Latest Posts from African Leadership Excellence Academy (@afleexac) on Telegram

African Leadership Excellence Academy Telegram Posts

African Leadership Excellence Academy
የኢትዮጵያን ብሎም የአፍሪካን ሁለንተናዊ ሰላም ዲሞክራሲና ልማት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የማይተካ ሚና ካላቸው ወሳኝ አካላት አንዱ አሰተማማኝ አቅም ያለው አመራር መኖር በመሆኑ፤ ተከታታይና ሁሉን አቀፍ የአመራር ልማት በሁለም ደረጃ ማካሄድ አስፈሊጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በንድፈ-ኃ
1,875 Subscribers
2,199 Photos
82 Videos
Last Updated 01.03.2025 06:10

The latest content shared by African Leadership Excellence Academy on Telegram


የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር አመራሮች እና ባለሞያዎች በአፍሌክስ ስልጠና መውሰድ ጀመሩ

ሱሉልታ የካቲት 10/2017 ዓ.ም (አፍሌክስ)- አፍሌክስ ለባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር አመራሮች እና ባለሞያዎች መስጠት በጀመረው 2ተኛ ዙር የአመራር ልማት ስልጠና 270 የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አመራሮች እና ባለሞያዎች ተሳታፊ መሆን ችለዋል።

የሃገሪቱን ተቋማት የአመራር ብቃት ለማሳደግ በመስራት ላይ የሚገኘው አፍሌክስ ከባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ፤ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አመራሮች እና ባለሞያዎች 2ተኛ ዙር ስልጠና በአመራር ልማት ማዕከሉ መስጠት ጀምሯል።

ስልጠናው የአመራሩን ብቃት በማጠናከር ኪነ ጥበብ፣ ባህል፣ እና ስፖርት ለሃገር አንድነት እና ብልጽግና ያላቸውን ሚና አጠናክሮ ለማስቀጠል ያለመ እንደሆነ ተገልጿል።

በመክፈቻ ስነ ስርዐቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የባህልና ስፖርት ሚኒስትሯ ክብርት ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ “የዚህ ስልጠና ዋነኛ አላማ ባህልና ስፖርትን ለሃገረ መንግስት ግንባታ ለማዋል የሚያችለንን አቅም ማሳደግ ነው።” ብለዋል።

አያይዘውም ያደጉ ሃገራት ገጽታቸውን ለመገንባት ከተጠቀሙባቸው መሳሪያዎች መካከል ባህልና ስፖርት ዋነኞቹ መሆናቸውን ጠቅሰው፣ “ኢትዮጵያ ያሏትን ቱባ ባህሎችም ሆነ የስፖርቱን ዘርፍ ለሃገራዊ አንድነት እና ገጽታ ግንባታ ለማዋል ሃላፊነታችንን እየተወጣን ነው ወይ? ብለን ራሳችንን መጠየቅ ይኖርብናል።” ሲሉ ተናግረዋል።

አፍሌክስ ለጤና ሚኒስቴር እና ለተጠሪ ተቋማት አመራሮች ስልጠና መስጠት ጀመረ

ሱሉልታ የካቲት 10/2017 ዓ.ም (አፍሌክስ)-በአመራር መስኩ የጾታ እኩልነትን የማረጋገጥ አላማ ያለው የፐብሊክ ሊደሺፕ ፎር ጀንደር ኢኳሊቲ (PL4GE) ፕሮጀክት ለጤና ሚኒስቴር እና በስሩ ለሚገኙ ተጠሪ ተቋማት የስራ ሃላፊዎች በአፍሌክስ ስልጠና መስጠት ጀምሯል።

የአፍሌክስ፣ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር እና የግሎባል ሴንተር ፎር ጀንደር ኢኳሊቲ ትብብር ውጤት የሆነው ይህ ፕሮጀክት በአመራር ዘርፍ የጾታ እኩልነትን ለማረጋገጥ በመስራት ላይ ይገኛል።

ዛሬ ሱሉልታ በሚገኘው የአፍሌክስ የአመራር ልማት ማዕከል የተጀመረው ስልጠናም የዚሁ አካል ሲሆን የጤና ሚኒስቴር አመራሮችን እንዲሁም በስሩ የሚገኙ ተጠሪ ተቋማትን የስራ ሃላፊዎች ያሳተፈ ነው።

የጤና ሚኒስቴርን ወክለው ስልጠናውን በንንግር ያስጀመሩት ዶ/ር አስናቀ ዋቅጅራ በጤናው አመራር ዘርፍ የጾታ እኩልነትን ለማረጋገጥ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አበክሮ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

ከሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር በመክፈቻው ላይ ንግግር ያደረጉት ትፍስሂት ሰለሞን (ዶ/ር) በሃገራችን በየመስኩ ባለው አመራር ዘንድ የጾታ እኩልነትን ለማረጋገጥ የሚሰራው ስራ አካል የሆነው ይህ ፕሮጀክት ሙሉ በሙሉ ወደትግበራ መግባቱ ደስ የሚያሰኝ መሆኑን ገልጸው፣ በጤናውም ሆነ በሌላው መስክ የጾታ እኩልነትን ለማረጋገጥ የሚሰራው ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

የፕሮጀክቱ የስራ ሃላፊ ኢሳያስ ታዬ (ዶ/ር) PL4GE በርካታ ሂደቶችን አልፎ ለዚህ በቅቷል ብለው፣ ለዚህም ጉልህ አስተዋጽዖ ላበረከቱ የፕሮጀክቱ አስተባባሪዎች ምስጋና አቅርበዋል።

ስልጠናው ከየካቲት 10 እስከ 12 እንደሚቆይ ተገልጿል።

Leadership-centered systems thinking Is essential for effective leadership in today’s complex environment.

This approach emphasizes understanding the needs, perspectives, and experiences of people within the system, fostering a culture of empathy and collaboration.

Leaders who adopt this mindset prioritize the well-being of their team members, recognizing that engaged and satisfied individuals drive organizational success.

By actively listening to feedback and involving team members in the decision-making process, leaders create an inclusive atmosphere where everyone feels valued.

Moreover, human-centered system thinking encourages leaders to view challenges holistically.

Instead of addressing problems in isolation, they consider the interconnectedness of various elements within the organization, enabling more sustainable and effective solutions.

ለምን መሪዎች?

መሪነት በማዕረግ ወይም በሹመት ብቻ የተገደበ አይደለም:: እያንዳንዳችን ልንይዘው የምንችለው አስተሳሰብ እና ኃላፊነት ነው።

መሪ ለመሆን በምንመርጥበት ጊዜ በአካባቢያችን ያሉትን የመምራት፣ የማነሳሳት እና የማበረታታት ሚና እንጫወታለን። ግን ሁል ጊዜ መሪ ለመሆን መጣር ያለብን ለምንድን ነው?

መሪዎች ለውጥ ይፈጥራሉ። ተግዳሮቶችን እና እድሎችን ይለያሉ፣ ሌሎችን በጥልቅ እንዲያስቡ እና አዲስ ነገር እንዲፈጥሩ ያበረታታሉ። የመሪነት ባህልን በማጎልበት ችግሮችን በጋራ መፍታትና በማህበረሰባችን ውስጥ እድገትን ማምጣት እንችላለን።

አመራር ጽናትን ያዳብራል። ጠንካራ መሪዎች መመሪያ እና ድጋፍ ይሰጣሉ፣ ሌሎች ተግዳሮቶችን እንዲያስሱ ይረዷቸዋል። ሁላችንም የመሪነት አስተሳሰብን ስንከተል፣ መሰናክሎችን ለማሸነፍ የጋራ አቅማችንን የሚያጠናክር የድጋፍ መረብ እንገነባለን።

ከዚህም በላይ መሪ መሆን ማለት አርአያ መሆን ማለት ነው። የእኛ ተግባራቶች እና ውሳኔዎች ለሌሎች አርአያ ይሆናሉ፣ በባህሪያቸው እና በአስተሳሰባቸው ላይ ተጽእኖ ያሳድራሉ።

የታማኝነት፣ የመተሳሰብ እና የተጠያቂነት ባህሪያትን በማካተት፣ በዙሪያችን ያሉትን ወደ አቅማቸው እንዲወጡ እናበረታታለን።

በመጨረሻም፣ አመራር ስለ ግንኙነት ነው። ግንኙነቶችን መገንባት እና ትብብርን ማጎልበት ነው። በዕለት ተዕለት ህይወታችን ውስጥ ለመሪነት ቅድሚያ ስንሰጥ ሁሉም ሰው ዋጋ ያለው ሆኖ የሚሰማውን እና የበኩሉን አስተዋፅኦ ለማድረግ ስልጣን ያለው አካባቢ እንፈጥራለን።

ለራሳችን ብቻ ሳይሆን ለበለጠ ጥቅም ሁሌም መሪ ለመሆን መጣር አለብን። በጋራ፣ በሁሉም የህይወታችን ዘርፍ እንደ መሪ ሚናችንን በመቀበል ብሩህ የወደፊት ጊዜ መፍጠር እንችላለን።

Always Matter, Never Mind? Always
Mind, Never Matter in Leadership

In leadership, balancing what truly matters and what can be dismissed is essential.

"Always Matter" emphasizes prioritizing core values, team well-being, and the mission, fostering trust and inspiring collective goals. "Never Mind" encourages leaders to focus on what is essential and dismiss distractions that hinder progress.

"Always Mind" highlights the importance of being aware of team dynamics and the broader implications of decisions, fostering open communication and adaptability.

Lastly, "Never Matter" reminds leaders to let go of ego and unnecessary conflicts, promoting a learning environment where growth is valued over perfection.

By embodying these principles, leaders can create a thriving and empowering environment for their teams.

🎉አፍሌክስ በኢትዮጵያ🇪🇹 ብሎም በአፍሪካ🌍 የመጀመሪያ በሆነው የሴቶች የአመራር ልማት መርሃ-ግብር ያበቃቸውን ሴት አመራሮች ሊያስመርቅ 3 ቀናት ብቻ ቀርተዋል🎉

"ዛሬ እንደተቋምም እንደሃገርም የምንወስነው ውሳኔ ውጤት በወደፊቱ ትውልድ የምንታይበትን መንገድ ይወስናል።" አቶ ዛዲግ አብርሃ የአፍሌክስ ፕሬዝደንት

የገቢዎች ሚኒስቴር አመራር እና ከፍተኛ ባለሙዎች በአፍሌክስ ሲወስዱ የቆዩት ስልጠና ተጠናቀቀ።

ሱሉልታ የካቲት 9/2017 ዓ.ም (አፍሌክስ)- ስነ ምግባራዊ አመራር ላይ ትኩረቱን አድርጎ ለ3 ቀናት ያህል በገቢዎች ሚኒስቴር ለከፍተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት አመራር እና ከፍተኛ ባለሙያዎች ሲሰጥ የቆየው ስልጠናው ዛሬ ተጠናቋል።

በመጨረሻ ቀን ውሎው የአፍሌክስ ፕሬዝደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ስነ ምግባራዊ ውሳኔ ሰጪነትን የተመለከተ ሰፊ ገለጻ አድርገዋል።

ውሳኔ ሰጪነት ከሰው ልጅ ተፈጥሮ ጋር በእጅጉ የተቆራኘ ነው ያሉት አቶ ዛዲግ፣ ውሳኔ መስጠት ለምን ያስፈልጋል ከሚለው ጥያቄ ተነስተው፣ ትክክለኛ ውሳኔ እንዳንሰጥ የሚያደርጉን ነገሮች ምንድናቸው፣ አንድ ሰው ትክክለኛ ውሳኔ ለመወሰን ምን ምን ሂደቶችን ማለፍ አለበት የሚሉትን ሃሳቦች አንስተዋል።

ውሳኔ ሰጪነት ሳይንስ ነው፣ ስለዚህ ሳይንስ ማወቅ ትክክለኛ ውሳኔ መስጠት እንድንችል ይረዳናል ብለዋል።

የገቢዎች ዘርፍ ለሃገር ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት በመሆኑ በዚህ ዘርፍ የሚወሰኑ ውሳኔዎች ተጽዕኖአቸው የጎላ ነው ሲሉ ተናግረው የውሳኔ ሰጪነትን ጥበብ ከዘርፉ ጋር እያገናኙ አስረድተዋል።

አመራሮች ስነ-ምግባርን የተላበሱ እንዲሆኑ የሚያደርጓቸውን ምክንያቶች ዘርዝረው፣ የስነ-ምግባራዊ አመራር ባህርያትን አብራርተዋል።

በአፍሌክስ አዘጋጅነት በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሲሰጥ የቆየው ስልጠናው ተሳታፊዎች ዘርፈብዙ እውቀት እንዲጨብጡ ያስቻለና አሳታፊ እንደነበር ተገልጿል።

🎉አፍሌክስ በኢትዮጵያ🇪🇹 ብሎም በአፍሪካ🌍 የመጀመሪያ በሆነው የሴቶች የአመራር ልማት መርሃ-ግብር ያበቃቸውን ሴት አመራሮች ሊያስመርቅ 4 ቀናት ብቻ ቀርተዋል🎉

የአፍሌክስ ፕሬዚደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ከNBC Ethiopia ቴሌቪዥን ጊዜ ግስ ፕሮግራም ጋር በነበራቸው ክፍል 2 ቆይታ ያለፈውን እና መጪውን ጊዜ ያብራራሉ "የጦርነት ሂሳብ አይገባቸውም... አደገኛውን መንገድ መርጠዋል" ይሉናል። እነማንን ይሆን? ማስፈንጠሪያውን በመጠቀም ሙሉውን እንድትከታተሉ ጋብዘናል፡-
https://www.youtube.com/watch?v=qUs4UhNa3yU

Just now ·
#Happening_Now!!!
#አሁን!
"የሰው ልጅ ትክክለኛ ውሳኔ መወሰን ከፈለገ ራሱን ማወቅ፣ የሰው ልጅ ተፈጥሮን መረዳት ይጠበቅበታል" ዛዲግ አብርሃ
👉የሰውን ልጅ ትክክክለኛ ውሳኔ የመስጠት አቅም ከሚቀንሱት ነገሮች አንዱ ኮግኒቲቨ ባያዝ ይባላል❗️
👉ኮግኒቲቨ ባያዝ ምንድነው
🔹ስሜታዊነት
🔹ማህበረሰባዊ ተጽዕኖ
🔹ደመነፍሳዊነት
🔹ልማድ
🔹ሌሎች፣ ሌሎች ጉዳዮች በውሳኔ ሰጪነታችን ላይ ያላቸው ተጽዕኖ ምን ይመስላል
የአፍሌክስ ፕሬዝደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ስነ
-ምግባራዊ ውሳኔ አሰጣጥን በተመለከተ ለገቢዎች ሚኒስቴር አመራሮች ስልጠና እየሰጡ ነው።