የአማራ ክልል ዩኒቨርሲቲዎች የመደበኛ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜን አራዘሙ
👉 #ደብረብርሃን_ዩኒቨርሲቲ ነባር የቅድመ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች የ2017 ትምህርት ዘመን የምዝገባ ጊዜ መራዘሙን አሳውቋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው የ2017 ትምህርት ዘመን ምዝገባ መስከረም 29 እና 30/2017 ዓ.ም ይከናወናል ብሎ የነበረ ቢሆንም፤ 'የዝግጅት ስራዎች ባለመጠናቀቃቸው ምክንያት' የነባር ተማሪዎች መግቢያ ላልተወሰነ ጊዜ የተራዘመ መሆኑን ገልጿል፡፡ #DebreBerhanUniversity
👉 #እንጅባራ_ዩኒቨርሲቲ ለ4ኛ ዓመት መደበኛ ተማሪዎች አድርጎት የነበረውን ጥሪ አራዝሟል። የ4ኛ ዓመት መደበኛ ተማሪዎች የ2017 ትምህርት ዘመን ምዝገባ መስከረም 29 እና 30/2017 ዓ.ም ይከናወናል ተብሎ የነበረ ቢሆንም፤ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ባለመጠናቀቃቸው ምክንያት የምዝገባ ጊዜው ወደ ጥቅምት 14 እና 15/2017 ዓ.ም የተራዘመ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል። #InjibaraUniversity
👉 #ደብረማርቆስ_ዩኒቨርሲቲ ለነባር የቅድመ እና የድኅረ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች አድርጎት የነበረውን ጥሪ አራዝሟል። የነባር የቅድመ እና የድኅረ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች የ2017 ትምህርት ዘመን ምዝገባ መስከረም 29 እ ና 30/2017 ዓ.ም ይከናወናል ተብሎ የነበረ ቢሆንም፤ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ባለመጠናቀቃቸው ምክንያት የምዝገባ ጊዜው ላልተወሰነ ጊዜ የተራዘመ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል። #DebreMarkosUniversity
👉 #ደብረታቦር_ዩኒቨርስቲ የነባር የቅድመ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች የ2017 ዓ.ም የምዝገባ ጊዜን አራዝሟል። ዩኒቨርሲቲው የነባር የቅድመ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች የ2017 ትምህርት ዘመን ምዝገባ ከመስከረም 28 እስከ 30/2017 ዓ.ም ይከናወናል ብሎ የነበረ ቢሆንም፤ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ባለመጠናቀቃቸው ምክንያት የምዝገባ ጊዜው ላልተወሰነ ጊዜ የተራዘመ መሆኑን አሳውቋል። #DebreTaborUniversity
@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library