Последние посты የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe (@yahyanuhe) в Telegram

Посты канала የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe

የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe
﷽ | Muslim | Theology | Comparative Religion | Philosophy | Student | Teacher |
17,102 подписчиков
1,132 фото
242 видео
Последнее обновление 06.03.2025 16:56

Похожие каналы

Emmersive Learning
3,373 подписчиков
ASHRAF COMPARATIVE
1,719 подписчиков

Последний контент, опубликованный в የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe на Telegram

የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe

14 Jan, 08:53

7,990

አንዷ ፕሮቴስታንት ደግሞ የዛሬ አመት አካባቢ ካሊፎርኒያ ላይ እሳት ይታየኛል የሚል "የትንቢት ንግግር" ተናግራለች ብለው ፕሮቴስታንቶቹ በመደነቅ ሲያዘዋውሩት አየሁ። የካሊፎርኒያ ግዛት ማለት በየአመቱ እሳት የማይጠፋበት ግዛት ነው። ይህ የተለመደ ኹነት ከመሆኑ ጋር ትንበያ የሚፈልግም አይደለም። አስቡት "ሀገራችን ላይ የኑሮ ውድነቱ በሚቀጥለው አመት ካሁኑ ይብሳል" ብየ ተናግሬ የሚቀጥለው አመት ላይ ጠብቃችሁ በንግግሬ ስትደነቁ..!በሁሉም ነገር "አሜን" አትበሉ..!

⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/Yahyanuhe
የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe

13 Jan, 18:36

7,036

ከጅል ሰው ጋር መሟገት፣ ጅሎቹ ሁለት መሆናቸውን ከማረጋገጥ የዘለለ ፋይዳ የለውም።

https://t.me/Yahyanuhe
የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe

12 Jan, 12:28

6,824

ክርስቲያን የሆነ ሀኪም ብለህ የስራ ማስታወቂያ ከምታወጣ፣ የሆስፒታሉን ራዕይ፣ተልእኮ እና እሴቶች የሚቀበል ብለህ ታለዝበዋለህ።

ትርጉሙ ግን ያው ነው።

ምስሎቹን ይመልከቱ

https://t.me/Abuyusra3
የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe

12 Jan, 08:42

5,843

በሎስ አንጀለስ የእሳት አደጋ የማርያም ምስል ያለበት ቤት አለመቃጠሉን የሚገልጽ የቆየ ምስል በመያዝ ካቶሊክን የሚተቹት የኛው ወገኖች ሰፊ ትንታኔ እያቀረቡ ነው። ቤቱ እሳት አደጋን መከላከል በሚችሉ ቁሳቁሶች መገንባቱን ባለቤቱ መናገሩን የሰሙ አልመሰለኝም። የቴክኖሎጂ ዘመን ባይሆን ኑሮና ስህተቱ በፍጥነት ባይታረም ኑሮ ለአንድ የገድል ታሪክ መፈጠር ምክንያት ይሆን ነበር።

⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/Yahyanuhe
የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe

11 Jan, 20:01

615

የገዛ ህዝባቸውን በእምነታቸው ምክንያት ሒጃብና ሶላት ለሚከለክል የፖለቲካ ኢሊት ምርኩዝ የሆነ ግለሰብ ሌላን ሰው ሙስሊምነቱን በመጠቀም በሴኩላሪዝም ለማሸማቀቅ ሲሞክር ማየት ያስገርማል።
የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe

10 Jan, 06:57

2,293

ዲያቆን ቴዎድሮስ አበበ ከሰሞኑ የነበረውን የ"አእላፋት መዝሙር" አስመልክቶ ተቃውሞውን አሰምቷል። የቤተ ክርስቲያኗን ስርኣት የተከተለ አይደለም የሚል ነው ወቀሳው፣ ይህ አካሔድ የምዕራባውያኑን የካቶሊክ መንገድ የሚወዱ "አፍቃሪ ካቶሊኮች" ሀሳብ እንደሆነ ገልጿል። እንዳለውም የነዚያን ግብረ ሰዶማውያን ሰዎች አካሔድ መቀበል ከሆነ ጉዳዩ እንደ ሀገር ለሌላውም ስጋት እንደሆነ ግልጽ ነው።

https://vm.tiktok.com/ZMkPxUFrC/
የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe

09 Jan, 07:59

2,684

የዚህ ግሩፕ አላማ በቲክቶክ የሚለቀቁ የንፅፅር ቪዲዮዎች ኮፒ ሊንክ እና ሼር ተደርገው ቫይራል እንዲወጡ ማድረግ ነው። ወደዚህ ግሩፕ የምትቀላቀሉ ሰዎች ለዚሁ ተልዕኮ ብቻ የምትፈልጉ መሆኑን ማወቅ ይኖርባችኋል።

® https://t.me/ethiomuslimTik
የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe

07 Jan, 15:11

3,307

"አምላክ ከፈጠራቸው ፍጡራን ማህጸን ተወልዷል" የሚለውን ታሪክ ከልቡ የተቀበለን ሁሉ አላህ ቀናውን መንገድና አቅሉን እንዲመልስለት ዱዓየ ነው።
የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe

06 Jan, 18:00

4,352

የባቲ ከተማ የቀድሞ ከንቲባና እና የአቢዘር ማኅበረሰብ አቀፍ ልማት ድርጅት የፕሮጀክት ኃላፊ የነበሩት አቶ አህመድ ለስራ ጉዳይ ከከሚሴ ሲመለሱ በደረሰባቸው የመኪና አደጋ ወደ አኼራ ሒደዋል፣ አላህ ይዘንላቸው ቀብራቸውንም ሰፊ ያድርግላቸው። ለየቲም ጉዳይ ሲባትሉ ውለው የዱንያ ፍጻሜያቸው በዚያው መንገድ ሆነ፣ አላህ ልፋታቸውን ከተቀበላቸው ያድርጋቸው።

አቢዘር ከምስረታው ጀምሮ በርካታ ፈተናዎችን የተሻገረ ተቋም ነው። ከብርቱ ወንድማችን ጀማል እልህ አስጨራሽ ጥንሰሳ ጀምሮ አላማውን የተረዱ በርካቶችን ከጎኑ አሰልፎ ሰፊ ስራዎችን እየሸፈነልን ያለ ተቋም ነው። አላህ ይቀበላችሁ፣ ወንድማችሁንም የሚተካ የተሻለ መሪ ይወፍቃችሁ።
የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe

06 Jan, 14:30

3,653

ኦርቶዶክስን ከማደስ ወደ ማዘመን

(ሀሳቡ ላይ ብቻ አስተያየት ስጡ፣ ስድብ አይፈቀድም)

የተሐድሶ እንቅስቃሴ እንዳቆጠቆጠ ገደማ ማኅበረ ቅዱሳን አንድ አነስተኛ ጥናት አዘጋጅቶ ነበር። በወቅቱ ተሐድሶ የሚባሉ አካላት ዋነኛ መከራከሪያ የነበረው ራሳቸውን የቤተ ክርስቲያኗ አለኝታና ተቆርቋሪ አድርጎ ማቅረብ ነበር። ቤተ ክርስቲያኗን እንደሚቀበሉና ጠንካራ ቤተ ክርስቲያን እንዲኖር እየታገሉ እንዳሉ አብዝተው ይገልጹ ነበር። ማኅበረ ቅዱሳን ይህንን እንዲህ ሲል ይጠቅሰዋል፦

"ተሐድሶዎች በርግጥ ኦርቶዶክሳውያን ናቸው? የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የምታምነውን ይቀበላሉ? ለአንዳንዶች እንደሚመስላቸውስ ተሐድሶ የቤተ ክርስቲያኒቱ አስተዳደራዊ ችግሮች ተፈትተው ጠንካራ የሆነች ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ለማየት የሚደረግ ትግል ነው?"

(የተሐድሶ መናፍቃን ዘመቻ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ላይ፥ አዘጋጅ ማኅበረ ቅዱሳን ገጽ 36)

መጽሀፉ ይህንን ጥያቄ ያነሳበት ምክንያት የተሐድሶ ሰዎች ከነሱ በላይ የቤተ ክርስቲያኗ ተቆርቋሪ የሌለ እስኪመስል ድረስ ሰፊ ሽፍን እንቅስቃሴ ያደርጉ ስለነበር ነው። መጋቢ በጋሻው እና ዘማሪ ትዝታው (በድሮ የማዕረግ ስማቸው) EBS ቴሌቭዥን ላይ በገዙት የእሁድ ጠዋት የአየር ሰአት ትልቅ ሽፋን ይሰጡ የነበሩት የእቅበተ እምነት ስራዎች ላይ ነበር። በተለይም በፕሮቴስታንት በኩል የሚነሱ ጥያቄዎችን ለመመለስ በመሞከር የኦርቶዶክሱን ቀልብ ለመያዝ ይጥሩ ነበር።

ኢየሱስ በዮሐንስ ወንጌል ማርያምን "አንቺ ሴት" ማለቱን ተከትሎ በፕሮቴስታንቶች ለሚነሱ ጥያቄዎች ሰፊ ውይይት በማድረግ ለመመለስ ሲሞክሩ በግሌ በወቅቱ ተመልክቻለሁ። ከዚያ እይታየ በኃላ እስኪያቆሙ ድረስ ተከታትያቸዋለሁ። ትኩረታቸው እቅበተ እምነት ተኮር ከመሆኑ ጋር "የኦርቶዶክሱ አለኝታ" ተደርገው በመሳላቸው ሳቢያ የጠዋት ፕሮግራሙን መከታተሌን አስታውሳለሁ።

እነዚህ ሰዎች የቤተ ክርስቲያን ተቆርቋሪ መስለው መቅረባቸው ምዕመኑን በቀላሉ እንዲያሳስቱት ጠቅሟቸዋል። ማኅበረ ቅዱሳን ለዚህም ነበር በመጽሀፉ ይህንን ጉዳይ ለምዕመኑ ለማብራራት የተለያዩ አቋሞችን በመዘርዘር የተሐድሶ ሰዎች ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አቋም እንደሚለይ ለማሳየት የደከመው። በመጽፋቸው ከዘረዘሯቸው ነጥቦች ውስጥ የተሐድሶ መለያ አድርገው ያቀረቡት የቤተክርስቲያኗን ታሪክና ትውፊት ማጣጣል ወይንም ዝቅ አድርጎ የማየት መንገድ አንዱ ነው።

የተሐድሶ ሰዎች ቤተ ክርስቲያኗን ወደ ሚፈልጉት አላማ ለማምጣት መርህ አልባ ከመሆናቸው ጋር ማንኛውም መንገድ ከመጠቀም ወደ ኃላ እንደማይሉ መጽሀፉ ይጠቅሳል። በነሱ እሳቤ በተለይም ገድላትና ድርሳናትን ማሳነስ/Undermine/ በቀላሉ ኦርቶዶክስን የማፍረስ ዘዴ ነው የሚል እሳቤ በመያዛቸው ይህኛው አካሔድ ትልቁ የስኬት መንገድ ነው። መጽሀፉ እንዲህ ይላል፦

"ስለዚህ አዲሱ ስልት “የጥንቷ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ትክክል ነበረች - The ancient Orthodox was the right Church" የሚል ነው፡፡ ይህም ማለት ቤተ ክርስቲያንን ከውጭ ከመቃወም ይልቅ ውስጥ ገብቶ ምእመን፣ ካህን፣ ሰባኪ መስሎ ከፕሮቴስታንት እምነትና ባህል ውጭ ያለውን ነገር ሁሉ “ይህ የጥንቷ ቤተ ክርስቲያን ትምህርት አይደለም፣ ይህን እገሌ የጨመረው ወይም የቀነሰው ነው ´ እያሉ ቤተ ክርስቲያኗ ኦርቶዶክሳዊ ዶግማዋ፣ ቀኖናዋና ትውፊቷ በሙሉ ጠፍቶ ፍጹም የጠራች የነጣች ድሀ ፕሮቴስታንት እስክትሆን ድረስ መሥራት ነው"

(የተሐድሶ መናፍቃን ዘመቻ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ላይ፥ አዘጋጅ ማኅበረ ቅዱሳን ገጽ 45 እና 46)

ይህ የተሐድሶ መንገድ የቻለውን ያክል ምዕመን ወስዶ አገልግሎቱ ያበቃለት በመሆኑ አዲስ መንገድ ሳያስፈልግ አልቀረም። ፕሮቴስታንቶቹ ምን አይነት መንገድ እንደነደፉ በትክክል ባላውቅም በግል ካየሁት አንጻር ግን ቸርቿን ከታሪክና ትውፊቷ በማላቀቅ የማዘመን ስራ ሌላኛው አዲሱ ስትራቴጁ እንደሆነ መገመት ይቻላል።

የድሮ ምልምሎች የቤተ ክርስቲያኗ ሊቃውንት፣ መምህራንና ካህናት ሲሆኑ የአሁኖቹ ደግሞ ትምህርት ቀመስ የሚመስሉ ለቸርቿ የአለኝታነት ስሜት መፍጠርን አላማ ያደረጉ ግለሰቦች ናቸው። እነዚህ ከቀድሞዎቹ የሚለዩት ቆብና ጥምጣም ባለማድረግ እንጅ የቤተ ክርስቲያኗን ትውፊቶች ዝቅ በማድረግና ለመድረክ የማይመጥኑ አድርጎ በማቅረቡ ረገድ ልዩነት የላቸውም።

ከቀድሞዎቹ ስህተት የተማሩት ነገር ቢኖር ገድላትና ድርሳናትን በግልፍተኝነት መስደብ ልክ አለመሆኑን ነው። በቀላሉ እነዚያን መጽሀፍ ለውይይት የማይበቁ መሆናቸውን በመናገር ገሸሽ ማድረግ ከተቻለ መስደቡና ማንቋሸሹ ረጅም ጉዞን ከማሳጠር የዘለለ አስፈላጊ አለመሆኑን ነው። ይህኛው ብልጥ አካሔድ/Smart move/ ይመስላል።

በግል ለእኔ እንደ አንድ ሙስሊም ሁለቱም ተመሳሳይ ናቸው። አንድ ሰው ፕሮቴስታንትም ቢሆን ኦርቶዶክስም ቢሆን ከእምነት አንጻር የሚፈጥረው ለውጥ አለ ብየ አላምንም። እንደ ሀገር ባለን የጋራ መስተጋብር ግን የቤተ ክርስቲያኗ ትውፊት በምዕራቡ አለም በተቃኘው ዘመን አመጣሽ ጸያፍ ባህል እንዲቀየር አልመኝም። ቤተ ክርስቲያኗ ግብረ ሰዶማዊነትና መሠል ጸያፍ ተግባሮችን መቃወሟን ለመደገፍ ትውፊቷን መቀበል አይጠበቅብኝም።

በዚህ ረገድ የሀገራችን የፕሮቴስታንት ቸርቾች ተግባሩን ሊቃወሙ ይቅርና ዋናዎቹ የኛ ሀገር ቤተ ክርስቲያናት ሳይቀር በትብብር/Partner/ የሚሰሩ ከነዚሁ ደጋፊ የሆኑ የውጭ ቸርቾች ጋር ነው። እነዚህ አካላት ለችግራችን በቂ ናቸው ብየ አምናለሁ። ኦርቶዶክሱን በራሳቸው መንገድ በመለወጥ ለዚህና መሠል ምዕራባዊ ፍላጎታቸው ማዋላቸው እንደ ሀገር አደገኛውን መንገድ ከማስጀመር የዘለለ ጥቅም የለውም።

▣ ይህ መልካሙን ከመመኘት የተጻፈ የግል አመለካከት ነው

(የሕያ ኢብኑ ኑህ)