Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2 @mormto2 Channel on Telegram

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

@mormto2


This is official Telegram Channel of Ministry of Revenues Medium Taxpayers Branch No 2.
Join the channel.

Ministry of Revenues - Medium Taxpayers Branch No2 (English)

Welcome to the official Telegram Channel of the Ministry of Revenues Medium Taxpayers Branch No2! Are you looking to stay updated on tax information and regulations for medium-sized businesses? Look no further than this channel, where you will find all the latest news, guidelines, and tips to help you navigate the world of taxes. Whether you are a business owner, financial advisor, or simply interested in tax matters, this channel is the perfect place for you. By joining our channel, you will have access to valuable insights and resources that will help you make informed decisions when it comes to your tax obligations. Stay connected with us and never miss out on important updates from the Ministry of Revenues Medium Taxpayers Branch No2. Join us today and be part of a community dedicated to promoting tax compliance and transparency. Don't wait any longer - join the channel now!

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

18 Feb, 12:27


IFRS የተመለከተ ስልጠና ተሰጠ
********************************
(የካቲት 11/2017ዓ.ም፡ የመካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር 2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት)


ከተለያዩ የሥራ ክፍሎች ለተውጣጡ የቅርንጫ ጽ/ቤቱ ሰራተኞች IFRS (INTERNATIONAL FINANCIAL REPORTING STANDARDS) አተገባበር ላይ ስልጠና ተሰጠ፡፡

ወ/ሮ አስቴር አዱኛ በቅርጫፍ ጽ/ቤቱ የተቋማዊ አቅም ግንባታ ዘርፍ ም/ስራ አስኪያጅ ባስተላለፉት የመክፈቻ ንግግር አንደገለፁት የተቋሙን ሰራተኞች አቅም በመገንባት ለግብር ከፋዩ ጥራት ያለውና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት ውጤታማ የገቢ አሰባሰብ በመዘርጋት ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ በብቃት መሰብሰብ እንደሚያስፈልግ እና በዚህም የሰራተኛውን አቅም መገንባት ትልቅ ድርሻ እንዳለው፣ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱም የተለያዩ ስልጠናዎችን በመስጠት የራሱን ድርሻ እየተወጣ እንዳለ የዛሬው ስልጠናም የዚሁ አካል መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ሰልጣኞችም የወሰዱትን ስልጠና ወደተግባር መቀየር እንደሚጠበቅባቸው እና ለሌሎች የስራ ባልደረቦቻቸው በማጋራት የእርስ በርስ አቅም ማጎልበት እንደሚያስፈልግ፤ በቀጣይም ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የተለያዩ ስልጠናዎችን ለሰራተኞቹ እንደሚሰጥ አስታውቀዋል፡፡

ስልጠናው ከታክስ ጋር በተገናኘ የIFRS አጠቃቀም ምን ይመስላል? ስራ ላይስ እንዴት ይውላል? በሚለው ላይ ሰፋ ያለ ማብራሪያ በአቶ አይተነው እንዳሌ የታክስ ኦዲት ቡድን አስተባባሪ የተሰጠ ሲሆን በሰው ሀይል አመራርና ልማት የሥራ ሂደት ተዘጋጅቷል፡፡

የስልጠናው ዋና ዓላማ ከታክስ ጋር በተገናኛ የ IFRS አተገባበር ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን እና በስራ ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመሙላት ሲሆን ከስራቸው ጋር ቀጥታ ግንኙነት ያላቸው ሰራተኞች ተሳትፈውበታል፡፡

ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

18 Feb, 09:19


የክፍል ሁለት ፈተና ተሰጠ

*************************************



የክፍል ሁለት ስልጠናን ላጠናቀቁ ሰልጣኞች የክፍሉ ማጠናቀቂያ ፈተና ዛሬ የካቲት 11 ቀን 2016ዓ.ም ተሰጠ፡፡ ሰልጣኞች በክፍል ሁለት ስልጠናቸው ቀጥተኛ ያልሆኑ ታክሶች ላይ የተጨማሪ እሴት ታክስ፣ የቴምብር ቀረጥ አስተዳደር እና የሱር ታክስ አስተዳደር ሥርዓት፣ የሽያጭ ታክስ (Turn over tax)፣ ኤክሣይዝ ታክስን በተመለከተ ስልጠና ወስደዋል፡፡

ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

14 Feb, 13:35


የመጀመሪያው ዙር የጥያቄና መልስ ውድድር ተካሄደ
******************************************



(የካቲት 7/2017 ዓ.ም፡ መካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር 2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት)

ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በስሩ ካሉ ስምንት ትምህርት ቤቶች የታክስና የጉምሩክ ክበባትን በማቋቋም የመጀመሪያ ዙር የጥያቄና መልስ ውድድር አካሂዷል፡፡

ግብርን እና ቀረጥን በተመለከተ ጥልቅ ግንዛቤ ያለው በአመለካከቱ የተለወጠ፤ የታክስ ሞራሉ ከፍ ያለ ዜጋ መቅረፅና ማፍራት በማስፈለጉ መንግስት ልዩ ትኩረት በመስጠት በስርዓተ ትምህርት ውስጥ በማካተት ከቅድመ መደበኛ እስከ 12ኛ ክፍል በተለያዩ የትምህርት አይነቶች ላይ አንዲካተት በማድረግ ግንዛቤ እየተፈጠረ ይገኛል፡፡

በተጨማሪም በተተኪው ትውልድ ላይ ከሚሰሩ ትግባራት መካከል የታክስ እና ጉምሩክ ክበባትን በትምህርት ቤቶች በማቋቋም የጥያቄ እና መልስ ውድድር ማካሄድ አንዱ ነው፡፡

ታክስ እና ቀረጥ ለሀገር ያለውን ፋይዳ በመረዳት የሚሰበሰበው ገቢ ሀገርን እንደ ሀገር ለማስቀጠል ዋነኛ መሳሪያ መሆኑን አወቆ ግብሩን በታማኝነት በወቅቱ የመክፈል ባህልን ያዳበረ ትውልድ መቅረፅ የጥያቄና መልስ ውድድሩ ዋና ዓላማ ነው፡፡

ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

13 Feb, 13:58


"ለጠንካራ ተቋም ግንባታ የላቀ የሪፎርም ጉዞ"
**********************************

(የካቲት 6/2017 ዓ.ም፡ መካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት)

የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር የሪፎርም ስራዎች የፍኖተ ካርታ በተመለከተ በገቢዎች ሚኒስቴር የሚሰጠው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተጀመረ፡፡ በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የሚገኙ አመራርና ሰራተኞችም የግንዛቤ ማሰጨበጫ ስልጠናውን በቴሌ ሚት (Telemeet) ተከታትለዋል፡፡

የስልጠናውን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የገቢዎች ሚኒስቴር ሚንስትር ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሴ ባስተላፉት መልዕክት በያዝነው በጀት ዓመት በሀገራችን ታሪክ እጅግ ከፍተኛውን ገቢ ለመሰብሰብ አቅደን ከፍተኛ አፈፃፀም የተመዘገበበት ሲሆን ይህም በአመራሩ እና በፈፃሚው ያልተቆጠበ ጥረት መምጣቱን ገልፀው ለዚህም ምስጋና አቅርበዋል፡፡

በሀገራችን የገቢዎችና የጉምሩክ አገልግሎት እረጅም ታሪክ ካላቸው ተቋማት አንዱ ነው፡፡ አሁን ያለንበትም ወቅት የተቋሙን ተጨባጭ ሁኔታ በመረዳት የገቢው ዘርፍ ፍኖተ ካርታ ሪፎርም የተዘጋጀ ሲሆን ይህን የተሳካ ለማድረግ ከሰራተኛው ምን ይጠበቃል ለሚለው ባለን አቅም ላይ ተጨማሪ አቅምን በመገንባትና ዘመናዊ የታክስ አስተዳደር ስርዓት በመዘርጋት ሪፎርሙን ውጤታማ ማድረግ የሁሉም ድርሻ መሆኑን እና የገቢው ዘርፍ የሪፎርም ፍኖተ ካርታን በተመለከተ ለሁሉም ሰራተኛ ግንዛቤ መፍጠር የስልጠናው ዋና ዓላማ መሆኑን በአፅንኦት ገልፀዋል፡፡

በቀረበው የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር የሪፎርም ስራዎች ፍኖተ ካርታ ሰነድ ላይ በቅርንጫፍ ጽ/ቤት አመራርና ሰራተኞች ጋር ውይይት የተደረጉ ሲሆን ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ቶሉ ፊጤ የተሰጠ ሲሆን የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ በአጠቃላይ ለተነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
የዛሬው ስልጠና የመጀመሪያ ዙር ሲሆን በነገው ዕለትም ለሁለተኛ ዙር ሰልጣኞች ስልጠናው የሚሰጥ ይሆናል፡፡

ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

11 Feb, 12:26


የክፍል ሁለት ስልጠና ተጠናቀቀ
******************************************

(የካቲት 4/2017 ዓ.ም፡ መካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት)

ለ አስራ ሰባተኛ ዙር ሰልጣኞች ሲሰጥ የነበረው ቀጥተኛ ያልሆኑ ታክሶችን የተመለከተው የክፍል ሁለት ስልጠና ተጠናቀቀ፡፡

ሰልጣኞች በክፍል ሁለት ስልጠናቸው ቀጥተኛ ያልሆኑ ታክሶችን በተመለከተ አምስት ሞጁሎችን የወሰዱ ሲሆን የተጨማሪ ዕሴት ታክስ (VAT፣ ኤክሣይዝ ታክስ፣ የቴምብር ቀረጥ እና የሱር ታክስ አስተዳደር ሥርዓት በተመለከተ ሰፋ ያለ ስልጠና ወስደዋል፡፡

የዛሬው ስልጠና የሽያጭ ታክስ (Turn over tax)፣ የሱር ታክስ አስተዳደር እና የቴምብር ቀረጥ አስራር ሥርዓት የተመለከተ ሲሆን በአቶ አወቀ ግዛው ከፍተኛ የትምህርት ባለሙያ ተሰጥቷል፡፡

በዚህም የታክሶቹን ምንነት፤ የሚመለከታቸው አካላት እና የማይመለከታቸው ግብይቶች ይለያሉ፤የታክሶቹ ምጣኔዎች፣ ታክሶቹ የሚሰሉበት የዋጋ መሰረት በታክሶቹ ዙሪያ ያሉ አስተዳደራዊ እና የወንጀል ቅጣቶች፤ የቴምብር ቀረጥ የሚከፈልባቸው ሰነዶች፣ ቀረጡን እንዲከፍል ግዴታ የተጣለባቸዉ አካላትን በተመለከተ በስልጠናው ከተብራሩ ርዕሰ ጉዳዮች ውስጥ ይገኙበታል፡፡

በክፍል ሁለት ስልጠና ቀጥተኛ ያልሆኑ ታክሶችን በተመለከተ የታክስ አዋጅ፣ ደንብ እና መመሪያዎች ላይ ሰፋ ያለ ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን ከሰልጣኞች ለቀረቡ የተለያዩ ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሾች ተሰጥተውባቸዋል፡፡

ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

11 Feb, 11:07


ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

08 Feb, 12:19


******************************************

The imposition of tax on a person who has derived income not otherwise taxable under the income tax proclamation taxation of a residual category of income.

a person who derives any income that is not taxable under Schedule 'A', 'B', 'C, or the other Articles of Schedule 'D' is liable for income tax at the rate of 15% on the gross amount of the income. Tax is imposed under the Article at the time the income is "derived" by the person.


This applies to both residents of Ethiopia and non-residents. In the case of a non-resident, income is taxable only if the income is Ethiopian source income.

To read a full article clicks the link:-https://tinyurl.com/p7v5nw25

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

07 Feb, 12:24


https://youtu.be/_Q_lT7RNww4

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

07 Feb, 11:07


ልዩ መለያ ኮድ (QR Cod) የተካተተበት የደረሰኝ ህትመት ጥያቄ የማቅረቢያ ቀነ ገደብ እስከ የካቲት 30 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ እንዲራዘም ተወሰነ

ጥር 30/2017 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)

ከዚህ ቀደም የደረሰኝ ህትመት ጥያቄ ማቅረብ የሚቻለው እስከ ጥር 30 ቀን 2017 ዓ.ም ብቻ መሆኑ በተገለጸው መሰረት ቁጥራቸው 88,717 የሆኑ ግብር ከፋዮች የህትመት ጥያቄ ማቅረብ መቻላቸውን የገቢዎች ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሤ ከክልል እና ከተማ አስተዳደር የገቢ ዘርፍ አመራሮች ጋር በበይነ መረብ ባደረጉት ውይይት ገልጸዋል፡፡

ሆኖም በተለያዩ ምክንያቶች የህትመት ጥያቄያቸውን ያላቀረቡ ግብር ከፋዮች መኖራቸውና ይህን ታሳቢ በማድረግ የህትመት ጥያቄ ማቅረቢያ ቀነ ገደብ እስከ የካቲት 30 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ እንዲራዘም በውይይቱ ተወስኗል፡፡

እንደ ሀገር በገቢው ዘርፍ የሚሰተዋሉ ክፍተቶችን ለማረም በርካታ የሪፎርም ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ክብርት ሚኒስትር ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሴ በውይይቱ የገለጹ ሲሆን በተለይም የማንዋል ደረሰኝ አጠቃቀም እና አስተዳደር ስርዓትን በማሻሻል የሚፈለገውን የገቢ ዕድገት ማስመዝገብ ያሰፈልጋል ብለዋል፡፡

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫ፡- https://shorturl.at/ZLOQR

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

01 Feb, 08:13


*********************************

1/A taxpayer required to file a tax declaration under a tax law shall file the declaration in the approved form and in the manner provided for in the Regulation.

2/ the Authority may, by notice in writing, require a taxpayer to file by the due date set out in the notice:

a) A fuller declaration in relation to a tax declaration already filed; or

b) Such other tax declaration as the Authority specifies in the notice.

3/Sub-article (2) (a) of this Article shall not apply when the tax declaration already filed is a self-assessment declaration.

4/The Authority shall not be bound by a tax declaration or information provided by, or on behalf of, a taxpayer and the Authority may determine a taxpayer's tax liability based on any reliable and verifiable sources of information available to the Authority.

To read a full article clicks the link: - https://tinyurl.com/pxb376cv

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

01 Feb, 06:56


https://youtu.be/A8j5iSHtaeU?si=FxvSMonKKn35tIDH

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

31 Jan, 20:25


ውድ ግብር ከፋያችን!
የታህሳስ ወር 2017 ተጨማሪ እሴት ታክስ የማስወቂያ እና መክፈያ ጊዜ ከጥር 1 እስከ ጥር 30 ቀን 2017 በመሆኑ በወቅቱ ባለማሳወቅና ባለመክፈል በታክስ አስተዳደር የተጣሉ ቅጣቶች የሚያስከትል መሆኑን አዉቀዉ በቀሩት ቀናት በኢ-ፋይሊንግ ሲስተም እንዲያስታወቁ እያሳሰብን ለሚያስፈልግ ማንኛዉም ድጋፍ ሜክሲኮ ገነት ሆቴል ፊትለፊት ካሳ ግራንድ ሞል በሚገኘው ቢሯችን 5ኛ ፎቅ በአካል በመገኘት ወይም ከታች በተገለጹ ስልክ ቁጥሮች በመደወል ማንኛዉንም ድጋፍ መጠየቅ እንደሚችሉ እናሳውቃለን፡፡
የኢ-ታክስ ማሳወቂያ IP Address https://etax.mor.gov.et/Login/Login ይጠቀሙ፡፡
በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ገቢዎች ሚኒስቴር
የመካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር 2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት
Follow our Social Media pages at:
Facebook: -https://web.facebook.com/info.mto2/
Telegram: - https://t.me/mormto2
YouTube: - http://www.youtube.com/@MinistryofRevenues-MTO2
E-mail:- [email protected]
Telephone: - 011-5-58-46-41 /011-5-58-30-02/

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

31 Jan, 13:15


ለርቀት የሞጁለር ሰልጣኞች ገለፃ ተካሄደ
******************************************


(ጥር 23/2017 ዓ.ም፡ መካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት)

ለድርጅት ባለቤቶችና ስራ አስኪያጆች ም/ስራ አስኪያጆችና የሒሳብ ክፍል ኃላፊዎች በቀጥተኛ ታክሶችን የተመለከተውን የክፍል አንድ የሞጁለር ስልጠና ገለፃ ተሰጠ፡፡


ቀጥተኛ የሆኑ የታክስ ዓይነቶችን ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ እና የወጪ መጋራት፣ ከቤት ኪራይ እና ከንግድ ስራ የሚገኝ ገቢ ግብር እንዲሁም ከተከፋይ ሂሳቦች ላይ ታክስ ቀንሶ የማስቀረት አስተዳደርን እና የሂሳብ መዝገብ አያይዝን በተመለከተ ያሉ አዋጆች፣ ደንቦችና መመሪያዎች እንዲሁም የታክሶቹ ምጣኔዎች ላይ ገለፃው በወ/ሪት ንፅህት አሰፋ የታክስ ከፋዮች ትምህርት ዋና መሪ ባለሙያ ተሰጥቷል ፡፡

ከታክስ ህጎችና መመሪያዎች እንዲሁም ደንቦች ጋር በተያያዘ ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡


ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

30 Jan, 13:22


ቀጥተኛ ያልሆኑ ታክሶች /Indirect Tax/ ላይ ስልጠና ተጀመረ
********************
(ጥር 22/2017 ዓ.ም፡ መካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት)

በገቢዎች ሚኒስቴር የመካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር 2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ለአስራ ሰባተኛ ዙር ሰልጣኞች ቀጥተኛ ያልሆኑ ታክሶች/Indirect Tax/ የተመለከተውን የክፍል ሁለት ስልጠና ዛሬ ጥር 22 ቀን 2017ዓ.ም መስጠት ጀመረ፡፡

ስልጠናው አዲሱን የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ መሰረት ያደረገ ሲሆን የታክሱ ሽፋን፣ ኃላፊነት የተጣለባቸው ግለሰቦችና ድርጅቶች፣ የታክሱ ምጣኔ እንዲሁም በአዲሱ አዋጅ ተካተቱ ለውጦች ላይ በስፋት ማብራሪያ በወ/ሮ ካሰች አስራት የታክስ ከፋዮች ትምህርት መሪ ባለሙያ ተሰጥቷል፡፡

ኤክሣይዝ ታክስ፣ የሱር ታክስ አስተዳደር፣ የቴምብር ቀረጥ እና ሥርዓት እንዲሁም የሽያጭ ታክስ (Turn over tax) በክፍል ሁለት የሚሰጡ ቀጥተኛ ያልሆኑ/Indirect Taxes አይነቶች ናቸው፡፡

ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

30 Jan, 05:47


ውድ ግብር ከፋያችን!!
በQR ኮድ የተደገፈ የማንዋል ደረሰኝ ከየካቲት 3/2017 ዓ.ም ጀምሮ በመላው ሀገራችን ተግባራዊ ይደረጋል፡፡ ስለሆነም ግብር በምትከፍሉበት ቅ/ፅ/ቤት ወይም ታክስ ማዕከል የጊዜ ገደቡ ከመጠናቀቁ በፊት የደረሰኝ ህትመት ጥያቄ በማቅረብ ከብርሃን እና ሰላም ማተሚያ ድርጅት በማሳተም በግብይታችሁ ጥቅም ላይ እንድታውሉ እናሳስባለን፡፡
የገቢዎች ሚኒስቴር

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

29 Jan, 17:19


ለግብር ከፋዮቻችን በሙሉ
የኢ-ታክስ ማሳወቂያ IP Address ማስተካከያ በመደረጉ ምክንያት ከዚህ በፊት ስትጠቀሙበት የነበረው ሊንክ አገልግሎት የማይሰጥ ስለሆነ ለተፈጠረው የአግልግሎት አሰጣጥ መስተጓጎል ይቅርታ እየጠየቅን በሚከተለው ሊንክ እንድትጠቀሙ እንጠይቃለን፡፡
https://etax.mor.gov.et/Login/Login

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

29 Jan, 13:06


*******************************

ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ወደ ሀገር የሚገቡ ዕቃዎች ከታክሱ ነጻ ተደርገዋል፡-

 በቪዬና የዲፕሎማቲክ ግንኙነት ኮንቬንሽን ሚሲዮኖች፣ ዲፕሎማቶች ወይም የኩንሱላር ጽ/ቤቶች ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነጻ እስከሆኑ ድረስ እነዚህ ሚሲዮኖች፣ ዲፕሎማቶች ወይም የኩንሱላር ጽ/ቤቶች ወደ አገር የሚያስገቡዋቸው ዕቃዎች፤

 በዓለም ዐቀፍ ስምምነት ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ የተደረጉ ዓለም ዐቀፍ ድርጅቶች ወደ አገር የሚያስገቧቸው ዕቃዎች፤

 በፋይናንስ፣ በቴክኒክ፣ በሰብዓዊ ዕርዳታ ወይም በአስተዳደር ድጋፍ የዓለም ዐቀፍ ስምምነት ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነጻ እስከተደረገ ድረስ የውጭ አገር መንግሥት ወደ አገር የሚያስገባቸው ዕቃዎች፤

 በጉምሩክ ደንብ ከጉምሩክ ቀረጥ ነፃ እስከተደረገ ድረስ መንገደኛው ይዞት የሚመጣ የግል መገልገያ ዕቃ፤

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ፡-https://tinyurl.com/5n86h45k

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

29 Jan, 12:22


የገፅ ለገፅ ገለፃ ተሰጠ
***********
(ጥር 21/2017 ዓ.ም፡ መካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት)


የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር አውጥተው ምንም ዓይነት የታክስ አካውንት ላልከፈቱ ባለሀብቶች የገፅ ለገፅ ገለፃ ተደረገ፡፡

ማንኛውም ገቢ የሚያገኝ ሰው ግብር የመክፈል ግዴታ እንዳለበት የገቢ ግብር አዋጁ አንቀጽ 9 እንደሚደነግግ በመጥቀስ በግብር ከፋይነት ስለመመዝገብ፣ ለታክስ ከፋይነት የመመዝገብ ግዴታ ያለባቸው ሰዎች፣ የታክስ ደረሰኝ አጠቃቀም እና አስተዳደር፣ አስተዳደራዊ ቅጣት/Administrative penalties እንደሚያስከትል ገለፃ ከተሰጠባቸው ርዕሰ ጉዳዮች ውስጥ ይገኙበታል፡፡

በተጨማሪም ከተከፋይ ሂሳብ ላይ የተቀነሰ ግብር(WITHHOLDING TAX)፣ የስራ ግብር (EMPLOYMENT INCOME TAX)፣ የጡረታ (PENSION) ቆርጠዉ በማስቀረት ማሳወቅ እና መክፈል እንዳለባቸዉ እንዲሁም ንግድ ፍቃድ አዉጥተዉ ስራ በሚጀምሩበት ጊዜ ንግድ ትርፍ ግብር፣ የአክሲዩን ትርፍ ድርሻ፣ ተጨማሪ እሴት ታክስ የሚከፈልበት አቅርቦት፣ ኤክሳይስ ታክስ (ምርቶቹ ኤክሳይስ ታክስ የሚከፈልባቸው ከሆነ) የታክስ አካውንት/ Tax account በመክፈት ግብራቸውን በወቅቱ አሳውቀው መክፈል እንደሚገባቸው ተገልጾል፡፡ ገለፃው በአቶ አወቀ ግዛው የታክስ ከፋዩች ትምህርት ከፍተኛ ባለሙያ ተሰጥቷል፡፡

ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

28 Jan, 13:11


"የጀመርነውን የትሪሊየን ጉዞ ለማስቀጠል አገልግሎት አሰጣጣችንን ቀልጣፋ ማድረግ ወሳኙ ቁልፍ ነው!" ወ/ሮ አስቴር አዱኛ
******************************************
(ጥር 20/2017 ዓ.ም፡ መካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት)


በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ለሚገኙ የስራ ሂደት፣ ቡድኖችና ባለሙያዎች አድቫስድ ኤክሴል (Advanced Excel) ላይ ለአምስት ቀናት ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ፡፡

ስልጠናው በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የሰው ሀይል ስራ አመራርና ልማት የሥራ ሂደት አዘጋጅነት ከዋናው መስሪያቤት በተጋበዙ አሰልጣኞች የተሰጠ ሲሆን ከስራቸው ጋር ቀጥታ ግንኙነት ያላቸው ባለሙያዎች ተሳትፈውበታል፡፡ የተሻለ የመረጃ አያያዝ፣ አጠቃቀም እና ትንተና ስርዓትን በመዘርጋት ለግብር ከፋዩ ወቅታዊና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት ለገቢ አሰባሰቡ ምቹ መደላደል መፍጠር የስልጠናው ዋና ዓለማ ነው፡፡

የስልጠናው ተሳታፊዎችም አንደገለፁት ስልጠናው ለስራቸው ተጨማሪ አቅም እንደሆነላቸው እና በማንኛውም ቦታ ላይ መተግበር የሚያስችላቸው በመሆኑ ደስተኞች መሆናቸውን ገልፀው የስልጠናው ጊዜ ትንሽ ቀናቶች ተጨምረውበት ሰፋ ቢል የሚል አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡

እንደ ወ/ሮ አስቴር አዱኛ የተቋማዊ አቅም ግንባታ ዘርፍ ም/ሥራ አስኪያጅ ገለፃ ሀገራችን ገቢን በተመለከተ ወደ ትሪሊየን የተሸጋገረችበት ወቅት ነው ሚኒስቴር መስሪያቤቱም አገልግሎት አሰጣጡን ፈጣን እና ቀልጣፋ ለማድረግ የዲጂታል ቴክኖሎጂዎች እየተጠቀመ ይገኛል፡፡ እንደ ቅርንጫፍ ጽ/ቤታችንም የጀመርነውን የትሪሊየን ጉዞ ለማስቀጠል አገልግሎት አሰጣጣችን ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም ቀልጣፋና ፈጣን ማድረግ ያስፈልጋል ሰልጣኞችም የወሰዳችሁትን ስልጠና ተግባር ላይ በማዋል ለግብር ከፋዩ ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት የገቢ ዕቅዳችን ግብ እናሳካለን የሚል መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ አክለውም በቀጣይም ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የተለያዩ ስልጠናዎችን ለሰራተኞቹ በስፋት እንደሚሰጥ ጠቁመዋል፡፡


ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

24 Jan, 12:39


የማጠቃለያ ፈተና ተሰጠ
****************************
16/5/2017ዓ.ም

በሶስት ክፍሎች ተከፋፍሎ የሚሰጠውን የርቀት ሞጁለር ሥልጠና ላጠናቀቁ የድርጅት ባለቤት እና ሥራ አስኪያጆች የስልጠና ማጠቃለያ ፈተና ዛሬ ጥር 16 ቀን 2017ዓ.ም ተሰጠ፡፡

ሰልጣኞች በሶስት ክፍሎች ተከፋፍሎ የሚሰጠዉን የሞጁለር ስልጠና በአግባቡ ተከታተለው ያጠናቀቁ ናቸው፡፡

ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

23 Jan, 12:35


ከተከፋይ ሂሳቦች ላይ ታክስ ቀንሶ የማስቀረት አስተዳደር (withholding tax) ስልጠና ተሰጠ

(ጥር 15/2017ዓ.ም፡ መካከለኛ ግብር ካፋዮች ቁጥር 2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት)
ቀጥተኛ በሆኑ የታክስ ዓይነቶች ላይ ለ17ኛ ዙር ሰልጣኞች ሲሰጥ የነበረዉ የክፍል አንድ ስልጠና የተጠናቀቀ ሲሆን የዛሬው ስልጠና ከተከፋይ ሂሳቦች ላይ ታክስ ቀንሶ የማስቀረት አስተዳደር (withholding tax) የተመለከተ ነበር፡፡

ስልጣኞች በክፍል አንድ ስልጠናቸው ከመቀጠር የሚገኝ ግብር፣ የወጪ መጋራት አከፋፈል ሥርዓትን፣ ከንግድ ስራ የሚገኝ ገቢ ግብር፣ እንዲሁም የዛሬውን ስልጠና ከተከፋይ ሂሳቦች ላይ ታክስ ቀንሶ የማስቀረት አስተዳደር ስርዓት (withholding tax) በተመለከተ በሰፊው ስልጠና የተሰጠባቸው ርዕሰ ጉዳዮች ናቸው፡፡

የዛሬው ስልጠና በወ/ት ንጽህት አሰፋ የታክስ ከፋዮች ትምህርት ዋና መሪ ባለሙያ የተሰጠ ሲሆን ስለ ቅድመ ግብር ምንነትን እና ዓይነቶችን ፣ ግብር ቀንሰው ገቢ እንዲያደርጉ ግዴታ የተጣለባቸው ሰዎች/ ድርጅቶች መቼ፣ ከማን እና እንዴት ግብር ቀንሰው ገቢ ማድረግ እንደሚገባቸው ፣ግብር ቀንሶ የመያዝ ግዴታ የማይመለከታቸውን ሰዎች እና ግብይቶች ፣ ከተከፋይ ሂሳቦች ላይ ግብር ቀንሶ አለማስቀረት /ግዴታን/ አለመወጣት የሚያስከትለውን ውጤት በስልጠናው የተብራሩ ርዕሰ ጉዳዮች ናቸው፡፡
ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

23 Jan, 12:26


ቀጥተኛ ያልሆኑ ታክሶች ላይ ገለፃ ተካሄደ
*************************************
(ጥር 15 ቀን 2017ዓ.ም፡ መካከለኛ ግብር ካፋዮች ቁጥር 2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት)
ቀጥተኛ ያልሆኑ ታክሶች ላይ ያተኮረውን የክፍል ሁለት ስልጠና ለርቀት ሰልጣኞች ለድርጅት ባለቤቶች፣ ስራ አስኪያጆች፣ ም/ስራ አስኪያጆች እና የሒሳብ ክፍል ኃላፊዎች በታክስ ከፋዮች ትምህርት መሪ ባለሙያ በወ/ሮ ካሰች አስራት ገለፃ ተሰጠ፡፡

የታክሶቹ ምንነት፣ አከፋፈል እና ምጣኔ፣ ታክሶቹ የሚከፈልባቸው አቅርቦቶች የሚከናወኑበት ቦታ፤ ጊዜ እና ዕሴት ላይ በቂ እውቀት እንዲኖራቸዉ እና ሕግ እና ሥርዓቱን መሠረት በማድረግ ወቅቱን ጠብቀው ግብራቸውን አሳውቀው እንዲከፍሉ ማድረግ የገለፃው ዋና ዓላማ ነው፡፡

ሰልጣኞች ስልጠናቸውን በርቀት የሚከታተሉ እና የክፍል አንድ ስልጠና በአግባቡ ተከታትለው ያጠናቀቁ ሲሆን በቀጣይም የታክስ አስተዳደር ላይ የሚያተኩረውን የክፍል ሶስት ስልጠና ይወስዳሉ፡፡

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2
ስልክ፡-0115582842
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

22 Jan, 08:50


https://youtu.be/wk77LmugKAc

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

22 Jan, 08:39


Follow our Social Media pages at:

Facebook: - ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
Telegram: - https://t.me/mormto2
YouTube: - http://www.youtube.com/@MinistryofRevenues-MTO2
E-mail:- [email protected]
Telephone: - 0115582842

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

22 Jan, 05:59


የታክስ ስርዓት ዘርፍ የ2017 በጀት ዓመት የስድስት ወር ዕቅድ አፈፃፀምውይይት አካሄደ፡፡
********************************************************************************
(ጥር 13 ቀን 2017ዓ.ም ፡ መካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር 2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት)
የታክስ ስርዓት ዘርፍ በስሩ ከሚገኙ የታክስ ኦዲት የሥራ ሂደት፣የስጋት ስራ አመራርና የህግ ተገዥነት የስራ ሂደት፣የታክስ መረጃና የሽ/መ/መ አስተዳደር የስራ ሂደት ፣ የታክስ ከፋዮች ትምህርትና መረጃ አቅርቦት የስራ ሂደት እና በስራ ሂደቶቹ ስር ከሚገኙ ቡድኖች ጋር የ2017 በጀት ዓመት የ6 ወር ዕቅድ አፋፃፀም ውይይት አድርጓል፡፡

በውይይቱ እያንዳንዱ የስራ ክፍል በዚህ ስድስት ወር የተከናወኑ የዋና ዋና ስራዎች ሪፖርት እና በስራ ወቅት የገጠሙ ተግዳሮቶች እንዲሁም የተወሰዱ መፍትሄዎችን በተመለከተ በስራ ሂደት አስተባባሪዎች ዝርዝር ሪፖርት የቀረበ ሲሆን ባጠቃላይ የተሰሩ ስራዎች ዉጤት የሚለካዉ እንደ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የተሰጠን የገቢ ዕቅድ በተሳካ ሁኔታ መፈጸም እንደመሆኑ ለሚሰበሰበዉ ገቢ ያለውን ድርሻ ፤ባለሙያው ስነ-ምግባርን ተላብሶ የተሰጠውን ተልዕኮ ከመፈፀም አንፃር ያለው ቁርጠኝነት እንዴት ነው የሚሉት በውይይቱ የተነሱ ዋና ዋና ነጥቦች ናቸው፡፡

በቀረቡ ሪፖርቶች እና አስተያየቶች መሰረት ቀጣይ አቅጣጫ ያስቀመጡት የታክስ ስርዓት ዘርፍ ም/ሥራ አስኪያጅ የሆኑት ወ/ሮ ሮዛ ጀማል በ6 ወር ውስጥ የነበሩትን ጠንካራ ጎኖች በማስቀጠል እና እያንዳንዱ የስራ ክፍል ያሉበትን ክፍተቶች ለይቶ በመውሰድ እና በማሰተካከል በቀጣይ ወራቶች የተሻለ ገቢ ለመሰብሰብ እርብርብ ማድረግ ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡

በማጠቃለያ የሰራተኛው የስራ ስዓት አጠቃቀም እና የደንብ ልብስ ጋር ተያይዞጠበቅ ያለ አቅጣጫ አስቀምጠዉ ዉይይቱ ተጠናቆል ፡፡

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

13 Jan, 07:24


የመጀመሪያው ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄ ይገኛል

ጥር 05/2017 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)

የገቢዎች ሚኒስቴር እና የጉምሩክ ኮሚሽን የ2017 በጀት ዓመት የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም የግምገማ መድረክ በቢሾፍቱ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል፡፡

በመድረኩም የገቢዎች ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሴ፣ የታክስ ስርዓት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ መስከረም ደበበ፣ የታክስ ኦፕሬሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ አብዱራህማን ኢድ ጣሂር፣ የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ክቡር ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ፣ ምክትል ኮሚሽነር ክበርት ምስራቅ ማሞ፣ ምክትል ኮሚሽነር ክብርት ሙሉወርቅ ደረሰ፣ ምክትል ኮሚሽነር ክቡር አዝዘው ጫኔ፣ የሁለቱ ተቋማት ዳይሬክተሮች እንዲሁም የቅ/ጽ/ቤት ስራ አስኪያጆች እና ምክትል ስራ አስኪያጆች እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡

መድረኩ በአባገዳ እና አደስንቄ ምረቃ የተጀመረ ሲሆን እንደ 2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ግማሽ ዓመት በታክስ እና ጉምሩክ ተግባራት አፈፃፀም በታዩ ውጤታማ አፈፃፀሞች እንዲሁም የታዩ ክፍተቶች ዙሪያ ሪፖርት ቀርቦ ሰፊ ውይይት እንደሚካሄድ ተጠቅሷል፡፡

በመጨረሻም በቀጣይ ስራዎች ዙሪያ አቅጣጫ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በተክሉ ኤልያስ
ፎቶ፡- እስካለም ሰፊው

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

11 Jan, 06:57


የተመዘገበ ሰው ግዴታዎች
**********************************

ታክስ የሚከፈልበትን የስራ እንቅስቅሴ በማይንቀሳቀስ የሥራ ቦታ የሚያከናውን ማናቸውም የተመዘገበ ሰው-

✓ ታክስ የሚከፈልበትን እንቅስቃሴ በሚያካሂድበት ዋንኛ የስራ ቦታ በግልጽ በሚታይ ሥፍራ ዋናውን የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ የምስክር ወረቀት የመለጠፍ፣

✓ የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ የምስክር ወረቀት ቅጂ ታክስ የሚከፈልበት እንቅስቃሴ በሚያካሂድባቸው ሌሎች የስራ ቦታዎች ሁሉ በግልጽ በሚታይ ሥፍራ የመለጠፍ፣ ግዴታ አለበት፡፡

 የተመዘገበ ሰው ለተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገበበትን ዝርዝር መረጃ ታክስ የሚከፈልበትን ስራ በሚያከናውንበትን ዌብሳይት፤ የማህበራዊ ሚዲያ እና ሌላ የኤሌክትሮኒክ መድረክ ላይ ማስፈር አለበት፡፡

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ፡- https://tinyurl.com/762f5ev6

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

10 Jan, 08:09


የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ስኬታማነት ለማስቀጠል ገቢን በአግባቡ መሰብሰብ ይገባል፡- አቶ አሕመድ ሽዴ
**************

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ስኬታማነት ለማስቀጠል የታክስ መሰረቱን በማስፋት ገቢን በአግባቡ መሰብሰብ እንደሚገባ የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ገለጹ።

የፌደራልና የክልል የፋይናንስ፣ የገቢዎች እና የፕላን መስሪያ ቤቶች የምክክር መድረክ በጅማ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ በመድረኩ እንደገለፁት፤ ባለፉት ስድስት ዓመታት በተደረገው የኢኮኖሚ ማሻሻያ ሥራ ጠንካራ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል።

በኢትዮጵያ ከፍተኛ የልማት ሥራዎች መካሄዳቸውንና የተለያዩ ድጎማዎችን ተከትሎ የመንግስት ወጪ ከፍ ማለቱን የጠቀሱት ሚኒስትሩ፤ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ በአግባቡ መሰብሰብ እንደሚገባም ገልፀዋል።

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ስኬታማነት ለማስቀጠል የታክስ መሰረቱን በማስፋት በፌደራልም ሆነ በክልሎች ገቢ ላይ በትኩረት መስራት ያስፈልጋል ተብሏል።

በምክክር መድረኩ የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ፣ የገቢዎች ሚኒስትር አይናለም ንጉሴ እንዲሁም የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋን (ዶ/ር) ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የፌደራልና የክልል የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተሳታፊ ሆነዋል።

በገንዘብ ሚንስቴር የተዘጋጀው የውይይት መድረክ ለሁለት ቀናት የሚቆይ ሲሆን፣ በሀገሪቱ ዘመናዊ የታክስ አሰባሰብ፣የክፍያ ሥርዓትና በጀትን በአግባቡ ለመጠቀም የጋራ አደረጃጀት እንደሚፈጥርም ይጠበቃል።

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

09 Jan, 12:13


የክፍል ሁለት ፈተና ተሰጠ
*******************


የክፍል ሁለት ስልጠናን ወስደው ላጠናቀቁ የአስራ ስድስተኛ ዙር ሰልጣኞች የማጠናቀቂያ ፈተና ዛሬ ጥር 1 ቀን 2017 ዓ.ም ፈተና ተሰጠ፡፡


ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

06 Jan, 06:50


መረጃው ለሁሉም ግብር ከፋዮች እንዲደርስ ያጋሩት

ታሕሳስ 28/2017 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)

የገቢዎች ሚኒስቴር ግብር ከፋዮችን በግብር ሕግ ተገዥነታቸው ልክ እየለየ እውቅና እና ሽልማት መስጠት ከጀመረ ዓመታት መቆጠሩ ይታወቃል፡፡ ግብር ከፋዮቹንም በአንጻራዊነት የሚለይበት የመመዘኛ መስፈርቶችን በገቢ እና በጉምሩክ ዘርፍ ለይቶ በማዘጋጀት እየሰራ ይገኛል፡፡

ይሁን እንጂ በተለየዩ ጊዜያት አጭበርባሪዎች ይህንን እንደአጋጣሚ በመጠቀም በሐሰተኛ ማንነት ከገቢዎች ሚኒስቴር ለድርጅቶች ባለቤት ወይም ሥራ አስኪያጆች በተንቀሳቃሽ ስልክ እንደተደወለ በማስመሰል ለሽልማት ብቁ እንድትሆኑ እናደርጋለን በማለት በስልክ በማስፈራራትና በማደናገር ገንዘብ ለመቀበል የሚጥሩ አካላት ስልቶችን በመቀያየር ግብር ከፋዩን በማጭበርበር ላይ ናቸው፡፡

በመሆኑም በዚህ መልክ የሚፈፀሙ የማጭበርበር ወንጀሎችን ለመከላከል ግብር ከፉዩ እና ማህበረሰቡ ከአጭበርባሪዎች እራሳችሁን እንድትጠብቁ ሚኒስቴሩ ያሳስባል።

የገቢዎች ሚኒስቴር

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

04 Jan, 12:05


እናስታዉስዎ!

በቀሪ ቀናት ሊኖር ከሚችል አላስፈላጊ ወረፋ ይድኑ ዘንድ በወቅቱ የሚጠበቅብዎትን ኃላፊነት ይወጡ!

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

27 Dec, 06:10


https://youtu.be/FjaQmYZs57Y

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

27 Dec, 06:09


380 ቢሊየን ብር ገቢ ተሰበሰበ

ታሕሳስ 18/2017 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)

ባለፉት አምስት ወራት 380 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡን የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የገቢዎች ሚኒስትር ዓይናለም ንጉሴ ገለፁ።

ሚኒስትሯ ባለፉት የለውጥ አመታት የገቢ አሰባሰብ አፈጻጸምን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ፤ በሀገር ደረጃ የተያዙ የልማት ዕቅዶችን ተግባራዊ ለማድረግ ዋነኛ አቅም ተደርጎ የሚወሰደው የሀገር ውስጥ ገቢን ማሻሻልና ማሳደግ ነው ብለዋል።

ይህም የህዝብ የልማት ፍላጎትን ደረጃ በደረጃ የሚመልሱ መሰረተ ልማቶችን መገንባት እንደሚያስችል ገልጸው፤ ከዚህ አኳያ በገቢ አሰባሰብ ሂደቱ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የገቢ አቅምን ማሻሻል የሚያስችሉ መሰረታዊ ለውጦች መከናወናቸውን ተናግረዋል።

ለአብነትም የፖሊሲና የህግ ማዕቀፎችን ማሻሻልና አገልግሎት አሰጣጡን ማሳለጥ የሚያስችሉ የቴክኖሎጂ አሰራሮችን መዘርጋት መቻሉን አንስተው፤ ማሻሻያዎቹ በገቢ አሰባሰብ ሒደቱ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት እንዳስቻሉ አመልክተዋል።

በዚህም በ2010 ዓ.ም የፌደራል ገቢ 176 ቢሊየን ብር እንደነበር አስታውሰው÷ አሁን ላይ በአምስት ወር ብቻ 380 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡን ተናግረዋል።

እንደ ሀገር የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ሊደግፍ የሚችል እና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ እንዲኖር የገቢ አሰባሰብ ሂደት ላይ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።

ባለፉት የለውጥ ዓመታት የኢትዮጵያን የብልፅግና ጉዞ ሊደግፍ የሚችል የሀገር ውስጥ የፋይናንስ አቅም መገንባቱንም አረጋግጠዋል።

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

26 Dec, 13:07


ለተቋሙ ሰራኞች የሚሰጠው ስልጠና ቀጥሏል

*****************************
(ታህሳስ 17/2017 ዓ.ም፡ መካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት)


ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የሰራተኛውን አቅም ለመገንባ እየሰጠ ያለውን ስልጠና አጠናክሮ በመቀጠል ከተለያዩ የስራ ክፍሎች ለተውጣጡ ሰራተኞች ለሁለተኛ የዳታዌርሀውስ (Data warehouse) እና አድቫንስድ ኤክሴል (Advanced Excel) ላይ ለሁለት ቀን የሚቆይ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል፡፡

የስልጠናው ተሳታፊዎች ቀጥታ ከስራው ጋር ግኑኝነት ያላቸው እና በሰራተኞች ላይ ያለውን የክህሎት ክፍተት በመሙላት የሰራተኛውን አቅም በመገንባት ውጤታማ የገቢ አሰባሰብ ሂደት መዘርጋት የስልጠናው ዋና ዓላማ መሆኑን ወ/ሪት ሄለን አስፋው የስልጠና ምልመላ ከፍተኛ ባለሙያ ገልፀዋል፡፡ ስልጣኖች ብዙ አዳዲስ ነገሮችን ያገኙበት እና ከስራቸው ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያለው በመሆኑ የክህሎት ክፍተታውን በመሙላት ጥራት ያለው አገልግሎት ለግብር ከፋዩ ለመስጠት እንደሚያግዛቸው ጠቁመዋል፡፡

ስልጠናው በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የሰው ሀይል አመራርና ልማት የሥራ ሂደት አዘጋጅነት በአቶ ዮሴፍ መለስ የታክስ ከፋዮች ስጋት ስራ አመራር ቡድን አየተሰጠ ይገኛል፡፡ አቶ ዮሴፍ እንደገለፁት ስልጠናው በዋናነት ሁለት መሰረታዊ ዕውቀቶች ላይ ያተኮረ ነው አንደኛው የተቋሙን የመረጃ ቋት እና አድቫንስድ ኤክሴልን የተመለከተ ሲሆን መረጃዎችን በቀላሉ ለማግኘት፣ የዳታ ንፅፅሮሽን ለመስራት፣ የሶስተኛ ወገን መረጃን ለማግኘት እና ውሳኔዎችን መረጃ ላይ ተመስርቶ በወቅቱ ለመስጠት ስልጠናው አጋዥ መሆኑን ገልፀዋል፡፡


ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

26 Dec, 11:34


የክፍል አንድ ገለፃ ተደረገ
************************
(ታህሳስ17/2017ዓ.ም፡ የመካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር 2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት)


ቀጥተኛ ታክሶችን የተመለከተውን የክፍል አንድ የሞጁለር ስልጠና ስልጠናቸውን በርቀት ለሚከታተሉ ድርጅት ባለቤቶች፣ ስራ አስኪያጆች፣ ም/ስራአስኪያጆች እና ለሂሳብ ክፍል ኃላፊዎች ተሰጠ፡፡

ቀጥተኛ የሆኑ የታክስ ዓይነቶች ላይ ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ እና የወጪ መጋራት ፣ ከቤት ኪራይ እና ከንግድ ስራ የሚገኝ ገቢ ግብር እንዲሁም ከተከፋይ ሂሳቦች ላይ ታክስ ቀንሶ የማስቀረት አስተዳደርን (Withholding) እና የሂሳብ መዝገብ አያይዝን በተመለከተ ያሉ አዋጆች፣ ደንቦችና መመሪያዎች እንዲሁም የታክሶቹ ምጣኔዎች እና የአሰራር ስርዓቶች ላይ ገለፃ ተሰጥቷል፡፡ ገለፃው በወ/ሮ ካሰች አስራት የትምህርት መሪ ባለሙያ እና በአቶ አወቀ ግዛው የትምህርት ከፍተኛ ባለሙያ ተሰጥቷል፡፡


በስልጠናው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት ወ/ሮ ሀና ንጉሴ የታክስ ከፋዮች ትምህርትና መረጃ አቅርቦት የስራ ሂደት ስራ አስኪያጆችና ባለቤቶች የታክስ ህጉን አዉቀዉ ድርጅታቸዉን መምራት እንዲሁም የታክስ ህጉን በማክበር በፍቃደኝነት ታክስ የማሳወቅ እና የመክፈል ባህል እንዲያጎለብቱ እንዲሁም ትክክለኛ ግብር ለመክፈል ትምህርቱ ይጠቅማል ያሉ ሲሆን ሃላፊነቸዉን ለመወጣት እና ህጉን ለማወቅ መምጣታቸውን አድንቀው አጠቃላይ የሞጁለር ስልጠናው ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡


ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

26 Dec, 10:49


የማጠቃለያ ፈተና ተሰጠ
****************************


በሶስት ክፍሎች ተከፋፍሎ የሚሰጠውን አስራ ሶስት ሞጁሎችን ላጠናቀቁ 14ኛ እና 15ኛ ዙር የሞጁለር ትምህርት ሰልጣኞች የክፍል ሶስት ስልጠና ማጠቃለያ ፈተና ዛሬ ታህሳስ 17 ቀን 2017ዓ.ም ተሰጠ፡፡

ሰልጣኞች በክፍል ሶስት ስልጠናቸው የታክስ አሰተዳደርን የተመለከቱ የተለያዩ አዋጆች፣ መመሪያዎች እና ደንቦች ላይ ስልጠናቻውን በአግባቡ ተከታተለው ያጠናቀቁ ናቸው፡፡

ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

07 Dec, 08:22


https://www.youtube.com/watch?v=pE9YnUWxGis

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

06 Dec, 08:15


1) በአንድ የታክስ ጊዜ ማንኛውም ታክስ ከፋይ መክፈል ለሚገባው ታክስ በሚያገኘው ማስረጃ ላይ በመመሥረት የስጋት ታክስ ስሌት ሊያዘጋጅ ይችላል፡፡

2) ተፈጻሚ ሊሆን የሚችለው፦

ሀ) ታክስ ከፋዩ ለታክስ ጊዜው የታክስ ማስታወቂያ ያላቀረበ እንደሆነ፤ እና
ለ) ታክሱ በታክስ ስሌት የሚሰበሰብ ሲሆን ብቻ ነው፡፡

3) የስጋት ታክስ ስሌት፦

ሀ) ታክስ ከፋዩ ለታክስ ጊዜው የታክስ ማስታወቂያ የሚያቀርብበት ቀን ከመድረሱ በፊት ሊዘጋጅ ይችላል፤ እንዲሁም
ለ) በሚዘጋጅበት ጊዜ ፀንቶ ባለ ሕግ መሠረት መዘጋጀት አለበት፡፡

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ፡-https://t.ly/qhYJg

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

19 Nov, 07:45


•ንግድ ስራ ፈቃድ ወይም የሙያ ፈቃድ ለማደስ፣

•ጨረታ ለመካፈል ወይም ለመሳተፍ፣

•ለተሽከርካሪዎች ወይም ለኮንስትራክሽን ማሽነሪዎች ዓመታዊ ምዝገባና ምርመራ /ክላውዶ/ ለማድረግ፣

•የባንክ ብድር ለማግኘት፣

•የመድን ካሳ ለማግኘት፣

•የድርጅት ስም ወይም አድራሻ ለመለወጥ፣

•የንግድ ስራ ሀብት መቀነስን ሳይጨምር የንግድ ዘርፍ ቅነሳ ለማድረግ፣

•የግል ድርጅቶች ማህበራዊ ዋስትና የጡረታ መዋጮ ስለመከፈሉ ማረጋገጫ ለማግኘት፣

ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

18 Nov, 12:20


"የህልም ጉልበት፤ ለዕምርታዊ ዕድገት"
******************************
(ህዳር 9/2017ዓ.ም፡ የመካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር 2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት)

"የህልም ጉልበት፤ ለዕምርታዊ ዕድገት" በሚል መሪ ሀሳብ ለቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የስራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች የዙም ስልጠና ተሰጠ፡፡

ወ/ሮ አስቴር አዱኛ የተቋማዊ አቅም ግንባታ ዘርፍ ም/ስራ አስኪያጅ ባስተላለፉት የመክፈቻ ንግግር እንደገለፁት ስልጠናውን በአግባቡ በመከታተል በተለያዩ ዘርፎች የሀገራችን ብልፅግናና እድገት እውን ለማድረግ እየተሰሩ ያሉትን ዘመን ተሻጋሪ ስራዎች ለማስቀጠል የሰራተኛው ሚና የማይተካ መሆኑን ጠቁመው ስልጠናውን በንቃት መከታተል እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል፡፡

በስልጠናው ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ እንደገለፁት ስልጠናው አሁን ሀገራችን ያለችበትን ደረጃ ሰራተኛው ማስገንዘብ እና ከፊታችን የሚጠብቁንን ትልልቅ ስራዎች በብቃት ለማሳካት ቁርጠኛ የሆነ ሰራተኛ እንደሚያስፈልግ እና በስልጠናውም የእኔ ድርሻ ምንድነው ለሀገሬ ምን አስተዋፅዖ አመጣለው የሚለውን ማስረፅ የሥልጠናው ዓላማ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡

"የህልም ጉልበት፤ ለዕምርታዊ ዕድገት" የሚል ሰነድ በጉምሩክ ኮሚሽን የሕግ-ተገዥነት ምክትል ኮሚሽነር አዘዘው ጫኔ በሰፊው ማብራሪያ የተሰጠበት ሲሆን በቀረበው ሰነድ መነሻነት ከመድረኩ ለተነሱት ጥያቄዎችና አስተያየቶች ከበላይ አመራሮች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡


ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

18 Nov, 12:11


በ24ኛው የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የጎዳና ላይ ውድድር ተሳታፊ የነበሩ የቅርንጫፍ ጽ/ቤታችን ሰራተኞች

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

18 Nov, 05:17


• ውዝፍ የታክስ ዕዳ ወይም ወቅታዊ የታክስ ክፍያ የፈጸመ መሆን፣

• ውዝፍ የታክስ ዕዳ ወይም ወቅታዊ የታክስ ዕዳ ለመክፈል የክፍያ ስምምነት የገባና በውሉ መሠረት እየተከፈለ ስለመሆኑ የሚያሳይ ማስረጃ ማቅረብ፤

• ታክስ ከፋዩ ዓመታዊ የንግድ ትርፍ ግብር ማስታወቂያ እና መክፈያ የመጨረሻ ቀን ከመድረሱ በፊት የንግድ ስራ ፈቃድ ለማደስ፣በጨረታ ለመሳተፍ ፣የባንክ ብድር ለመውሰድ እና የጉዳት ካሳ ለማግኘት የሚቀርብ የታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀት ጥያቄ ከሆነ ጥያቄው ከቀረበበት የግብር ዘመን በፊት ላሉት ጊዜያት ታክሱን አስታውቆ ግዴታዉን የተወጣ ስለመሆኑ፣

• በደረሰው የታክስ ውሳኔ ማስታወቂያ ላይ ቅሬታ ያለው ታክስ ከፋይ በታክስ ውሳኔ ቅሬታ አጣሪ የሥራ ክፍል ወይም ይግባኝ ሰሚ ኮሚሽን ወይም በየደረጃው ለሚገኝ ፍርድ ቤት ቅሬታውን አቅርቦ በመታየት ላይ የሚገኝ ስለመሆኑ የጽሁፍ ማስረጃ ማቅረብ አለበት፡፡

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ፡-https://t.ly/vSqIx

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

13 Nov, 13:46


ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

13 Nov, 13:35


በታክስ አስተዳደር ዙሪያ ገለፃ ተሰጠ
******************************
(ህዳር 4/2017ዓ.ም፡ የመካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር 2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት)


በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ለድርጅት ባለቤቶችና ስራ አስኪያጆች እየተሰጠ ያለው የርቀት ስልጠና በመቀጠል ዛሬ የክፍል ሶስት ገለፃ ተካሄደ፡፡

የዛሬው ገለፃ የታክስ አስተዳደር ጉዳዮች ዙሪያ ያጠነጠነ ሲሆን ገለፃው በወ/ሮ ሀና ንጉሴ የታክስ ከፋዮች ትምህርትና መረጃ አቅርኖት የስራሂደት እና በወ/ሪት ንፅህት አሰፋ የታክስ ከፋዮች ትምህርት ዋና መሪ ባለሙያ በታክስ አስተዳደር ስር ያሉ የተለያዩ አዋጆች፣ መመሪያዎችና ደንቦችን በተመለከተ ገለፃ ተሰጥቷል፡፡

በተጨማሪም በስልጠናው ወቅት ከሽያጭ መመዝገቢያ መሳሪያ እና አጠቃቀም ጋር ተያይዞ ከሰልጣኞች በሰለጠኑት ስልጠና መሰረት አገልግሎት ይሰጣል? በሚለው ላይ በአቶ ቴውድሮስ ጋሻው የታክስ መረጃና የሽ/መ/መ/አስተዳደር የሥራሂደት በክፍሉ ስለሚከናወኑ ተግባራት ገለፃ ያደረጉ ሲሆን አጠቃላይ በታክስ አስተዳደር ዙሪያ ባሉ ጉዳዮች ላይ በአሰልጣኞች ምልሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡

ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

12 Nov, 13:09


አንድ ተቀጣሪ በአንድ ወር ውስጥ ከአንድ በላይ ለሆኑ ቀጣሪዎች የማይሰራ ወይም ግብርን ቀንሶ ገቢ የማድረግ ግዴታ ያለበት ካልሆነ በስተቀር ግብሩን የማስታወቅ ግዴታ የለበትም፡፡

አንድ ተቀጣሪ በአንድ ወር ውስጥ ከአንድ በላይ ቀጣሪዎች ያሉት ወይም ከራስ ገቢ ላይ ግብር ቀንሶ የመያዝ ግዴታ ያለበት እንደሆነ፣ ተቀጣሪው ከየሦስት ወሩ መጨረሻ በኋላ ባሉት 30 ቀናት ውስጥ የግብር ማስታወቂያ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡


አንድ ተቀጣሪ ግብር የማሳወቅ ግዴታ የሌለበት ሲሆን ቀጣሪው ለተቀጣሪው የሚሰጠው ግብር ተቀንሶ ቀሪ መሆኑን የሚያሳየው ደረሰኝ ለዚህ አዋጅና ለታክስ አስተዳደር አዋጅ ዓላማ ሲባል ቀጣሪው በየወሩ መክፈል በሚኖርበት ግብር ላይ እንደተሰጠ የግብር ውሳኔ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

12 Nov, 11:58


ቀጥተኛ በሆኑ ታክሶች ላይ ስልጠና ተጀመረ
**********************
(ህዳር 3/2017ዓ.ም፡ የመካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር 2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት)

ቀጥተኛ በሆኑ ታክሶች ላይ የሚያተኩረውን የክፍል አንድ ስልጠና ለአስራ አምስተኛ ዙር ሰልጣኞች መስጠት ተጀመረ፡፡ የዛሬው ስልጠና ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ እና የወጪ መጋራትን የተመለከተ ነው፡፡

ስልጠናው በአቶ አወቀ ግዛው የታክስ ከፋዮች ከፍተኛ የትምህርት ባለሙያ የተሰጠ ሲሆን ከመቀጠር የሚገኝ ግብር ምንነት፣ ታክሱ የሚከፈልበት ምጣኔ፣ የአይነት ጥቅሞችን በተመለከተ፣ ከታክስ ነፃ የተደረጉ እና በገደብ ነፃ የተደረጉ ገቢዎች ላይ በዝርዘር የተብራሩ ርዕሰ ጉዳዮች ናቸው፡፡

ቀጥተኛ የሆኑ የታክስ ዓይነቶች ላይ ከቤት ኪራይ እና ከንግድ ስራ የሚገኝ ገቢ ግብር፣ ከተከፋይ ሂሳቦች ላይ ታክስ ቀንሶ የማስቀረት አስተዳደር ስርዓት (withholding tax) እንዲሁም የዛሬውን ስልጠና ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ እና የወጪ መጋራትን በተመለከተ ሰልጣኞች በክፍል አንድ የሚወስዱዋቸው የሞጁለር ስልጠናዎች ናቸው፡፡


ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

12 Nov, 09:25


ፈተና ተሰጠ
******************************
(ህዳር 3/2017ዓ.ም፡ የመካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር 2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት)
በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ሲሰጥ የነበረውን ስልጠና የክፍል ሶስት ስልጠና ላጠናቀቁ የአስራ ሶስተኛ ዙር ሰልጣኞች የክፍል ሶስት የማጠናቀቂያ ፈተና ተሰጠ፡፡
ሰልጣኞች በክፍል ሶስት በታክስ አስተዳደር ዙሪያ ባሉ ህጎች፣ መመሪያዎችና ደንቦች ላይ ያተኮረውን ስልጠና በአግባቡ ወስደው አጠናቀዋል፡፡


ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

12 Nov, 07:34


ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

06 Nov, 13:49


Follow our social media Pages:-
Telegram፦ https://t.me/mormto2
Facebook፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
E-mail፡- [email protected]
YouTube፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

06 Nov, 11:43


https://youtu.be/dsu3EQLZBfM

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

05 Nov, 11:10


የክፍል ሶስት ስልጠና ተጠናቀቀ
************************************

(ጥቅምት 26/2017ዓ.ም፡ የመካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር 2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት)

ለአስራ ሶስተኛ ዙር ሰልጣኞች ሲሰጥ የነበረው የክፍል ሶስት ስልጠና የተጠናቀቀ ሲሆን በዛሬው ስልጠና የታክስ አስተዳደር እና የግብር ከፋይ መብትና ግዴታ ላይ ያተኮረ ነው፡፡

የታክስ አስተዳደር ላይ የታክስ ማስታወቂያ አቀራረብን፣ ሰነድን የማቅረቢያ ወይም ታክስ የመክፈያ ጊዜ በተመለከተ፤ ታክስን በኤሌክትሮኒክስ የታክስ ሥርዓት መጠቀም ያለውን ጥቅም ፤ታክስን ባለማሳወቅ የሚያስከትለው ቅጣት በተመለከተ ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡ በተጨማሪም በታክስ አስተዳደር ሕጉ መሰረት የግብር ከፋይ መብትና ግዴታዎችን እንዲሁም አለመግባባት ሲፈጠር ምን ምን መደረግ እንዳለበት በመለየት በታክስ ለሚፈጸሙ ቅጣቶች እንዲሁም ሽልማቶች ላይ ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡

ሰልጣኞች በታክስ አስተዳደር አዋጅ መሠረት ታክሱን በወቅቱ ለገቢ መሥሪያ ቤቱ እንዲያሳውቁ እና እንዲከፍሉ ማድረግ የሥልጠናው ዓላማ ነው፡፡

ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

04 Nov, 13:28


ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

04 Nov, 12:15


የግብር አሰባሰቡን በተመለከተ ድጋፍና ክትትል በመካሄድ ላይ ይገኛል

(ጥቅምት 25 /2017ዓ.ም፡ የመካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር 2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት)
************************************************

የ2016 ዓ.ም የግብር ማሳወቂያና መክፈያ ወቅትን አስመልክቶ የግብር አሰባሰብ ሂደቱ ሥነ-ምግባርን የተላበሰ እና ቀልጣፋ አገልግሎት ለግብር ከፋዩ መስጠት ይቻል ዘንድ የተቋማዊ ስጋት ስራ አመራርና ሥነ-ምግባር ቡድን ድጋፍና ክትትል በማድረግ ላይ ይገኛሉ።

ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

04 Nov, 11:28


 በታክስ ማስታወቂያ የተገለጸው የታክስ መጠን ታክስ ከፋዩ ሊከፍል ከሚገባው ትክክለኛ የታክስ መጠን ያነሰ እንደሆነ (ልዩነቱ “የታክስ ጉድለት” ተብሎ የሚገለጽ) የታክስ ጉድለቱን መጠን 10% (አሥር በመቶ) ቅጣት ይከፍላል፡፡
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ፡-https://t.ly/x3lJ_

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

02 Nov, 13:14


(ጥቅምት 23/2017ዓ.ም፡ የመካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር 2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት)
************************************************
የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ግብር ከፋዮች በቀሩት ጥቂት ቀናት ግብራቸውን አሳውቀው በመክፈል በመጨረሻ ሰዓት ከሚያጋጥም የሲስተም መጨናነቅ እንዲድኑ የሚያሳስብ ቅስቀሳ በታክስ ከፋዮች ትምህርት ክፍል አማካኝነት ተጠናክሮ በመቀጠል ዛሬ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዙሪያ ባሉ አካባቢዎች ተካሂዷል፡፡

ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

01 Nov, 14:18


(ጥቅምት 22 /2017ዓ.ም፡ የመካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር 2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት)
************************************************

በቀሩት ጥቂት ቀናት ግብራቸውን አሳውቀው በመክፍል በመጨረሻ ሰዓት ከሚያጋጥም የሲስተም መጨናነቅ እንዲድኑ የሚያሳስብ የቅስቀሳ ፕሮግራም የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ግብር ከፋዮች ባሉበት ክፍለ ከተሞች በታክስ ከፋዮች ትምህርት ክፍል አማካኝነት ተጠናክሮ በመቀጠል ዛሬ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ዙሪያ ባሉ አካባቢዎች ተካሂዷል፡፡


ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

01 Nov, 13:05


የገቢዎች ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱን የግብር አሰባሰብ ሂደት ምልከታ አደረጉ፡፡
የገቢዎች ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱን የግብር አሰባሰብ እንቅስቃሴን በተለያዩ ክፍሎች ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን ግብሩን ለመሰብሰብ እየተደረገ ያለውን ጥረት በማድነቅ በቀጣይ ቀናት መፈፀም ይገባል ያሉቸውን ተጨማሪ ተልዕኮዎች ሰጥተዋል፡፡

ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

01 Nov, 10:26


(ጥቅምት 22 /2017ዓ.ም፡ የመካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር 2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት)
************************************************


የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱን የጥቅምት ወር ገቢ አሰባሰብን በተመለከተ በዋናው መስሪያት ቤት ድጋፍና ክትትል ተካሄደ፡፡

ድጋፍና ክትትሉ በአቶ አብዱራህማን ኢድ ጣሂር የታክስ ኦፐሬሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ የተመራ ሲሆን አጠቃላይ የገቢ አሰባሰቡን በተመለከተ በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ቶሉ ፊጤ ገለፃ ተደርጎላቸዋል፡፡

ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

26 Oct, 09:15


ለዘገየ ክፍያ የሚከፈል ወለድ
 
1.      በታክስ መክፈያ ጊዜው ወይም ከዚያ በፊት ታክሱን ያልከፈለ ታክስ ከፋይ ታክሱ መከፈል ከነበረበት ቀን ጀምሮ ተከፍሎ እስካላቀበት ቀን ድረስ ባልተከፈለው መጠን ላይ ለዘገየው ክፍያ ወለድ የመክፈል ግዴታ አለበት፡፡
 
·       የዘገየ ክፍያ የወለድ መጣኔ ከላይ የተጠቀሰው ጊዜ ከመጀመሩ በፊት ባለው ሩብ ዓመት በንግድ ባንኮች ሥራ ላይ በዋለው ከፍተኛው የማበደሪያ ወለድ መጣኔ ላይ 15% (አሥራ አምስት በመቶ) ተጨምሮበት ይሆናል፡፡
 
·       የዘገየ ክፍያ ወለድ የተከፈለበት ታክስ መከፈል የማይኖርበት ታክስ ሆኖ የተገኘ እንደሆነ ለታክሱ ከፋዩ ይመለስለታል፡፡
 
 
·       በዘገየ ክፍያ ላይ የሚታሰብ ወለድ ታክስን በመክፈያ ጊዜው ባለመክፈል ከሚጣለው ቅጣት በተጨማሪ ይሆናል፡፡
 
 
·       በዘገየ ክፍያ ላይ ወለድ በነጠላ ወለድ የሚሰላ ሲሆን የሚታሰበውም በየቀኑ ይሆናል፡፡
 
·       ባለሥልጣኑ በዘገየ ክፍያ ላይ ወለድ የመክፈል ግዴታ ላለበት ታክስ ከፋይ መክፈል ያለበትን የወለድ መጠንና የመክፈያ ጊዜውን የሚገልጽ ማስታወቂያ ይሰጠዋል፡፡
 
2/ ታክስ ከፋዩ መክፈል ያለበትን በዘገየ ክፍያ ላይ የሚታሰብ ወለድ የሚገልፀው ማስታወቂያ ባለሥልጣኑ የሚሰጠውን የታክስ ስሌት ማስታወቂያ ጨምሮ በማንኛውም ማስታወቂያ ውስጥ ሊካተት ይችላል፡፡
 

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

26 Oct, 07:51



(ጥቅምት 16/2017ዓ.ም፡ የመካከለኛ ግብር ካፋዮች ቁጥር 2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት)
************

የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ግብር ከፋዮች በቀሩት ጥቂት ቀናት ግብራቸውን አሳውቀው በመክፍል በመጨረሻ ሰዓት ከሚያጋጥም የሲስተም መጨናነቅ እንዲድኑ የሚያሳስብ ቅስቀሳ ተጠናክሮ በመቀጠል በየካ ክፍለ ከተማ ዙሪያ ባሉ አካባቢዎች ተካሂዷል፡፡ ቅስቀሳው በታክስ ከፋዮች ትምህርት ክፍል የተዘገጀ ነው፡፡


ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

24 Oct, 14:18


የክፍል ሦስት ስልጠና ተጀመረ
*****
(ጥቅምት 14/2017ዓ.ም፡ የመካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር 2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት)
ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ለአስራ ሶስተኛ ዙር ሰልጣኞች በታክስ አስተዳደር ዙሪያ ባሉ ህጎች፣ መመሪያዎችና ደንቦች ላይ ያተኮረውን የክፍል ሶስት ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡

ስልጠናው በአቶ አወቀ ግዛው ከፍተኛ የትምህርት ባለሙያ ተሰጥቷል፡፡ የዛሬው ስልጠና የታክስ ከፋይ ምዝገባ፣ ስረዛ እና ክሊራንስ አሰጣጥን የተመለከተ ሲሆን ሰልጣኞች በታክስ አስተዳደር ህግ መሰረት ለግብር ከፋይነት ምዝገባ፣ ለውጦችን ስለማሳወቅ፣ ክሊራንስ አሰጣጥ ዙሪያ መሰረታዊ የህግ ዕውቀት ኖሯቸው እንዲሰሩ ማድረግ የስልጠናው ዋና አላማ ነው፡፡

ከግብር ከፋይነት ምዝገባ ጋር ተያይዞ ግለሰብ ግብር ከፋይ ለምዝገባ በሚሄድበት ወቅት የብሔራዊ መታወቂያ /National Id/ እንደ ቅድመ ሁኔታ እየተጠየቀ ይገኛል ብሔራዊ መታወቂያው ለሁሉም ተደራሽ ስላልሆነ ሚኒስቴር መስሪያቤቱ ጉዳዩን በምን መልኩ ያየዋል?፣ አንድ ድርጅት የንግድ ስራውን አቋርጦ ምዝገባው ከተሰረዘ አመታት በኋላ መቀጠል ቢፈልግ ድጋሚ ወደነበረበት ለመመለስ /Active/ ለማድረግ የጊዜ ገደብ አለው ወይ?፣ አንድ ትሬዲንግ የጅምላ መሸጫ በተለያዩ ቦታዎች ቢከፍት በሁሉም ቦታዎች ላይ መመዝገብ አለበት ወይ? የሚሉና ሌሎች ጥያቄዎች ከሰልጣኞች የተነሱ ሲሆን ከአሰልጣኞች ምላሽ እና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
ሰልጣኞች በክፍል ሶስት ስልጠና የታክስ አስተዳደር አዋጅ ላይ ያሉ የተለያዩ የታክስ ድንጋጌዎች እንዲሁም ፣ መመሪያዎችና ደንቦችን በተመለከተ ስልጠና ይወስዳሉ፡፡

ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

24 Oct, 11:40


(ጥቅምት 14/2017ዓ.ም፡ የመካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር 2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት)

በታክስ ከፋዮች ትምህርት ክፍል አማካኝነት የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ግብር ከፋዮች ግብራቸውን በወቅቱ በመክፈል በመጨረሻ ቀናት ከሚያጋጥም የሲስተም መጨናነቅ እንዲድኑ የሚጠይቅ የቅስቀሳ ፕሮግራም በቦሌ ክፍለ ከተማ በሚገኙ የተለያዩ ቦታዎች ላይ ተካሄደ፡፡

ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

24 Oct, 08:16


የእርጅና ተቀናሽ

በግብር ዓመቱ በሙሉ ጥቅም ላይ ያልዋለ ዋጋው የሚቀንስ ሀብት

አንድ ወጋው የሚቀንስ ሀብት በግብር ዓመቱ ከፊል ለሆነው የዓመቱ ጊዜ ብቻ በጥቅም ላይ የዋለ እንደሆነ የሚፈቀደው የእርጅና ተቀናሽ ወጪ ከጠቅላላ የዓመቱ የእርጅና ቅናሽ ሂሳብ ላይ ጥቅም ላይ ያልዋለበት የዓመቱ ከፊል ጊዜ ተመጣጣኝ በሆነ መቶኛ ከተቀነሰ በኋላ ያለው ተቀናሽ ወጪ ብቻ ነው፡፡

ለንግድ ስራ በጥቅም ላይ የዋለው የህንፃ ክፍል

1.በግብር ከፋይ የተገነባ ህንፃ የእርጅና ቅናሽ መታሰብ የሚጀምረው ሀብቱ የንግድ ስራ ገቢውን ለማስገኘት ለአገልግሎቱ ዝግጁ ከሆነበትና አገልግሎት መስጠት ከጀመረበት ቀን አንስቶ ሲሆን ተቆጣጣሪው ባለስልጣን ለግብር ከፋዩ የህንፃ ግንባታው ስለመጠናቀቁ የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ከሰጠበት ጊዜ በፊት ሊሆን አይችልም፡፡

2.ለእርጅና ተቀናሽ አያያዝ ከጠቅላላው የህንጻ ስፋትና ዋጋ ለንግድ ስራው ጥቅም ላይ የዋለው የህንጻው መጠን ዋጋ ተለይቶ ካልቀረበ በወለሉ ስፋት መቶኛ በማስላት ዋጋው ተለይቶ መቅረብ አለበት፡፡

3.ከላይ በተጠቀሰው መሰረት ግብር ከፋዩ ለይቶ ካላቀረበ ከጠቅላላ የህንጻው ዋጋ ለንግድ ስራው የዋለውን የህንጻው ስፋት መጠን በማስላት ባለስልጣኑ በራሱ ወስኖ ተቀናሽ ያደርጋል፡፡

4.ጥቅም ላይ የዋለ የህንጻ ክፍል ማለት የህንጻው ክፍል ለሌላ ዓላማ እስካልዋለ ድረስ ግብር ከፋዩ ህንጻውን ለኪራይ አገልግሎት ዝግጁ ያደረገ ከሆነ ህንጻው ባይከራይም ለኪራይ አገልግሎት ጥቅም ላይ እንደዋለ ተቆጥሮ ከቤት ኪራይ በተገኘ ገቢ ላይ ግብር በሚሰላበት ጊዜ እንደወጪ ተቀናሽ ሊያዝለት ይገባል፡፡

5.በዚህ አንቀጽ 2 እና 3 የተደነገገው ድንጋጌ ለኪራይ ገቢ ግብርም በተመሳሳይ ተፈጻሚ ይሆና፡፡
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ፡-https://t.ly/JGDJJ

Ministry of Revenues -Medium Taxpayers Branch No2

23 Oct, 13:02


ለገቢዉ ከፍተኛ አስተዋጾ ከሚያደርጉ ግብር ከፋዮች ጋር ውይይት ተካሄደ
****************************
(ጥቅምት 13/2017ዓ.ም፡ የመካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር 2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት)

የመካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር 2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በታክስ ከፋዮች ትምህርት ክፍል አዘጋጅነት በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ለገቢዉ ከፍተኛ አስተዋጾ ከሚያደርጉ ግብር ከፋዮች ጋር ውይይት አካሄደ፡፡

ውይይቱን የመሩት የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ቶሉ ፊጤ ሲሆኑ በበርካታ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ እንዲሁም ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ ዛሬ የጠራናችሁ ግብራችሁን በወቅቱ በመክፈል የሀገር የጀርባ አጥንት የሆናችሁ ግብር ከፋዮቻችን ናችሁ፡፡ ለዚህም ትልቅ ምስጋና አለን ያሉ ሲሆን ግብር ከፋዩ ባለበት ሆኖ ግብሩን አሳውቆ እንዲከፍል የተለያዩ የኢ- ፋይሊንግ እና ኢ-ፔይመንት አማራጮች በመኖራቸው ከመጨረሻ ሰዓት ከሚያጋጥም የሲስተም መጨናነቅ እና ቅጣት ለመዳን ዲጄታል ቴክኖሎጂን መጠቀም እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡ ዲጂታል ቴክኖሎጂን ተጠቅሞ ግብርን መክፈል አገልግሎትን ያቀላጥፋል፣ ወጪ እና መመላለሶችን ይቀንሳል እንዲሁም አላስፈላጊ ግንኙነቶችን ይቀንሳል በማለት ግብር ከፋዩ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ግብሩን በወቅቱ እንዲከፍል አስገንዝበዋል፡፡ በተጨማሪም የህግ ተገዢነት የሽልማቱ አንደኛው መስፈርት ግብርን በወቅቱ አሳዉቆ መክፈል መሆኑን በመልዕክታቸውን አስተላልፈዉ በዋናነት ይህንን መድረክ ያዘጋጀዉን የታክስ ከፋዮች ትምህርት የስራ ሂደትን አመስግነዋል፡፡

ወ/ሮ ውብስራ ሙሉአዳም የታክስ ኦፕሬሽን ዘርፍ ም/ስራ አስኪያጅ ሽልማት የወሰዱ ድርጅቶች የቅድሚያ አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን እና ከሲሰተም ጋር የሚያጋጥሙ ችግሮችን አሁን ላይ መስተካከላቸውን ገልፀዋል፡፡ አክለውም ከሀምሌ 1 ቀን 2016ዓ.ም ጀምሮ እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2017ዓ.ም ድረስ ባሉት አራት ወራቶች ውስጥ ግብር ከፋዩ ግብሩን እንዲከፍል የተቀመጡ ወራቶች መሆናቸውን አስታውሰው አሁንም በቀሪ ቀናቶች ግብርን በወቅቱ በመክፈል ከአላስፈላጊ ቅጣት እንዲድን አሳስበዋል፡፡

ተሳታፊዎች አሉ ያሉዋቸዉን ችግሮች ለመፍታት ተቀራርቦ ለመነጋገር መድረኩ መዘጋጀቱን አመስግነው አሉ የሚሏቸውን ችግሮች እና ቢስተካከሉ ያሉዋቸው አሰራሮች ላይ አስተያየታቸውን የሰጡ ሲሆን ከመድረኩም ምላሽ ተሰጥቷቸዋል፡፡


ግብር÷ ለሀገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@ministryofRevenues-MTO2
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

8,195

subscribers

2,069

photos

24

videos