የንፁሀን ጭፍጨፋው ዓለም ዓቀፍ ትኩረት እንዲያገኝ ጥሪ ቀረበ።
"በጎጃም ቀጠና የንጹሃን ጭፍጨፋ አሁንም እንደቀጠለ ነው፤ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ይህን ጉዳይ በትኩረት እንዲመለከተው ማሳሰብ እንፈልጋለን" አርበኛ ዝናቡ ልንገረው
በንፁሃን ላይ የሚደርስ የጭፍጨፋ ወንጀል አሳሳቢ መሆኑን የአማራ ፋኖ በጎጃም ምክትል ሰብሳቢና ወታደራዊ አዛዥ ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው ለኢትዮ 251 ሚዲያ በላከው መረጃ ገለጸ።
"በጎጃም ቀጠና ድጎ ፅዮን ቢቡኝ ወረዳ ወይንውሃ ከተማ የገባው የጠላት 72ኛ ክፍለጦር ህዝቡን በጅምላ እየሰበሰበ እየረሸነ ይገኛል፤ አርሶ አደሮችን እያገተ መሳሪያ አላችሁ አምጡ እያለ በሰውነታቸው ላይ ኮሸኮሽ እያንጠፈጠፈ የሌላቸውን ሰዎች ክላሽ ገዝተው እንዲያስገቡ በማድረግ ገዝተው ካስገቡ በኋላም እየተረሸኑ ይገኛሉ" ሲል የአማራ ፋኖ በጎጃም ወታደራዊ አዛዥ ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።
የወይን ውሃ ከተማ ነዋሪም ከተማውን ለቀው እየተሰደዱ ይገኛል። ይህ ሕዝብ በየቀኑ በጅምላ ከሚጨፈጨፍ ከፋኖ ጋር ተሰልፎ እንዲዋጋ እና ከሞት ራሱን እንዲያድን ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው ጥሪ አቅርቧል።
በቢቡኝ ዙሪያ ብቻ ከመስከረም 1 ቀን 2017 ዓ.ም. እስከ ጥቅምት 12 ቀን 2017 ዓ.ም እስካሁን 30 የሚሆኑ ንፁሃን በአብይ አህመድ ተላላኪ ሰራዊት ተገድለዋል ያለው ዋና አዛዡ ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው፤ ጎጃም ውስጥ እየተፈፀመ ያለው የንፁሃን ጭፍጨፋም የከፋ ሆኖ አግኝተነዋል ሲል ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።
ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!
https://t.me/ethio251media