የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom

@aybcschool


ይህ የደቀ መዝሙርነት ትምህርት ቤት መማርያ ክፍል ነው!

የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom

22 Oct, 10:39


የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom pinned «ትምህርት 1:- ቅዱሳን መጻሕፍት ======================== ውድ ተማሪዎች: ይህ የመጀመሪያው ትምህርት በይፋ የሚለቀቅበት ቀን ነው። የዚህ ትምህርት ትኩረት "መጽሐፍ ቅዱስ" ነው። ቅዱሳን መጻሕፍት በሰብአዊ ሰው ድነት ላይ ያላቸውን ሚና ለማስተዋል እንዴት እንደተጻፉ: ማን እንደጻፋቸው: በአጻጻፋቸው ላይ የሰውን እና የእግዚአብሔርን ሚና በሰፊው ማጥናት ተገቢ ነው። የእግዚአብሔርን…»

የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom

20 Oct, 14:08


ትምህርት 1:- ቅዱሳን መጻሕፍት
========================

ውድ ተማሪዎች:
ይህ የመጀመሪያው ትምህርት በይፋ የሚለቀቅበት ቀን ነው። የዚህ ትምህርት ትኩረት "መጽሐፍ ቅዱስ" ነው።

ቅዱሳን መጻሕፍት በሰብአዊ ሰው ድነት ላይ ያላቸውን ሚና ለማስተዋል እንዴት እንደተጻፉ: ማን እንደጻፋቸው: በአጻጻፋቸው ላይ የሰውን እና የእግዚአብሔርን ሚና በሰፊው ማጥናት ተገቢ ነው።

የእግዚአብሔርን ቃል ተአሚነት ማወቅ ለመንፈሳዊ ሕይወት ጠንካራ መሰረት መጣል ነው::

ይህ ትምህርት በጽሑፍና በድምጽ የታገዘ ነው:: ጽሑፎቹን መጀመሪያ ካነበባችሁ በሁዋላ የድምፅ መልእክቶቹ ይለጠፋሉ:: በመጪው አርብ ሳምንት የመጀመሪያውን ፈተና ትወስዳላችሁ!!

ጥያቄ ካላችሁ በውስጥ መስመር መላክት ትችላላችሁ!

የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom

19 Oct, 13:02


ውድ ተማሪዎች:

በኮርስ መምሪያው መሰረት የመጀመሪያው ትምህርት የሚለጠፈት ጊዜ ደርሷል:: ነገ ይለጠፋል::

ሳምንቱን ሙሉ አጥንታችሁ አርብ ለት ፈተና ይሰጣል:: ፈተናው በቴሌግራም የሚሰጥ ነው::

መጽሕፍ ቅዱስ እና ማስታወሻ ደብተር ይዛችሁ በሚገባ እንድታጠኑ እናሳስባለን! ተባርኩ!!

የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom

19 Oct, 12:59


የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom pinned «መጽሐፍ ቅዱስን በግል: በጥልቀት: በጸሎትና በትህትና መመርመር እጅግ አስፈላጊ ነው:: አስተማሪዎች: ቀሳውስትና ካህናት ያሉትን በመስማት ብቻ ጠንካራ እና የሰይጣንን ፈተና ማለፍ የሚችል ሕይወት መመስረት አይቻልም:: ውድ ተማሪዎች: ከላይ የተለጠፈው ጸሑፍ ትምህርት ቤቱ ሁሉም የመጸሐፍ ቅዱስ ተማሪ ሊያደርገው የሚገባም ነገር አስቀምጧል:: አንብቡት! ተባረኩ!!»

የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom

15 Oct, 14:41


መጽሐፍ ቅዱስን በግል: በጥልቀት: በጸሎትና በትህትና መመርመር እጅግ አስፈላጊ ነው:: አስተማሪዎች: ቀሳውስትና ካህናት ያሉትን በመስማት ብቻ ጠንካራ እና የሰይጣንን ፈተና ማለፍ የሚችል ሕይወት መመስረት አይቻልም::


ውድ ተማሪዎች:

ከላይ የተለጠፈው ጸሑፍ ትምህርት ቤቱ ሁሉም የመጸሐፍ ቅዱስ ተማሪ ሊያደርገው የሚገባም ነገር አስቀምጧል:: አንብቡት!


ተባረኩ!!

የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom

14 Oct, 15:26


ውድ ተማሪዎች፡

የትምህርቱን መመሪያ በዚህ ጽሑፍ ውስጥ ታገኛላችሁ። ጥልቅ እና አስፈላጊ የሆኑ ትምህርቶች ተካትተዋል።

ላልሰሙ አሰሙ። ያልተመዘገበ ዘመድ፤ ወዳጅ ቤተሰብ ካላችሁ አስመዝግቡ!


ተባረኩ።

ትምህርት ቤቱ

የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom

13 Oct, 15:08


ውድ አዳዲስ ተማሪዎች:

እንኳን ወደ ትምህርት ቤታችን ገጽ በሰላም መጣችሁ:: ለትምህርቱ የሚያስፈልጉ ዝግጅቶችን ከነገ ጀምሮ መጠቆም እንጀምራለን::

ምናልባት ከዚህ በፊት ገጻችንን ተቀላቅላችሁ በተለያየ ምክንያት ትምህርቱ ያመለጣችሁ አሁንም እንደገና ከታች ያለው የመመዝገቢያ ፎርም በመሙላት ተመዝግባችሁ መማር ትችላላችሁ!

ጥያቄ ካላችሁ በውስጥ መስመራችን ላኩልን!

https://t.me/AYBibleClubVirtual

እግዚአብሔር ይባርካችሁ!

https://forms.gle/eRvb3pWDskXy7KVJ7

የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom

05 Oct, 11:51


የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom pinned «https://forms.gle/eRvb3pWDskXy7KVJ7»

የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom

03 Oct, 01:50


የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom pinned Deleted message

የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom

29 Sep, 00:15


https://forms.gle/eRvb3pWDskXy7KVJ7

የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom

07 Jun, 11:00


መግቢያ
በኃጥያት መውደቃችን የመለኮትን ንግግር በቀጥታ እንዳንሰማ አድርጎናል። እግዚአብሔር አምላክ በቀጥታ ሊናገረን ስላልቻለ በጸጋው በተለያዩ መንገዶች የፍቅር ቃሉን ላከልን። በብዙ ዘመናት በተለያዩ መንገዶች ከተናገረን በሁዋላ በመጨረሻው ዘመን በልጁ በክርስቶስ ኢየሱስ አማካኝነት ተናገረን። ቃሉ ሥጋ በመሆነ ጸጋንና እውነትን ተመልቶ በመካከላችን ተመላለሰ። ሙት የሆነው መንፈሳዊ ጆሮአችን ሊሰማው ስላልቻለ እንደጠላት ቆጠርነው። ሥጋዊው ጆሮ የሥጋን እንጂ የመንፈስን ድምጽ ሰለማይሰማ በፍቅር ሲቀርበን አልተቀበልነውም። “የምናገራችሁን ሁሉ አሁን ልታስተዉሉት አትቸሉም” በማለት በመንፈሳዊ ጎዳና የጀመርነውን እድገት በመንፈስ ቅዱስ ስጦታው እንድንቀጥል አደረገ።

የመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮት በሰው ሁለንተዊ የሕይወት ግንኙነትና ብልፅግና ላይ ወሳኝ ተፅዕኖ አለው። ለማህበረሰብ ደህንነት መሰረታዊ የሆኑ፤ የቤተሰብን ጥምረት ጠብቆ ለማኖር የሚጠቅሙ፤ ለአንድ አገር ብልፅግና የመሰረት ድንጋይ የሆኑ፤ ለግለሰብ የአላማ ጥንካሬ፤ ደስታ፤ ሞገስና የዘላለም ሕይወትን ለማግኘት ማረጋገጫ የሚሆኑ መሰረታዊ መመሪያዎችን ይገልጣል። የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ወሳኝ መዘጋጃ የማይሆንበት ምንም አይነት የሕይወት ደረጃና ልምምድ የለም። የእግዚአብሔር ቃል ሲጠና እና ሲነብብ የሰው ፍልስፍና ከሚሰጠው ጠቅላላ እውቀት በላይ ጠንካራ እና ሕያው የሆነ የአዕምሮ ጥንካሬን ይሰጣል። ለሰዎችም የባህርይ ጥንካሬ፤ አስተማማኝነትን፤ ማስተዋልን እና መልካም ፍርድን እየሰጠ ለእግዚአብሔር ክብርና ለአለም በረከት ያሳድጋቸዋል።

የእግዚአብሔር ቃል ሕይወታችንን በሙሉ የሚቆጣጠር፤ የኑሮ መመሪያችን፣ የሕሊና ሕጋችን ሊሆን ይገባዋል። የንግግራችን መለኪያ፤ የቃላችን መሰረት፤ የፍርዳችን መነሻ፤ የእምነታችን ምክንያት፤ የዝማሪያችን ምንጭ፤ የመነሳትና የመቀመጣችን እንዲሁም ሁለንተናችን ነው። የትምህርት፤ የቤተሰብን፤ የስራ፤ የእረፍት፤ የማንነት፤ የኢኮኖሚ መሰረታችን የእግዚአብሔር ቃል ይሁን። ወደ ከነዓን ከመግባታቸው ትንሽ ቀደም ብሎ እግዚአብሔር ለእስራኤላዉያን ያስታወሳቸው ይህንኑ ነበር። “እኔም ዛሬ አንተን የማዝዘውን ይህን ቃል በልብህ ያዝ። ለልጆችህም አስተምረው፥ በቤትህም ስትቀመጥ፥ በመንገድም ስትሄድ፥ ስትተኛም፥ ስትነሣም ተጫወተው። በእጅህም ምልክት አድርገህ እሰረው፤ በዓይኖችህም መካከል እንደክታብ ይሁንልህ። በቤትህም መቃኖች በደጃፍህም በሮች ላይ ጻፈው”። ኦሪት ዘዳግም 6:6-9

ይህ ትምህርት እርስዎንና ቤተሰብዎን በእግዚአብሔር ቃል ለማነጽ፤ እንዲሁም የኢየሱስ ደቀ መዝሙር በመሆን ለሌሎች ይህን የከበረ ቃል ያሰሙ ዘንደ ለማስታጠቅ የተዘጋጀ ነው። በጸሎትና በትጋት ሲጠና መንፍስ ቅዱስ ሕይወትን በቃሉ ይለውጣል። በሁሉም ቦታ የክርስቶስን መንፈስ ለማንጸባረቅ ያግዛል።


የወጣቶች መጽሐፍ ቅዱስ ማሕበር
ደቀ መዝሙርነት ትምሕርት ቤት
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ

የደቀ መዝሙርነት ት/ቤት - Classroom

23 Jan, 20:41


Channel created