የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ከጥቅምት 7-9/2017 ዓ.ም ድረስ በአዳማ ከተማ ሲያካሄድ የነበረውን 37ኛ መደበኛ የምክር ቤት ስብሰባውን ባለ 14 ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት አጠናቀቀ።
👉1. መምህራንን እየተፈታተነ ያለው ከፍተኛ የኑሮ ውድነት፣
👉2. ረጅም ጊዜ አገልግሎት ያላቸው መምህራን የደረጃ እድገት ወይም የእርከን ጭማሪ አለመኖር፣
👉3. በአንዳንድ ክልሎች የመምህራን ደሞዝ በጊዜ አለመከፈል ብሎም እየተቆራረጠ በፐርሰንት መከፈል፣
👉4. ያለመምህራን ዕውቅናና ፈቃድ በተለያዩ ምክንያቶች የደሞዝ መቆረጥ፤ ይሄንን የሚቃወሙትን ደግሞ ማዋከብና ማንገላታት፣
👉5. ቀደም ብሎ የተጀመረው የመምህራን የመኖሪያ ቤት እና የመሥሪያ ቦታ በሚፈለገው ፍጥነት እየተከናወነ ያለመሆን
👉6. የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራን የቤት አቅርቦት ጭራሽ አለመጀመሩ፣
👉7. በትርፍ ሰዓት ክፍያ ላይ ተደራራቢ ግብር መቆረጡ፣
👉8. የመጽሐፍትና ሌሎች ግብአቶች እጥረት፣
👉9. የክረምት መምህራን ስልጠናና ያጋጠሙ ችግሮች እና ሌሎችም ይገኙበታል
በቀረቡት ጥያቄዎች ዙሪያ የኢፌዴሪ ትምህርት ሚንስቴር የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ኮራ ጡሹነ እና በት/ት ሚንስቴር የመምህራንና ትምህርት አመራሮች ዴስክን ጨምሮ ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ምላሽ የሰጡ ሲሆን ከመምህራን ጥቅማ ጥቅም ጋር በተያያዘ እየታየ ያለው ጥያቄ የተጀመረው የትምህርት ሴክተር ሪፎርም ተጠናቆ ተግባራዊ ሲሆን ብዙ ጉዳዮች እንደሚፈቱ ገልፀዋል። #አዩዘሀበሻ
@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library