Últimas publicaciones de FMC (Fana Media Corporation) (@waltatveth) en Telegram

Publicaciones de Telegram de FMC (Fana Media Corporation)

FMC (Fana Media Corporation)
This is Fana Media Corporation’s (FMC) official Telegram channel.

For more updates please visit https://shorturl.at/ehosX https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured
49,143 Suscriptores
44,682 Fotos
231 Videos
Última Actualización 06.03.2025 12:53

El contenido más reciente compartido por FMC (Fana Media Corporation) en Telegram

AddisWalta - AW

30 Nov, 10:47

2,797

ኢትዮጵያ ከድህነት ለመውጣት ካላት ቁርጠኝነት አንጻር ብልጽግናን ማረጋገጥ የሁሉም ዜጎች የወል እውነት ነው - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ኅዳር 21/2017 (አዲስ ዋልታ) ኢትዮጵያ ከድህነት ለመውጣት ካላት ቁርጠኝነት አንጻር ብልጽግናን ማረጋገጥ የሁሉም ዜጎች የወል እውነት ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ብልጽግና ፓርቲም ህብረ ብሔራዊ ወንድማማችነት እንዲሁም እውነት፣ እውቀትና ጥበብን መለያው አድርጎ ባለፉት አምስት ዓመታት ፈተናዎችን ወደ ድል በመቀየር በርካታ ስኬቶችን አስመዝግቧል ብለዋል።

በፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና ማህበራዊ ዘርፎች የተመዘገቡ ድሎችም የዜጎችን ተጠቃሚነት በተግባር ያረጋገጡ መሆናቸውንም ገልጸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸውም በቀጣይ አምስት ዓመታት ደግሞ አዳዲስ ድሎችን በማስመዝገብ ከራሷ አልፋ ለሌሎች የምትተርፍ ሀገር ለመገንባት እንሰራለን ብለዋል።
AddisWalta - AW

30 Nov, 10:09

2,755

ጠ/ሚ እና የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝደንት ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የብልጽግና ፓርቲ 5ኛ ዓመት የምስረታ በዓል የማጠቃለያ መርኃ ግብር ተካሄደ

ኅዳር 21/2017 (አዲስ ዋልታ) የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝደንት ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የብልጽግና ፓርቲ አምስተኛ ዓመት የምስረታ በዓል የማጠቃለያ መርኃ ግብር በዛሬው እለት በዓደዋ መታሰቢያ ተካሄደ።

በመርኃ ግብሩ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝደንት ዐቢይ አሕመድን (ዶ/ር) ጨምሮ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት ተመስገን ጥሩነህ፣ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈጉባኤ አገኘሁ ተሻገር፣ የክልል ርዕሰ መስተዳደሮች እና የከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች እንዲሁም የፓርቲውና የመንግሥት ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ተካሂዷል።

የብልጽግና ፓርቲ አምስተኛ አመት የምስረታ በዓል "የሀሳብ ልእልና ለሁለንተናዊ ብልጽግና" በሚል መሪ ሀሳብ በተለያዩ ሁነቶች ሲከበር መቆየቱ ይታወሳል።

በዓሉ እስከዛሬዋ እለት ድረስ በፓናል ውይይት፣ የአቅመ ደካሞችን ቤት በማደስ፣ በደም ልገሳ፣ በማስ ስፖርት፣ በፎቶ አውደርእይ፣ በከተማ ጽዳት በመሳሰሉ ተግባራት ሲከበር ቆይቷል።
AddisWalta - AW

30 Nov, 07:40

3,159

ዩክሬን በኔቶ ስር ብትሆን ጦርነቱ ይቆማል - ዘሌንስኪ

ኅዳር 21/2017 (አዲስ ዋልታ) የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘሌንስኪ ተፋፍሞ የቀጠለው የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት እንዲቆም ከተፈለገ ዩክሬን በሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (ኔቶ) ጥላ ስር መግባት አለባት ሲሉ ገለጹ።

ዘሌንስኪ በሩሲያ ያልተያዙ የሀገሪቱ ግዛቶች በኔቶ ስር ቢሆኑ ጦርነቱን ማስቆም ይቻላል የሚል ሀሳብ እንዳላቸው ተናግረዋል።

ከስካይ ኒውስ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት አሁን ኬይቭ በያዘችው ግዛት የኔቶ አባልነትን እንደሚቀበሉ ተጠይቀው ምላሽ ሰጥተዋል።

ዘሌንስኪ እንደሚቀበሉ ገልጸው ነገር ግን ይህ የሚሆነው ኔቶ በመጀመሪያ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ባለው ድንበር መሰረት ለመላው የዩክሬን ግዛት እውቅና ከሰጠ እና ጥያቄው ከቀረበ ብቻ ነው ብለዋል።

ከዚያም ዩክሬን በአሁኑ ጊዜ በሩሲያ ቁጥጥር ስር የሚገኘውን ግዛት በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለማስመለስ እና ለመደራደር እንደምትሞክር አስታውቀዋል።

የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት በዚህ ጉዳይ እስካሁን ምንም አይነት ጥያቄ እንዳልቀረበላቸው ገልጸዋል።

ኔቶ በአሁኑ ጊዜ በሩሲያ ቁጥጥር ስር ያሉትን ግዛቶች ጨምሮ ለመላው ዩክሬን አባልነት መስጠት አለበት ሲሉ የገለፁት ዘሌንስኪ ለከፊሉ የአገሪቱ ግዛት ብቻ መስጠት በሩሲያ የተያዙ አካባቢዎችን አሳልፎ እንደመስጠት ይወሰዳል ብለዋል።
AddisWalta - AW

30 Nov, 06:58

2,957

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ላይቤሪያ ሞንሮቪያ ዳግም በረራ ጀመረ

ኅዳር 21/2017 (አዲስ ዋልታ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ላይቤሪያ ሞንሮቪያ የመንገደኞች በረራ ዳግም መጀመሩን አስታወቀ።

በማስጀመሪያ መርኃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው፣ የላይቤርያ ትራንስፖርት ሚኒስትር ሰርሊፍ ቴይለር፣ በኢትዮጵያ የላይቤርያ አምባሳደር ሉዊስ ሻሬን፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ማኔጅመንት አባላት እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
AddisWalta - AW

30 Nov, 06:15

3,176

ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከእስያ መሠረተ ልማት ኢንቨስትመንት ባንክ ፕሬዝዳንት ጋር ተወያዩ

ኅዳር 21/2017 (አዲስ ዋልታ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከእስያ መሠረተ ልማት ኢንቨስትመንት ባንክ ፕሬዝዳንት ጂን ሊኩን ጋር ተወያዩ።

“ዛሬ ጠዋት ከእስያ መሠረተ ልማት ኢንቨስትመንት ባንክ ፕሬዝዳንት ጂን ሊኩን ጋር በኢትዮጵያ እና ባንኩ መካከል ሊኖር ስለሚችለው የአረንጓዴ ኢነርጂ፣ አቪዬሽን እና መሠረተ ልማት ትብብር ዙርያ ተወያይተናል” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል።
AddisWalta - AW

29 Nov, 14:43

4,170

ወንጀል እንዲፈፀም በአደባባይ መገፋፋት

#ሕግ_ይዳኘኝ

ማኅበራዊ ሚዲያን ለመልካም ተግባር የሚጠቀሙ ብዙዎች ቢኖሩም አንዳንዶች በተለይ ደግሞ በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ግለሰቦች ግን ጥላቻ ከመስበክ አልፈው ቡድኖች በሆነ አካል ወይም አካባቢ ላይ ወንጀል እንዲፈጽሙ ጭምር ሲቀስቅሱ ይስተዋላል፡፡

ወንጀል ፈጻሚ ቡድኖች ለተጨማሪ ጥፋት እንዲነሳሱ ያሞግሷቸዋል ወይም የፈጸሙትን ወንጀል ጥሩ አስመስለው ወይም የሚበጅ አድርገው ያቀርባሉ፡፡

ይህ ድርጊት በሀገራችን የወንጀል ሕግ አንቀጽ 480 መሰረት የሚያስጠይቅ ነው፡፡

በዚህ አንቀጽ መሰረት ማንም ሰው በቃል፣ በጽሑፍ፣ በምስል፣ በአካል እንቅስቃሴ ወይም በሌላ አድራጎት በአደባባይ፡-

ሀ) በሕብረተሰብ፣ በግለሰብ ወይም በንብረት ላይ የኃይል ድርጊት ወይም ከባድ ወንጀል እንዲፈፅም ሌላውን ሰው የገፋፋ እንደሆነ፣

ለ) የዚህ ዓይነቱን ወንጀል ወይም አድራጊውን ያሞገሰ ወይም በጅቷል ያለ እንደሆነ፤ ወይም

ሐ) ዓላማውን ከተቀጣው ሰው ጋር አንድ በማድረግ፣ የጥፋተኛውን ድርጊት በመደገፍ ወይም

ባለሥልጣኖችን በመንቀፍ የገንዘብ ነክ ቅጣት እንዲከፍል በሕግ አግባብ ለተፈረደበት ሰው ቅጣት ክፍያ የሚሆን የገንዘብ መዋጮ የጠየቀ ወይም የሰበሰበ እንደሆነ በእሥራት ወይም በመቀጮ ይቀጣል፡፡

በብርሃኑ አበራ
AddisWalta - AW

29 Nov, 14:03

3,971

በ6 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዶላር የተሸጠው ሙዝ ተበላ

ባለፈው ሳምንት ዓለምን ጉድ ያስባለውና ለጨረታ ቀርቦ በ6 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዶላር የተሸጠው ሙዝ ጨረታውን ባሸነፈው ግለሰብ ተበላ።

ባለፈው ሳምንት ማውሪዚዮ ካቴላን የተባለው ጣሊያናዊ የጥበብ ሰው በፕላስተር ከግድግዳ ያጣበቀው ሙዝ ኒው ዮርክ ከተማ ውስጥ በተካሄደ ጨረታ በ6 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዶላር መሸጡ አይዘነጋም።

አጫራቹ ድርጅት ይፋ እንዳደረገው በክሪፕቶከረንሲ ንግድ የበለፀገው ቻይናዊ ጀስቲን ሱን የተባለ ግለሰብ ሌሎች ተጫራቾችን አሸንፎ “ኮሜዲያን” የተባለውን የጥበብ ሥራ ረቡዕ ዕለት የራሱ ማድረጉ ዓለምን ያነጋገረ ዜና ነበር።

ጨረታውን ያሸነፈው ሱን “በሚቀጥሉት ቀናት እኔው ራሴው ሙዙን በመብላት የዚህ ልዩ የጥበብ ማዕድ ተቋዳሽ እሆናለሁ” ማለቱ አይዘነጋም። ይህንንም ተከትሎ ጀስቲን ሱን በርካታ ጋዜጠኞች እና ተፅዕኖ ፈጣሪ ሰዎች በተገኙበት ሙዙን በልቶታል።

ጀስቲን ሙዙ እስከዛሬ ከበላቸው ሙዞች የተለየ እንደሆነ ከበላው በኋላ ተናግሯል። እንዲሁም ሙዙን መብላቱ በራሱ የኪነ ጥበብ ስራው ላይ የታሪክ አካል ሊሆን ይችላል ማለቱን ፍራንስ ቲዌንፎር አስነብቧል።
AddisWalta - AW

29 Nov, 12:52

3,886

አትሌት የማነ ፀጋይ የኢትዮጵያ አትሌቶች ማህበር ፕሬዝዳንት ሆኖ ተመረጠ

ኅዳር 20 /2017 (አዲስ ዋልታ) በ5ኛው የኢትዮጵያ አትሌቶች ማህበር ጠቅላላ ጉባኤ አትሌት የማነ ፀጋይን ፕሬዝዳንት አድርጎ መረጠ።

በጉባኤው የማህበሩ ከ2014 እስከ 2016 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም እና ፋይናንስ ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል።

ማህበሩ አዳዲስ የስራ አስፈጻሚ አባላትን የመረጠ ሲሆን አትሌት የማነ ፀጋይን የማህበሩ ፕሬዝዳንት አድርጎ መምረጡን የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን መረጃ አመላክቷል።
AddisWalta - AW

29 Nov, 10:45

4,089

በአዲስ አበባ የባቡር ትራንስፖርት ታሪፍ ላይ ጭማሪ ተደረገ

ኅዳር 20/2017 (አዲስ ዋልታ) የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት ታሪፍ ማሻሻያ መደረጉን የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ አስታወቀ፡፡

በዚሁ መሠረት ከታኅሣስ 1 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በመዲናዋ ተግባራዊ የሚደረግ የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር አገልግሎት ታሪፍ አሁን እየተሰጠበት ካለው 10 ብር ወደ 20 ብር ማሻሻያ መደረጉን አስታውቋል፡፡

ድርጅቱ ከሰሜን ወደ ደቡብ (ከጊዮርጊስ - ቃሊቲ) እና ከምስራቅ ወደ ምዕራብ (ከአያት - ጦር ኃይሎች) የትራንስፖርት አገልግሎት በመስጠት በየቀኑ በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ መንገደኞችን እንደሚጓጉዝ ተገልጿል፡፡
AddisWalta - AW

29 Nov, 10:40

3,515

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኒውዮርክ የሚያደርገውን ሳምንታዊ በረራ ወደ 7 አሳደገ

ኅዳር 20/2017 (አዲስ ዋልታ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአዲስ አበባ ወደ ኒውዮርክ የሚያደርገውን ሳምንታዊ በረራ ከአራት ወደ ሰባት ማሳደጉን አስታውቋል፡፡

አየር መንገዱ ከኅዳር 22 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ከአዲስ አበባ ወደ ኒውዮርክ በሳምንት አራት ጊዜ ሲያደርግ የነበረውን በረራ ነው ወደ ሰባት ያሳደገው፡፡

በዚህም ከፊታችን እሑድ ጀምሮ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኒውዮርክ ከተማ ዕለታዊ በረራ እንደሚጀምር በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ላይ ባሰፈረው መረጃ አመላክቷል፡፡