BAHIR DAR UNIVERSITY (ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ)

@bduethiopia


Bahir Dar University (BDU) is a public University established in 2000 by merging two former higher education institutions: Bahir Dar Polytechnic Institute (1963) and Bahir Dar Teachers’ College (1972).

BAHIR DAR UNIVERSITY (ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ)

21 Oct, 16:47


ለዩኒቨርሲቲው መምህራን በአፈጻጸምና ግምገማ ላይ መሰረት ያደረገ የሦስት ቀን የTOT ስልጠና በመሰጠት ላይ ነው
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ (ጥቅምት 11/2017 ዓ.ም)
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከተለያዩ የአካዳሚክ ክፍሎች ለተውጣጡ መምህራን በአፈጻጸምና ግምገማ ላይ መሰረት ያደረገ የTOT ስልጠና (TOT Training on Performance-Based Assessment) በሚል ርዕሰ ጉዳይ ከዛሬ በ11/02/17 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ የአቅም ግንባታ ስልጠና በፔዳ ግቢ የስልጠና ማዕከል በሙያው በሰለጠኑ መምህራን በመሰጠት ላይ ነው፡፡
ስልጠናውን በንግግር ያስጀመሩት የዩኒቨርሲቲው የፈተና ማዕከል (Testing Center) ዳይሬክተር ዶ/ር ጥሩወርቅ ታምሩ ማዕከሉ የሚያከናውናቸው ተግባራት የዩኒቨርሲቲውን የፅንሰ ሃሳብም ሆነ የተግባር ትምህርቶችን የፈተና ጥራት የማሻሻል፣አገር አቀፍ፣የውጭና የቅጥር ፈተናዎች ጥራታቸውን ጠብቀው ማዘጋጀትና ማስፈተን እንዲሁም ዓለም አቀፍ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ፈተና (International English Language Tasting Center /IELTC/) እና የመሳሰሉ ፈተናዎችን መስጠት መሆኑን አስስረድተዋል፡፡
እንደ ዳይሬክተሯ ገለፃ የሶስቱ ቀን ስልጠና ዓላማ ተግባር ተኮር ለሆኑ ትምህርቶች የመመዘኛ መሳሪያዎችን ለማሻሻል ታልሞ የተዘጋጀ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በተጨማሪም ከስልጠናው መልስ ይህ ሰልጣኞች ከተለያዩ የተግባር ተኮር ምዘናዎች ጋር ተዋውቀው ምዘናዎችን በመስራት በኮሌጃቸው ላሉ መመህራን ስልጠናውን በመስጠት ተደራሽ እንደሚያደርጉት እና የተለያዩ መመዘኛዎችን አዘጋጅተው ለማሰልጠኛ ማኑዋሉ ተጨማሪ ግብዓት እንደሚሰጡ በንግግራቸው ጠቁመዋል፡፡
ለሰልጣኞች የተግባር ስልጠናውን የሚሰጡ መምህራን በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ካሉ ስድስት የአካዳሚክ ክፍሎች ማለትም ከባህሕር ዳር ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት፣ ከኢትዮጲያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት፣ ከሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ፣ ከግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ፣ ከሳይንስ ኮሌጅ እና ከስፖርት አካዳሚ የተውጣጡ 32 አሰልጣኝ መምህራኖች መሆናቸውን ዶ/ር ጥሩወርቅ አክለው ገልፀዋል፡፡
ስልጠናውን ያዘጋጁት የዩኒቨርሲቲው የፈተና ማዕከል እና የስልጠና ዳይሬክቶሬት በጋራ ሲሆኑ ስልጠናው ከ11/02/17-13/02/17 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ የስራ ቀናት የሚሰጥ መሆኑ ታውቋል፡፡

BAHIR DAR UNIVERSITY (ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ)

21 Oct, 15:59


Bahir Dar University Collaborates with Yu. A. Gagarin Research and Test Cosmonaut Training Center for Insightful Sessions on Space Exploration

Bahir Dar University hosted two consecutive engaging video conferencing sessions in collaboration with the Yu. A. Gagarin Research and Test Cosmonaut Training Center in Russia. These sessions featured esteemed guests Peter Dubrov, a prominent cosmonaut from the state corporation Roscosmos, and Natalia Pavlenko, a specialist from the GCTC.

The event aimed to shed light on the history and significance of peaceful space exploration.

Peter Dubrov shared his personal experiences as a cosmonaut, detailing the challenges and triumphs of space travel. His firsthand accounts not only highlighted the technical aspects of space missions but also emphasized the impact of these explorations on science studies.

On the other hand, Natalia Pavlenko captivated the audience with insights into the evolution of space missions discussing, among others, the beginning of the space age, the first space testers, and the first multiseat spacecraft.

The sessions went interactive, with students and faculty from Bahir Dar University participating by raising questions. Both presenters took the time to respond thoughtfully, fostering exchange of ideas.

Feedback from participants highlighted the inspiring nature of both sessions, which are believed to encourage students to explore careers in space science and related fields.

Bahir Dar University extends its gratitude to the Yu. A. Gagarin Research and Test Cosmonaut Training Center for this invaluable opportunity.