እውነታዊ ታሪኮች ✌ (@yenebiyat_tarik) Kanalının Son Gönderileri

እውነታዊ ታሪኮች Telegram Gönderileri

እውነታዊ ታሪኮች ✌
ይህ ግሩፕ የተከፈተበት ዋነኛው አላማ
😯 አጓጊ ታሪኮችን
😯 የነቢያቶችን ታሪኮች
😯 የነቢያት አስተምህሮቶች
😯 ሀዲሶችን
የምንለቅበት የምንማማርበት channel
9,452 Abone
683 Fotoğraf
204 Video
Son Güncelleme 01.03.2025 03:05

እውነታዊ ታሪኮች tarafından Telegram'da paylaşılan en son içerikler


የኻን ዩንስ ጎዳናዎች በቀሳም ወታደሮች ተጥለቅልቀዋል። ከሲንዋር ቤት ፍርስራሽ ስር የወራሪዋን ሶስት እስረኞች ለቀይ መስቀል ለማስረከብ ከሜዳው ተሰይመዋል። 

ሁሉም ካልተፈቱ የገሀነም እሳት በጋዛ ላይ ይዘንባል የተባለለት ዛቻና መግለጫ የቀሳሞችን ውሳኔ አልቀለበሰም። ሁሉንም እስረኞች ሊፈቱ ይቅርና አሜሪካ እንዲፈቱላት የጠየቀችው ስድስት ዜጎቿም አይለቀቁም። ትራምፕም ሆነ ኔታንያሁ ከሙጃሂዶቹ ፍላጎት ውጪ መራመድ አልቻሉም።

ከመረካከቢያ መድረኩ ጀርባ የጀግንነት ጥቅሶች በደማቁ ተፅፈዋል። እንዲህ የሚሉ መፈክሮች ከባነሩ ሰፍረዋል:-
"ወደ ቁድስ እንጂ ስደት የለም"
"ኢየሩሳሌም ሆይ! ወታደሮችሽ መሆናችንን መስክሪ"
"እንደ ፀሐይ ክር ይህን ሁሉ ተሻገርን"

እነርሱ ቀሳሞች ናቸው ትራምፕን ሳይቀር ያስገረሙ
  "የተለዩ ግትሮች ሲበዛ ከባድ ከሆኑ ሰዎች ጋር ነው እየተደራደርን ያለነው" ብሎ ነበር ድርድሩ ገና ከመጀመሩ።


                 Mahi Mahisho

@yenebiyat_tarik

🍃 #ሱረቱ አል-ፋቲሀ..........የአላህን ቁጣ
ትከላከላለች::

🍃 #ሱረቱ ያሲን .........ከቂያማ ቀን ጥማት
ትከላከላለች::

🍃 #ሱረቱ አል-ዱኻን..........ከቂያማ ቀን ጭንቀት
ትከላከላለች::

🍃 #ሱረቱ አል-ሙልክ..........ከቀብር ቅጣት
ትከላከላለች::

🍃 #ሱረቱ አል-ካፊሩን..........በሞት ሰአት ከኩፍር
ትከላከላለች::

🍃 #ሱረቱ አል ኢኽላስ..........ከኒፋቅነት
ትከላከላለች::

🍃 #ሱረቱ አል-ፈለቅ..........ከምቀኝነት
ትከላከላለች::

⭐️ #አንድ #አይሁዳዊ ሙስሊሞችን ፊትና ውስጥ
ለማስገባት ይፈልግና ወደ ሙስሊሞች ሀገር ጉዞ
ይጀመራል፡፡ ልክ እንደደረሰም የከተማይቷ ጫፍ
ላይ አንድ እረኛ ወጣት ያገኛል አስ እስኪ ፈተናውን
#ከሱ ልጀምር ይላል ከብዙ ጫወታዎች በውሀላ

#ሙስሊም በመምሰል ጥያቄውን ይሰነዝርበታል:-

#አይሁዳዊው:-ይህ ቁርአን ግን የበዛ
አይመስልህም ለምን ግን ተመሳሳይ ተመሳሳይ
የሆኑትን ቦታዎች አጥፍተን ከ30 ጁዝ
አንቀንሰውም እንደገና 30 ጁዝ መሀፈዙ ራሱ
ይከብዳል...

#እረኛው #ወጣት :-አዎ ልክ ነህ ግን አንድ ጥያቄ
ልጠይቅህ ቁርአን ውስጥ እየተደጋገሙ
የሚመጡትን ከማጥፋታችን በፊት ከሰውነትህ
ውስጥ ተደጋጋሚ የሆኑትን አናጠፋም!! #ለምሳሌ
☞ከአይኖችህ ውስጥ አንዱን
☞ከጆሮዎችህ ወስጥም
አንዱን
☞ከእግሮችህ ውስጥም አንዱን......

#አይሁዳዊውም በጣም ይደናገጥና እንዲህ
ይላል:-
#እረኛዎቻቸው አንዲህ ከሆኑ ኡለማኦቻቸው ምን
ያህል ጠንካሮች ናቸው ሲል ይደነቃል ...
ወድያውም ከተማዋን ለቆ ይወጣል::
Like እና ሼር ያድርጉ!

🔗SHARE 🔗SHARE
▬▬▬▬▬▬▬▬
@yenebiyat_tarik share&join
▬▬▬▬▬▬▬▬

ለ12 አመታት ማየት ያልቻለችው ሳዑዳዊቷ እንስት ማየት ቻለች

ኑፍ አል ራሺዲ የተባለችው ሳዑዳዊት የአይኗ ብርሀን  ከተመለሰ በኋላ በአንድ ቀን የሦስቱ ወንድ ልጆቿን ሰርግ  ማየቷ ተነግሯል።

ከ12 አመት በፊት አይኗ የጠፋባት ሳውዲያዊት ሴት በሀገሯ ቀዶ ጥገና ከተደረገላት በኋላ በቅርቡ ለማየት ችላለች።

  በኬሚካል ሳቢያ እይታዋን ያጣችው  ኑፍ አል ራሺዲ ማየት ባለመቻሏ  የደረሰባትን ስቃይ ስታስታውስ እንባዋን መቆጣጠር አልቻለችም።

ኑፍ አል ራሺዲ የተባለችው ሳዑዳዊት የአይኗ ብርሀን  ከተመለሰ በኋላ በአንድ ቀን የሦስቱ ወንድ ልጆቿን ሰርግ  ማየቷ ተነግሯል።

ከ12 አመታት የስቃይ ጊዜ በኋላ የማየት ግለሰቧ    ከቅድስቷ ከተማ መዲና መኪናዋን ከሴት ልጆቿ ጋር በመንዳት ወደ ዋና ከተማዋ ሪያድ አድርሳለች።

ኑፍ ከሳውዲው ቴሌቪዥን ጋር ባደረገችው ቃለ ምልልስ መኪናዋን ወደ ሪያድ እራሷ ለመንዳት ቃል መግባቷን እና አስደሳች እና ደህንነቱ የተጠበቀ ጉዞ የመሄድ ህልሟ እውን መሆኑን ገልጻለች።

ዓይኔን ካገኘሁ ወደ መካ ሄጄ ዑምራ እንደማደርግ  ቃል ገብቻለሁ ያለችው ግለሰቧ   "አላህን የተመሰገነ ይሁን ዑምራን አደረኩ" ብላለች።

በመኪናዬ ከመዲና ወደ ሪያድ ለመሄድም ቃል ገብቸ ነበር ምኞቴም ተፈጽሟል፣ ከሴት ልጆቼ  ጋርም   ጥሩ አሳልፌያለሁ ስትትል ተናግራለች።

ኑፍ የተሳካ ቀዶ ጥገና ያደረገችበትን  የሆስፒታሉን ሰራተኞች  ያመሰገነች ሲሆን ለሰራተኞቹ የክብር ስነ ስርዓት ለማድረግ እንደምትፈልግ ተናግራለች።

ዶ/ር ሳሚ ቢን ሃሚድ የተባሉት የኮርኒያ አማካሪ አንዳንድ የቤት ውስጥ ኬሚካሎች ለዓይን እይታ ስለሚያደርሱት አደጋ አስጠንቅቀዋል።

ለእይታ መጥፋት ከሚዳርጉ ዋና ዋና ምክንያቶች መካከል የቤት ውስጥ ሳሙናዎች እና የመኪና ባትሪዎች መሆናቸውን ጠቁመው ከእነዚህ ንጥረ ነገሮች ጋር በተያያዘ ጥንቃቄና የደህንነት እርምጃዎችን መከተል ያስፈልጋል ብለዋል።

@yenebiyat_tarik
@yenebiyat_tarik

መልካም ጁምዓ

اللهم صلى  على نبينا محمد

ስ ለ ሻዕባን ወር አጫጭር ጥቆማዎች በተለይ ስለ ኒስፍ ለይል


☞ በሸይኽ ሙሐመድ ሷሊህ አል ዑሰይሚን

«ሙስሊሞች ሆይ ያለነው በሻዕባን ወር ላይ ነውና በዚህ ወር ዙርያ አንድ ስድስት ነጥቦችን በማውሳት ልንከተለው ስለሚገባን ግዴታችን እናብራራለን።

📍የመጀመርያው ነጥብ
የሻዕባን ወር ከሌሎች ወራት በተለየ ሁኔታ በፆም ይለያልን? አዎን ይለያል ። ምክንያቱም ነቢዩ [ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም] «በዚህ ወር ፆም ያበዛሉ። ከወሩ ጥቂት ቀናት እስኪቀራቸው ወሩን ይፆሙት ነበርና።»
በዚህም ሱና መሰረት የአላህ መልእክተኛን [ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም] በመከተል በዚህ በሻዕባን ወር ፆም ማብዛት አለብን።

📍ሁለተኛው ነጥብ
የሻዕባን ወር አጋማሽ ቀን ፆምን የተመለከተው ነው። ይህንን ቀን ለይቶ መፆምን የሚመለከቱ ከነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ያልተገኙና ትክክለኛ ያልሆኑ ደካማ ሀዲሶች ተነግረዋል። በነዚህ ተመርኩዞ ይህንን ዒባዳ መፈፀም ደግሞ አይቻልም። ከነቢዩ ለመተላለፉ ባልተረጋገጠ ማንኛውም ነገር አላህን ማምለክ አይፈቀድም። በመሆኑም የሻዕባን አስራ አምስተኛው ቀንን ለይቶ መፆም የሌለ ነገር ነው። ከመልእክተኛው ለመገኘቱ መረጃ ከሌለ ደግሞ ቢደዐ ነው።

📍ሶስተኛው ነጥብ፤ የሻዕባን ወር አስራ አምስተኛው ቀን ሌሊት ትሩፋትን ይመለከታል።
ልክ ቀኑን መፆም የተረጋገጠ መረጃ እንደሌለው ሁሉ ለሌሊቱም ከሌሎች ሌሊቶች በላጭ ነው ተብለው የተነገሩት ሀዲሶች ከነቢዩ [ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም] ለመነገራቸው ትክክለኛ መረጃ የሌላቸው ደካማዎች ናቸው።
ስለሆነም የሻእባን አጋማሽ ሌሊት ልክ እንደ ረቢዕ ወር ሌሊት፣ እንደ ረጀብ ወር ሌሊት እንጂ የተለየ ነገር የለውም። ተነገረ የተባለውም መረጃ ቀድሜ እንደገለፅኩት ደካማዎች ናቸው።

📍አራተኛው ነጥብ
ይህችን የአስራ አምስተኛዋን ሌሊት ለየት አድርጎ ዝግጅት ፈጥሮ ማሳለፍ ቢደዐ ነው። ነቢዩ [ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም] ለየት አድርገው ያሳዩን፣ ሌሊቱን የሚሰገድ አምልኮትም ዝግጅትም የለምና። ስለዚህ ምሽቷ ልክ እንደ ሌሎች ምሽት ናት። አንድ ሰው ከዚያች ሌሊት በፊትም የለይል ሰላት መስገድ ልምዱ ከነበረ በዚያች ሌሊትም ተነስቶ መስገዱ ልክ እንደበፊቱ ነውና ችግር የለውም። ካልሆነና በፊት የማይሰግድ ከነበረ ዛሬ በሻዕባን "ለይለቱ ኒስፍን" ለየት አድርጎ መስገድ የለበትም። ምክንያቱም ከአላህ መልዕክተኛ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ያልተገኘ ተግባር ነውና። ከዚህም የከፋው ደግሞ አንዳንዱ ሰው የሆነ ያህል ረከዓ በዚህ ምሽት ይሰገዳል በሚል ለየት ያደርገዋል። ይሁንና ከነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ይህንን ምሽት ነጥሎ ለየት ማድረግ ስላልተገኘ ይህችን ምሽት በሰላት ልዩ አናደርግም።

📍አምስተኛው ነጥብ
የአላህ ሱብሃነሁ ለነገሮች የሚያደርገው ውሳኔ በሻዕባን አስራ አምስተኛዋ (አጋማሽ) ምሽት ነውን

ምላሹም አይደለም ሲሆን፤ ምሽቷም የመወሰኛይቱ ሌሊት [ለይለቱል ቀድር] አይደለችምና ነው። ምክንያቱም "ለይለቱል ቀድር" በረመዳን ውስጥ የምትገኝ ምሽት ናት። ሃያሉ አላህ እንዳለው፤
”إنا انزلناه“
"እኛ አወረድነው" ማለትም ቁርኣንን ለመጀመርያ ግዜ ያወረድነው ማለቱ ነው። ይህም ሙሉ ምዕራፉ ሲነበብ እንዲህ ይላል፤

إِنَّا أَنزَلْنَاهُ فِي لَيْلَةِ الْقَدْرِ ﴿١﴾ وَمَا أَدْرَاكَ مَا لَيْلَةُ الْقَدْرِ ﴿٢﴾ لَيْلَةُ الْقَدْرِ خَيْرٌ مِّنْ أَلْفِ شَهْرٍ ﴿٣﴾ تَنَزَّلُ الْمَلَائِكَةُ وَالرُّوحُ فِيهَا بِإِذْنِ رَبِّهِم مِّن كُلِّ أَمْرٍ ﴿٤﴾ سَلَامٌ هِيَ حَتَّىٰ مَطْلَعِ الْفَجْرِ ﴿٥﴾
Al-Qadr☞ القدر:- [1-5]

[እኛ (ቁርኣኑን) በመወሰኛይቱ ሌሊት አወረድነው፡፡ (1)መወሰኛይቱም ሌሊተ ምን እንደ ኾነች ምን አሳወቀህ? (2)መወሰኛይቱ ሌሊት ከሺሕ ወር በላጭ ናት፡፡ (3) በርሷ ውስጥ መላእክትና መንፈሱ በጌታቸው ፈቃድ በነገሩ ሁሉ ይወርዳሉ፡፡ (4) እርስዋ እስከ ጎህ መውጣት ድረስ ሰላም ብቻ ናት፡፡(5)]
ይህ ክስተትና ምሽቱም መቼ እንደሆነ ሲገልፅ እንዲህ ይላል፤

(شَهْرُ رَمَضَانَ الَّذِي أُنزِلَ فِيهِ الْقُرْآنُ هُدًى لِّلنَّاسِ وَبَيِّنَاتٍ مِّنَ الْهُدَىٰ وَالْفُرْقَانِ ۚ فَمَن شَهِدَ مِنكُمُ الشَّهْرَ فَلْيَصُمْهُ ۖوَمَن كَانَ مَرِيضًا أَوْ عَلَىٰ سَفَرٍ فَعِدَّةٌ مِّنْ أَيَّامٍ أُخَرَ ۗ يُرِيدُ اللَّـهُ بِكُمُ الْيُسْرَ وَلَا يُرِيدُ بِكُمُ الْعُسْرَ وَلِتُكْمِلُوا الْعِدَّةَ وَلِتُكَبِّرُوا اللَّـهَ عَلَىٰ مَا هَدَاكُمْ وَلَعَلَّكُمْ تَشْكُرُونَ) البقرة:- 185

[(እንድትጾሙ የተጻፈባችሁ) ያ በርሱ ውስጥ ለሰዎች መሪ ከቅን መንገድና (እውነትን ከውሸት) ከሚለዩም ገላጮች (አንቀጾች) ሲኾን ቁርኣን የተወረደበት የረመዳን ወር ነው፡፡ ከእናንተም ወሩን ያገኘ ሰው ይጹመው፡፡ በሽተኛ ወይም በጉዞ ላይ የኾነም ሰው ከሌሎች ቀኖች ቁጥሮችን (በልኩ) መጾም አለበት፡፡ አላህ በእናንተ ገሩን (ነገር) ይሻል፡፡ በእናንተም ችግሩን አይሻም፡፡ ቁጥሮችንም ልትሞሉ አላህንም ቅኑን መንገድ ስለመራችሁ ታከብሩትና ታመሰግኑት ዘንድ (ይህን ደነገግንላችሁ)፡፡ (185)]

በዚህም መረጃ መሰረት ለይለቱል ቀድር ማለትም ፈጣሪያችን አላህ ለማንኛውም ነገር ሁሉ አመታዊ ውሳኔ የሚሰጥበት ምሽት በረመዳን ወር ውስጥ የምትገኝ አንዲት ሌሊት መሆኗን እንረዳለን። ምክንያቱም ሌሊቷ ቁርኣን የወረደባት ሌሊት ነች ። ቁርኣን ደግሞ የወረደው በረመዳን ወር ነውና የመወሰኛይቱ ምሽትም የምትገኘው በረመዳን እንጂ በሌላ ወር አይደለም። ስለሆነም የሻዕባን አጋማሽ ሌሊት  "ለይለቱል ቀድር" የመወሰኛይቱ ምሽት አይደለችም። በዚያች ሌሊትም ለአመቱ የሚሆን ምንም የሚወሰን ነገር የለም።

📍ስድስተኛው ነጥብ፦ የሻዕባን ወር አጋማሽ ቀን ላይ አንዳንዶች ምግብ አዘጋጅተው ለድሆች በሚል የሚያከፋፍሉትና የእናት እራት፣ የአባት እራት ወይም የወላጆች እራት የሚሉት [እንዲሁም ባገራችን የእህል ዘሮችን ባንድ ላይ ሰብስቦ በመቀቀልና ከዚያም መጀመርያ ግቢ ውስጥና ውጪም በመበተን አመቱ የጥጋብ የርጋታ ይሁንልን የሚሉት] ሁሉ ከነቢዩ ያልተላለፈልን ከሰሃቦችም ሪድዋኑላሂ አለይሂም ያልተገኘ መጤ የሆነ ቢድዐ ነው።

👆 እነዚህን ስድስት ነጥቦች ጠቅሼ ብቆጥራቸውም ሌሎች ላብራራቸው የሚገቡ ሆነው ያለፍኳቸው እንዳሉ ግልፅ ነው።  አላህ እኛንም እናንተንም ሱናን የሚያሰራጩ፣ ቢድዐን የሚያስጠነቅቁና ተመርተው የሚመሩ (ቅን ሆነው የሚያቀኑ) ያድርገን። ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም በጁምዓ ኩጥባቸው ወቅት እንደገለፁት ከምሪቶች ሁሉ በላጩ የሳቸው ምሪት ነውና ቅኑን መንገድ የሚከተሉ፣ በሳቸው አመራርም የሚመሩ ያድርገን። «በማስከተል፤ ከንግግሮች ሁሉ በላጩ የአላህ ኪታብ ነው። ከአመራሮች ሁሉ በላጩም የሙሀመድ ምሪት ነው። መጥፎ ጉዳይ ማለት መጤዎቹ ናቸው። ሁሉም ፈጠራዎች ጥመት ናቸውና።»ብለዋል።


منقول

ኒስፋ ሸዐባን

የዛሬዋ ሌሊት

اليوم بعد المغرب هيجتمع شرف الزمانين.....
اليوم  بعد المغرب إن شاء الله هتبدأ ليلة النصف من شعبان وتوافقها ليلة الجمعة.

ليلة النصف من شعبان هي الليلة التي أرضى فيها الله رسوله ﷺ وجَبَر خاطره بالقبلة التي كان يتمناها ويرضاها....

وقد قال عطاء بن يسار عنها: ما من ليلة بعد ليلة القدر أفضل من ليلة النصف من شعبان، يتنزل الله تبارك وتعالى إلى السماء الدنيا، فيغفر لعباده كلهم، إلا لمشرك أو مشاجر أو قاطع رحم.

ادعوا كثيرًا، واستغفروا كثيرًا، وأكثروا من الصلاة على النبي وذكِّروا غيركم.. فمن دعا إلى هُدىً كان له من الأجر مثل أُجورِ من تَبِعهُ لا ينقصُ ذلك من أُجُورِهِم شيئًا

اللهم أعِنّا وبلِّغنا رمضان في عفوٍ وعافية

⭕️ የኮንቲነር ቤቶችና ጊዜያዊ መጠለያ ድንኳኖች በረፈህ በኩል መግባታቸውን ቀጥለዋል። ጋዛን መልሶ ለመገንባት ማሽኖች ከባባድ መኪኖችን ጨምሮ ሎደር ዶዘርና ግሬደር መግባት ጀምሯል። ተገጣጣሚ ቤቶች ነዳጅ የጫኑ መኪናዎች የህክምና ቁሳቁሶች ወደ ጋዛ በመዝለቅ ላይ ይገኛሉ።

ይህን ተከተረሎ
"ሥነ ምግባራዊ ክስረት በፖለቲካዊ ውድቀት የተሞላ ስምምነት። ባጭሩ ሀማስ አስፈራርቶ የሚፈልገውን አገኘ" ሲል ኢብኑ ገፊር መናገሩን የወራሪዋ ሚዲያ ዘግቧል።

⭕️ የፍልስጤም ሙጃሂዶች በማዕከላዊ ጋዛ ሰርጥ ኑሰይራት ካምፕ አቅራቢያ በሲቪል መኪና ውስጥ ሰርገው የገቡ የወራሪዋ የስለላ ድርጅት አባል ናቸው የተባሉ ሶስት ሰዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ይፋ አድርጓል።

ተጠርጣሪዎቹ መኪናቸውን እያሽከረከሩ ለመሸሽ ቢሞክሩም በስተመጨረሻ በሙጃሂዶቹ እጅ ወድቀዋል።

                 Mahi Mahisho

@yenebiyat_tarik

ሁላችሁም እንደ ሚታቁት  ለታላቁ ረመዳን ወር  ሁለት ሳምንት ብቻ ነው የቀረው እኛም በየቤታችን የለያዩ ቅድመ-ዝግጅት እያደረግን እንገኛለን ነገር ግን የቲሞች እና አቅመ ደካማዎች የኛን እጅ እየጠበቁ ይገኛሉ ሰለሆነም ሁላችንም #ሁለት_መቶ_ብር ( 200) ብቻ በመውጣት የ10 ሰው የረመዳን አስቤዛ እንሸፊን ።

የአንድ ሰው ሙሉ የረመዳን አስቤዛ 4500 ነው ።
እዚህ ግሩፕ ውስጥ ያለነው ሰዎች ሙሉ የአንድ ሰው የረመዳን አስቤዛ በግል መሽፈን ባንችል እንኳን 200 ብር ብቻ በመዋጣት የ10 ሰው የረመዳን አስቤዛ መሽፈን እንችላለን ።

#በሁለት_መቶ_ብር ብቻ ፆመኛን በማስፈጠር የነብዩን (ሰ.ዕ ወ) ብስራት እንቋደስ !

#ሁላችንም ተሳታፊ በመሆን የቲሞች እና አቅመ ደካማዎች ረመዷንን በደስታ እንዲያሳልፉ እናድርግ።
ዘመቻ  #ከዛሬ_ሰ_ ጀምሮ_እስከ_ጅምዓ የሚቆይ ይሆናል።

የክፍያ ዘዴዎች
1) commercial bank (CBE)
1000674564078
2) zamzam Bank
0028509090101
በቴሌብር በfundraising (ለበጎ አድራጎት) በመጭን ወደ ታች በመውረድ Junudullah የሚል በመፈለግ ገቢ ማድረግ ይችላሉ ።
የቴሌብር ሌላ አማራጭ
በmerchant ID 901777
  Operator  ID 187137 መጠቀም ይችላሉ ።

ግልጽ ያልሆነ ነገር ከለ እንዲሁም ደረሴኝ በTelegram ለመላክ በዚህ ስ.ቁ +251937067800 ተጠቀሙ ።

ለሌሎች ሰዎች ሼር በማድረግ የአጅሩ ተካፋይ እንሁን።
@junudullahcharity
#share_share_share

~✿❁࿐❁✿~
ስንደናቀፍ፣ ስንደነግጥ፣ ስንቸገር፣ ስንታመም፣ ተስፋ ስንቆርጥ ...ሶላት የተዛባ የሕይወት ሚዛናችንን ማስተካከያ ናት።

ሲከፋን፣ ስንቆጣ፣ ስንበሳጭ ... ድንበር አልፈን እንዳንሄድ፣ ምላሻችን መጥፎ እንዳይሆን ሶላት የሕይወታችን መቆጣጠሪያ ፍሬን ናት፡፡

ሶላት ወደ ዋናው መንገድ የምትመልሰን መሪያችን፤ ከዋናው ጣቢያ ጋር የምታገናኘን ኔትወርካችን ናት።
ያ ረብ ሶላትን አስወድደን፡፡ በሱና እና በግዴታው ከሚፀኑትም አድርገን።


@yenebiyat_tarik