"መንክረ-መንክራት"
የአንጾኪያው ሊቀ ጳጳሳት ቅዱስ ባስልዮስ እንዳስተማረው።
የእግዚአብሔር ገቢረ ተኣምራት ሁሉ ግሩማን ናቸው አይመረመሩም። ቅዱስ ዳዊት ሥራህ ግሩምና ድንቅ ነው ይላልና....
ግና ከድንቅም ድንቅ አምላክ በሥጋ በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት የተወሰነበት ከሃሊነቱ አይደንቅም..?? አይረቅም..? ኢሳይያስ ስለ ነገረ ትሥጉቱ ሲናገር የተወለደው ሕጻና ድንቅ መካር ኀያል አምላክ የዘላለም አባት የሰላም አለቃ ይለዋልና..(ኢሳይያስ 9፥6) መንክር(ድንቅ) የሚባል ከሕሊናት ሁሉ የሚያልፍ የማይመረመር ሥራ ነው።
የአንጾክያ ሊቀ ጳጳሳት ባስልዮስ ሲናገር "እስመ ኢሳይያስ ነቢይ ክቡር በውስተ ነቢያት ሰመዮ መንክረ መንክርኒ ውእቱ ግብር ዘኢይትረከብ..." 'ከነቢያት መካከል የከበረ ነቢይ ኢሳይያስ መንክር(ድንቅ) ብሎታልና መንክር(ድንቅ) የሚባልም የማይመረመር ሥራ ነው። (ሃይ-አበው ዘባስልዮስ ም 96 ቍጥር 27)
ዓለማትን በእጁ የያዘ አሕዛብ ሁሉ በፊቱ በገንቦ እንዳሉ የውሃ ጠብታ የሆኑለት ሰማይ ዙፋኑ ምድርም መረገጫው የሆነ አምላክ ሥጋ ሆነ አበው እንደ ተናገሩትም <<ወልደቱሂ ኮነ ብርሃነ መድኀኒትነ>> (ልደቱም የደኅንነታችን መታወቂያ ሆነልን) ሃይ-አበው ዘባስልዮስ ምዕ 96 ቍጥር 23)
መልካም ዕለተ ሰንበት 🙏