SECONDARY SCHOOL NEWS/2ኛ ደረጃ ት/ቤት መረጃ Odeeffannoo Mana b/saa Sadarkaa 2ffaa

@ethiose9_12


secondary school is government school in Addis Ababa ,Ethiopia which is located around UNESA near ODA bus highway to TuluDimitu. The school strives for educational quality.📚🖊🖍✏️🇪🇹

SECONDARY SCHOOL NEWS/2ኛ ደረጃ ት/ቤት መረጃ Odeeffannoo Mana b/saa Sadarkaa 2ffaa

08 Oct, 16:58


MOE FACEBOOK PAGE

SECONDARY SCHOOL NEWS/2ኛ ደረጃ ት/ቤት መረጃ Odeeffannoo Mana b/saa Sadarkaa 2ffaa

08 Oct, 16:57


ማስታወቂያ
የተቋም እና የትምህርት መስክ ምርጫን ይመለከታል
በ2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በመደበኛ እና በRemedial ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች የተቋም እና የትምህርት መስክ ምርጫችሁን በየትምህርት ቤታችሁ በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ መስከረም 30/2017 ዓ.ም ድረስ መሙላት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር
መስከረም 2017

2. ማስታወቂያ
በምደባ ወቅት አዎንታዊ ድጋፍ ለሚሹ ተማሪዎች
በ2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በመደበኛ እና በRemedial ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ እና በምደባ ወቅት አዎንታዊ ድጋፍ ለምትሹ ተማሪዎች ማመልከቻችሁን በ https://student.ethernet.edu.et በኩል ብቻ እንድትልኩ እየገለጽን ምንም አይነት ማመልከቻ በአካል የማንቀበል መሆኑን እናሳውቃለን።
የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር
መስከረም 2017

SECONDARY SCHOOL NEWS/2ኛ ደረጃ ት/ቤት መረጃ Odeeffannoo Mana b/saa Sadarkaa 2ffaa

06 Oct, 19:30


የመሬት መንቀጥቀጥ በሚያጋጥም ጊዜ መደረግ የሚገባቸዉ የጥንቃቄ እርምጃዎች

👉  ከቤት ውጭ ከሆኑ - ከዛፎች፣ ከሕንፃዎች፣ ከኤሌትሪክ ምሶሶዎች እና ሌሎች ወድቀው ጉዳት ሊያደርሱ ከሚችሉ ነገሮች መራቅ እና ገላጣ ሜዳ አካባቢ መቆየት።

👉በቤት ውስጥ ከሆኑ - በበር መቃኖች፣ በኮርነሮች እና ኮሪደሮች ተጠግቶ ማሳለፍ። ከእሳት ምድጃዎች፣ ከተሰቀሉ ፍሬሞች እና የግድግዳ ጌጦች፣ ከመጽሐፍ መደርደሪያዎች እንዲሁም ከመስኮት አካባቢ መራቅ። የጋዝ ምድጃዎችን በተቻለ ፍጥነት ማጥፋት ካልሆነም ከአካባቢው መራቅ።

👉  አሳንሰር (ሊፍት) በፍፁም አለመጠቀም። ከደረጃዎች አካባቢ መራቅ።

👉መኪና እያሽከረከሩ ከሆኑ- የኤሌትሪክ መተላለፊያ ምሶሶዎችን፣ ዛፎችና ሽቦዎች አካባቢ አለመቆም፣ የኤሌትሪክ መስመር ምሶሶዎች እና ሽቦዎች ተሽርካሪው ላይ ከወደቁ ከመኪናው ለመውጣት አለመሞከር፣ በተቻለ ፍጥነት ገላጣ ወደሆነ አካባቢ መኪናን ማቆም መሆናቸውን ከእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

SECONDARY SCHOOL NEWS/2ኛ ደረጃ ት/ቤት መረጃ Odeeffannoo Mana b/saa Sadarkaa 2ffaa

06 Oct, 19:03


ከደቂቃዎች በፊት በአዋሽ ፈንታሌ ተራራ አካባቢ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል።

ይህ የመሬት መንቀጥቀጥ በሬክተር ስኬል 4.9 ተመዝግቧል።
ይህ ክስተት ከአዲስ አበባ በሰሜን ምስራቅ አቅጣጫ በ165 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ባለ አካባቢ የተከሰተ ነው።

ሆኖም የዚህ መሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት በደሴ መስመር እስከ ኮምቦልቻ፣ አዲስ አበባ፣ መተሃራ እና ሌሎችም ቦታዎች ድረስ ተሰምቷል። ባለፉት ቀናት አነስተኛ መጠን ያላቸው ተመሳሳይ አይነት የመሬት ንዝረቶች ሲያጋጥሙ መቆየታቸውንም ባለሙያዎች አመልክተዋል።

በዛሬው ሁኔታ አዲስ አበባ ላይ ከዚህ የከፋ ሁኔታ ሊያጋጥም እንደማይችልም ባለሙያዎቹ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

ዜጎች የመሬት መንቀጥቀጥ በሚያጋጥምበት ወቅት ባለመደናገጥ ራሳቸውን ከአደጋ ሊጠብቁ ስለሚችሉባቸው መንገዶች መረጃ ሊይዙ እንደሚገባም መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

የጥንቃቄ መልእክቶቹን እና የዘርፉን ባለሙያዎች ምክረ ሃሳቦች ከመገናኛ ብዙሃን እንድትከታተሉ መልእክታችንን እናስተላልፋለን።

SECONDARY SCHOOL NEWS/2ኛ ደረጃ ት/ቤት መረጃ Odeeffannoo Mana b/saa Sadarkaa 2ffaa

20 Sep, 22:21


https://t.me/hamsTer_kombat_bot/start?startapp=kentId733974993

SECONDARY SCHOOL NEWS/2ኛ ደረጃ ት/ቤት መረጃ Odeeffannoo Mana b/saa Sadarkaa 2ffaa

09 Sep, 14:43


የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤትን አስመልክቶ የትምህርት ሚኒስትሩ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።

ሚኒስትሩ እንደገለጹት ለአገር አቀፍ ፈተና ከተቀመጡ 674,823 ተማሪዎች ውስጥ 36, 409 ወይም 5.4 በመቶ የማለፊያው ውጤት ማግኘታቸውን ገልጸዋል። የማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ቁጥር ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ጊዜ በ9,114 ተማሪዎች ብልጫ እንዳለውም ተናግረዋል።

በዚህም በተፈጥሮ ሳይንስ 28,158 ወይም 9 በመቶ በማህበራዊ ሳይንስ 8,251 ወይም 2 በመቶ የማለፊያ ውጤት ማምጣታቸውን አመላክተዋል።

በፈተናው 1,221 ተማሪዎች ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገባቸውን የገለጹ ሲሆን በባለፈው ዓመት ከተመዘገበው 220 አንጻር የተሻለ ውጤት መሆኑም ተገልጿል። ቀደም ሲል በነበረው የመሰናዶ ትምህርት በትግራይ ክልል ፈተናቸውን ከወሰዱ ተፈታኞች መካከል ከ700 በተፈጥሮ ሳይንስ ከትግራይ ቀላሚኖ ት/ቤት አንድ ተማሪ 675 ማስመዝገቡን ገልጸዋል።

በተመሳሳይ በዚህ ዓመት ፈተናቸውን ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል ከ600 በተፈጥሮ ሳይንስ ከአዲስ አበባ አግዚሊየም ካቴድራል ት/ቤት 575 (በሴት ተማሪ) በማህበራዊ ሳይንስ ከአዲስ አበባ ኢትዮ ፓረንትስ 538 (በሴት ተማሪ) ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል ።

በዚህ ዓመት ሁሉም ክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች ከአምናው በተሻለ ተማሪዎችን ማሳለፋቸውን የገለጹት ሚኒስትሩ 1,363 ት/ቤቶች ግን ምንም ተማሪ አለማሳለፋቸውን ጠቁመዋል።

ክቡር ሚኒስትሩ በመጨረሻም 50 በመቶና በላይ ያመጡት በቀጥታ ወደ ዩኒቨርሲቲ እንደሚገቡ ጠቅሰው የተወሰኑ ተማሪዎችም በሪሜዲያል ፕሮግራም ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተናግረዋል። ምንጭ: ትምህርት ሚኒስቴር ፌስቡክ ገፅ

SECONDARY SCHOOL NEWS/2ኛ ደረጃ ት/ቤት መረጃ Odeeffannoo Mana b/saa Sadarkaa 2ffaa

09 Sep, 12:41


አንድም ተማሪ ያላሳለፉ ትምህርት ቤቶች

👉አዲስ አበባ - 4

👉አፋር - 33

👉ቤንሻንጉል - 36

👉አማራ - 56

👉ኦሮሚያ - 55

👉ሶማሊያ - 156

👉ትግራይ - 52

👉በሀረሪ ክልል የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ሁሉም አሳልፈዋል። ይህ ማለት ሁሉም ተማሪዎችን አይደለም።

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library

SECONDARY SCHOOL NEWS/2ኛ ደረጃ ት/ቤት መረጃ Odeeffannoo Mana b/saa Sadarkaa 2ffaa

09 Sep, 12:41


36074 ማለትም 5.4% ተማሪዎች ያለፉ ሲሆን ከባለፉት ሁለት አመታት የተሻለ ውጤት ተመዝግቧል ።

700,000 ተማሪዎች ወድቀዋሉ ።

ሃረሪ ክልል ሁሉንም ተማሪዎችን አሳልፎል ።

ከፍተኛው ውጤት 675 ከትግራይ ክልል ነው ።

1363 ትምህርት ቤቶች ደግሞ ምንም ተማሪ አላሳለፉም ።

ውጤታችሁን ከስር በተቀመጠው ሊንክ ከለሊት 6 ሰዓት ጀምሮ ማየት ትችላላችሁ ።

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library

SECONDARY SCHOOL NEWS/2ኛ ደረጃ ት/ቤት መረጃ Odeeffannoo Mana b/saa Sadarkaa 2ffaa

09 Sep, 12:41


የ 12ኛ ክፍል ውጤት ከሌሊቱ 6 ሰዓት ጀምሮ ይለቀቃል!

26.6 % ተማሪዎች ኦንላይ ከተፈተኑት ማለፍ ሲችሉ

4.4% በወረቀት ከተፈተኑት አልፈዋል

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library

SECONDARY SCHOOL NEWS/2ኛ ደረጃ ት/ቤት መረጃ Odeeffannoo Mana b/saa Sadarkaa 2ffaa

09 Sep, 12:41


ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡት ሴቶች ናቸው

👉በተፈጥሮ ሳይንስ ካቴድራል ትምህርት ቤት 575/600

👉በማህበራዊ ሳይንስ ኢትዮ ፓረንትስ 538/600

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library

SECONDARY SCHOOL NEWS/2ኛ ደረጃ ት/ቤት መረጃ Odeeffannoo Mana b/saa Sadarkaa 2ffaa

09 Sep, 12:41


አዲስ አበባ 10,690 ተማሪዎች በማሳለፍ ከፍተኛውን ስፍራ ይዟል።

አዲስ አበባ ካስፈተናቸው ተማሪዎች 21.4 በመቶ አሳልፏል።

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library

SECONDARY SCHOOL NEWS/2ኛ ደረጃ ት/ቤት መረጃ Odeeffannoo Mana b/saa Sadarkaa 2ffaa

09 Sep, 12:41


#Breaking_News

5.4% ተማሪዎች ብቻ
አልፈዋል!

የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናውን ከወሰዱት ተማሪዎች 5.4% ይህም ማለት 36 ሺ 4 መቶ ተማሪዎች አልፈዋል ብቻ ማለፋቸውን ትምህርት ሚኒስቴር ይፋ አድርጓል ።

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library

SECONDARY SCHOOL NEWS/2ኛ ደረጃ ት/ቤት መረጃ Odeeffannoo Mana b/saa Sadarkaa 2ffaa

09 Sep, 12:41


የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ከፍተኛ ውጤት ይፋ ሆኗል

የትግራይ ክልል 675 ከ 700 ወንድ

ከፍተኛ ውጤት በናቹራል ሳይንስ ተማሪ 575 ሴት

ከፍተኛ ውጤት በሶሻል ተማሪ 538 ሴት

በአጠቃላይ ከፍተኛ ውጤት ከ500 በላይ ያመጡ ተማሪዎች ባለፈው አመት 273  ነበሩ በአሁኑ 1220 ከ500 በላይ ያመጡ ተማሪዎች ናቸው ።

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library

SECONDARY SCHOOL NEWS/2ኛ ደረጃ ት/ቤት መረጃ Odeeffannoo Mana b/saa Sadarkaa 2ffaa

09 Sep, 12:41


ከፍተኛው ውጤት ከትግራይ 675 ከ 700

675 highest - Male -Tigray - Natural

በትምህርት ዓይነት ከፍተኛ ውጤት የተገኘው በትግራይ ክልል በሲቪክስ ትምህርት ሲሆን ዝቅተኛው የሂሳብ ትምህርት ነው።

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library

SECONDARY SCHOOL NEWS/2ኛ ደረጃ ት/ቤት መረጃ Odeeffannoo Mana b/saa Sadarkaa 2ffaa

09 Sep, 12:41


የወንዶች አማካይ ውጤት - 30.66

የሴቶች አማካይ ውጤት - 28

አማካኝ ውጤቱ - 29.7

የአዳሪ ትምህርት ቤቶች የተሻለ ውጤት አስመዝግበዋል

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library

SECONDARY SCHOOL NEWS/2ኛ ደረጃ ት/ቤት መረጃ Odeeffannoo Mana b/saa Sadarkaa 2ffaa

26 Aug, 19:21


4. የትምህርት ጥራትን የማረጋገጥ ሥራ ተሰናስሎ መሰራትን ፣ ሁለንተናዊ ርብርብን እና በቅንጅታዊ ትግበራ መንቀሳቀስን የሚጠይቅ መሆኑ ፤


5. የትምህርት ተቋማት ደረጃቸዉን እንዲጠብቁ ፤ ምቹና ማራኪ እንዲሆኑ እንዲሁም እድሜያቸዉ ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ ለማድረግ እና የትምህርት ባለድርሻ አካላት በትምህርቱ ስራ ላይ በባለቤትነት እንዲሳተፉና ባለቤት እንዲሆኑ በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ የሰራናቸው ስራዎች እመርታዊ ለውጦችን ማሳየት መቻላቸው፡፡ በተለይም ማህበረሰቡ በከፍተኛ ደረጃ እንዲሳተፍ በማድረግ በእውቀት ፣ በጉልበትና በግብዓት 6.4 ቢሊየን ብር ሀብት በመሰብሰብ ለትምህርት ስራ ማዋል መቻሉ ፤

6. አዲሱ ስርዓተ ትምህርት በተቀመጠለት የጥራት ደረጃ እንዲተገበር ያስችል ዘንድ የሁሉም የትምህርት ባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ ስራ እና በባለቤትነት የመንቀሳቀሱ ተግባር ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ የሚኖረው ሚና እጅግ የጎላ መሆኑ ፤


7. የከተማ ግብርና ስራ በሁሉም ት/ቤቶች ላይ መተግበሩ፤

8. በአካልና በአዕምሮ የዳበረ ጤናማ ዜጋ ለማፍራት እንዲቻል በሁሉም ትምህርት ቤቶች የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎች መደረጋቸው፤


9. ለተማሪዎች ዩኒፎርም እና መማሪያ ቁሳቁሶች እንዲቀርቡ መደረጉ፤

10. ለ779,231 ተማሪዎችን 3.2 ቢሊዮን ብር በመመደብ የት/ቤት ምገባ መርሃ ግብርን አጠናክሮ በማስቀጠል መቻሉ፤


11. የመምህራንን ችግር በማጤን ለመምህራንና ለትምህርት ቤት አመራሮች የመኖሪያ ቤት በመሰጠት እና የተቀሩትን መምህራን በማህበር በማደራጀት ቅድሚያ ቤት መስራት የሚችሉበትን ማዕቀፍ መዘርጋቱና ወደ ስራ መግባቱ፤

12. በአለማቀፍና በግል ትምህርት ቤቶች ላይ ይታዩ የነበሩ ጥሰቶችን በአግባቡ በመፈተሸ ይስተዋሉ የነበሩ ክፍተቶች እንዲታረሙ መደረጉ፤


13. በቴክኖሎጂ የዳበረ ትውልድ ከመፍጠር አካያም የመማር ማስተማር ስራዉን በቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድግ የኢስኩል ሲስተም መተግበሩ ፤

14. የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማት ለማጠናከር ስኩል ኔት በተሰራባቸው ትምህርት ቤቶች ላይም የኮንፒዉተር ግብዓቶችን ማድረስ መቻሉ ፤ ለ2017 የትምህርት ዘመንም የተማሪዎች ምዝገባ ሙሉ በሙሉ የኢስኩል ሲስተም እንዲተገበር መደረጉ ፤

SECONDARY SCHOOL NEWS/2ኛ ደረጃ ት/ቤት መረጃ Odeeffannoo Mana b/saa Sadarkaa 2ffaa

26 Aug, 19:21


የአዲስ አባባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ክቡር ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ “የላቀ ትጋት ለትምህርት ጥራትና ለሀገር ብልፅግና!” በሚል መሪ ሀሳብ በመካሄድ ላይ በሚገኘው በ31ኛው ከተማ አቀፍ የትምህርት ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር ያነሳቸው ነጥቦች


(ነሀሴ 20/2016 ዓ.ም)

1. በ30ኛው የትምህርት ጉባኤ ላይ የትምህርት ስብራቶቻችን ናቸው ተብለው የተገመገሙ ተግዳሮቶችን ለማከም የተኬደባቸው ርቀቶች ያሳዩን ተጨባጭ ለውጥ በእኩል ወደፊት የመግፋት ጉልበታችንንና ትጋታችንን ከጨመርን እያከናወነው ያለው የአዕምሮ ልዕልና የማልማት ስራችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ውጤታማ እንደሚሆን፤

2. የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ትራንስፎርም በማድረግ ሞዴል ተቋማተን በመገንባታ ለአለም ፣ ለአፍሪካና ለክልል አመራሮች ተሞክሮ ማካፈል መቻሉ፤


3. በ2016 የትምህርተ ዘመን በተሰጡ የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተናዎች ማለትም በ6ኛ ክፍል በሁሉም የትምህርት ዓይነቶች አማካኝ 50ና በላይ ያመጡ ተማሪዎች ከነበረበት 70.6% ወደ 94.3% እንዲሁም በ8ኛ ክፍል አማካኝ 50ና በላይ ያመጡ ተማሪዎች ከነበረበት 70.6% ወደ 79% መድረሱ የተመዘገበው ውጤት ከዚህ ቀደም ከተመዘገቡት አንጻር ሲታይ የላቀ መሻሻል የታየበት መሆኑ ፤