Feta Daily News

@fetadaily


Feta Daily News

22 Oct, 14:19


ተመድ የኬኒያ ውሳኔ አሳስቦኛል አለ❗️

የኬንያ መንግሥት በመዲናዋ ናይሮቢ ይኖሩ የነበሩ አራት ጥገኝነት ጠያቂ ቱርካውያንን በአስገዳጅ ሁኔታ ወደ አገራቸው እንዲመለሱ አድርጓል።

ይህ ድርጊትም ሰዎችን ነጻነታቸው እና ሕይወታቸው አደጋ ላይ የሚወድቅበት በመሆኑ ሁኔታው እንዳሳሰበው የመንግሥታቱ ድርጅት አስታውቋል።

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ከፍተኛ የስደተኞች ኮሚሽን ከኬንያ ወደ ቱርክ የተመለሱት ስደተኞች ሁኔታ እንዳሳሰበው ገልጿል።

የመንግሥታቱ ድርጅት ይህንን መግለጫ ያወጣው በኬንያ መዲና ናይሮቢ ባለፈው አርብ ጥቅምት 08/2017 ዓ.ም. በርከት ያሉ ውጭ አገር ዜጎች መታገታቸውን ተከትሎ ነው።

Feta Daily News

22 Oct, 12:32


ለኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት አዲስ ኮሚሽነር ተሾመ

የተቋሙ ኮሚሽነር የሆኑት ሃና አርዓያስላሴ የፍትህ ሚኒስትር ሆነዉ በጠቅላይ ሚኒስትሩ መሾማቸውን ተከትሎ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽንን በምክትል ኮሚሽነርነት ሲመሩ የነበሩት ዘለቀ ተመስገን ( ዶ/ር) የኮሚሽነርነት ቦታን ተረክበዋል።

ዘለቀ ከጣልያን ቱሪን ዩኒቨርሲቲ በህዝብ አለምአቀፍ ሕግ የዶክትሬት ዲግሪ ማጠናቀቃቸው የተገለፀ ሲሆን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽንን ከመቀላቀላቸዉ በፊት የኢፌዲሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የቢሮ ሃላፊ ሆነው አገልግለዋል።

በኢትዮጵያ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ሆነው የሰሩት ዘለቀ ተመስገን ( ዶ/ር) የሀገሪቷን የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን ለመሳብና ለማበረታታት የተቋቋመውን ተቋም በኃላፊነት እንዲመሩ ተሹመዋል።

Feta Daily News

22 Oct, 10:31


https://youtu.be/jBWO89Yqz8I?si=CTomJ0oBGxLWSiav

Feta Daily News

22 Oct, 08:34


የፊፋ ፕሬዚዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ምሽት አዲስአበባ ገቡ

የዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር(ፊፋ) ፕሬዝዳንት ጆያኒ ቪንቼንዞ ኢንፋንቲኖ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) 46ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገብተዋል።

ፕሬዚደንቱ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ(ዶ/ር) እና የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሞትሴፔ(ዶ/ር) እንዲሁም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

Feta Daily News

22 Oct, 07:42


በትግራይ ክልል ከጦርነቱ በፊት ለተሰጡ ብድሮች ፖለቲካዊ መፍትሔ ተጠየቀ❗️

በትግራይ ክልል ከተካሄደው ጦርነት በፊት ለንግዱ ማህበረሰብ ተሰጥተው መመለስ ያልቻሉ ብድሮች እና ወለድን በተመለከተ፤ የፌደራል መንግስት “ፖለቲካዊ መፍትሔ” እንዲሰጥ የሚጠይቅ የፊርማ ማሰባሰብ በክልሉ ባሉ 52 ከተሞች እየተካሄደ ነው።

አርብ የተጀመረው የፊርማ ማሰባሰብ በዛሬው ዕለት ተጠናቅቆ “ወደ ክልሉ ማዕከል ይላካል” ተብሎ እንደሚጠበቅ የትግራይ ክልል የንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ጠቅሶ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል።

Feta Daily News

21 Oct, 14:19


የቢትኮይን ዋጋ ከሶስት ወራት በኋላ ዳግም አሻቀበ

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የብዙዎችን ትኩረት እየሳበ የመጣው የምናባዊ መገበያያ ገንዘቦች ጉዳይ ዋጋቸው ከፍ እና ዝቅ ሲል ቆይቷል።

በያዝነው የፈረንጆቹ 2024 ዓመት መጀመሪያ ወራት ላይ የምናባዊ መገበያያ ገንዘቦች ዋጋ በፍጥነት እየጨመረ ቢመጣም ላለፉት የተወሰኑ ወራት ደግሞ ዋጋቸው ዳግም አሽቆልቁሎ ነበር፡፡
ከነዚህ ምናባዊ መገበያያ ገንዘቦች መካከል አንዱ የሆነው ቢትኮይን ከሰሞኑ ከነበረበት የዋጋ ማሽቆልቆል ወደ መጨመር ተሸጋግሯል።

የቢትኮይን ዋጋ እየጨመረ የመጣው ከሁለት ሳምንት በኋላ በሚካሄደው የአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ላይ ዋነኛ እጩ የሆኑት ዶናልድ ትራምፕ የማሸነፍ እድላቸው ጨምሯል ከተባለ በኋላ ነው፡፡

Feta Daily News

21 Oct, 12:27


የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር የመምህራን ደሞዝ በጊዜ አለመከፈል አሁንም ችግር ሆኖ መቀጠሉን ገለጸ

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር በአንዳንድ ክልሎች የመምህራን ደሞዝ በጊዜ አለመከፈል ብሎም እየተቆራረጠ በፐርሰንት መከፈል አሁንም ችግር መሆኑን አስታዉቋል፡፡ማህበሩ 37ኛ መደበኛ የምክር ቤት ስብሰባዉን አካሂዷል፡፡

በዚህ ስብሰባ ወቅትም የኑሮ ዉድነት መምህራንን እየተፈታተነ መሆኑን ገልጾ፤ በአንዳንድ ክልሎች የመምህራን ደሞዝ በጊዜ አለመከፈል አሁንም ችግር ሆኖብኛል ብሏል፡፡ያለመምህራን ዕውቅናና ፈቃድ በተለያዩ ምክንያቶች ደሞዝ እንደሚቆረጥ የተነሳ ሲሆን፤ ይሄንን የሚቃወሙ ደግሞ ማዋከብና ማንገላታት እንደሚደርስባቸዉ ተገልጿል፡፡

Feta Daily News

21 Oct, 10:20


https://youtu.be/M8lmD_ADJBU?si=Gof0_476AVzHAt_i

Feta Daily News

21 Oct, 08:34


የእስራኤልን የማጥቃት እቅድ የሚያሳይ ሚስጥራዊ ሰነድ ከአሜሪካ ደህንነት ሾልኮ መውጣቱ ተዘገበ

እስራኤል በኢራን ላይ የምትፈጽመውን የበቀል ጥቃት እቅድ ያሳያል የተባለ ጥብቅ ሚስጥራዊ ሰነድ ከአሜሪካ ደህንነት ሾልኮ ወጥቷል ተብሏል።

አሜሪካ፣ እስራኤል ልትፈጽመው የምትችለውን የማጥቃት እቅድ የሚዳስሰው ሚስጥራዊ ሰነድ እንዴት እንደወጣ ምርመራ እያካሄደች መሆኑን ኤፒ ሶስት የአሜሪካ ባለስልጣናትን ጠቅሶ ዘግቧል።

ኤፒ ያናገራቸው አራተኛው የአሜሪካ ባለስልጣን ሰነዱ ትክክለኛ ይመስላል ብለዋል።

ሰነዶቹ የወጡት ከአሜሪካ ጂኦስፓሺያል ኢንተሊጀንስ ኤጀንሲ ሲሆን እስራኤል ኢራን ባለፈው ጥቅምት አንድ ለፈጸመችባት የባለስቲክ ሚሳይል ጥቃት ምላሽ ለመስጠት መሳሪያዎቿን ጥቃት ለመፈጸም ወደሚያስቸል ቦታ ማንቀሳቀሷን ጠቅሷል።

Feta Daily News

21 Oct, 07:49


የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከፍተኛ የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው

8ኛው ዓመታዊ የአፍሪካ ሕብረት የተባበሩትና መንግስታት ድርጅት ከፍተኛ የትብብር ምክክር መድረክ በሕብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

በምክክሩ ላይ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋቂ ማህማት እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝን ጨምሮ የተቋማቱ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

በውይይቱ የአፍሪካ ሕብረት እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የትብብር ማዕቀፎች አፈጻጸም እንደሚገመገም ኢዜአ በዘገባው አመላክቷል፡፡

ሁለቱ ተቋማት ሰላም እና ደህንነትን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ያላቸው ትብብር ላይ ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል።

የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋቂ ማህማት እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ምክክሩን አስመልክቶ ከሰዓት በኋላ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጡ ለማወቅ ተችሏል።

አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በኢትዮጵያ የስራ ቆይታ ለማድረግ ዛሬ ማለዳ አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወቃል። ዋና ፀሐፊው እድሳት የተደረገለትን የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ሕንጻን ይመርቃሉ ተብሎም ይጠበቃል።

Feta Daily News

19 Oct, 14:26


የኔታኒያሁ መኖሪያ ቤት ላይ የድሮን ጥቃት ተፈጸመ❗️

የሊባኖሱ ሄዝቦላህ ቡድን በእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያን ኔታንያሁ መኖሪያ ቤት ላይ የድሮን ጥቃት መፈጸሙ ተሰምቷል።

የድሮን ጥቃቱ በሰሜን ቴል-አቪቭ ኬሳሪያ አካባቢ የሚገኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያን ኔታንያሁ መኖሪያ ቤት ላይ መፈጸሙ ነው የተነገረው።

የእስራኤል ጦር ጥቃቱን አስመልክቶ በሰጠው መግለጫ፤ መነሻው ከሊባኖስ የሆን ድሮን በኬሳሪያ የሚገኝ የጠቅላይ ሚኒስተር ኔታንያሆ መኖሪያ ቤት ላይ በቀጥታ ጥቃት መፈጸሙን አረጋግጧል።

ጥቃቱ በተፈጸመበት ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያን ኔታንያሁ እና ባለቤታቸው እንዲሁም ቤተሰቦቻው በቤቱ ውስጥ እንዳልነበሩ እና በሰው ላይ የደረሰ ጉዳት እንደሌለም ነው የእስራኤል ጦር ያስታወቀው።

Feta Daily News

19 Oct, 12:41


ዘመን ባንክ ከሁለት ነጥብ ሶስት ቢሊዮን ብር በላይ የተጣራ ትርፍ ማስመዝገብ መቻሉን ገለጸ

የባንክ ኢንዱስትሪውን ከተቀላቀለ 16 ዓመታትን ያስቆጠረው ዘመን ባንክ 2.39 ቢሊዮን ብር ትርፍ ማስመዝገቡን እና ባለፈዉ ዓመት ካገኘዉ ትርፍ 579 ሚሊዮን ወይም 32 በመቶ ጭማሪ ማድረጉን ገልጿል።

የባንኩን እጠቃላይ ሀብት በ23.9 በመቶ በማሳደግ ወደ 59.2 ቢሊየን ብር ያደረሰዉ ባንኩ በተጠናቀቀው ሂሳብ ዓመት መጨረሻ ላይ የደንበኞች ተቀማጭ ገንዘብ 43.61 ቢሊየን ብር ደርሷል ብሏል።

የባንኩ 16ኛዉ የባለአክስዮኖች መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ እንደተገለፀዉ የተከፈለ ካፒታሉን 7.5 ቢሊዮን ብር ማድረሱንና ከቀደመው በጀት ዓመት በ2.45 ቢሊዮን ብር ከፍ ያለ መሆኑ ተመላክቷል በአሁኑ ወቅት አጠቃላይ የባንኩ የተፈረመ ከፒታል 14.97 ቢሊየን ብር መሆኑን ሪፖርቱ ያሳያል፡፡

Feta Daily News

19 Oct, 10:33


https://youtu.be/mdTxaz2NaCo?si=he9sQdhvK9i4d6Y_

Feta Daily News

19 Oct, 08:36


በአማራ ክልል ከስልሳ በላይ ሰዎች በኮሌራ መሞታቸው ተሰማ❗️

ባለፉት ስምት ወራት በአማራ ክልል 66 ሰዎች በኮሌራ ወረርሽኝ መሞታቸውን የክልሉ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ከ4 ሺሕ በላይ ሰዎች ደግሞ በወረርሽኙ መያዛቸውን ገልጿል።

በተቋሙ የበሽታዎች እና የጤና ሁኔታዎች ምላሽ አፈፃፀም ባለሞያ ሲስተር ሰፊ ድርብ፤ ካለፈው ዓመት መጋቢት ወር መጨረሻ ጀምሮ እስከ ትላንት ጥቅምት 7 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በ41 ወረዳዎች በተከሰትው የኮሌራ ወረርሽኝ 66 ሰዎች ሲሞቱ ከ4 ሺ በላይ በወረርሽኙ መያዛቸውን ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።

Feta Daily News

19 Oct, 07:31


የሰሜን ኮሪያ ወታደሮች ወደ ዩክሬን❗️

ሰሜን ኮሪያ በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ወታደሮቿን በዩክሬን ምድር ለማስፈር መዘጋጅቷ ተገልጿል።

የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቨሎዲሚር ዘለንስኪ በሰጡት ማብራሪያ ሰሜን ኮሪያ የጦር ሀይሏን ከሩሲያ ጦር ሀይል ጎን ለማሰለፍ የጦር ሀይሉም ብዛት ከአስር ሺ በላይ እንደሆነ አስታውቀዋል።

እንደዘለንስኪ ማብራሪያ የሰሜን ኮሪያ ወታደሮች ገና እግራችው በሩሲያ በጊዜያዊነት በተያዘው የዩክሬን ምድር እንደረገጠ ነው የታወቀው።

የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት /ኔቶ/ ዋና ፀሃፊ ሩት በበኩላቸው በሰጡት መግለጫ የሰሜን ኮሪያ ወታደሮች በዩክሬን ጦርነት ስለመሳተፋቸው የተረጋገጠ መረጃ የለም ነው ያሉት ዘገባው የአይ ኒውስ ነው።