Neueste Beiträge von አዲስ ሪፖርተር - NEWS (@addis_reporter) auf Telegram

አዲስ ሪፖርተር - NEWS Telegram-Beiträge

አዲስ ሪፖርተር - NEWS
🔖 ይህ የአዲስ ሪፖርተር የቴሌግራም ገፅ ነው !

=> በቻናሉ
📌 ፈጣን ፥
📌 ትኩስ ፥
📌 ወቅታዊ እና
📌 አዳዲስ መረጃዎች እንደወረዱ በቅፅበት ፥ በትኩሱ ይደርሳችኋል !

🔖 ይወዳጁን ፤ በእርግጥም ይወዱታል !
For promotion @Addis_reporter_bot

#ADDIS ABABA, ETHIOPIA
37,413 Abonnenten
10,211 Fotos
227 Videos
Zuletzt aktualisiert 01.03.2025 12:34

Der neueste Inhalt, der von አዲስ ሪፖርተር - NEWS auf Telegram geteilt wurde.


ካሳቫ/Cassava‼️
ካሳቫ የተባለው ስራስር በእንጀራ ላይ ተጨምሮ እንዲሸጥ ተፈቀደ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምግብና መድሃኒት ባለሥልጣን ካሳቫ የተባለው ሥር በእንጀራ መልክ እንዲቀርብ መፈቀዱን አስታውቋል።

ካሳቫ የስራስር አይነት ሲሆን፤ በተለይ በደቡቡ የሀገሪቱ ከፍል ምርቱ በብዛት ይገኛል።

የባለሥልጣኑ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ እንጋ እርቀታ ስሙ ካዛቫ የተባለ ሥር  ከምግብ ምድብ ውስጥ እንዲገባ በማድረግ ከእንጀራ ምርት ጋር ተቀላቅሎ ለምግብነት እንዲቀርብም መፈቀዱን ተናግረዋል።

ነገር ግን ይህን ተገን በማድረግ ሌላ ባዕድ ነገር የሚቀላቅል ስለማይጠፋ በተቻለ አቅም  የቁጥጥር ሥራ ይሠራል ብለዋል።

የካሳቫ ተክል ከፍተኛ የካርቦሀይድሬት መጠን ያለው ሲሆን በቫይታሚን ሲ የበለፀገ ነው።

ካሳቫ የስኳር በሽታን፣የልብ በሽታን እንዲሁም የህዋስ እርጅናን/cell aging/ እንደሚከላከል ሳይንሳዊ ጥናቶች ያሳያሉ።

ካሳቫ ተክል መነሻው ከመካከለኛው አሜሪካ ሲሆን ወደ አፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ የገባው  በፈረንጆች 1558 በፖርቹጋሎች ሲሆን ተክሉን በማብቀል ከአፍሪካ ሀገራት ኮንኮ ቀዳሚዋ እንደሆች ታሪክ ያስረዳል።

አሁን በአብዛኛው የአፍሪካ ሀገራት በስፋት የሚመረት ሲሆን በሀገራችንም በደቡብ ኢትዮጵያ በስፋት ይመረታል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter

በኢትዮጵያ የወንዶች የዘር ማስተላለፊያ ቱቦን በመቋጠር  ስለሚሰጠው የወሊድ መከላከያ ያለው ግንዛቤ አነስተኛ ነው ተባለ

ፖስት ፒል የወሊድ መከላከያ ለድንገተኛ የሚወሰድ ቢሆንም  በርካቶች አቅደው እየወሰዱት መሆኑ  ተገቢ እንዳልሆነ ተጠቁሟል። 

ፖስት ፒል አስተማማኝነቱ ከሌሎች  በእቅድ ከሚወሰዱት አንጻር 15 በመቶ ላይሰራ የሚችልበት ሁኔታ  መኖሩን  በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል የማህጸን እና ጽንስ ሃኪም እንዲሁም የስነተዋልዶ እና የቤተሰብ እቅድ ሰብስፔሻሊስት ዶክተር ዘሪሁን በተለይ ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን  ተናግረዋል።  

ሁሉም የወሊድ  መከላከያዎች  የጎንዮሽ ጉዳት ሊኖራቸው ቢችልም በ72 ሰዓት የሚወሰደው ግን ከፍተኛ  ራስ ምታት፣ የወር አበባ መዛባት እና ድካም እንዲሁም ገና በጥናት ላይ ቢሆንም ከማህጸን ውጪ እርግዝና ሊፈጠር እንደሚችል ተነግሯል።

በኢትዮጵያ  የተለመደው የወንዶች  የወሊድ መከላከያ  ኮንዶም ቢሆንም ጥናት እየተደረገባቸው ያሉ እንዲሁም ቋሚ የወሊድ መከላከያዎች ይገኛሉ። በሴቶች የተለመደው ቋሚ የሚባለውን  የማህጸን ማስቋጠር የወሊድ መከላከያ ዘዴ እና ከአንድ በላይ ሚስቶች ያሏቸው ወንዶች በኩል ቋሚ የሆነ የዘር ማስተላለፊያ ቱቦ በመቋጠር  የእርግዝና መከላከያ  መኖሩን ባለሙያው አንስተዋል።

ይሁን እና ግን ይህ የህክምና ዘዴ ኢትዮጵያ ውስጥ  የሚሰጥ ቢሆንም  ህብረተሰቡ ዘንድ ያለው ግንዛቤ አነስተኛ ኑው። ህክምናው በኢትዮጵያ በበርካታ ሆስፒታሎች የሚሰጥ ነው።በሌላ በከል በቅርቡ  ልክ እንደ ስኳር መድሃኒት ራስ በራስ በመውጋት የሚወሰዱ የወሊድ መከላከያ ዘዴዎች አገልግሎት  ላይ እየዋሉ መሆኑን  በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል የማህጸን እና ጽንስ ሃኪም እንዲሁም የስነተዋልዶ እና የቤተሰብ እቅድ ሰብስፔሻሊስት  ዶክተር ዘሪሁን በየነ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።

Via : dagu

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter

የውጭ ሃገር የሥራ ስምሪት ሥራ ዕድል  በሥራና ክህሎት ሚኒስትር

ወደ አውሮፓ (Sweden and Norway) ገበያ ለመግባት ቀደም ብሎ በተጀመረ ጥረት የዝግጅት ምዕራፍ ተጠናቆ ወደ ተግባር ተገብቷል። በመሆኑም በስምምነቱ መሰረት የተጠየቁ የሞያ ዘርፎች የሚከተሉት ናቸው።

1. ካርዲዬሎጂስት 
2. የማርኬቲንግ ባለሙያ 
3.  ኬሚካል ኢንጅነር 
4.  ባስ ድራይቨር 
5.  አርክቴክት
6.  አካውንታን
7. አውቶሞቲቭ ቴክኒሽያን ባለሙያ
8.  የላብራቶሪ ቴክኒሺያን
9.  የአይ ቲ ባለሙያ
10. የፋርማሲ ባለሙያ
11.  የሽያጭ ባለሙያ 
12. የሶፍትዌር ባለሙያ 
13. ሜዲካል ዶክተር 
14. የኮምፒተር ጥገና ባለሙያ
15. ነርስ
16. ግራፊክስ ዲዛይነር
17. የፀጉር ባለሙያ  
18. የደንበኛ አገልግሎት ባለሞያ

🟥 ፈጥነው ታች ባለው ሊንክ ይመዝገቡ

⁉️ማሳሰቢያ:- VPN ወይም Psiphon መጠቀም ይኖርባችሗል

👇👇👇👇👇Apply Now👇👇👇👇👇👇👇
                        👇👇👇👇         
https://reportervacancy.com/new-jobs-labor-and-skill-minister-of-ethiopia/

---------Follow Our Website---------
                      👇👇👇👇👇👇
         https://reportervacancy.com

----------Join Our Telegram-------
                               👇👇👇👇👇
    
https://t.me/reporter_vacancy

በኢኮኖሚያዊ ሉአላዊነቴ ጣልቃ መግባት አስቧል ያለችው ቱኒዝያ ከአለምአቀፉ የገንዘብ ተቋም/IMF ጋር ግንኙነቷን ሙሉ ለሙሉ አቋረጠች‼️

የሰሜን አፍሪካዊቷን አገር በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚደግፍ የሚገለፅለት IMF የቱኒዝያ መንግስት የዋጋ ንረትን ለመቋቋም የሚያደርገውን ድጎማ እንዲያቋርጥ እንዲሁም የታክስ ማሻሻያ እንዲደረግ ሲመክር ቆይቷል።

ይህን እና ሌሎች ምክሮች ጣልቃ መግባት እና ገደብን ያለፈ ነው ሲል የቱኒዝያ መንግስት ኮንኗል።

በዚህም ሻክሮ የነበረውን ግንኙነት ሙሉ ለሙሉ ለማቋረጥ መወሰኑ ነው የተገለፀው።
ኢትዮጵያ የ IMF ምክረ ሀሳብን በመቀበል የታክስ እና የአገልግሎት ክፍያ ማሻሻያ ማድረጓ የሚታወቅ ነው።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter

ጥንቃቄ‼️

በአዲስ አበባ ከተማ የአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት በሽታ መከሰቱን የጤና ባለሙያዎች ጠቆሙ

በመዲናዋ ውስጥ የአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት (አተት) በሽታ እንደተከሰተ የጤና ባለሙያዎች ለሚድያችን በሰጡት ቃል አሳወቁ።

የበሽታው መከሰትን ለመሠረት ሚድያ ያረጋገጡት እነዚህ በአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ስር ባሉ ጤና ጣቢያ የሚሰሩ የጤና ባለሙያዎች ስጋቱ ለህዝብ ይፋ ሆኖ የጥንቃቄ እርምጃዎችን በተመለከተ መልዕክት አለመተላለፉ የበለጠ ጉዳት እንዳያስከትል ስጋታቸውን ገልፀዋል።

"ሰሞኑ ከፍተኛ የአተት በሽታ ተከስቷል፣ ነገር ግን ምንም እየተባለ አይደለም። እኛም በየጤና ጣቢያ ሸራ ወጥራቹ ዝም ብላችሁ ስሩ እየተባልን ነው" ያለው አንድ የጤና ባለሙያ በአስደንጋጭ መልኩ 'vibrio cholerae' የተባለው የኮሌራ አምጪ ተህዋስም በምርመራ ወቅት በከተማው ውስጥ መገኘቱን ተናግሯል።

"እንደምናውቀው አተትም ሆነ ኮሌራ በጣም ተላላፊ ነው፣ ነገር ግን እየሆነ ያለው ነገር ፍፁም ተቃራኒ ነው" የሚሉት የጤና ባለሙያዎቹ ከ100 በላይ የበሽታው ተጠቂዎች አሁን ላይ ባሻ ወልዴ ተብሎ በሚጠራው የአራዳ ክፍለ ከተማ ጤና ማዕከል ገብተው እንደሚገኙ አረጋግጠዋል።

"አሁን በዚህ ሰአት በርካታ ታማሚዎችን ካለ በቂ መከላከያ እና መሸፈኛ እያከምን ነው፣ አስቸኳይ መፍትሄ እንሻለን" ያሉን ሌላኛው የጤና ባለሙያ ናቸው።

ከሰሞኑ በጋምቤላ ክልል ኑዌር ብሔረሰብ ዞን አራት ወረዳዎች የአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት በሽታ ተከስቶ የዘጠኝ ሰዎችን ሕይወት መንጠቁ ታውቋል።

በዚህ ዙርያ ከጤና ሚኒስቴር ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት በመሞከር ማብራርያ እናቀርባለን።

Via : Meseret Media

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter

ምርጫው የእርሶ ነው !

"ባንክ ሲቆጥቡ 7% ወለድ ያገኛሉ
የአያት አክሲዮን ባለቤት ሲሆኑ ግን በግማሽ ያተርፋሉ"

በ2016 ዓ.ም ብቻ

❇️የ100,000 ብር የአያት አክሲዮን ድርሻ ያላቸው 45,020 ብር አትርፈዋል

❇️የ1,000,000 ብር የአያት አክሲዮን ድርሻ ያላቸው 450,200 ብር አትርፈዋል

❇️የ2,000,000 ብር የአያት አክሲዮን ድርሻ ያላቸው 900,400 ብር አትርፈዋል

❇️የ5,000,000 ብር የአያት አክሲዮን ድርሻ ያላቸው 2,251,000 ብር አትርፈዋል

❇️የ10,000,000 ብር የአያት አክሲዮን ድርሻ ያላቸው 4,502,000 ብር አትርፈዋል

❇️ከተመዘገቡ ከ1 ወር ጊዜ ጀምሮ የትርፍ ተካፋይ ስለሚሆኑ  ከ112,500 ብር ጀምሮ ፈጥነው በመመዝገብ የ8 ግዙፍ ድርጅቶች ባለቤት በመሆን በቶሎ የትርፍ ተካፋይ ይሁኑ

❇️ ትርፋማ የሆነውን የአያት አክሲዮንን ለእርስዎ ፣ ለታዳጊ ልጅዎ  ፣ ለቤተሰብዎ እና ለወዳጅ ዘመድዎ በስጦታ ያበርክቱ

❇️ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ዲያስፖራዎች ባላችሁበት ወይንም በወዳጆቻችሁ በኩል የአያት አክሲዮን ባለቤት መሆን ትችላላቹህ

☎️ ለበለጠ መረጃ
0912024560 በቀጥታ 
በቴሌግራም 
ወይንም  በዋትሳፕ ይደውሉ 

መረጃ‼️

የኤርትራ ሰራዊት በተቆጣጠራቸው ሁለት የኢሮብ ወረዳዎች ያሉ ነዋሪዎችን የኤርትራን ዜግነት ተቀበሉ ብሎ እያስገደዳቸው መሆኑን በህዝብ የእምባ ጠባቂ ተቋም የመቀሌ ቅርንጫፍ ተናገረ፡፡

በዚህም ምክንያት ህዝቡ አጣብቂኝ ውስጥ መግባቱንና ስራውንም መከወን እንዳልቻለ ጠቅሷል፡፡

ተቋሙ እንደነገረን ከሆነ ይህ ዓመት ከተጀመረ የተቀበለው የህዝብ አቤቱታ 83 ብቻ ነው፡፡

ከተቀበላቸው አብዛኞቹ ቅሬታዎች ከመቀሌና አካባቢው የመጡ ናቸው ይህም ምክንያቱ የትራንስፖርትና ተያያዥ ኢኮኖሚያዊ ችግሮች በመኖራቸው ነው ያሉን በህዝብ የእምባ ጠባቂ ተቋም የመቀሌ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ የሆኑ አቶ ፀሐዬ አምባዬ ናቸው፡፡

ኃላፊው እንደሚሉት የኤርትራ ሰራዊት በተቆጣጠራቸው ሁለት የኢሮብ ወረዳዎች ያሉ ነዋሪዎችን የኤርትራን ዜግነት ተቀበሉ ብሎ እያስገደዳቸው ነው፡፡

ነዋሪዎቹ ህልውናቸው አደጋ ውስጥ ገብቷል፤ ገሚሱ ወደ አዲግራት እየሸሸ ነው ገሚሱ ደግሞ የሚመጣውን ለመጋፈጥ እዚያው ቀርቷል ብለውናል፡፡

በአካባቢዎቹ በርካታ ችግሮች ቢኖሩም ያሉበት ሁኔታ ወደ እምባ ጠባቂ ተቋም መጥተው አቤቱታቸውን ለማሰማት እንደማያስችላቸው አቶ ፀሐዬ ነግረውናል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ በህውሃት መሪዎች መካከል የተፈጠረው መከፋፈል ወደ ከተማና ወረዳ በመውረዱ ህዝቡ በሁለት ከንቲባዎች ለመመራት ተገዷል፤ ለማን አቤት ማለት እንዳለበት ግራ ተጋብቷልም ይላሉ፡፡

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter

መረጃ‼️

የሱዳን ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር፣ ለዓለማቀፍና ቀጠናዊ ድርጅቶች በኬንያ ላይ ቅሬታውን በጽሁፍ ሊያስገባ መኾኑን አስታውቋል።

ሚንስቴሩ ይህን ርምጃ የሚወስደው፣ የሰዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይልና አጋር ቡድኖች ናይሮቢ ውስጥ ባካሄዱት ስብሰባ ትይዩ መንግሥት ለማቋቋም መወሰናቸውን ተከትሎ ነው።

በኬንያ ድርጊት የተቆጣችው ሱዳን፣ ናይሮቢ የሚገኙ አምባሳደሯን ማስወጣቷንና የኬንያ የሻይ ቅጠል ምርት ወደ ገበያዋ እንዳይገባ ማገዷን ትናንት በይፋ ገልጣለች።

ለሱዳን ትይዩ መንግሥት ለማቋቋም ከተስማሙት ቡድኖች መካከል፣ የኮርዶፋን ግዛትን የሚቆጣጠረው አማጺ ቡድን መሪ አብድላዚዝ አል ሂሉ ይገኙበታል።

የትይዩ መንግሥቱ መስራቾች ትይዩ መንግሥቱን ይፋ የሚያደርገት፣ ሱዳን ውስጥ እንደሚኾን ተገልጧል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter

ምርጫው የእርሶ ነው !

"ባንክ ሲቆጥቡ 7% ወለድ ያገኛሉ
የአያት አክሲዮን ባለቤት ሲሆኑ ግን በግማሽ ያተርፋሉ"

በ2016 ዓ.ም ብቻ

❇️የ100,000 ብር የአያት አክሲዮን ድርሻ ያላቸው 45,020 ብር አትርፈዋል

❇️የ1,000,000 ብር የአያት አክሲዮን ድርሻ ያላቸው 450,200 ብር አትርፈዋል

❇️የ2,000,000 ብር የአያት አክሲዮን ድርሻ ያላቸው 900,400 ብር አትርፈዋል

❇️የ5,000,000 ብር የአያት አክሲዮን ድርሻ ያላቸው 2,251,000 ብር አትርፈዋል

❇️የ10,000,000 ብር የአያት አክሲዮን ድርሻ ያላቸው 4,502,000 ብር አትርፈዋል

❇️ከተመዘገቡ ከ1 ወር ጊዜ ጀምሮ የትርፍ ተካፋይ ስለሚሆኑ  ከ112,500 ብር ጀምሮ ፈጥነው በመመዝገብ የ8 ግዙፍ ድርጅቶች ባለቤት በመሆን በቶሎ የትርፍ ተካፋይ ይሁኑ

❇️ ትርፋማ የሆነውን የአያት አክሲዮንን ለእርስዎ ፣ ለታዳጊ ልጅዎ  ፣ ለቤተሰብዎ እና ለወዳጅ ዘመድዎ በስጦታ ያበርክቱ

❇️ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ዲያስፖራዎች ባላችሁበት ወይንም በወዳጆቻችሁ በኩል የአያት አክሲዮን ባለቤት መሆን ትችላላቹህ

☎️ ለበለጠ መረጃ
0912024560 በቀጥታ 
በቴሌግራም 
ወይንም  በዋትሳፕ ይደውሉ 

ህወሃት እና ኢሳያስ‼️

የህወሓት ጀነራሎች ከኢሳያስ አፈወርቂ ጋር በድብቅ ተገናኝተው እንደነበረ ዘግቧል‼️

መቀመጫው ፈረንሳይ ያደረገው African intelligence የተባለ ሚዲያ እንደዘገበው ፥ የህወሓት ጀነራሎች ከኢሳያስ አፈወርቂ ጋር በድብቅ አስመራ ላይ መገናኘታቸውን ገልጿል።

እነጌታቸው ረዳ በዚህ ጉዳይ የደፂን የህወሓት ቡድን ሲከሱ እንደነበረ ይታወሳል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter