Latest Posts from አማራ ፋኖ በሸዋ (@shewaamharafano) on Telegram

አማራ ፋኖ በሸዋ Telegram Posts

አማራ ፋኖ በሸዋ
1,668 Subscribers
263 Photos
43 Videos
Last Updated 06.03.2025 12:29

Similar Channels

Fano Media 27🦅✊🏿
1,945 Subscribers

The latest content shared by አማራ ፋኖ በሸዋ on Telegram

አማራ ፋኖ በሸዋ

16 Oct, 14:43

1,235

ማስጠንቀቂያ…!

"…ሰሞኑን የአርበኛ ሌ/ኮለኔል አሰግድ መኮነን ስልክን በመጠቀም ሰዎችን እየመረጡ  "Bonda" የሚባል  በኢንሳ የበለፀገ malnware ለግለሰቦች በቴሌግራም እና በሌሎች ማህበራዊ ሚድያ አገልግልቶች እየላኩ ይገኛል። በመሆኑም ይሄን link በሚነካበት ጊዜ ስልክ ላይ የሚገኙ መረጃወችን ከመመንተፍ በተጨማሪ በስልክ ላይ Remote acess software እንዲጫንበት በማድረግ የስልኩን GpS, Microphone እና camera በመጠቀም ወገን ላይ ጥቃት እየደረሰ ይገኛል።

"…በተጨማሪም በተለያየ link መልኩ በአንዳንድ ወገኖች በኩል የሎተሪ ዕጣ በሚመስል እና ሽልማት በማስመሰል የሚላኩ ሊንኮች ባለቤታቸው ይለያይ እንጅ ተመሳሳይ የስለላ እና የሳይበር ጥቃት ስልቶች በመሆናቸው ሊንኮችን ከመከፈት እንድትቆጠቡ እናሳስባለን ብለዋል የመረጃው ምንጮች።

"…በሌላ በኩል በሀገረ አሜሪካ በሚኖረው በአምሀ እና በዋን ዐማራዎች በኩል የሳታላይት ስልክ ተገዝቶ የተላከላችሁም ዛሬ የደረሰው የስልኩ ተጠቃሚ ፋኖ አይነት የድሮን አደጋ እንዳይዳርስባችሁ የሳታላይት ስልካችሁን አስወግዱ ተብላችኋል። ይሄ የፋኖ አመራሮች መልእክት ነው።

"…በምንም ዓይነት መልኩ የተለጠፈው ዓይነት ሊንክ ከጋሽ አሰግድም ሆነ ከሌላ አካል ስልካችሁ ላይ ብታዩ ወዲያው አስወግዱት። እንዳትከፍቱት ተመክራችኋል። ሴራውን ፍርስ ነው።

• ርእሰ አንቀጹን ልለጥፍ ነኝ። ጠብቁኝ።
አማራ ፋኖ በሸዋ

15 Oct, 12:54

1,733

ህፃኑ የዕናቱን አስከሬን ተደግፎ ደም እየፈሰሰው ተገኘ።
እናት ልጇን አዝላ ተገደለች !

አገዛዙ በአማራ ህዝብ ላይ የሚያካሒደውን የዘር ማጥፋት ዘመቻ ተባብሶ ቀጥሏል።

ነዋሪነቷ ሰሜን ሸዋ ዞን አሳግርት ወረዳ ሶጠን ቀበሌ የሆነችው የሁለት ልጆች እናት ወ/ሮ አስበራ መሀመድ ኑር በረኸት ወረዳ መጥተህ ብላ ከተማ ልጇን አዝላ በመጓዝ ላይ ሳለች በአገዛዙ ሀይል በጥይ ተደብድባ ተገድላለች።

ጥቅምት 1 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ልዩ ስሙ 03 ቀበሌ በተባለ ስፍራ ራሱን መከላከያ ነኝ ብሎ በሚጠራው ቡድን በጥይት ተደብድባ ተገድላለች።

ማህበረሰቡ በስፍራው ሲደርስም ህፃን ልጇ ጭምር በጥይት ተመትቶ ደም እየፈሰሰው ከእናቱ አስከሬን ጎን ተገኝቷል።

የሁለት ልጆች እናት የሆነችው አስበራ መሀመድ ኑር የሁለት አመት ልጇ ከወደቀችበት  ስፍራ አጠገብ ቁጭ ብሎ  ሲያለቅስና ደም ሲፈስሰው በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ የፋኖ አባላት አግኝተውት ለቅርብ ቤተሰቦቿ አስረክበዋል።

ድል በግፍ ለሚገደለው አማራ ህዝብ!
ድል ለፋኖ!
አማራ ፋኖ በሸዋ

08 Oct, 15:48

1,762

     ቀን መስከረም 28/1/2017

"…የመንገድ ክልከላውን አስመልክቶ ከዐማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ መመሪያ

"…ከመስከረም 23 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የሲቪሊያንን ሕይወት ለመታደግ ሲባል እንዲሁም የሥርዓቱን ለመጣል ከምናደርገው ዘርፈ ብዙ ትግል መካከል አንዱ በመላው የዐማራ ክልል መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንዲደረጉ በተሰጠው መመሪያ መሠረት ትዕዛዙን ሕዝባችን ተፈፃሚ አድርጎ ቆይቷል።

"…የተላለፈው ትእዛዝ ወታደራዊ ኦፕሬሽኖችን ለማከናወን ይገጥመን የነበረውን መሰናክል በማስወገድ እና ሲቪሊያንንም በመጠበቅ ረገድ ትልቅ አስተዋፅኦ ነበረው። በሌላ በኩል የዐማራ ሕዝብ ከፋኖ ጋር እንደቆመ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ እና ለሀገራችን ሕዝብ በይፋ ማረጋገጥ ተችሏል።

"…በመሆኑም የተሰጠውን የጥንቃቄ መመሪያ ያለምንም መሸራረፍ ለፈጸመው ሕዝባችን ከፍ ያለ ክብር ያለን መሆኑን እየገለፅን ከነገ መስከረም 29 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ:-

1ኛ፦ ከየትኛውም አቅጣጫ ወደ ምዕራብ፣ ሰሜን፣ ወልቃይት ሰቲት ሁመራ እና ማዕከላዊ የጎንደር ዞኖች የሚደረግ የመንገደኞች ጉዞ፥

2ኛ፦ በዐማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የሚደረግ የተሽከርካሪ እንቅስቃሴ፦

3ኛ፦ እንዲሁም በሁሉም የወሎ ቀጠናዎች ብቻ የመንገድ ትራንስፖርት የተፈቀደ በመሆኑ መንገድ ክፍት የተደረገ መሆኑን እናሳውቃለን።

"…በሌሎች አካባቢ ያለውን ነባራዊ ሁኔታው ሲፈቅድ እየታዬ ተለዋጭ ትእዛዝ የሚሰጥ መሆኑን እንገልፃለን።

• ዘመቻ መቶ ተራሮች ይቀጥላል...

ክብር ለተሰው ሰማዕታት!
ድል ለአማራ ሕዝብ!

የዐማራ ፋኖ በጎንደር
የዐማራ ፋኖ በጎጃም
የዐማራ ፋኖ ሸዋ እዝ
የዐማራ ፋኖ በወሎ
አማራ ፋኖ በሸዋ

30 Sep, 22:45

2,114

እንዴት አያችሁት የሰሞኑን የበአዲኖችን እስር ? የኦሮሙማ ቡድን ገረዱን በአዴን እየበላት እየዋጣት ይመስላል አይደል .. አይ የባንዳ መጨረሻው
አማራ ፋኖ በሸዋ

27 Sep, 18:11

2,312

https://vm.tiktok.com/ZMh6QmcJy/
አማራ ፋኖ በሸዋ

19 Sep, 17:44

2,337

ሁለት ሞት በዳባት

ፋኖዎቻችን በዳባት ከተማ ውስጥ በከተመ ጠላት ላይ በድንገት ዘነቡ፤ አንድ ቀን ቀደም ብሎ ደግሞ ደባርቅ ከተማን ቀጨም በማድረግ ከጠላት አፅድተዋት ነበር። በደባት የሆነው ግን ሌላም አስገራሚ ነገር ነበረው…

በዳባት የዘነቡት ፋኖዎቻችን በከተማዋ ውስጥ የነበሩትን የፋሽስቱን ስርዓት ኃይሎች ግንባር መብጣት ሲጀምሩ፣ በርካታ ሁለት የግራ እግር ሚሊሽያዎች ወደ አራዊት ሰራዊቱ ወታደራዊ ካምፕ ይፈረጥጡ ጀመር። ከተማው ውስጥ ከፀዳው አራዊት ሰራዊት የተረፈ ሰራዊት ካምፑ ውስጥ ነበር፤ ይህ ሰራዊትም ሽምጥ እየፈረጠጠ የመጣውን የሚሊሽያ መንጋ ወደ ካምፕ አላስገባም ብሎ አውላላ ሜዳ ላይ በተነው።

ሁለት የግራ እግሩ ሚሊሽያ በአንድ ጫፍ ክህደት፣ በሌላ ጫፍ አፈሙዝ ከበበው። አፈሙዙ የፋኖዎቻችን ነበር። አንድ ሚሊሽያ አባት ከእነ 2 ሚሊሽያ ልጆቹ ጨምሮ፣ ከ60 በላይ ሚሊሽያ ግንባር ግንባሩን ተበጣ። አራዊት ሰራዊቱ በር ቢዘጋባቸውም፣ ምድር ግን ሆዷን ከፍታ ሆዳሞቹን ተቀበለቻቸው።

የከዱን ፍጡራን ተከዱ፤ ሁለት ሞትም ሞቱ። የእነዚህ ሁለመና ሆዶች የመጨረሻዋ እስትንፋስ፣ ለህይወት ታሪክ ጻህፍት ፈተና ሆኖ አልፏል።

ቻው!
አማራ ፋኖ በሸዋ

11 Sep, 09:06

2,396

በዱር በገደል በጫካ በዝናብ በውርጭ በበረሀ በፀሀዩ ላይ ያላችሁ የአማራ ሞት ,መፈናቀል, ሰደት ,ጭቆናው መታረዱ ,መደፈሩ መንከራተቱ ይበቃ ብላችሁ ከሞቀ ቤታችሁ ወጥታችሁ ታላቅ ተጋድሎ ,መሥዋዕትነት የምትከፋሉ ፋኖዎቻችን እንኳን አደረሳችሁ!! ይህ አመት ይህን ጨቋኝ ስረአት ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ የምንገረስስበት: ይህን ታላቅ ህዝብ ወደ ቀድሞ ታላቅነቱ ክብሩ ከፍታው የምንመልስበት አመት ፈጣሪ ያድርግልን:: በግፍ የታረዱ ,በጅምላ የተገደሉትን ደም የምንመልስበት ያለቀሱትን አንገቱን የደፋውን አባታችንን ቀና እንዲል የእናታችንን እንባ የምናብስበት የድል አመት ይሁንልን:: .. በመጨረሻም በአገር ውስጥም በውጭም ያላችሁ ይህን ቅዱስ ትግል የምትደግፉ ሁሉ እንኳን አደረሳችሁ!! ..በስደት በጭንቀት ያለኸው ወገናችን አይዞን ልጆችህ እየደረስንልህ ነው..መልካም አዲስ አመት ይሁንልህ አማራው።
አማራ ፋኖ በሸዋ

11 Sep, 06:48

2,025

የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ዋና አዛዥ
ከ አርበኛ ሀብቴ ወልዴ
የተላለፈ የ2017 ዓ.ም የአዲስ ዓመት መልዕክት!
***
በቅድሚያ በራሴ እና የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ሥም፡- ለመላው የአማራ ሕዝብ፤ በጎጃም፣ በሸዋ፣ በወሎና በጎንደር ላላችሁ ለጋራ ዓላማ፤ የጋራ መስዋዕትነት እየከፈልን ላላችሁ ወንድሞቻችን፤ የሕልውና ትግሉ የዲፕሎማሲ ግንባር ተሰላፊ ለሆነው የዲያስፖራ ወገናችን እንኳን ለአዲሱ ዓመት በጀግንነት አደረሳችሁ!!

በመቀጠል፡- የአማራ ትግል ወዳጆች፣ በፋሽስቱ የብልጽግና አገዛዝ ጭቆናና ብዝበዛ ውስጥ ላለው መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ እንኳን ለአዲሱ ዓመት በፅናት አደረሰን፤ አደረሳችሁ የሚል መልዕክቴን አስተላልፋለሁ!!

በድል የደመቅንበት 2016 ዓ.ም.፡- እጅግ ፈጣን የመደራጀት፣ የማጥቃትና የጠላትን ኃይል የመበተን አቅም የፈጠርንበት፣ የሕልውና ትግሉ በማይቀበለስ ደረጃ መድረሱ የተረጋገጠበት የድል ዓመት ነበር፡፡

ነፃ ቀጠናዎችን በማስፋት፣ የሕዝባዊ አስተዳደር ልምምዶችን ያሳደግንበት፤ ወታደራዊ፣ የመረጃና አስተዳደራዊ አቅሞችን የፈጠርንበት፤ የትግል ቅርጽና ይዘት ያለው አደረጃጀት እውን ያደረግንበት፤ ከኢትዮጵያ አልፎ በዓለማቀፉ ማኀበረሰብ ዘንድ የአማራ ትግል አጀንዳ የጎላበት፣ በጥቅሉ አማራ ታሪኩን ያደሰበት፣ ትውልዱም የራሱን ደማቅ ታሪክ በደምና አጥንቱ የፃፈበት ታሪካዊ የድል ዓመት ነበር፡፡

ዓመቱ ፋሽስም ወገቡ የተሰበረበት፤ ፋኖነት የአማራ መዳኛ መሆኑ የተረጋገጠበት ሆኗል፡፡

በተለይም የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ተተርከው የማያልቁ ብዙ ጀብዱ፤ እልፍ ገድሎችን ፈጽሟል፡፡ በሰፊ ቀጠና እየተንቀሳቀሰ በደምና አጥንቱ የማይሞት ታሪክ ሰርቷል፡፡ እጅግ አስደናቂ ጀብዱዎች የተፈፀሙባቸው በርካታ ዘመቻዎች በጋራ ታቅደው፤ በጋራ ተተግብረዋል፡፡ በዚህም የጠላት የሰው ኃይል ተራቁቶ ቀፎው ቀርቷል፡፡ በዓለማቀፍ የጦርነት ሕጎች መሠረት ምርኮኞችን በአግባቡ በመያዝ የሞራልና የሕግ ተገዥነታችንን ለዓለም አስመስክረናል፡፡

"አማራን ትጥቅ ብቻ ሳይሆን ቀበቶውንም እናስፈታዋለን" ያሉንን ትጥቃቸውን እያስፈታን፤ ፋሽስታዊ አስተሳብ የተሸከሙበትን አዕምሯቸውን እያጠብን የአማራነትን ልክ አሳይተናቸዋል፡፡"እናፀደዋለን" ያሉንን እየመነጠርን፤ ርቃናቸውን አስቀርተን በድል መራመዳችንን ቀጥለናል!!

የትግሉ ባለቤት የሆነው የአማራ ሕዝብ ከአብራኩ ለተገኙ ፋኖ ልጆቹ፣ ስንቅና የመረጃ ምንጭ ሆኖ የተሳተፈበት በመሆኑ ዓመቱን በድል ደምቀን ለማሳለፍ አቅም ሆኖናል፡፡

በሌላ በኩል ዓመቱ የሕልውና ትግሉ አልጋ ባልጋ የሆነበት ሳይሆን የደም ዋጋ እየከፈልን የመጣንበት፤ በርካታ ወንድሞቻችንን የገበርንበት በመሆኑ አዲሱን ዓመት 2017 ዓ.ም. በጀግንነት ስንቀበል የጀግኖች ሰማዕታትን የትግል አደራ ከግብ ለማድረስ የትግል ቃል-ኪዳናችንን በማደስ ነው፡፡ አማራነት በጀግኖች ደም ደመቆና ተከብሮ ይኖራል!

በትግላችን ውስጥ ያረጋገጥነው እውነት፣ አማራነት በእሳት ተፈትኖ ራሱን እንደንሥር አድሶ ከፍ ብሎ በመብረር ላይ ነው፡፡ ዛሬ የአማራ ሕዝብ አምጦ የወለደው ፋኖ የሕዝብ ልጅ ስለመሆኑ በተግባር ታይቷል፡፡ ፋሽስምን ብቻ ሳይሆን በፋሽስም ጥላ ስር ያሉ ሌባ፣ ቀማኛ፣ አጋችና ዘራፊዎችን በመቅጣት የሕዝብ ወገንተኝነቱን አሳይቷል፡፡

ያለፈው የትግል ዓመት፣ ፋኖ በአስተሳሰብና በተግባር ከአማራ ሕዝብ የተገኘ፤ ጠንካራ ማህበረሰባዊ ግንኙነት እና የትግል ሥነ-ምግባር ያለው እውነተኛ ታጋይ መሆኑን ያሳየበት የድል ዓመት ነበር፡፡

ይህ ያስጨነቀው ጠላት የትግል ስልቱን በመቀያየር የሕልውና ትግሉን የድጋፍ መሰረት ለመሸርሸር፤ ሕዝባችንን ለማማረር፤ የትግል ትኩረት አቅጣጫ ለማሳት፤… የተለያዩ የቀውስ ታክቲኮች፣ የተደራጁ ወንጀሎች፣ የሐሰት ፕሮፖጋንዳዎች፣ ከፋፋይ አጀንዳዎች ቢረጩም አማራ የብረት አጥር ሆኖ መክቶታል፡፡

በዚህ ድል ኩራት የሚሰማን ሆኖ፣ አሁንም ጠላት በባከነ ሰዓት በእኩይ ሴራዎቹ የቀጠለ በመሆኑ እንደአማራ በአዲሱ ዓመት የትግሉን ፍፃሜ ለማሳመር ኳሷን በአግባቡ መቆጣጠር፣ የመጨረሻውን ሳቅ ለመሳቅ ኳሷን የድል መረቡ ላይ ለማሳረፍ በብርቱ ጥንቃቄ ማጥቃት አለብን! የትግል ሜዳው ላይ ዋጋ እየከፈልን ያለነውን የአማራ ፋኖ መስዋትነት ማክበር የሚቻለው፣ የሕልውና ትግሉን ከጠላት ሴራ በመጠበቅ፤ አማራዊ የብረት አጥሩን በማጥበቅ ነው!!

እንደአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ፣ በአዲሱ የትግል ዓመት አማራነት በፈተናዎች የሚፀና እንጂ የሚበተን ማንነት አንዳልሆነ ለወዳጅ ጠላት እናረጋግጣለን!

ትግላችን የቱንም ያህል ፈታኝና መራራ ቢሆንም በሞት ሸለቆ ሳይታለፍ ታሪክ አይቀየርምና ለአማራ ሕዝብ ዘላቂ አሸናፊነት የማይተካ ሕይወታችንን ዋጋ እየከፈልን አዲሱን ዓመት ዘላቂ ድል የሚመጣበት የድል ዘመን እንደምናደርገው አንጠራጠርም፡፡ ለዚህም ‹አማራዊ ሕብረት፤ ለአማራ ሕልውና!› በሚል ከፍታችን አስጠብቀን በድል እንበራለን፡፡

በአዲሱ ዓመት 2017 ዓ.ም የሕልውና ትግሉ ዘመኑን ወደዋጀ ሁለገብ ትግል ለማሳደግ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ ለዚህም ከሥጋና የትግል ወንድሞቻችን ጋር በአንድነት በመቆም፣ በጋራ አመራር ስትራቴጂካዊ ድል እንደምናረጋግጥ እናበስራለን፡፡

በመጨረሻም፡- የአማራ ሕዝብ ትግል በፈተና የተሞላ፤ መራራና ዋጋ የሚከፈልበት እንደሆነ በመጣንበት የትግል መንገድ እናውቃለን፡፡ ነገር ግን ዋጋ የምንከፍለው ለአማራ ሕልውና መረጋገጥ፤ አማራ አንገቱን ቀና አደርጎ እንዲሄድ፤ ለዘላቂ ጥቅሞቹ መከበር ነው፡፡ ፈተናና መከራው የቱንም ያህል ቢበረታ ድሉ አይቀሬ ነው፡፡

2017 የትግል ዘመን የአማራ ሕዝብ የዘላቂ አሸናፊነትና የነጻነት ዓመት ይሆናል!

አርበኛ ሀብቴ ወልዴ
የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ዋና አዛዥ
ጎንደር-አማራ-ኢትዮጵያ
ጷግሜ 5/2016 ዓ.ም.
አማራ ፋኖ በሸዋ

08 Sep, 17:48

1,681

ሰበር ዜና!

የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ናደው ክፍለ ጦር
   በቅርቡ ወደ አማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ናደው ውስጥ የተካተተው በፋኖ ጥላሁን የሚመራው  ራስ አበበ አረጋይ ብርጌድ ሻለቃወች ከአገዛዙ የብልፅግና ሰራዊት በሁለት ቦታ አንገት ለአንገት ተያይዞ ሲደመስሰው ውሏል።

የመጀመረሚያው በመርሃቤቴ ወረዳ ገረን ቀበሌ ፋኖን እደመስሳለሁ በሚል የህልም ቅዠት ጨዋታ ወደ ቦታው ያመራው ወንበዴው ሰራዊት ያሰበበት ቦታ ሳይደርስ ልዩ ስሙ ቀርጫ ቀርጫ የሚባል ቦታ ላይ በአናብስቶቹ የፋኖ አባላት በደፈጣ ውጊያ አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቶ ብዛት ያለው የአገዛዙ ሰራዊት ሙትና ቁስለኛ ሆኗል።

ይህ ወንበዴ ሰራዊት በደረሰበት ክፉኛ ምት ብስጭት ውስጥ የገባው የአገዛዙ ሰራዊት ወደ ከተማው ሲመለሱ ምንም የማያውቁ  በየመንገዱ ያገኛቸውን ሲቪል ሰወች እየደበደበ እና በሰብል ጥበቃና በእንስሳት ጥበቃ ላይ የነበሩ ህፃናትን ማለትም የ10 አመት ሴት ልጅ የ11እና የ12አመት ወንድ ልጆችን   በጥይት በመምታት ሶስቱም ህፃናት በህክምና ላይ እንዳሉ ለማወቆ ችለናል።

ሁለተኛው ሬሽን በመጫን ወደ መርሀቤቴ አለምከተማ ለመቀባበል ከለሚ የወረደ እና ከአለም ከተማ የወረደ የጠለት ሃይል በጀማ ድልድይ አቅራቢያ ወደ የጎፍ ለመሻገር ሲሞክር የነበረው የአገዛዙ ጥምር ጦር በክንደ ነበልባሎች የራስ አበበ አረጋይ ብርጌድ የፋኖ አባለት በበርሲና ወንዝ ላይ ሙትና ቁስለኛ ሲሆን ሌላኛው እድል ቀንቶት ከፋኖ ጥይት ያመለጠው  የጠላት ሃይል እግሬ አውጪኝ ብሎ ወደ መጣበት ፈርጥጧል።

   ይህ በእንዲህ እንዳለ ሽንፈቱን የተከናነበው የአገዛዙ ቡድን ጀማ በረሃ ላይ በግል ሰራ ተሰማርቶ ግሮሰሪ የሚሰራን ግለሰብ የፋኖ ሃብት ነው በማለት ለብዙ ጊዜ ሲሰራበት የነበረውን የግሮሰሪ እና ማለትም ፍሪጅ ብዛት 2፤ ጀነሬተር፤ ባዶ እና ያለበት የቢራ ካሳ፤ በዛት ያለቸው የምግብ ቤት ዕቃወችን ብረት ድስት እንጀራ እና ያልተጋገረ ሊጥ ጭልፋ ሳይቀር ጠራርጎ በመጫን ወደየመጣበት የሄደ ሲሆን ይህ ዘራፊ ሰራዊት የወንበዴነት  ተግባሩን በግልፅ ያሳየበት ዕለት ነው።           

              ከሸዋ የትግል ሜዳ
                      
ጳጉሜ 3/2016ዓ.ም
ክብር ለተሰውት

   ሪፖርተር ግራ አዝማች ፈለቀ ታደሰ
የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ናደው ክፍለጦር የሚዲያና ኮምንኬሽን ተጠሪ ክፍል
አማራ ፋኖ በሸዋ

08 Sep, 09:04

1,431

የደጋዳሞቱን ደፈጣ የሚያስታውስ ግዙፍ ኦፕሬሽን በጎንደር ምድር ላይ ተፈጽሟል። በሺህ የሚቆጠር የብርሐኑ ጁላ ጦር ወደ አዲሱ ዓመት ሳይሸጋገር ቀርቷል። ክብር ለጎንደር አማራ ፋኖ