉም በተሰጠው ምድብ ላይ የበኩሉን ድርሻ ለማበርከት ይሠራል።

በዚህ የአገልግሎት አሰራር ውስጥ ሦስት ነገሮች ልዩ ልዩ ተብለው ሲጠቀሱ (ስጦታው፣ አገልግሎት፣ አሠራር) በተቃራኒው ደግሞ ሦስት ነገሮች ደግሞ አንድ ነው ተብሎአል (መንፈስ፣ ጌታ/ኢየሱስ ክርስቶስ፣ እግዚአብሔር)።

መንፈስ ቅዱስ በቀጥታ የፀጋ ሥጦታዎች አከፋፋይ፣ የቤተክርስትያን የቅርብ የበላይ ተመልካች ተደርጎ ቀርቦአል። ኢየሱስም ጌታ ስለሆነ የተለያየ የፀጋ ስጦታ በተቀበሉት በባሪያዎቹ የሚገለገል አንድ ንጉሥ ነው። የሰው ልጆችን የድነት ፕሮግራም በተለይ በቤተክርስትያን በኩል የተገለጠውን የማዳን ሥራ በበላይነት የሚቆጣጠር እግዚአብሔር አብ ነው።

ይህ ትልቅ የድነት ወንጌል የደረሰን ቅዱሳን በሙሉ ከመንፈስ ቅዱስ የተለያዩ የፀጋ ስጦታዎች ተችረናል። ስለሆነም ሕብረት በምናደርግበት በማንኛውም ቤተክርስትያን ውስጥ የተሰጠንን ስጦታ በአግባቡ በመጠቀም ለአካሉ ግንባታ እንድናውለው ጌታ ይርዳን።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት
አንድ ሆኖ እንደ ልዩ ልዩ፤ ልዩ ልዩ ሆኖ እንደ አንድ የሚሰራበት ቤት ቤተክርስትያን ነች።

የዛሬው ፀሎት
መንፈስ ቅዱስ ሆይ! ባንተ በጎ ፈቃድና ቸርነት የሰጠኸኝን የፀጋ ስጦታ በጥንቃቄ አገልግዬበት ሽልማቴን እንድቀበል እስከ መጨረሻው እንድጸና እባክህ እርዳኝ። አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

23 Jun, 05:06


በቤተክርስቲያን ውስጥ ማገልገል

32ኛ ሳምንት
4ኛ ቀን

አንዳንዶቹ ሐዋርያት፣ አንዳንዶቹ ነቢያት፣ አንዳንዶቹም ወንጌል ሰባኪዎች፣ ሌሎቹ ደግሞ እረኞችና አስተማሪዎች ይሆኑ ዘንድ የሰጠ እርሱ ነው፤" ኤፌሶን 4፥11

ቤተክርስቲያን እንደ ፋብሪካ ነች። ጥሬ እቃ ገብቶ ያለቀለት ያማረ ምርት ሆኖ የሚወጣበት ቦታ ነች። አንዳንዴም ደግሞ የወታደራዊ የማሰልጠኛ ተቋምም ትመስላለች። ምልምል ሰልጣኝ ገብቶ ብቁ ወታደር ሆኖ የሚወጣበት።

የቅዱሳን ሕብረት፣ የክርስቶስ ቤተክርስቲያን የለውጥ አምባ ነች። የሰው የውስጥ ማንነቱ በወንጌል ቃል ተጠርቦ፣ በፀሎት ተሟሽቶ፣ በልዩ ልዩ የፀጋ ስጦታዎች ዕለት ዕለት ተለውጦ የሚታይበት ቦታ ነች።

ከላይ በተጠቀሱት በአምስቱ የአገልግሎት ቢሮዎች በዋናነት ለምን ተፈለጉ ያልን እንደሆነ መልሱ "የክርስቶስ አካል ይገነባ ዘንድ፣ ቅዱሳንን ለአገልግሎት ሥራ ለማዘጋጀት..."(ኤፌ 4፥12) ነው።

ቤተክርስቲያን ቅዱሳን ለመልካም ሥራ ብቁ ለመሆን የሚሰሩበትና የሚዘጋጁበት የማሰልጠኛ ተቋም ነች። የዝግጅቱም ጥግ ክርስቶስን መምሰል ነው። ይህ በእያንዳንዱ አማኝ ሕይወት ውስጥ መከወን ያለበት ትልቅ ፕሮጀክት ነው።

በአጠቃላይ በቤተክርስቲያን ውስጥ በአምስቱ የአገልግሎት ቢሮዎች አማካኝነት የሚደረገው አገልግሎት በዋናነት አማኞችን ለማነጽ፣ ለማሰልጠንና ለማዘጋጀት ነው።

ወዳጆቼ! ሕብረት በምናደርግባት በእውነተኛዋ የክርስቶስ ቤተክርስቲያን ውስጥ ስንሰበሰብ ለመተናነጽ፣ ለመገነባባት እንድንተጋ ጌታ ፀጋውን ያብዛልን።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት
ቤተክርስቲያን የመገንቢያና የመዘጋጃ ቦታ ነች።

የዛሬው ፀሎት
ጌታ ሆይ በደምህ በዋጀሃት ቤተክርስቲያንህ ውስጥ የሚደረጉት ማንኛውም አገልግሎቶች ለመተናነጽና ለመልካም ሥራ ብቁ ለመሆን እንዲሆን እለምንሃለሁ። አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

10 Jun, 19:17


በቤተክርስቲያን ውስጥ ማገልገል

32ኛ ሳምንት
3ኛ ቀን

ይህ ሁሉ ከእግዚአብሔር ነው፤ እርሱ በክርስቶስ አማካይነት ከራሱ ጋር አስታረቀን፤ የማስታረቅንም አገልግሎት ሰጠን፤ 2ቆሮ 5፥18

ዓለም ከፈጣሪዋ ከእግዚአብሔር ጋር ሰላምተኛ ሆና የኖረችው ለአጭር ዘመን ብቻ ነበር። ቀደምት ወላጆቻችን የእባቡን ምክር ተከትለው በኃጢአት ከወደቁ በኋላ ከእግዚአብሔር ጋር ግልጽ ጠላትነት ተጀመረ።

ከውድቀት በፊት የነበረው ሰላማዊ መስተጋብር ሁሉ ተናጋ ሰው ከእግዚአብሔር ጋር ሰውም ከሌላው ሰው ጋር በጠላትነት መፈላለግ ተጀመረ። ጥላቻ፣ መገዳደል፣ ጦርነት የዓለም ሕዝቦች ቋሚ የኑሮ ዘይቤ ሆነ።

እግዚአብሔር ከምህረቱ የተነሳ ይህ ጠላትነት እንዲቀጥል አልፈለገም። ልጁን ልኮልን እርሱ በከፈለው ውድ ዋጋ ከራሱ ጋር አስታረቀን። ከዚህም የተነሣ ቀድሞ ጠላቶቹ የነበርነውን ወገኖቹና ወዳጆቹ አደረገን።

ከእርሱ ጋር የታረቅነውን ልጆቹን የእንደራሴነትን ማዕረግ ሰጥቶን አሁንም ከእግዚአብሔር ጋር ተጣልተው ያሉትን እንድናስታርቅ የማስታረቅ አገልግሎት ሰጠን።

በምድር ላይ ትልቁ አገልግሎት የእርቅ አገልግሎት ነው። እግዚአብሔር በልጁ አማካኝነት ለታረቃቸው ልጆቹ ከሰጣቸው አገልግሎቶች ትልቁና ዋነኛው የማስታቅ አገልግሎት ነው። ቤተክርስቲያን በዚህ ምድር ላይ የተተከለችበት ዋነኛው አገልግሎት የማስታረቅ ሥራ ነው።

ስለዚህ በዙሪያችን ያሉት ሰዎች ከእግዚአብሔር ጋር እንዲታረቁ ወንጌልን በቃልና በኑሮ እንድንመሰክርላቸው የጌታ መንፈስ ያንቃን።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት
በምድር ላይ ትልቁ አገልግሎት የእርቅ አገልግሎት ነው።

የዛሬው ፀሎት
እግዚአብሔር ሆይ የተሰጠኝን የአሸማጋይነት ማዕረግ በመረዳት በወንጌል መልዕክት አማካኝነት ጠላቶችህ የሆኑትን ሰዎች ከአንተ ጋር እንዳስታርቅ እርዳኝ። አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

19 Apr, 03:41


በቤተክርስቲያን ውስጥ ማገልገል

32ኛ ሳምንት
2ኛ ቀን

ከዚያም አሮንን የተቀደሰውን ልብስ አልብሰው፤ ካህን ሆኖ ያገለግለኝ ዘንድ ቅባው፤ ቀድሰውም። ዘፀ 40፥13

በሁለቱም ኪዳናት ውስጥ እግዚአብሔር በመረጣቸው ሕዝቦች መገልገልን ይፈልጋል። በቀደመው ኪዳን ውስጥ እግዚአብሔር ከአስራት ሁለቱ የእስራኤል ነገዶች የሌዊን ልጆች ለአገልግሎት ለይቷቸው በቤተመቅደሱ ውስጥ እንዳሰማራቸው ከኦሪት መጽሐፍ እናነባለን።

ከሌዊ ልጆችም ደግሞ የአሮን ዘሮች ትልቅ ጥንቃቄና ቅድስና የሚፈልገውን የቤተመቅደሱን የውስጠኛ አገልግሎት እንዲከውኑ ሾሟቸው ነበር።

እግዚአብሔር በብሉይ ኪዳን ዘመን ውስጥ ከሕዝቡ ጋር ሕብረት በሚያደርግበት በመገናኛው ድንኳን ውስጥ የሚያገለግሉትን ካህናት መርጦ፣ እንዴት ማገልገል እንዳለባቸው ቀጭን መመሪያ ሰጥቷቸው  ነበር።

የቀደመው የቤተመቅደሱ አገልግሎት ሥርዓት ከአዲስ ኪዳን ጋር ሲነጻጸር በአዲስ ኪዳን ጻሐፊዎች የኩነኔ፣ ያረጀ፣ የሕግ፣ አግላይ ተደርጎ ተገልጾአል።

ጳውሎስ ያንን የቀደመውን ሥርዓት "ሰዎችን የሚኰንነው አገልግሎት የከበረ ከሆነ፣ የሚያጸድቀው አገልግሎት የቱን ያህል ይበልጥ የከበረ ይሆን!" (2ቆሮ 3፥9) በማለት ከአዲስ ኪዳኑ አገልግሎት ጋር ያገናኛል።

በየትኛውም ዘመን ግን እግዚአብሔር ከመረጠቻው ሕዝቦቹ ጋር ለመገናኘት አገልግሎት አንደኛው መስመሩ ነው። ስለዚህ እግዚአብሔርን የማገልገል እድል ያገኘን ቅዱሳን እርሱን በመፍራትና በማክበር እንድናገለግለው ፀጋው ይብዛልን።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት
እግዚአብሔር በመረጣቸው ልጆቹ መገልገልን ይፈልጋል።

የዛሬው ፀሎት
እግዚአብሔር ሆይ አንተን ማገልገል እንደ ትልቅ ዕድል አይቼ በጉጉትና በትጋት በፊትህ እንዳገለግልህ እርዳኝ። አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

15 Apr, 22:08


በቤተክርስቲያን ውስጥ ማገልገል

32ኛ ሳምንት
1ኛ ቀን

❝እያንዳንዱ ሰው በተቀበለው የጸጋ ስጦታ ሌላውን ያገልግል፤❞ 1ኛ ጴጥ 4: 10

በቤተክርስቲያን ውስጥ አማኝና የጸጋ ስጦታ ሲገናኙ የሚፈጠረው ምግባር አገልግሎት ይባላል። አገልግሎት እራሳችንን ሕያውና ቅዱስ መስዋዕት አድርገን በእግዚአብሔር ፊት ቅዱሳንን ለመጥቀም ማቅረብ ነው።

አገልግሎት ከተግባር ሳይሆን ከልብ ነው የሚጀምረው። ሁሉም አማኝ በመድረክ ላይ ቆሞ ማገልገል አለበት ባይባልም በቤተክርስቲያን ውስጥ ግን የራሱ ድርሻ እንዳለው መታወቅ ይኖርበታል።

በቤተክርስቲያን ውስጥ የምናበረክተው አገልግሎት ከሁለንተናዊ መሰጠት የሚመነጭ መሆን አለበት። ፍራንሲስ ቻን እንደ ተናገረው "እርሱ ሁለንተናችንን ካልሆነ ግን ምናችንንም አይፈልግም። አንድ ሰው ሁለመናውን ለክርስቶስ ሳይሰጥ እራሱን አገልጋይ ብሎ መጥራቱ ከንቱ ነው።"

ከፀጋ ስጦታዎች መካከል የፈለግነውን የመምረጥ መብት አልተሰጠንም። ቃሉ የሚለው ❝እነዚህ ሁሉ የዚያው የአንዱ መንፈስ ስጦታዎች ሲሆኑ፣ ለእያንዳንዱ ሰው እርሱ ራሱ እንደ ፈቀደ ይሰጠዋል❞ (1ኛ ቆሮን 12: 11) ነው።

የእኛ ድርሻ የፀጋ ስጦታን በቅንነት መፈለግና መንፈስ ቅዱስ እንደ ወደደ ሲሰጠን በደስታና በትህትና ተቀብለን በዚያ ማገልገል ብቻ ነው።

በተሰጠን መክሊት አትርፈን አንድ ቀን በጌታ ፊት ስንቆም "❝መልካም፥ አንተ በጎ ታማኝም ባሪያ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ። (ማቴ 25: 21) የሚለውን ቃል ከእግዚአብሔር ለመስማት ተግተን እንድንሰራ መንፈሱ ያበርታን።

ወዳጆች እንትጋ! አገልግሎትን የሰው፣ የግለሰብ፣ ከዚያም አልፎ የቤተክርስቲያንም ጉዳይ ብቻ አናድርግ። አገልግሎት የጠራንን ክርስቶስን በመታዘዝ የተላክንበትን በትጋት እየሰራን በተሰመረልን መስመር ላይ ሩጫችንን ፈጽመን የማለፍ ጉዳይ ነው።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት
እግዚአብሔርን ማገልገል ትልቅ እድል ነው!

የዛሬው ፀሎት
እግዚአብሔር ሆይ ታማኝ አድርገህ የፀጋ ስጦታን ስለ ሰጠኸኝ አመሰግንሃለሁ። በተሰጠኝ መክሊት አትርፌ አንድ ቀን ለሽልማት በፊትህ መቆም እንድችል እርዳኝ።" አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

14 Apr, 22:45


የቤተክርስቲያን ተልዕኮ 2 - ደቀመዝሙር ማድረግ

31ኛ ሳምንት
7ኛ ቀን


ክርስቶስንና የትንሣኤውን ኀይል እንዳውቅ፣ በሥቃዩ ተካፋይ እንድሆንና በሞቱም እርሱን እንድመስል እመኛለሁ። ፊል 3፥10

ሐዋርያው ጳውሎስ በአዲስ ኪዳን መጽሐፍት ውስጥ ከተጻፉልን የእምነት አርበኞች ውስጥ በነገር ሁሉ ክርስቶስን ለመምሰል የጣረ ያለ አይመስልም።

የጳውሎስ የመጨረሻው ፍል አምሮት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን በኑሮው፣ በአገልግሎቱ አልፎም በአሟሟቱ እንኳን እርሱን መምሰል ነው። በሮም እስር ቤት ውስጥ ሆኖ ከእስር ስለ መለቀቁ ጉዳይ ሳይሆን አሟሟቱ የክርስቶስ የመምሰል ያለ መምሰሉ ነው የሚያሳስበው።

እውነተኛ ደቀመዝሙር ውስብስብ ፍልስፍና፣ የተለየ መረዳትና አስተምህሮ የለውም። ሙሉ በሙሉ የክርስቶስን ትምህርት የሚያስተጋባ ነው።

እግዚአብሔር አብ በመጨረሻው የሽልማት ቀን እንደ መለኪያ የሚጠቀመው የልጁን ሕይወት ነው። የሁላችንም ሕይወትና አገልግሎት ተመዝኖ ዋጋችንን የምንቀበለው ምን ያህል ክርስቶስን ይመስላል በሚል ነው።

ስለዚህ ወዳጆቼ በዚህ የመጨረሻ ዘመን እግዚአብሔር የሰጠንን ዕድል ተጠቅመን እውነተኛ ደቀመዛሙርት ሆነን ሌሎች ቅዱሳንንም የክርስቶስ ደቀመዝሙርት እንድናደርግ መንቃት ይሁንልን።

የዚህን ሳምንት ጥናት እንዲህ ብለን ብንቋጭ ጥሩ ነው። ከእምነታችን ጀማሪና ፈጻሚ በላይ በሕይወታችንና በአገልግሎታችን ልንመስለው የተገባን ስለማይኖር እኛም እንደ ሐዋርያው ጳውሎስ ክርስቶስን በነገር ሁሉ ለመምሰል እንድንጥር እግዚአብሔር ፀጋውን ያብዛልን።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት
የደቀመዝሙርነት ሕይወት ጥጉ ክርስቶስን በነገር ሁሉ መምሰል ነው።

የዛሬው ፀሎት
ጌታ ሆይ እኔም እንደ አባቶቼ በነገር ሁሉ አንተን ለመምሰል የምጥርበት ቁርጠኛ ልብ እንድሰጠኝ እለምንሃለሁ። አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

13 Apr, 21:44


የቤተክርስቲያን ተልዕኮ 2 - ደቀመዝሙር ማድረግ

31ኛ ሳምንት
6ኛ ቀን


እርስ በርሳችሁ ብትዋደዱ፣ ሰዎች ሁሉ የእኔ ደቀ መዛሙርት እንደ ሆናችሁ በዚህ ያውቃሉ። ዮሐ 13፥35

ጌታችን የእርሱ ደቀመዝሙር መሆናቸንን ዓለም ለይተው የሚያውቁበት ዋነኛው ምልክት በንግግራችን፣ በአለባበሳችን፣ ወይንም በምናሳየው የተለየ ምልክት ሳይሆን እርስ በእርሳችን ባለን ፍቅር መሆኑን ነግሮናል።

ፍቅር ለሌላው ክርስቲያን ወዳጃችን ከክርስቶስ የተካፈልነውን ምህረት፣ ፀጋ፣ ርህራሄ ስናካፍላቸው በመካከላቸን በቅሎ አብቦ በአካባቢያችን ላሉት ሰዎች የሚታይ ጥሩ መአዛ ያለው ዛፍ ነው።

የጌታችን ዋነኛው የባህሪዩ መገለጫ ፍቅር ነው። እኛም ከእርሱ በተካፈልነው ፍቅር መሰረት እርስ በእርሳችን በቃልና በተግባር ስንዋደድ ሰዎች የክርስቶስ ተከታዮች መሆናችንን በቀላሉ ይለዩናል።

ሰዎች እኛን የክርስቶስ ደቀመዝሙር መሆናችንን ማወቃቸው በራሱ ዋነኛ ግብ አይደለም። ትልቁ ዓላማ የዲያብሎስን ፍቃድ ስናደርግ የኖርነውን እኛን ለውጦ የፍቅር ልጆች ያረገንን የክርስቶስ ፍቅር እነሱም እንዲቀምሱ ሰዎችን ከኢየሱስ ጋር ማስተዋወቅ ነው።

በሐዋርያት ዘመን ለቅዱሳን በምታደርገው በተግባር የተገለጠ ፍቅር በብዙዎች ዘንድ በፍቅር የምትወደደው ዶርቃ የተባለች ደቀመዝሙር ነበረች። ሉቃስ ስለ እርሷ እንዲህ በማለት መስክሯል። "እርሷም ዘወትር በትጋት በጎ ነገር እያደረገችና ድኾችን እየረዳች ትኖር ነበር።" (ሐዋ 9፥36)።

የኢዮጴዋ ዶርቃ ቅዱሳን ሁሉ እግዚአብሔር በሰጣቸው ዕድል እራሳቸውን ሳይሆን የክርስቶስ ፍላጎት እንዲሁም የወገኖችን ጥቅም ማዕከል አድርገው መኖር እንዳለባቸው ጥሩ ምሳሌ የሆነችልን እህታችን ናት።

ወዳጆቼ! መዋደድ ወቻል በራሱ ከጌታ ዘንድ የሚሰጥ እድል ነው! ብዙዎች በሰይጣን ባርነት ውስጥ ስላሉ ለወገኖቻቸው እውነተኛ ፍቅር መስጠት አይችሉም።

እኛ የክርስቶስ ፍቅር በልባችን ውስጥ የፈሰሰ ቅዱሳን እርስ በእርሳችን በመዋደድ የወንጌል ድምፅ በመሆን የጌታችንን የማዳን ጥር ለዓለም እንድናስተጋባ እግዚአብሔር ይርዳን።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት
ፍቅር የክርስቶስ ደቀመዛሙርት ዋነኛ መታወቂያቸው ነው።

የዛሬው ፀሎት
ጌታ ሆይ እርስ በእርሳችን በመዋደድ በጥላቻ እየታመሰች ላለችው ዓለም ብርሃን እንድንሆን እባክህ እርዳን። አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

13 Apr, 05:14


የቤተክርስቲያን ተልዕኮ 2 - ደቀመዝሙር ማድረግ

31ኛ ሳምንት
5ኛ ቀን


አንዳንዶቹ ግን ግትር በመሆን፣ ለማመን ፈቃደኞች አልነበሩም፤ የጌታንም መንገድ በገሃድ ያጥላሉ ነበር። ስለዚህ ጳውሎስ ትቷቸው ሄደ፤ ደቀ መዛሙርትንም ለብቻቸው ወስዶ በጢራኖስ የትምህርት አዳራሽ ውስጥ በየዕለቱ ያነጋግራቸው ነበር። ሐዋ 19፥9

ሐዋርያው ጳውሎስ በሁለተኛው የወንጌል ጉዞ ቤተክርስቲያንን ከተከለባቸው ከተማዎች አንዷ የኤፌሶን ከተማ ነች። ይህች ከተማ አርጤምስ በተባለች የሴት ጣዖት አምልኮ የተዋጠች ናት።

ሐዋርያው ጳውሎስ የወንጌል ችቦ በዚያ ከተማ ውስጥ ሲያበራ ከጨላማቸው ተላቀው ወደ ክርስቶስ ብርሃን ለመምጣት ብዙዎቹ አሻፈረኝ ቢሉም የተወሰኑት ግን በኢየሱስ በማመን ወደ ሕይወት ወጡ።

በዚያ ከተማ ውስጥ ቀጣይ ትልቁና ከባዱ ስራ አማኞችን በማስተማር የክርስቶስ ደቀመዝሙር ማድረግ ነው። ጳውሎስ በዚህ የሚታማ አይደለምና በጢራኖስ የትምህርት አዳራሽ ውስጥ በየዕለቱ አሰለጠናቸው።

ይህንን ማድረጉንም ሁለት ዓመት ስለ ቀጠለ፣ በእስያ አውራጃ ይኖሩ የነበሩት የአይሁድና የግሪክ ሰዎች ሁሉ የጌታን ቃል ለመስማት ቻሉ።

በአጠቃላይ በኤፌሶን ከተማ የነበረውን ቆይታ ሲናገር "ከእናንተው መካከል እንኳ የራሳቸውን ደቀ መዛሙርት ለማፍራት እውነትን የሚያጣምሙ ይነሣሉ። ስለዚህ ተጠንቀቁ፤ ሦስት ዓመት ሙሉ ሌሊትና ቀን ምንም ያህል ሳላቋርጥ በእንባ እያንዳንዳችሁን እንደ መከርኋችሁ አስታውሱ።"
(ሐዋ 20፥30-31) ይላቸዋል።

ደቀመዝሙር ማድረግ ቀላልና የጅምላ ሥራ አይደለም። ጥንቃቄ የሚፈልግ፣ ትዕግስትን የሚሻ፣ መስዋዕትነት የሚጠይቅ፣ ሥርዓተ ትምህርት ተቀርጾለት በፀሎት የሚሰራ ብርቱ አደራ ነው።

ሐዋርያው ጳውሎስን በእንባ እንዲያገለግልና በጽናት እንዲያስጠነቅቅ ያደርግ የነበረው ደቀመዝሙር ማድረግ የግብር ይውጣ ስራ ባለመሆኑ ነው።

ዛሬም ቢሆን ደቀመዝሙር የማድረግ ሥራ ቀላል ሥላልሆነ ብዙ አገልጋዮች አድካሚውን ጥሪ ተቀብለው በትጋት ከመስራት ይልቅ የቤተክርስቲያን መደበኛ ፕሮግራምና በተለምዶ የሚደረጉ ስብስቦች እንዳይቋረጡ ከማድረግ ባለፈ ዋጋ ሲከፍሉ አይታይም።

ስለዚህ የተሰጠንን ደቀመዝሙር የማፍራት ተልዕኮ እንደገና በማደስ እግዚአብሔር በሰጠን ዕድል መንገዳችንን እንድናስተካክል ጌታ ይርዳን።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት
ደቀመዝሙር ማፍራት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ከባድ ሥራና አደራ ነው።

የዛሬው ፀሎት
እግዚአብሔር ሆይ ደቀመዝሙር የማድረግን ሥራ ቸላ ብዬ የፕሮግራም አድማቂ ብቻ እንዳልሆን እባክህ እርዳኝ። አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

12 Apr, 03:29


የቤተክርስቲያን ተልዕኮ 2 - ደቀመዝሙር ማድረግ

31ኛ ሳምንት
4ኛ ቀን


ከዚህ በኋላ፣ ሕዝቡን ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ወደ እርሱ ጠርቶ እንዲህ አላቸው፤ “ሊከተለኝ የሚወድድ ቢኖር ራሱን ይካድ፤ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ።”  ማር 8፥34

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሁሉንም አካታች የሆነ ብርቱ መልዕክት ነገራቸው። የእርሱ ተከታይ መሆን የሚያስከፍለውን ዋጋ በግልጽ አስታወቃቸው።

የደቀመዝሙርነት ጥሪ የደረሰው አማኝ ሁሉ የኢየሱስ ተከታይ ለመሆን ዋጋውን በሚገባ መተመን አለበት። የደቀመዛሙርነት ሕይወት ታዋቂነትን፣ የክብር ደረጃ፣ ሃብትና ነፍሳችንን መስዋዕት ሊያስደርገን ይችላል።

በተጨማሪ ለክርስቶስ ሥም ብለን መጠላትን፣ መነቀፍን፣ መዋረድን፣ መደብደብን፣ መገፋትን ያስከትላል። ይህም እንግዳ ነገር ሳይሆን በኢየሱስና ሐዋሪርያቱ ላይ እንዲሁም ባለፉት ሁለት ሺህ አመታት ውስጥ በአማኞች ላይ ሲፈጸም የነበረ ተግባር ነው።

እራስን መካድ ማለት ማንነታችንን ሙሉ ለሙሉ ለክርስቶስ ጌትነት አስገዝተን በእርሱ ፍቃድ ለመመራት ራስን አሳልፎ መስጠት ነው።  እራስን መካድ ትዕቢተኝነታችንን የምንቀብርበት ጉድጓድ ነው።

እራስን መካድ ዕለት ዕለት መስቀልን ተሸክሞ ከመኖር ጋር ተገናኝቶ ነው የተነገረው። ይህም አሮጌውን አዳማዊ ባህርይ ለማስወገድ ከክርስቶስ ጋር መተባበራችንን፣ ለክርስቶስ ስም ብለን እስከ ሞት ታዛዥ መሆን እንዳለብን የሚያመለክት ነው።
 
እራሳችንን ሳንክድ የምናደርገው መስዋዕትነት ሁሉ ልክ አትሌቶች ክብር፣ ዝናና ጥቅም ለማግኘት ብለው እንደሚለፉት አይነት ነው። ጌታ ኢየሱስ ማንኛውንም አይነት መስዋዕትነት ከመክፈላችን በፊት እራሳችንን መስዋዕት አድርገን እንድናቀርብ ነው የሚፈልገው።

በአጠቃላይ ደቀመዝሙርነት  ትልቅ ብድራትና አክሊል ያለበት ነገር ግን መራራ ዋጋ የሚያስከፍል የከበረ የሕይወት ስርዓት ነው። ስለዚህ ይህ የከበረ የደቀመዝሙርነት ግብዣ የቀረበልን አማኞች በጽናት እስከ ፍጻሜው እንድንጓዝ ጌታ ይርዳን።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት
ደቀመዝሙርነት ትልቅ መስዋዕትነት የሚጠይቅ የከበረ የሕይወት ስርዓት ነው።

የዛሬው ፀሎት
ጌታ ኢየሱስ ሆይ የቀረበልኝን የደመዝሙርነት ሕይወት ግብዣ ተቀብዬ ተገቢውን ዋጋ ሁሉ እየከፈልኩ እስከ ፍጻሜው እንድሄድ እርዳኝ። አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

11 Apr, 07:29


የቤተክርስቲያን ተልዕኮ 2 - ደቀመዝሙር ማድረግ

31ኛ ሳምንት
3ኛ ቀን


የእግዚአብሔርም ቃል እየሰፋ ሄደ፤ የደቀ መዛሙርቱም ቍጥር በኢየሩሳሌም እጅግ እየበዛ ሄደ፤ ከካህናትም ብዙዎቹ ለእምነት የታዘዙ ሆኑ። ሐዋ 6፥7

ወንጌልን ብቻ መስበክ የቤተክርስቲያንን ተልዕኮ ግማሽ ሙሉ ብቻ ነው የሚያደርገው። የክርስቶስ አዳኝነት በመቀበል ከሰይጣን አገዛዝ ያመለጡ ሁሉ ያመኑበትን እውነት በሚገባ ለመረዳት በጥንቃቄ መማር ግድ ይላቸዋል።

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለዚህ ነው ከወንጌል ምስክርነት ጎን ለጎን ደቀመዝሙር የማድረግን ትዕዛዝ ለሐዋርያቱ የሰጣቸው። እነርሱም ሳይታክቱ በክርስቶስ ያመኑበትን ደቀመዝሙር ለማድረግ ቀን ከሌት ሲለፉ የነበረው።

በቤተክርስቲያን ታሪክ ውስጥ ከሐዋርያት ቤተክርስቲያን በላይ ብዙ ደቀመዝሙር ያፈራች ቤተክርስቲያን ያለች አይመስልም። ያመኑትን በሙሉ በሚገባ በማስተማር የክርስቶስ ተከታዮች እንዲሆኑ አጥብቀው ይተጉ ነበር።

በኢየሩሳሌም ከተማ ስደት በደረሰባቸው ጊዜ በተበተኑበት ከተማ ሁሉ የመጠለያ ካንፕ ከመፈለግ ይልቅ የክርስቶስን ወንጌል በድፍረት መስበክ መቻላቸው የክርስቶስ ደቀመዝሙር ስለ መሆናቸው ትልቅ ማሳያ ነው።

በየትኛውም ዘመን የቤተክርስቲያን ተልዕኮ ስኬት የሚለካው ወንጌልን በመስበክ ሰዎችን ወደ ክርስቶስ ባመጣቻቸው ብቻ ሳይሆን የመጡትን በማስተማር የጌታ ደቀመዝሙር ባደረገቻቸው ልክ ነው። 

በእኛም ዘመን በቤተክርስቲያን አዳራሽ ውስጥ የተገኙትን አማኞች ሁል ጊዜ በስብከት እያሟሟቅን ከመሸኘት ይልቅ ያመኑትን እውነት በትክክል እንዲረዱ ብናስተምራቸው ብዙ ደቀመዝሙር ማፍራት በቻልን ነበር።

አሁንም በቀረን ዘመን በተሰጠን እድል በኢየሩሳሌም ከተማ እንደ ነበረችው እንደ ሐዋርያት ቤተክርስቲያን እጅግ ብዙ ደቀመዛሙርት ማፍራት እንድችል እግዚአብሔር ይርዳን።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት
የቤተክርስቲያን ስኬት ማሳያ ያፈራቻቸው ደቀመዛሙርት ብዛት ነው።

የዛሬው ፀሎት
ጌታ ሆይ ትዕዛዝህን በመቀበል ብዙ ደቀመዛሙርት ለማፍራት እንድንተጋ ፀጋህን አብዛልን።  አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

09 Apr, 21:04


የቤተክርስቲያን ተልዕኮ 2 - ደቀመዝሙር ማድረግ

31ኛ ሳምንት
2ኛ ቀን


ደቀ መዝሙር ከመምህሩ አይበልጥም፤ ነገር ግን በሚገባ የተማረ ሰው ሁሉ እንደ መምህሩ ይሆናል። ሉቃ 6፥40

"ደቀመዝሙር ማለት ተማሪ፣ ተከታይ፣ ሰልጣኝ፣ ለማጅ ማለት ነው። በዳተኝነት መምህሩን የሚከተልና ከእርሱ እውቀትን ብቻ የሚቀስም ሳይሆን በነገር ሁሉ መምህሩን ለመምሰል የሚጥር ነው። ዳን ስፓደር

ደቀመዝሙር ሕይወቱን ለመማር የሰዋ ሰው ነው።   ደቀመዝሙር የራሱ ትምህርት የለውም። ለመማር የሚጥረው ከመምህሩ የሚነገረውን ብቻ ነው። ከተማረም በኋላ የሚያስተጋባው የአስተማሪውን ፍልስፍና ብቻ ነው።

ጌታችን እንደ ነገረን ደቀመዝሙር በምንም ስሌት አስተማሪውን ሊበልጥ እንደማይችል ነው። በደንብ ከተማረ ግን እንደ አስተማሪው መሆን  ይችላል። ጌታችን አማኞችን የእርሱ ደቀመዛሙርት የምናደርግበት ስልት ማስተማር መሆኑን ነግሮናል።

በቤተክርስቲያን ውስጥ በየትኛውም ዘመን የደቀመዝሙር ትምህርት ለቃሉ በታመኑ አገልጋዮች አማካኝነት የሚቀርብ ነው። እግዚአብሔር በየጊዜው ሕይወታቸው ምሳሌ የሚሆኑ ሰዎችን ይሰጠናል።

ጳውሎስ በነበረበት ዘመን ለሚያገለግሉአቸው ቅዱሳን "እኔ የክርስቶስን ምሳሌ እንደምከተል እናንተም የእኔን ተከተሉ።" (1 ቆሮ 11፥1) ይል ነበር። በተጨማሪም "ወንድሞች ሆይ፤ የእኔን አርኣያነት በመከተል ከሌሎች ጋር ተባበሩ፤ እኛ በሰጠናችሁ ምሳሌነት መሠረት የሚኖሩትንም አስተውሉ።" (ፊል 3፥17) ብሏል።

ስለዚህ የተሰጠን አጭር እድሜ በምናገኘው አጋጣሚ ሁሉ እግዚአብሔር ከሰጠን አገልጋዮችና ከክርስቶስ ሕይወት በመማር የእርሱ ደቀመዝሙር እንድንሆን ጌታ ይርዳን።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት
ደቀመዝሙር ሁለንተናውን ከክርስቶስ ለመማር የሰዋ ነው።

የዛሬው ፀሎት
ጌታ ሆይ ካንተ ሕይወት፣ ከቅዱስ ቃልህ እንዲሁም ከእውተኞች የቃልህ መምህራን ተምሬ የታመነ ያንተ ደቀመዝሙር እንድሆን እርዳኛ። አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

08 Apr, 22:52


የቤተክርስቲያን ተልዕኮ 2 - ደቀመዝሙር ማድረግ

31ኛ ሳምንት
1ኛ ቀን


❝ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው።❞  ማቴ 28:20

ሁለተኛው የቤተክርስቲያን ተልዕኮ ያመኑትን በማስተማር ደቀ መዛሙርት ማድረግ ነው። ድነት በነፃ በእምነት ያገኘነው ውድ ነገር ቢሆንም ደቀ መዝሙር መሆን ግን ሕይወታችንን መስዋዕት ማድረግ የሚጠይቅ ነው።

ደቀ መዝሙርነት ለጥቂቶች ብቻ የቀረበ ግብዣ ሳይሆን አማኞች ሁሉ ሊሆኑት የተገባ ብቸኛው የክርስቶስ መከተያ መንገድ ነው።

ደቀ መዝሙር ማለት ተከታይ፣ ተማሪ፣ ሰልጣኝ መምህሩን የሚመስል ማለት ነው።  ጆን ማካርተር "ደቀ መዝሙርነት እራስን መካድ፣ በትህትና ሌሎችን ለማገልገል በመስዋዕትነት መቅረብ፣ ለጌታ ሙሉ ለሙሉ መገዛትን ያካትታል" ይላሉ።

የክርስቶስ ደቀ መዝሙር መሆን ብዙዎች እንደሚሉት የማይመረቅ ተማሪ መሆን ማለት ነው። ሁሌም ከጌታ ኢየሱስ እግር ስር ተቀምጦ የሚሰለጥን፣ የአባቱን ድምፅ የማይሰለች ተወዳጅ ልጅ መሆን ነው።

ቢል ሃል የተባሉ ሰው እንደ ገለጹት "ደቀ መዝሙርነት በአንድ ጊዜ ፕሮግራም የምንገላገለው ዝግጅት አይደለም የሕይወት ዘመን ጉዞ ነው እንጂ።

ለጥቂት ወራት ለአዳዲስ አማኞች የተዘጋጀ መርሐ ግብርም ሳይሆን የእያንዳንዱ አማኝ የዕለት ተዕለት ምልልሱ ነው። ደቀ መዛሙርትን ማፍራት ከቤተክርስቲያን ተግባራት አንዱ ሳይሆን ዋነኛ ሥራዋ ነው።"

እውነተኛ ደቀ መዛሙርትን ለማፍራት የግድ የበሰሉ የተለወጡ ከጌታ የተማሩ አሰልጣኝ ደቀ መዛሙርት ያስፈልጉናል።

የደቀ መዝሙርነትን ባህል በቤተክርስቲያን ውስጥ እያደበዘዙ ካሉት ምክንያቶች አንዱ አማኞች ኢየሱስ ክርስቶስን የሕይወታቸው አዳኝ እንጂ በየዕለቱ የሚገዙለት፣ የሚታዘዙት፣ ፈቃዱን ለመረዳት የሚፈልጉ ጌታቸው አድርገው በኑሮአቸው ላይ ለመሾም ያለመፈለጋቸው ነው።

ስለዚህ አማኞች የተቀበሉትን ሕይወት ጠብቀው በክርስትና እያደጉና እየበሰሉ ኖረው፣ የምድር ጉዞአቸውን ጨርሰው፣ በክርስቶስ ፊት ለሽልማት የሚቆሙ እንዲሆኑ የደቀ መዝሙር ሥልጠና በዘመኗ ቤተክርስቲያን ውስጥ በሚገባ መሰጠት አለበት።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት
ደቀመዝሙርነት የሕይወት ዘመን ጉዞ ነው!

የዛሬው ፀሎት
ጌታ ኢየሱስ ሆይ አንተ እውነተኛ መምህሬ ነህ እኔም ያንተ ደቀ መዝሙር ነኝ!! ተግቼ እንድከተልህ፣ ከእግርህ ሥር ሆኜ እንድማር፣ በፍጹም ልቤ እንድታዘዝህ፣ በመጨረሻም አንተን እንድመስል አሳድገኝ። አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

07 Apr, 21:50


የቤተክርስቲያን ተልዕኮ 1 - የወንጌል ምስክርነት

30ኛ ሳምንት
7ኛ ቀን


ሥራህን ዐውቃለሁ። እነሆ፤ ማንም ሊዘጋው የማይችል የተከፈተ በር በፊትህ አድርጌአለሁ። ኀይልህ ትንሽ እንደ ሆነ ዐውቃለሁ፤ ሆኖም ቃሌን ጠብቀሃል፤ ስሜንም አልካድህም። ራእ 3፥8

"ቅዱሳን ስለ ክርስቶስ ወንጌልና በእርሱ በኩል የተገለጠውን እውነት በሦስት መንገድ ነው መመስከር ያለባቸው። እነዚህም በኑሮአቸው፣ በቃላቸውና በደማቸው ነው።" ቫቫሶር ፓወል

ለፊላደልፊያ ቤተክርስቲያን ትልቅ የወንጌል ምስክርነት ዕድል ተሰጣት። ማንም ሊዘጋው የማይችል የአገልግሎት በር ተከፈተላት። በየትኛውም ዘመን ያለች ቤተክርስቲያን እስከምትነጠቅ ቀን ድረስ ይህ አደራ ተሰጥቷታል።

ይህንን ወንጌል ለመስበክ ግን ሁሌም መስዋዕትነት ሕይወትና የመንፈስ ቅዱስ ኃይል ያስፈልጋል። ለፊላደልፊያ የተሰጣት የወንጌል ስብከት ዕድልና ያላት ኃይል የተመጣጠነ አይደለም።

ማንኛውም ቤተክርስቲያን በየትኛውም ዘመን ወንጌልን መስበክ እንደ አማራጭ የምታየው ጉዳይ አይደለም።

በትልቅ ተጋድሎ ውስጥ አልፋ የወንጌል ምስክርነት አደራዋን በታማኝነት የተወጣች ቤተክርስቲያን ታላቅ ሽልማት ይጠብቃታል።

ስለዚህ ለፊላደልፊያ የተዘጋጀላትን አክሊል እስከ መጨረሻው መጠበቅ እንዳለባት እንደተነገራት ሁሉ እኛም እስከ ፍጻሜው እንድንዘልቅ ጌታ ይርዳን።

"ቶሎ እመጣለሁ፤ ማንም አክሊልህን እንዳይወስድብህ ያለህን አጥብቀህ ያዝ።" (ራእ 3፥11)

ዛሬ የማሰላስለው እውነት
የወንጌል ምስክርነት ከጴንጤቆስጤ እስከ ንጥቀት ነው።

የዛሬው ፀሎት
እግዚአብሔር ሆይ የማዳን ፕሮግራምህ የተገለጠበትን የወንጌል መልዕክት እስከመጨረሻው በታማኝነት መስክሬ የድል አክሊል እንድቀበል እርዳኝ። አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media

Artios Media

06 Apr, 21:42


የቤተክርስቲያን ተልዕኮ 1 - የወንጌል ምስክርነት

30ኛ ሳምንት
6ኛ ቀን


አሕዛብ ይህን በሰሙ ጊዜ ደስ አላቸው፤ ለእግዚአብሔርም ቃል ክብርን ሰጡ፤ ለዘላለም ሕይወት የተዘጋጁትም ሁሉ አመኑ። ሐዋ 13፥48

በመጀመሪያው የወንጌል ጉዞ ወቅት ጳውሎስና በርናባስ በጲስድያ ወንጌልን ገልጠው ሰበኩ ከዚያ ልባቸው ዝግጁ የሆኑት በክርስቶስ አመኑ። የቀሩት ግን ምናልባትም ሰይጣን ቆይ በኋላ ትወስናለህ በማለት አዘናጋቸው።

አንድ ጊዜ ሉሲፈር የሰዎችን ልጆች በማሳት ተጨማሪ ነፍሳትን ወደ ሲዖል ለማስገባት በገሃነም ውስጥ ካሉት ጋኔኖች ውስጥ አደገኛ የማሳት ስልት ያለውን መርጦ ወደ ምድር ለመላክ አሰበ ይባላል። ይህንን ዓላማውን ይፋ በማድረግ መላክ የሚፈልጉት እቅዳቸውን ግልጽ እንዲያደርጉ ጠየቃቸው።

ከዚያ አንዱ ጋኔን እጁን አውጥቶ እኔን ላከኝ አለ። ምን አድርገህ ልታስታቸው ዘየድክ ሲለው "መንግስተ ሰማይ የሚባል ነገር በጭራሽ የለም በማለት አስታቸዋለው" አለው። ከዚህም ሉሲፈር በእያንዳንዱ ልብ ውስጥ የመንግስተ ሰማይ ናፍቆትና እውነት በተፈጥሮ ስላለ ይህንን ማስካድ የማይቻል ነው። ስለዚህ ይህ የሚያዋጣ አይደለምና አትሄድም አለው።

ከዚያ ሁለተኛው ሰይጣን ብቅ ብሎ የሚገርም የማሳት ስልት እንዳለውና መሄድ እንደሚፈልግ ተናገረ። ሉሲፈርም እስኪ መላውን ነገረን አለው " ጮሌውም ሰይጣን "ሲዖል የሚባል ነገር እንደሌለ ነግራያቸው አደናብራቸዋለሁ" አለው። ሉሲፈርም መልሶ "ሰዎች በተፈጥሮ በልባቸው ውስጥ ክፉና ደጉን የመለየት ሞራላዊ መለኪያ አላቸው። ካጠፉ ቅጣት እንደሚጠብቃቸው ይገነዘባሉ። ስለዚህ ይህ እቅድ የሚያዋጣ ስላልሆነ አትላክም" አለው።

የመጨረሻው በማታለል የተካነው ብቅ ብሎ ለመላክ ፈቃደኛ መሆኑን አሳወቀ። የማሳት ስልቱም ሲጠየቅ "መንግስተ ሰማይም ሲዖልም በመኖርና ባለመኖራቸው ሙግት አልከፍትም። ነገር ግን በቂ ጊዜ ስላላች ለውሳኔ መቸኮል አያስፈልግም በማለት አዘናጋቸዋለሁ" አለ። ይህኔ ሉሲፈር ፈገግ ብሎ "አንተ በፍጥነት ወደ ምድር ሂድ። የሰዎችንም ልጆች አስታቸው" ብሎ ላከው።

የቤተክርስቲያን ትልቅ ተልዕኮ በሰይጣን ተሸንግለው ለመወሰን ጊዜ እንዳላቸው በማሰብ በወንጌል ከማመን ለሚያመነቱ ሰዎች ቃሉን በጽናት መስበክና የሰይጣንን ሥራ እያፈረሰች መጸለይ አለባት።

ዛሬ የማሰላስለው እውነት
ሰዎች ለሰሙት የወንጌል እውነት መልስ እንዳይሰጡ የሚያዘናጋ አጋንንት ነው።

የዛሬው ፀሎት
ሰዎች ለሰሙት የምስራቹ ወንጌል ምላሽ እንዳይሰጡ የሚያዘናጋና በብዙ መልኩ የሚሸነግላቸው አጋንንት በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይመታ። አሜን!!!

መልካም ቀን!!

@artios_media
@artios_media
@artios_media