" መንግስትን በሃይል ለመፈንቀል የሚደረግ ሙከራ የሚወገዝና ተጠያቂነት የሚያስከትል መሆኑን ይፋ አደርገናል " - አቶ ጌታቸው ረዳ
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ መስከረም 29/2017 ዓ.ም ከቢቢሲ FOCUS ON AFRICA ጋር ቃለ ምልልስ አድርገው ነበር።
በዚህም ወቅት ፤ በህወሓት አመራሮች መካከል የተፈጠረው ልዩነት በውይይት የሚፈታበት መንገድ ዝግ እንዳልሆነ አመላክተዋል።
" ሆኖም በጊዚያዊ አስተዳደሩ ላይ እየተደረጉ ያሉ ህጋዊ ያልሆኑ ተግባራት / መንግስትን በኃል ለመፈቀል የሚደረግ ሙኩራ የሚወገዙና ተጠያቂነት የሚስከትሉ መሆናቸው ህዝብ እንዲያውቃቸው ማድረጋችን ልክ ነው " ብለዋል።
" ሂደቱን ተከትሎ የተጠያቂነት አስራር ተግባራዊ እንደሚሆን ሁሉም ሊያውቀው የሚገባ ጉዳይ ነው " ሲሉ አክለዋል።
የትግራይ ህዝብ ችግሮች በተባባሱበት ወቅት ለምን አንድነታችሁ መጠበቅ አቃታችሁ ? የሚል ጥያቄ የቀረበላቸው አቶ ጌታቸው " ይህ ትልቅ ወድቀት ነው ፤ እንደ ድርጅት እና ስራ አስፈፃሚ አባል የሆንኩበት ህወሓት ወድቀዋል ፤ ቢሆንም ጥቂት አመራሮች መሬት ላይ ያለው ተጨባጭ እውነት በመረዳት ለመፍታት ስንሞክር ቀላል የማይባል ፈተና እና እንቅፋት እየገጠመን ይገኛል " ብለዋል።
ከዚህ በመመለስ ግን ፈተናውን ለማለፍ ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ መሆናቸውን ገልፀዋል።
@my_oromia