Canal ✞ ፀሐየ ጽድቅ ✞ @tsehaye_tsidk en Telegram

✞ ፀሐየ ጽድቅ ✞

✞ ፀሐየ ጽድቅ ✞
👉ፀሐየ ጽድቅ
የሕይወት መብራት የጽድቅ ብርሃን

በዚህ channel ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን የጠበቁ ትምህርቶች እና መዝሙሮች እንዲሁም ቅዱሳንን እንዘክራለን ስለቅዱሳን እንማማራለን ዕለታዊ ዜና ቤተ-ክርስቲያ ስንክሳር ግጻዌ ጥያቄና መልስ እንዲሁም በየእለቱ አጥንትን የሚያጠነክሩ መንፈስን የሚያለመልሙ ጽሁፎችን ወደ እናንተ እናደርሳለን፡፡
ቻናሉን ይቀላቀሉ
@Tsehaye_Tsidk
ሼር ያርጉ!!
1,809 Suscriptores
818 Fotos
7 Videos
Última Actualización 12.03.2025 09:47

The Spiritual Significance of Light in Christian Faith

በክርስቲና ዘርፍ መረጃ ሐሳብ እና ዕውቀት የሚያወቃቸው ወደ ዕለታዊ አመራር ይበረከት፡፡ የሕይወት መብራት እና የጽድቅ ብርሃን ቅርጸ እውቀታችንን ይወላቸዋል፡፡ ወቅታዊ ትምህርቶችን ለመለክከት ሁሉም እንደ መዝሙር መዋቅር ይቀላቀሉ፡፡ ወደ ጻዕቅ ማህበረ ክርስቲን ባለሞያ ትምህርት ይነሳል፡፡ የዚህ ተናገር ህብረት ከሚነሳው ወይንም ከምንነ-ርዕይታ እንደ ዚህ ወደ የሆነ ሀሳብ ይወሰድ ይዞረዋል፡፡

ክርስቲን ቤተ ክርስቲያን ነው?

የቤተ ክርስቲያን ፍትሀት ወደ መነሻው ወይንም ወደ መረመር ይቀመጥ፡፡ በዚህ ሀሳብ ውስጥ የቤተ ክርስቲያን በአማርኛ የሚገኝ፡፡

ቤተ ክርስቲያን ወደ አንዳች ቤተ መድኃኒት ይርዳበት፡፡ እንዲህ የሚል ሳይታይ ምን ተቀመጥ፡፡

የክርስቲን መርሐግብር ምንድን ነው?

ከመወርወሪ ራዕይታ ይነወውና ለማሉሲቱ ጉዳይ ወደ ተሕፈሞ አብል፡፡

ለትናንት ዘንቀን ምን ናቸው ይሁን ህይወት በመለኪያ ለማጣራት ባሰፈ ይሁን ይችላል፡፡

መዝሙር ምን ነው?

መዝሙር የቅዱስ መዋቅርና ዝማሬዎች በነዚህ ጊዜ ውስጥ ይኒዳሉ፡፡

መዝሙር ወይም መዝገብ ድንጋዩ አለው፡፡ ይህ በመረመር ውስጥ ይቀመጥና መዝሙር ይወዳደራሉ፡፡

የመንፈሳዊ ዕድል ዋስትና?

አለው በመንፈሳዊ በበነቀ፡፡ ይህ ይለይያል ወይንም ማለት ወምላል፡፡

ወደ አለም ዘይሱ በዘንቀን ይሁን ስለ ይብልም ከላዕለ ሆኖም ይንፈነ ይነቃላል፡፡

ክርስቲናዊ መልስ እንዴት ይሆናል?

ወይ ኢይነማል ወይንነ ወደ ሕይወት ይምሉኤ፡፡ ይህ መረጃ በተለመደ ዕዱ አተርቂ ይቁል፡፡

ይህ ወይንም በዚህ ውስጥ ይምሉ እና ይታይቃል ወይ በመለስ ይነሳል፡፡

Canal de Telegram ✞ ፀሐየ ጽድቅ ✞

ምንድን ነው ይህ የቴሌግራም ቻናል ዝግጅት ነው? እንዴት በዚህ ቻናል እንደሚሰሩ ለምን ይህን ጽሁፎች መለየት ይቻላል? ኢትዮጵያን በተመለከተ በዚህ ቻናል ሥርዓት ቤተ ክርስቲያን እና መዝሙሮች እንዲሁም ቅዱሳን እንዘክራለን፡፡ በዚህ ቻናል ተመልክታዊ መረጃዎች ያለን እና ጽሁፍን ለመዋጋት በጣም በእናንተ ላይ እንወዳለን፡፡ ያስተዋወቃል በ@Tsehaye_Tsidk ለመቀላቀል፡፡

Últimas Publicaciones de ✞ ፀሐየ ጽድቅ ✞

Post image

ፕሮቴስታንታዊ enculturation በኢትዮጵያ ሰማይ ሥር ሲናኝ እያየን ነው። የዐደባባይ ዝርፊያዎች ቀጥለዋል።

እስካሁን ካቶሊኮች ነበሩ በየሔዱበት ሀገር የሚተገብሩትን የመመሳሰል ስልት (enculturation stratagy ይሉታል) እኛ ሀገርም ሲተገበሩ የነበሩት። ከትውፊታቸው፣ ከሥርዓታቸው የተለየ ቢሆን እንኳ በሔዱበት ሀገር ያለውን የቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ወስደው ይጠቀማሉ።

በዚህ ምክንያት ነው ቫቲካን የማትጠቀመውንና የማያምኑበትን ታቦት ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ካቶሊኮጭ የሚያከብሩ፣ ንግሥ የሚያነግሡ የሚመስሉት፣ መስቀል ደመራና ጥምቀትን በዐደባባይ ለማክበር የሚሞክሩት፣ ከቤተ ክርስቲያን ያስኮበለሏቸውን መርጌታዎች ተጠቅመው ማኅሌት የሚቆሙ የሚመስሉት፣ የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ነዋያተ ቅድሳት የሚጠቀሙት፣ ወዘተ (ይህ የEnculturation ስልታቸው ከክርስትና በጣም የራቀ ባህላዊ ሥርዓት ባላቸው ማኅበረሰቦች ዘንድ ቢሆንም እንኳ ይተገብሩታል።)

ይህን የሚያደርጉበት ዓላማና ግብ አላቸው።

፩ኛ ለጊዜው «አንድ ነን፤» የሚል መልእክት በማድረስ በኦርቶዶክሳውያን ምእመናን አእምሮና ምልከታ ዘንድ በአስተምህሮ ያለንን ልዩነት መሸፋፈንና፣ የተለያየ ሃይማኖት ተከታዮች የመሆናችንን እውነት ቀስ በቀስ መሸርሸርና ድንበሩን ማጥፋት ነው።

፪ኛ የመጨረሻ ግቡ ደግሞ በ«አንድ ነን፤» ተኩላዊ ቅሰጣ በተፈጠረው ምቹና ለም ልብ ላይ የራሳቸውን ትምህርት በቀስታ የመዝራትና ከትውልዶች በኋላ በኦርቶዶክሳዊው አስተምህሮ ምትክ የራሳቸውን ማንበር ነው።

፫ኛ የጠላት ዲያብሎስ ወኪሎች በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ የሚፈጽሙት መልከ ብዙ ጥቃት
ፍሬ አፍርቶ የቤተ ክርስቲያናችን ህልውና አደጋ ላይ ቢወድቅ የሚበተነውን ምእመን «አለንላችሁ» በማለት ወደ ራሳቸው መውሰድና ቤተ ክርስቲያንን መውረስ ሌላው ጊዜና አጋጣሚ የሚጠብቁለት ግባቸው ነው። ለዚህ ሥራ ስኬት የተዘጋጀ በጀትና የሰው ኃይል ስላላቸው ለመፈጸም አይቸገሩም።

አሁን ደግሞ ፕሮቴስታንቱም ወደ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በተሐድሶ ስም ለማስረግ ያደረገው ሙከራ ያሰበውን ያክል ስላልተሳካለት የካቶሊክን የመመሳሰል ስልት በመንግሥት በታገዘ ንጥቂያና ቅሰጣ ለመተግበር እየሞከረ ነው።

ከኦርቶዶክሳውያን ምን ይጠበቃል?

፩ኛ ይህን ሴራ ማወቅና ማሳወቅ የመጀመሪያው ራስን መከላከያ መንገድ ነው።

፪ኛ የተኛውን ቤተ ክህነት በመቀስቀስ፣ ወይም ፈቃደኛ የሆኑ ኦርቶዶክሳዊ የሕግ ሰዎችን በመጠቀም የቤተ ክርስቲያን አልባሳት፣ ነዋየ ቅድሳት፣ መጻሕፍት፣ ወዘተ ሕጋዊ ከለላ እንዲያገኙ ማድረግ ይኖርብናል።

፫ኛ ከሁሉ በላይ ግን የራሳችን፣ የቤተሰቦቻችንን እና በአካባቢያችን ያሉ ኦርቶዶክሳውያንን መንፈሳዊ ሕይወት መጠበቅ እና እንዲጠበቅ ድርሻችንን መወጣት፣ በቤተ ክርስቲያን ያለንን ሱታፌ ማሳደግ ቀዳሚው ነው።

~ @Wondwosen Wubie

@Tsehaye_Tsidk
@Tsehaye_Tsidk

11 Mar, 12:21
109
Post image

የሰውን ልጅ በሩህሩህነት አሸንፈው። ቀናተኛውን በመልካምነትህ እንዲደነቅ አድርገው፤ ሁሉንም ሰው ውደድ ነገር ግን ከሁሉም ሰው ጋር ርቀትህን ጠብቀህ ኑር።

             #አባ_እንጦንስ

09 Mar, 19:16
148
Post image

ቅዳሴ ተሰጥኦ (ማለትም በቅዳሴ መሀሉ ምዕመኑ የሚመልሰው ወይም የሚሳተፈው ) ነው

በየግሩፑ ያጋሩት
@Tsehaye_Tsidk
@Tsehaye_Tsidk

09 Mar, 10:22
174
Post image

#ምኩራብ
(የዐቢይ ጾም ሦስተኛ ሳምንት)

ምኩራብ ማለት ለአምልኮትና ለትምህርት ለህብረተሰቡ አገልግሎት የሚሰጥ የአይሁድ ቤተ ጸሎት ነው። ጌታ በመዋዕለ ስብከቱ በእስራኤል ሀገር ብዙ ምኩራቦች ስለነበሩ እየገባ ወንጌልን አስተምሮባቸዋል። በዚህም “ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ ወመሀረ ቃለ ሃይማኖት” እንዲል ቅዱስ ያሬድ ኢየሱስ ወደ አይሁድ ምኩራብ ገብቶ የሃይማኖት ቃልን አስተማረ። ከሚለው የቅዱስ ያሬድ ዜማ ሥያሜውን አግኝቷል።

በምኩራብ ጸሎትና ትምህርት ይፈጸምበታል። መሥዋዕት ግን አይከናወንም። መሥዋዕት ግን በታላቁ ቤተ መቅደስ በኢየሩሳሌም ብቻ ይፈጸም ነበር። በዚህ ሳምንት የሚነገረው ታሪክ ጌታ ቤተ መቅደሱን የገበያ ማዕከል አድርገው ሸቀጥ ዘርግተው በጉን ላሙን ርግቡን እየሸጡ አገኛቸው። በዚህ ተቆጥቶ በጉን ላሙን ርግቡን ከምኩራብ አስወጥቶ ሸቀጣቸውንና መደርደሪያቸውን እንዲሁም ወርቅና ብራቸውን በነፋስ በተነባቸው ይላል።

በዚህ ሁኔታ ከቤተ መቅደስ አስወጥቶ "ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች እናንተ ግን የሽፍቶችና የወንበዴዎች ዋሻ አደረጋችኋት" በማለት ወቅሷቸዋል። “አሰስሉ ወአውፅኡ ዘንተ እምዝየ ወኢትረስዩ ቤተ አቡየ ቤተ ምሥያጥ” እንዲል ዮሐ. 2፥16፤ ማቴ. 21፥13። ይህን ተአምር በማሳየት ቤተ ጸሎት የተቀደሰ ከገበያ የተለየ መሆኑን አስተምሮበታል።

በሰንበተ ምኩራብ ጌታ ወደ ቤተ መቅደስ ገብቶ ለዋጮችን ማስወጣቱ ወርቅና ብሩን በነፋስ መበተኑ ላሞችን በጎችን በጅራፍ መግረፉ ቤተ መቅደሱን ማንጻቱ ወዘተ ይነገራል።

(የዚህም በዓል ታሪክ ዝርዝር ሁኔታው ማቴዎስ 21፥12-13 ላይ ተጠቅሷል፡፡)

#የቅዳሴ_ምንባባት፦

ቆላስ. 2፥16-23
«እንግዲህ በመብል ወይ በመጠጥ ወይም ስለ በዓል ወይም ስለ ወር መባቻ ወይም ስለሰንበት ማንም አይፍረድባችሁ እነዚህ ሊመጡ ያሉት ነገሮች ጥላ ናቸውና፣ አካሉ ግን የክርስቶስ ነው፡፡ .......፡፡»

ያዕ. 2፥14-26
«ወንድሞቼ ሆይ፣ እምነት አለኝ የሚል፣ ሥራ ግን የሌለው ሰው ቢኖር ምን ይጠቅመዋል እምነቱስ ሊያድነው ይችላልን ......፡፡»

ሐዋ. 1ዐ፥1-9
«በቂሣርያም ኢጣሊቄ ለሚሉት ጭፍራ የመቶ አለቃ የሆነው ቆርኔሌዎስ የሚሉት አንድ ሰው ነበር፡፡ እርሱም ከቤተ ሰዎቹ ሁሉ ጋር እግዚአብሔርን የሚያመልክና የሚፈራ ለሕዝብም እጅግ ምጽዋት የሚያደርግ ወደ እግዚአብሔርም ሁልጊዜ የሚጸልይ ነበረ፡፡ ....፡፡"

#ምስባክ- መዝ 68፥9
እስመ ቅንዐተ ቤትከ በልዐኒ
ትዕይርቶሙ ለእለ ይትዔየሩከ ወድቀ ላዕሌየ
ወቀጻዕክዋ በጾም ለነፍስየ፡፡

(የቤትህ ቅንዓት በልታኛለችና
የሚሰድቡህም ስድብ በላዬ ወድቆአልና
ነፍሴን በጾም አስመረርኋት፡፡)

#ወንጌል፡- ዮሐ 2፥12-25
«ከዚህ በኋላ ከእናቱና ከወንድሞቹ ከደቀ መዛሙርቱም ጋር ወደ ቅፍርናሆም ወረደ፣ በዚያም ጥቂት ቀን ኖሩ፡፡ የአይሁድ ፋሲካም ቀርቦ ነበር ኢየሱስም ወደ ኢየሩሳሌም ወጣ፡፡ ወደ መቅደስም በሬዎችንና በጎችን ርግቦችንም የሚሸጡትን ገንዘብ ለዋጮችንም ተቀምጠው አገኘ፤ የገመድም ጅራፍ አበጅቶ ሁሉን በጎችንም በሬዎችንም ከመቅደስ አወጣቸው፣ .....፡፡»

(ከመድብለ ታሪክ እና ግጻዌ የተወሰደ)

#ይቀላቀሉን!!
@Tsehaye_Tsidk
@Tsehaye_Tsidk

09 Mar, 06:58
168