Anchore media አንከር ሚድያ ( በጋዜጠኛ መሳይ መኮነን)

@mesaymekonnen1


ይህ ©መሳይ መኮነን የተሰኘ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው።⬇️ለፈጣንና አዳዲስ መረጃዎች ጆይን👇
https://t.me/mesaymekonnen1

Anchore media አንከር ሚድያ ( በጋዜጠኛ መሳይ መኮነን)

18 Sep, 14:40


ብዙ ጊዜ እባክህ ስለ ሰላም ስበክ ትሉኛላችሁ። ሰላም በስብከት ቢመጣ ኖሮ፣ ከአብይ አህመድ በላይ ማን ስለ ሰላም የሰበከ ነበር። አብይ ግን በግራ ጎኑ ሰላም እየሰበከ፣ በቀኝ ጎኑ ጦርነት ሲቀፈቅፍ ይውላል።
ሰላም በስራ እንጅ በስብከት አይመጣም።ታሪክ እንደሚነግረን የአለማችን ደም አፋሳሽ ጦርነቶች የተፈጠሩትና የተመሩት በሰላም ሰባኪዎች ነው።

ከሃይማኖተኞች በላይ ስለ ሰላም የሚሰብክ አለ? በአለማችን ከተካሄዱ ጦርነቶች መካከል ከግማሽ በላይ የሚሆነው፣ ሃይማኖት ተኮር ጦርነት አየደለምን?

በክርስትና እና በእስልምና ከሰው ጋር ስትገናኝ የመጀመሪያው መልዕክት እኮ " ሰላም ላንተ ይሁን" የሚል ነው። ሰላም ለከ፤ ሰላም ለኪ፤ ሰላም ለከሙ ይላል ግዕዙ ። አረብኛው ደግሞ " አሰላሙ አለይኩም" ይላል። የአላህ ሰላም በአንተ ላይ ይሁን ማለት ነው።

የሃገሬ ሰው ጠዋት ሲነሳም፣ ሰላም አውለኝ ይላል።
ግን ሰላም አውለኝ ብለህ፣ ጦርነት ቢያግጥምህ፣ እግዚአብሔርን ወይም አላህን ተጠያቂ ማድረግ የለብህም። ስለሰላም እየጸለይኩ ለምን ሰላም አልሰጠኝም ብለህ እሱን ልትወቀሰው አትችልም። እሱ አዕምሮ ሰጥቶሃል። ሰላም በስብክት ሳይሆን በስራ እንደሚመጣ፣ ማሰብ ያንተ እንጅ የእሱ ግዴታ አይደለም።

ሌሎች ሃገሮች ሰላማቸውን እንዴት አገኙ ብለህ ጠይቅ። ሌሎች ሃገሮች ሰላማቸውን ያመጡት፣ የዜጎቻቸውን ነጻነት የሚያስከብር ስርዓት በመመስረታቸው ነው። ይህን ነጻ ስርዓት ታግለህ እውን ስታደርግ እንጅ፣ ቁጭ ብለህ ስለ ሰላም ስለሰበክ ቋሚ ሰላምን አታመጣም።

በአምባገንና ዘረኛ መንግስት ስር ደግሞ ቋሚ ሰላም ፍጹም የማይታሰብ ነው።
ሙሐሙድ አህመድ ሰላም ይሁን ብሎ የዘመረው እኔ ሳልወለድ ይመሰለኛል። እኔ ተወልጄ እስካረጅ ግን በኢትዮጵያ ሙሉ ሰላምን አላየሁም። የጎደለን ምንድነው? ደፈር ብለን let's find the missing link.
ጆይን👉 @mesaymekonnen1

Anchore media አንከር ሚድያ ( በጋዜጠኛ መሳይ መኮነን)

18 Sep, 04:49


ታሪካዊቷንና ስትራቴጂካዊቷን የጎንደር ከተማን ለመቆጣጠር በፋኖና በመከላከያ መካከል የሚካሄደው ውጊያ ቀጥሏል። ወደ ጎንደር የሚወስዱ መንገዶች በፋኖ ሃይሎች ተዘግተዋል። የአየር በረራም ተቋርጧል። ኢ ኤም ኤስ የፋኖ መሪዎችን አነጋግሯል። ጎንደር በፋኖ እጅ ከገባች፣ ባህርዳር ባለሳምንት ልትሆን ትችላለች።

በዚህ አጋጣሚ በሲቪሎችና በቅርሶች ላይ ጉዳት እንዳይደርስ ከባድ ጥንቃቄ ያስፈልጋል።

ይህ ©መሳይ መኮነን የተሰኘ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው።⬇️ለፈጣንና አዳዲስ መረጃዎች ጆይን👇
https://t.me/mesaymekonnen1

Anchore media አንከር ሚድያ ( በጋዜጠኛ መሳይ መኮነን)

05 Aug, 23:27


እንግዲህ በአያልቅበት አህመድ ''የኢትዮጵያ ቀውስ መፍትሄ የሚገኘው እዚህ መጽሀፍ ውስጥ ነው'' የተባለለት የዳንዔል ክብረት መጽሀፍ ይህ ነው። አሉባልታ የታጨቀበትን፥ ትርክት እናስተካክላለን ተብሎ ንትርክ የሞላበትን፥ የቡና ላይ ወሬ ተሰብስቦ የተጠቀጠቀበትን መጽሀፍ ነው አያልቅበት አህመድ የኢትዮጵያ የመዳን መንገድ ሲል ያሞካሸው። የአይጥ ምስክር ድንቢጥ ብለን ለጊዜው እንለፈው እንጂ ነገሩ እጅግ አሳፋሪ ነው።

እነዶ/ር ዳኛቸው ታላላቅ ፈላስፋዎችን እየጠቀሱ ያወደሱት መጽሀፍ ይህ ነው ማለት ነው? ፕ/ር አለማየሁ ቀጄላ(ይቅርታ ገ/ማርያም) ሲሞልጨንና ሲሸልልብን የነበረው ለዚህ ዝባዝንኬ መጽሀፍ ነው? ያ ሁሉ ግርግር፥ ድግስና ፌሽታ ይህቺን አሉባልታ ለማስመረቅ ነበር? ከመጽሀፉ አንዳንድ ገጾች ላይ ሳነብ ፊቴ ላይ ድቅን ያለችው የኦቴሎ ቲያትር ላይ ያለችው የእሪ በከንቱ ሰፈሯ አለሌ ሴት ናት። ወገቧን ይዛ አላፊ አግዳሚውን በስድብ ጥርግርግ የምታደርገዋ ኮማሪት። ዳንዔል አሉባልታና ስድብ አጭቆ በመጽሀፍ በማሳተም የመጀመሪያው አይደለም። የመጨረሻውም አይሆንም። ግን ሁሌም 'አሉባልተኛው ደራሲ' በሚል ሲጠራ ይኖራል።

መጽሀፉን እንድታነቡ አልጋብዝም። ተቃጥሎ አመዱ ኮሪደር አስፋልት ላይ እንዲበተን ታዟል 😜😜🤣😋

ይህ ©የመሳይ መኮነን የተሰኘ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው።⬇️ለፈጣንና አዳዲስ መረጃዎች ጆይን👇
https://t.me/mesaymekonnen1

Anchore media አንከር ሚድያ ( በጋዜጠኛ መሳይ መኮነን)

26 Jul, 10:13


እስካሁን ባለኝ መረጃ ሰሎሞን ገሪማ ፋኖን የተቀላቀለ የመጀመሪያው የትግራይ ተወላጅ ነው::


ይህ ©የመሳይ መኮነን የተሰኘ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው።⬇️ለፈጣንና አዳዲስ መረጃዎች ጆይን👇
https://t.me/mesaymekonnen1

Anchore media አንከር ሚድያ ( በጋዜጠኛ መሳይ መኮነን)

26 Jul, 10:10


የምንመኘው ውድ ዋጋ የተከፈለለት ትንታግ ትውልድ ተፈጥሯል። የምንሰራው የአማራ ህዝብ በሺ ዓመታት ተከብሮ የሚኖርበትን ዘላቂ ስርዓት ነው።መሰረታዊ ነገር የነገው ትውልድ ላይ መስራት ነው።

ጆይን 👉 https://t.me/mesaymekonnen1

Anchore media አንከር ሚድያ ( በጋዜጠኛ መሳይ መኮነን)

02 May, 13:22


ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ በአማራ ክልል ዳታ በተዘጋባቸዉ ቦታዎች ዳታ ለመጠቀም ከደቂቃዎች በኋላ ቪድዮዉ ይለቀቃል subscribe በማድረግ ይጠብቁን👇👇👇

https://youtube.com/@EthioYoutubechannel?si=F5stENXoeFG0nOtv

Anchore media አንከር ሚድያ ( በጋዜጠኛ መሳይ መኮነን)

12 Feb, 13:55


የብልጽግናው መንደር በአድዋ ሙዚየም ምርቃት አቅሉን ስቶ እየፈነጠዘ ነው። ታሪኩን የሰሩት የአድዋ ጀግኖች እንኳን ከድላቸው በኋላ እንዲህ ሰማይ ምድሩ አይበቃንም አላሉም። ጀግና ይሰራል እንጂ ብዙ አያወራም። ያዙኝ ልቀቁኝ አይልም። ጀግና ሁሉ በልቡ ነው። ሌሎች ይናገሩለታል፥ ይመሰክሩለታል እንጂ 'ከእኔ በቀር ጀግና የለም' ብሎ ጆሮ እስኪደነቁር አይጮህም። ብልጽግና በትልቁ አፍ ሰጥቶታል። ጆሮው ግን የዝሆን ነው። አማኑዔል ሆስፒታል ሲጠበቅ ቤተመንግስት የተገኘው የፓርቲው መሪ፥ ኢትዮጵያን በአውሮፕላን መስሎ 'ልትበር ሞተሯን እያሞቀች ነው' ሲል ይናገራል። 'እድልና ጥረት ከደጃፋችን ተገናኝቶ ታሪክ ሰራን' ሲልም ይመጻደቃል። በእርግጥ እድለኛ ነው። የደነዘዘና የነፈዘ ቲፎዞ ከጀርባው እንደጉድ ያጨበጭብለታል። አዶልፍ ሂትለር የጀርመንን ህዝብ አብዶ እንዳሳበደው ዓይነት ነገር።

ኢትዮጵያ ክንፏ ተሰብሯል። እግሯ ወልቋል። ሞተሯ ተበላሽቷል። በዘር ፖለቲካ ምሶሶዎቿ ወላልቀው ወደ አንድ አቅጣጫ ልትወድቅ እያዘመመች መሆኗ የማይደብቁት እውነት ነው። አብይ አህመድ በቅዥት ውስጥ ሆኖ ክንፍ አበጅቶላት በአየር ላይ ሊያከንፋት አካኪ ዘራፍ ይላል። አራቱም ሞተሮቿ በረሃብ እርዛት ጦርነትና ሙስና ተበላሽተው መጠገን እንዳይችሉ ሆነው ቀርተዋል። አብይ ዘንድ ወሬ በሽ ነው። እብደት ጤንነትን አስንቋል። ክህደት ነውርነቱ ተቀይሯል። ሀሰት ከእውነት በላይ ነግሷል። ምላስ ከአንጎል ልቆ ረዝሟል። አብይ አህመድ ጉም እያዘገነ፥ የተስፋ ዳቦ እያስገመጠ፥ አየሩን እያስመተረ፥ ስድስት ዓመታትን ዘለቀ። በቃህ ካልተባለ ይቀጥላል። በእርግጥም እድለኛ ነው።

በራሱ ቋንቋ መጠቀም ከተቻለ። ይሄ ግርግር አቧራ እንጂ አሻራ አይሆንም። ያንተ ዘመን የሚታወሰው በኢትዮጵያውያን ዕልቂት ነው። 1 ሚሊዮን በላይ የአድዋ ልጆችን ለእሳት የማገድክበት ጦርነት ዝንትዓለምህን ከስምህ ጋር ይነሳል። ያንተ ዘመን ኢትዮጵያውያን በዘር ፖለቲካ ተከፋፍለው በየአጥራቸው ሆነው የአድዋ ጀግኖች ያቆሙትን ምሶሶ እንዲገዘግዙ የተደረገበትን ቆሻሻና ክፉ አስተዳደርህን ያየንበት ነው። ሀገራችንን የምድር ሲዖል አድርገህ፥ ዜጋው በገዛ ሀገሩ በመቶ ሺዎች አፈናቅለህ፥ የአድዋ ልጆችን በሚሊዮን ቁጥር በረሃብ አለንጋ ጠብሰህ፥ ተስፋውን አድርቀህ፥ ጽልመትን አውርሰህ የቆየህበትን አስቀያሚ የስልጣን ዘመንህን ታሪክ በደማቁ ያስቀምጠዋል።

ይህቺ ግርግር አቧራ ናት። ከቀናት በኋላ በና ትጠፋለች። አድዋ በልባችን ውስጥ እንጂ ፒያሳ ባቆምከው ህንጻ የሚደምቅ አይሆንም። ሰው ገድለሃል። ኢትዮጵያውያንን ጨፍጭፈሃል። ሰራሁት ብለህ የምትመጻደቀው፥ ሰማይ ድረስ ቢቆለል ሃጢያትህን አያነጻውም። የክፋትና ሴጣናዊ ተግባርህን የሚደብቀው አይደለም። በፍጹም። ሳያላምጡ የሚውጡ፥ ሳይገባቸው የሚያጨበጩቡት ወፈ ሰማይ ደጋፊዎችህ የሚሰጡህ አድናቆት የልብህን ብርሃን እንዳጨለመው ይገባናል። ብዙም አይቆይም። አሻራ ስላልሆነ ይጠፋል። አቧራ ስለሆነ ይበናል። ታሪክ የሚያስታውስህ ባጨቀየኸውና ባቆሸሽከው እንጂ ባስጨበጥከው ጉም አይደለም።


ጆይን 👉 https://t.me/mesaymekonnen1

Anchore media አንከር ሚድያ ( በጋዜጠኛ መሳይ መኮነን)

30 Jul, 23:01


የዐማራ ህዝብ የሚታገልላቸው ዋና ዋና ጥያቄዎች፤

1) ህገመንግስት

የአሁኑ ህገመንግስት ሲረቀቅም ሆነ ሲጽድቅ የዐማራን ህዝብ ያገለለ ነበር፡፡ አሁን ዐማራ የሚሳተፍበት አዲስ ህገመንግስት ያስፈልጋል፡፡

2) መንግሥት

ሀ) ስልጣን ለህዝብ ማስረከብ፦
አሁን በስልጣን ላይ ያለው አገዛዝ ወንጀለኛ፣ ዘር አጥፊ፤ የኢትዮጵያ ጠላቶች ቀኝ እጅ፣ የኢትዮጵያን ዳር ድንበር ያስደፈረና በጥቅሟ የተደራደረ፣ የኢትዮጵያ አገራዊ ህልውና ዋና የስጋት ምንጭ፣ ዘረኛ እና ምንም አይነት እምነት የማይጣልበት፤ የዐማራን እና የመላውን ኢትዮጵያ ህዝብ አደጋ ውስጥ የጣለ በመሆኑ በአስቸኳይ ስልጣን ለኢትዮጵያ ህዝብ ማስረከብ አለበት፡፡
ለ) የሽግግር መንግስት፦
አሁን የዐማራም ሆነ የኢትዮጵያም ቁጥር አንድ የህልውና ፈተና እና የአገሪቱ ቀጣይነት አደጋ የሆነው ብልጽግና በአስቸኳይ ፈርሶ በምትኩ ከሁሉም ክልሎች የተውጣጡ፤ በአሁኑ አገዛዝ ቅንጣት ታክል ተሳርፎ የሌላቸው ተሰባስበው ጊዜያዊ የሽግግር መንግስት እንዲመሰርቱ ማድረግ፤
ሐ) በኢትዮጵያ ህዝብ በአጠቃላይ በዐማራ ህዝብ ደግሞ በተለይ የመከራ ዶፍ ያወረዱት የብልጽግና ባለስልጣናት ለፍርድ እንዲቀርቡ፡፡

3) ማንነትና ወሰን

ሀ) የተመለሱ ግዛቶች ጉዳይ፦
የወልቃይት ጠገዴ ጠለምትና ራያ ህዝብ የዘር ጭፍጨፋ ሰለባ ሆኖ መቆየቱ በሁሉም የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሀይሎች የእምነት ቃል እንዲሰጥበት፤
የትግራይ ክልል የሚያራምደውን መልሶ የመውረር ህልም ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በይፋ እንዲሰርዝ፤
በዘር ጭፍጨፋ የተሳተፉ አካላት ለፍርድ እንዲቀርቡ፤
ለዚህ ህዝብ ከዘር ጭፍጨፋ መትረፉን እውቅና የሚሰጥ የሞራል፣ የስነልቦናና የቁሳቁስ ካሳ እንዲደረግለት፡፡

ለ) ያልተመለሱ ግዛቶች ጉዳይ፦
ከቀድሞው ሸዋ ክፍለሀገር ተቆርሰው ወደኦሮሚያ ክልል የገቡ የአማራ አካባቢዎች ባስችውኳይ እንዲመለሱ፤
መተከል ወደነበረበት ጎጃም ክፍለ ሀገር እንዲመለስ፤

ሐ) የአዲስ አበባ ጉዳይ፦
የአዲስ አበባ ህዝብ አብላጫ የአማራ ህዝብ በመሆኑ የህዝብ ቁጥሩን ግምት ውስጥ ያስገባ መብትና ጥቅሙን የሚያስከብር አስተዳደር እንዲመሰረት፤
በአዲስ አበባ የአማራና ደቡብ ኢትዮጵያ ህዝብ ላይ የተፈጸመ የማፈናቀል፤ የማዋከብ፣ ቤት የማፍረስ እና ንብረት የመዝረፍ ወንጀል የቁሳቁስ፣ የሞራልና የስነልቦና ካሳ እንዲጠየቅበት፤
ቤታቸው የፈረሰባቸውና የተፈናቀሉ ባስቸኳይ ከበቂ ካሳ ጋር ወደይዞታቸው እንዲመለሱ፤

መ) አዲስ አበባን የሬሳ ሳጥን ውስጥ ያስገባ የሸገር ከተማ የሚባል የአፓርታይድ ድንበር ባስቸኳይ እንዲሰረዝ፣
በሸገር ከተማ ምክንያት የተፈናቀሉ ኢትዮጵያዊያን ባስቸኳይ ከበቂ ካሳ ጋር ወደይዞታቸው እንዲመለሱ፤
የፈረሰው ቤታቸው እንዲገነባላቸው፤ በአገዛዙ ይፋዊ ይቅርታ እንዲጠየቁ፤

ሠ) በኦሮሚያ ክልል የተፈጸመው አማራን ዘሩን የማጥፋት እና የማጽዳት ወንጀል ተዋንያን ለፍርድ እንዲቀርቡ፤
የግፍ ሰለባ ቤተሰቦች ካሳ እንዲከፈላቸው፤
የተፈናቀሉ ከበቂ መልሶ ማቋቋሚያ ጋር ወደቀያቸው እንዲመለሱ፤
ወደፊት ተመሳሳይ ወንጀል እንዳይፈጸምባቸው ማስተማመኛ ዘዴዎች እንዲቀየሱ፤
በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው የመማር እና ባህላቸውን የማበልጸግ መብታቸው እንዲከበር፤

4) በአማራ ክልል ብልጽግና ሙሉ በሙሉ ፈርሶ በምትኩ ህዝባዊ አስተዳደር በአስቸኳይ እንዲቋቋም፤
በአማራ ህዝብ ላይ በደል የፈጸሙ የፖለቲካና የደህነንት መዋቅሮች አባላት ለፍርድ እንዲቀርቡ፤
የክልሉ ገዥ ፓርቲ ለአማራ ህዝብ መወገን ሲገባው፤ ከጠላት ወግኖ ህዝቡን ሲወጋ በመኖሩ በአደባባይ ህዝቡን ይቅርታ እንዲጠይቅ፡፡

5) ሀይማኖት
መንግስትና ሀይማኖት የተለያዩ ናቸው የሚለውን መርህ በመጣስ አገዛዙ በሀይማኖቶች ውስጥ ገብቶ የፈተፈተው ሁሉ ወደነበረበት እንዲመለስ፤
ይሄንን ያደረጉ አካላትም ህዝብን ይቅርታ እንዲጠይቁ፤
በህግ የሚጠየቁም እንዲጠየቁ፡፡

6) ወያኔ እና ኦነግ፤ ወያኔያዊ እና ኦነጋዊ አስተሳሰቦች
ወያኔ እና ኦነግ በአማራ ህዝብ ላይ ላደረሱት በደል ከታሪክ እንዲፋቁ፤
እነሱን የሚያስታውስ ምንም አይነት ምልክት በህግ ክልክል እንዲሆን፤
የነሱን አስተሳሰብ ማራመድ በህግ የሚያስቀጣ እንዲሆን፤
አባላቱ በህዝቡ ላይ ላደረሱት በደል እየታደኑ ለፍርድ እንዲቀርቡ እና ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ፡፡
እነዚህ ድርጅቶች ለፈጸሙት ታሪክ ይቅር የማይለው የዘረኝነት ወንጀል የአማራን ህዝብ ይፋዊ ይቅርታ እንዲጠይቁ፡፡

7) የጥላቻ ንግግር
በወያኔና ኦነግ ፊታውራሪነት በአማራ ህዝብ ላይ የተካሄደ ግማሽ ክፍለ ዘመን የወሰደ የማጥላላት ዘመቻ ይቅርታ እንዲጠየቅበት፤
በሀሰት ለጠፋው ስም ማካካሻ ይሆን ዘንድ ማስተካከያ እንዲደረግበት፤
መልካምን ስምን ማደስና ማስመለስ በሚል ሰፊ የተዛባ ትርክት ማስተካከያ ስራ እንዲሰራ፤

8)) የዘር ማጥፋት
የአማራ ህዝብ የዘር ማጥፋት ወንጀል ሰለባ መሆኑ አገራቀፍ እና አለማቀፍ እውቅና እንዲሰጠው ማድረግ፤
የዘር ማጥፋቱ ተዋንያን ተለቅመው ለፍርድ እንዲቀርቡ፤
የዘር ማጥፋት ሰለባ ቤተሰቦች ካሳ እንዲከፈላቸው፤
መላው የአማራ ህዝብ ይፋዊ ይቅርታ እንዲጠየቅ፤
የዘር ማጥፋት ሰለባዎችን ማንነት የሚገልጽ መረጃ ተሰባስቦ የሚቀመጥበት ብሄራዊ ማለትም አገራቀፋዊና አለማቀፋዊ እውቅና ያለው “የአማራ የዘር ማጥፋት ወንጀል ሰለባዎች ሙዚየም” እንዲቋቋም፤

9) የጦር ወንጀል
ባለፉት ሁለት አመታት፤ ማለትም በአንደኛውና በሁለተኛው ዙር የወያኔ ወረራ ወያኔ በአማራ ህዝብ ላይ የጦር ወንጀል ፈጽሟል፡፡ ይሄንን ያደረጉ በሙሉ በአገራቀፍ እና በአለማቀፍ የጦር ወንጀለኝነት ህግ እንዲዳኙ፤
አሁን በብልጽግና አመራር ሰጭነት በደብረ ኤልያስና ሌሎች ስፍራዎች የጦር ወንጀሎች ተፈጽመዋል፤
የዚህ ተዋንያን በአገራቀፍ እና በአለማቀፍ የጦር ወንጀለኝነት ህግ እንዲዳኙ ማድረግ፤
ድል ለዐማራ ህዝብ!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!

Anchore media አንከር ሚድያ ( በጋዜጠኛ መሳይ መኮነን)

29 Jul, 00:53


ነበልባሉ 🔥🔥🔥 ትውልድ ተነስቷል!

አሁን ትግሉ ህዝባዊ መሠረት ያለው ''የመኖርና ያለመኖር'' ግብግብ ሆኗል። ግንባሩን ብትለው ወደኃላ የማይመለስ ፣ ትእግስቱ 'እጥጥ ሙጥጥ' ያለበት ፣ መገፋትና መበደል ያንገበገበው ''አንድም መኖር ነው ፣ አንድም መሞት ነው!'' ብሎ የቆረጠ ነበልባል 🔥🔥🔥 ትውልድ ተነስቷል!

ይህን ኃይል ሰማይ ምድሩን ጦር ብታዘንብ ልትገታው አትችልም። ስትመታው እንደምስማር ይጠብቃል ፣ ስትቆርጠው ሺህ ሆኖ ያቆጠቁጣል ፣ ስትገለው እየበዛ ይሄዳል!

ለህይወቱ የሚሳሳውና ለመኖር የሚጓጓው ፣ ህይወቱና ኑሮው የተመቸው ሰው ነው! እናማ ይህ የአማራ ትውልድ ''ሺህ አመት በባርነትና በስቃይ ከመኖር ፣ ፋሻዝምን ታግሎ አንድ ቀን መሞት ይሻላል!'' ብሎ ቆርጦ የተነሳ ነው!

ባይነሳ ነበር የሚገርመው አይደል?

አዎ! የጥላቻ ሰንኮፉ እስኪነቀል ፣ አማራነት የሚያስፈጅ ፣ የሚያሳድድ ፣ የሚያስበድልና የሚያስገድል የትርክት ማጥቂያ መሆኑ እስከሚያቆም ፣ 'ሁሉም እናቴ ሁሉንም ልጆቼ ' የምትል ሀገር እስክትኖረን ፣ ፍትህና እኩልነት እስኪረጋገጥ ፣ ....ድረስ ይህ ኃይል ታሊባን አሜሪካንን ለ20 አመት ከታገላትና አሸንፍ ካባረራትም በብዙ እጥፍ በሚልቅ ሁኔታ ይዋደቃል ፣ ይታገላል ፣ ያሸንፋል!

ፋሺዝም ይውደም‼️

Anchore media አንከር ሚድያ ( በጋዜጠኛ መሳይ መኮነን)

28 Jul, 02:44


ይህን እንደቀላል የምናልፈው አጀንዳ አይደለም‼️

''ማዳበሪያ ስጡኝ!'' ሲል ጥይት ያዘነበቡት ፣ ያለበትን መከራ ስናስተጋባ ከግብርና ቢሮ ኃላፊው ጀምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ፣ ''አርሷደሩን ከፊት አሰልፎ እንደጅራፍ በማስጮህ ፖለቲካ ለመቆመር እንጂ የማዳበሪያ እጥረት ኖሮ አይደለም!'' ሲሉ የተበሻቀጡበት የአማራ ገበሬ ፥  በአጠቃላይ በክልሉ በመኸር ሰብል መሸፈን ከነበረበት መሬት አርሶ ማብቀል የቻለው 50 ፐርሰንቱን ብቻ ነው። ከዚህ ውስጥ ''መሬቱ ፆም ከሚያድር ...!'' ተብሎ ካለአፈር ማዳበሪያ የተዘራም እንደሚኖር ይገመታል!

ብአዴን ህዝባችንን ካለበት ዘርፈ ብዙ የኑሮ ብስቁልናና መከራ ወደከፋ ረሀብና ስቃይ ሆነ ብሎ ከቶታል። በመከራው ተሳልቆበታል ፤ በኢኮኖሚ ተሽመድምዶና ለረሀብ እጅ ሰጥቶ ተመፅዋች እንዲሆን ፈርዶበታል!

Anchore media አንከር ሚድያ ( በጋዜጠኛ መሳይ መኮነን)

26 Jul, 19:07


የክህደት ወላፈን ....!

'' የሚያናግረንና የሚያስጮኸን ፣ ከሆዳችን የታመቀው እንደእቶን እሳት የሚፋጅ የክህደት ወላፈን ነው! ''

...የትህነግ ወራሪ ሀይል በ1983 የተጠቀመውን ካርታ እያነበበ ፣ በአንድ በኩል የአንባሰል ሰንሰለታማ ተራራዎችን አቆራርጦ በመምጣት በምንጩ ተሻግሮ በቦሩ ሜዳና በቦሩ ስላሴ ፣ ከጋሸና የተነሳው ኃይል በደላንታ መጥቶ በኩታበር አቅጣጫ ፣ ከሀይቅ በኩል የሚገሰግሰው ደግሞ የኒቦን ተራራ አልፎ ወደቦሩ ስላሴ ተጠግቷል። ደሴ ከተማን ለመያዝ በሶስት አቅጣጫ ከባድ ፍልሚያ ሆኗል። ደሴ ተጨንቃለች ፣ ነዋሪው ለቆ እየወጣ ነው ፣ ተቋማቶች ተዘግተዋል። የጠላት ጦር በቦሩ ስላሴ በኩል ተደጋጋሚ ሙከራ አድርጎ ነብሮቹን ፋኖዎች አልፎ መሄድ ራስ ምታት ሆኖበታል። በተደጋጋሚ ሰብሮ ለማለፍ የሞከራቸው ሙከራዎች በመክሸፋቸውም የበቀል እርምጃ ለመውሰድ እጅግ በርካታ ኃይሉን አስጠግቶ ከአናብስቶቹ ጋር ማዶ ለማዶ ተፋጠዋል።

በወቅቱ መከላከያው በፊኛ ውስጥ እንደተቋጠረ ውሃ መረጋጋት ተስኖት ፣ ''በዚህ ገባ ሲባል በዚህ ፈረሰ '' የተለመደ ዜና ሆኗል። በየደቂቃው የሚሰማው ''ደሴ ተያዘ ፣ አልተያዘ'' የሚል የጭንቅ ወሬ ብቻ ነው።

የመከላከያ አዛዦቹ ለፋኖ መሪዎች ''በቦሮ ስላሴ ያለው ነገር እየከፋ ስለመጣ ያላችሁን ተጨማሪ ሀይል ይዛችሁ ያንን በር ተከላከሉ!'' ሲሉ ትእዛዛቸውን አጠናከሩ።

ያቺን ቀን .... ለቀናት ረሀብና ውሃ ጥም ሳይበግራቸው በዚያ እጅን በሚቆላልፍ ብርድ ላይ የሰነበቱት ፋኖዎች ካሉበት ከምሽግ አልወጡም። ተጨማሪም ሀይል ገባ። ሰማይ ለአይን ለቀቅ ማድረግ ሲጀምር ቅልጥ ያለው ውጊያ ተጀመረ። ጀግኖቹ ከወዲያ ወዲህ እየተወናጨፉ እንደአንበጣ በመንጋ 'ግርርር...!'' ብሎ የመጣውን ሀይል ይለቅሙት ጀመረ። የቦሩ ስላሴ ተራራና ጫካ በወራሪው አስከሬን ተሞላ። ያንን በር አልፎ ደሴን መያዝ ቅዠት መሆኑ እስከሚገባቸው ድረስ ተረመረሙ። ይህን ተከትሎ ወደኃላ እያፈገፈጉ ተኩሱን እንደበረዶ ያዘንቡት ጀመር....

በዚህ እንደበረዶ በሚዘንብ የተኩስ ንዳድ መካከል አንበሳው ሞላ ደስዬና ይማም እብሬን የመሰሉ አርበኞቻችን ወደቁ! ሞላ ተመትቶ በወደቀበት ፣ ጎዶቹን ቆጣ ብሎ ''እኔን ለማንሳት አትድከሙ ፣ ሽፋን እሰጣችኃለሁ እናንተ ውጡ!'' አላቸው። ከወደቀበት ሆኖ እንኳ በጠላት ላይ እሳት ማዝነቡን አላቆመም ነበር። ሞላ ነበልባሉ ፣ ሞላ የወንዶች ቁና ....ሞላ የራያው መብረቅ....! እህህህህ...!

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ትጉ አባልና ደከመኝን የማያውቀው ብሎም በማናቸውም ጉዳዮች የቤተሰብ ያህል ከአጠገቤ የማይጠፋው ጀግናው ይማም እብሬም ፣ የአብንን የክተት ጥሪ ተከትሎ << ዘርሽ ወደፋኖ ማሰልጠኛ መግባቴ ነው! እኔ ብሞት እንኳ ለአንዲት ልጄ እናንተ አላችኃት!' >> ብሎኝ ወደካምፕ እንደሸኘሁት ሁሉ '' የልጄን ነገር አደራ...!'' እያለ በጀግንነት ተፋልሞ ይቺን ከንቱ አለም ጥሏት እብስ ጭልጥ አለ...! ዋ! ቦሩ ስ-ላ-ሴ...!

እነሞላ ደስዬ ባደረጉት ተጋድሎና በከፈሉት መስዋዕትነት ፣ ወራሪው ሀይል እንዳሰበው ቦሩ ስላሴን ተሻግሮ በቀላሉ ደሴን መቆጣጠር ሳይችል በመቅረቱ ወደኃላ ተመለሰ። የተፈራውም ተቀለበሰ። ሰፊ ስራ ተሰርቶ ነዋሪውም ወደከተማዋ መመለስ ጀመረ። መከላከያውም ትንፋሽ አግኝቶ ለመሰባሰብና ለማሰብ የሚሆን ጊዜ አገኘ። ከተማው ተረጋጋ ፤ ህዝቡ በሚያስደምም መልኩ ምግብና መጠጥ ተሸክሞ ምሽግ ድረስ እንደጅረት እየፈሰሰ ለሰራዊቱ ደጀንነትቱን ማሳየት ቀጠለ።

በዚያ ጦርነት እንደኔ በስፍራው ሆኖ በጠላት ላይ የደረሰውን ሽንፈት ፣ የተከናነበውን ውርደትና ያጋጠመውን ኪሳራ ፣ ''ደሴ ተያዘች!'' ሲባል '' ደሴ ተሸጠች እንጂ ተያዘች አትበሉኝ!'' ማለቱ አይቀርም!

እንግዲህ አመድ አፋሽ የሆኑት ፣ የተካዱት ብሎም ዛሬ ምስጋናና ሽልማቱ ቢቀር በቤታቸው እንኳ በሰላም እንዳይኖሩ ተደርገው የሚሳደዱት ሞላ ደስዬዎች ፣ ይማም እብሬዎች ናቸው።

የሚያናግረንና የሚያስጮኸን ፣ ከሆዳችን የታመቀው እንደእቶን እሳት የሚፋጅ ፣ የክህደት ወላፈን ነው!

''ውሀንስ የሚያናግረው ከውስጡ ያለው ድንጋይ ነው!'' ይባል የለምን ?

ክህደት‼️
ክህደት‼️
ክህደት‼️

Anchore media አንከር ሚድያ ( በጋዜጠኛ መሳይ መኮነን)

25 Jul, 23:05


<< ከደቡብ እና ከምዕራብ እዝ ያመጣነው 2 ኮር ሰራዊት እንዴት በደቡብ ወሎ እና ሰሜን ወሎ ያለውን የፋኖ ታጣቂ መደምሰስ አቃተው? እንዴትስ በዚህ ደረጃ ሊዋጉን ቻሉ? >>

ይህን ጠየቀው የሪፐብሊካን ጋርድ አዛዥ ጀነራል ብርሃኑ በቀለ ሰሞኑን በባህርዳር ከተማ ጀነራሎቹን ሰብስቦ በነበረበት ወቅት ነው!

ጓዶች! 1 ኮር ማለት ከ 30 እስከ 50 ሺህ ወታደር ያቀፈ ማለት ነው!

መገን ወሎ!

Anchore media አንከር ሚድያ ( በጋዜጠኛ መሳይ መኮነን)

21 Jul, 12:32


መፈንቅለ "መንግስት" ነው!

መከላከያ ከፖለቲካ ነፃ ነው የሚል ቀልድ አለ። አንዳንዴ ለማስመሰልም ይጥሩ ነበር።

አማራ ክልል ውስጥ በይፋ  በ24 ሰዓት ውስጥ አስተዳደር አፈርሳለሁ እያለ እየዛተ ነው።

በአማራ ምክር ቤት እንደሰማነው መከላከያ በአማራ ክልል ግልፅ  መፈንቅለ መንግስት እያደረገ ነው። በተለይ ጠለምት፣ ራያ፣ ወልቃይት ጠገዴና አበርገሌ ላይ መከላከያ ሰራዊት እያደረገ ያለው መፈንቅለ መንግስት ነው።  ከአማራ ክልል በድብቅ የተቀረፀው ድምፅ የሚያረጋግጠው ይህ ነው።  በአማራ ርስቶች ያሉ አስተዳደሮችን በ24 ሰዓት ውስጥ አፈርሳለሁ እያለ ነው።

ከአሁን ቀደምም ብርሃኑ ጁላ በአማራ ክልል ላይ ተመሳሳይ ነገር ብሏል። ይህ ሌላ ስም ሊሰጠው አይችልም። መፈንቅለ መንግስት ነው። የወረዳም ይሁን የዞን ጉዳዩ መፈንቅለ መንግስት ነው። የአማራ ህዝብ ይህን ከአሁኑ ካላስቆመ የሚመጣው የከፋ ነው። ካድሬው መታገል ያለበት ለራሱ ነው። ነገ በየስብሰባ አዳራሹ እየታነቀ የሚታሰረው በእነዚህ እብሪተኞች ነው። የራሱን ወገን አሳልፎ ከመስጠት የመጣበትን ከመገኑ ጋር ሆኖ ቢጋፈጥ ያዋጣዋል።

Anchore media አንከር ሚድያ ( በጋዜጠኛ መሳይ መኮነን)

18 Jul, 16:48


የኢትዮጵያን ኢንሳይደር ቢሮ በሩ ሳይሰበር ንብረቶቹ መዘረፋቸውን አሳውቋል። ይህን አስመልክቶ ሀቅ የሚዲያ ኮሚኒኬሽን የበተነው መግለጪያ ላይ ''ዘረፋው የተቀነባበረ'' እንደሆነ ገልጿል። ከዚህ ቀደም ኢትዮ 251 ሚዲያም ተመሳሳይ ዘረፋ ተፈጽሞበታል። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ እንዲሁ በር ሳይሰበርበት ንብረቶቹ ተወስደዋል። መሰል ድርጊቶች በሌሎች አካላት ላይም ተፈጽሟል። በጣም በተጠና ሁኔታ የሚደረገው እንዲህ ዓይነት እርምጃ የአገዛዙን ማፊያ አሰራር በግልጽ የሚያመለክት ነው።ከዚህ ጀርባ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የሚሉት አብይ አህመድ አምጦ የወለደው ተቋም እጁ እንዳለበት ይነገራል።

ወርቁ ጋቸና የሚባል በአብይ ሳምባ የሚተነፍስ ሰውዬ የሚመራው ይህ ተቋም የሲሲሊያ ማፊያዎችን የሚያስንቁ የወንጀልና የስለላ ስራዎች የሚሰራ እንደሆነ ይታወቃል። አብይ የሚፈራቸውን የራሱ ሰዎችን መኝታ ቤታቸው ካሜራ ገጥሞ የአልጋ ላይ ጨዋታቸውን ሳይቀር የሚቀርጽ እንደሆነ ውስጥ አዋቂዎች ይገልጻሉ። በካሜራ ውስጥ ድብቅ ገበናቸው የተቀረጸባቸው ሚኒስትሮችና ቁልፍ አመራሮች እንዳሉም ይነገራል። አፋቸው ተለጉሞ፡ ከሰውዬው ፍላጎት ውጪ ወለም ዘለም እንዳይሉ የሆኑ አመራሮች ይህንኑ ፈርተው እንደሆነም ይታወቃል። ይህ መስሪያ ቤት አብይ ድብቅ ወንጀል ሊሰራበት ያቋቋመው መሆኑ በግልጽ መታወቅ አለበት።

Anchore media አንከር ሚድያ ( በጋዜጠኛ መሳይ መኮነን)

16 Jul, 17:45


በፋኖ የተማረኩ የሚሊሻ እና የፖሊስ አባላት

"ህዎሓት ዳግም ሊዎረን ነው"በማለት ከሰሞኑንን ሚሊሻውን እርሻውን አስትተው ለ7 ቀናት ስልጠና ሊያስገቡት ነው።ሚስጥሩ ግን ከኦነግ ሰራዊት ጋር በማጣመር ፋኖ ጋር ሊያዋጉት ነው።

Anchore media አንከር ሚድያ ( በጋዜጠኛ መሳይ መኮነን)

15 Jul, 18:27


በአማራ ላይ የተከፈተ ጦርነት ነው! ኢትዮጵያዊያን ሊያወግዙት የሚገባ ነው!

ምሬ ወዳጆን ከወገኑ ባልተናነሰ መከላከያ ያውቀዋል። መከላከያ ሰራዊት ከራያና አካባቢው ከሸሸ በኋላ ለምሬ ፋኖ ራዲዮና ሌሎች መሳርያዎችን ሰጥቶት ትህነግ በያዘው አካባቢ ጭምር እየገባ ያደራጀ፣ የተዋጋ ጀግና ነው።

በጦርነቱ ወቅት ለትህነግ ሙሉ መኪና መሳርያ ያስረከበ ጀኔራል አለ። ምሬ በተቃራኒው ከትህነግ ሲማርክ የከረመ ጀግና ነው።

ትህነግ በተደጋጋሚ ሲያጠቃው ለከረመ ህዝብ የደረሰው የምስራቅ አማራ ፋኖ ነው።

መከላከያ ሲከበብ ከበባ የሰበረ ኃይል ነው።

ሞሬ ወደ ትግል የገባው ሀብቱን በትኖ ነው። ለህዝብ ዋጋ ከፍሏል። በእነ ምሬ ላይ የተከፈተው ጦርነት በአማራ ህዝብ ላይ የተከፈተ ጦርነት ነው። ሶስት አመት ሙሉ ጦርነት በከረመበት ራያ ላይ የተከፈተው ጦርነት መላው አማራ ላይ የታወጀ ነው። የትህነግ ጦርነት ጋብ ሲል ህዝብ በገዥዎቹ ዘመቻ እየተሰቃየ ነው።

ባንክ አልዘረፉም። አገር አልከዱም። ሌላ ህዝብ አልወረሩም። በራያ ላይ የተከፈተው ጦርነት  አማራን ለማዳከም የታቀደ  ነው።

በትግል ላይ ነን የሚል አካል አንዳንድ ጉዳዮችን እንደ ድል አይቶ ከመዘናጋት ወረራው እንዲቆም፣ እንዲመከት ማድረግ ላይ ማተኮር አለበት።

ፋኖ ዋጋ እንደከፈለላቸው፣ እንዳተረፋቸው የሚያውቁ የመከላከያ ሰራዊት አባላት እየከዱ ነው። የጦርነቱን አላማ ስለሚያውቁ ነው። የወረራውን ፀረ አማራ አላማ የሚያውቁ የሰራዊት አመራሮችና አባላት ጭምር አሁንም ይህን ወረራ መቃወም አለባቸው።

ያኔ! በርካቶች በሸሹበት መከታ የሆኑት እነ ምሬ ናቸው። ኢትዮጵያ ልትፈርስ ነው ሲባል ከግንባር የተገኙት እነ ምሬ ናቸው። አዲስ አበባ ሆነው ሲጨነቁ ለነበሩት እፎይታ የሰጡት እንደ ምሬ ያሉት ናቸው። የአማራ ብቻ ሳይሆኑ የአገር ባለውለታዎች ናቸው። ይህ ፀረ አማራ ዘመቻ መቆም አለበት። ኢትዮጵያዊያን ጭምር ሊያወግዙት ይገባል።

Anchore media አንከር ሚድያ ( በጋዜጠኛ መሳይ መኮነን)

14 Jul, 16:33


በቆቦ ከተማ አቅራቢያ በመከላከያ እና በፋኖ መካከል ከፍተኛ ተኩስ መካሄዱ ተገለጸ

አርብ ሐምሌ 7 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን በቆቦ ከተማ አቅራቢያ በተለይም ቀመሌ ተብሎ በሚጠራ ተራራ፤ በመከላከያ ሠራዊትና በፋኖ መካከል ትናንት ሐምሌ 6/2015 ከፍተኛ ተኩስ መካሄዱን የአካባቢው ነዋሪዎች ለአዲስ ማለዳ ገልጸዋል፡፡

የተኩስ ልውውጡ መካሄድ የጀመረው ትናንት ጠዋት 12 ሰዓት ላይ እንደነበር የገለጹት ነዋሪዎቹ፤ እስከ ምሽት ድረስ የቀጠለው የተኩስ ልውውጥ ወደ ከተማው መጠጋቱን እና ድንኳን ተብሎ ወደሚጠራው ተራራ መስፋፋቱን ተናግረዋል፡፡

በዚህም በቆቦ ከተማ ኹለት ንጹሃን መገደላቸውንና ሦስት ሰዎች ደግሞ ቆስለው ወደ ሆስፒታል መግባታቸውን ጠቁመው፤ የሟቾችና የቆሰሉ ሰዎች ቁጥር ከዚህም ሊጭምር ይችላል ብለዋል።

በከተማው ዙሪያ እየተካሄደ ባለው ተኩስ ፈንጂን ጨምሮ የሞርታር፣ ዲሽቃ እና የተለያዩ የከባድ መሳሪያዎች ድምጽ መሰማቱን ነው የጠቆሙት፡፡ 

ነዋሪዎቹ አክለውም በከተማዋ አቅራቢያ የሚገኝ ተራራ በርካታ የፋኖ አባላት ይኖራሉ ያሉ ሲሆን፤ የተኩስ ልውውጡም የመከላከያ ሠራዊት አባላቱ የፋኖ አባላቱን “ከተራራው እናስለቅቃለን” በሚል እንደተጀመረ ጠቁመዋል፡፡

በዚህም በርካታ የአንቡላንስ ተሽከርካሪዎች ከወልዲያ ከተማ ወደ ቆቦ መጓዛቸውን ጠቅሰው፤ ይህም በውጊያው ጉዳት የደረሰባቸው የመከላከያ ሠራዊት አባላትን ለማንሳት ሳይሆን እንዳልቀረ ተናግረዋል፡፡

ሰሞኑን በቆቦ ከተማና አካባቢው በመንግሥት የጸጥታ አካላትና በፋኖ መካከል ውጥረት ነግሶ እንደነበርና ባለፈው ሰኞ ሐምሌ 03/2015 የተኩስ ልውውጥ መካሄዱ ተመላክቷል።

በዚህም ፋኖን እንደግፋልን የሚሉ አካላት በቆቦ ከተማ በሚገኘው ፖሊስ ጣቢያ ላይ ሦሰት ቦንብ በመወርወር ጉዳት ማድረሳቸውና ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ የሕግ ታራሚዎች ማምለጣቸው ተመላክቷል፡፡

በመከላከያ ሠራዊት አባላትና በፋኖ መካከል የተካሄደውን የተኩስ ልውውጥ ተከትሎ፤ በቆቦ እና ወልዲያ ከተማዎች በርካታ የመከላከያ ሠራዊት አባል መግባቱንና በኬላዎች ጠንካራ ፈተሻ መኖሩን መረዳት ተችሏል።

በዛሬው ዕለት በአካባቢው የነበረው ተኩስ መቆሙንና የተዘጋው መንገድ ተከፍቶ መደበኛ እንቅስቃሴ መጀመሩን ነዋሪዎች ለአዲስ ማለዳ ገልጸዋል፡፡

በተያያዘም ረቡዕ ሐምሌ 05/2015 ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ በላሊበላ ከተማ በትራፊክ ፖሊስ እና በባጃጅ አሽከርካሪዎች መካከል በተፈጠረ አለመግባባት፤ አንድ ትራፊክ ፖሊስ አባል ሦስት የባጃጅ አሽከርካሪዎች ላይ ተኩስ በመክፈት አቁስሏቸው መሰወሩን ተነግሯልል፡፡

በዚህም “የትራፊክ ፖሊስ አባሉ ለሕግ ይቅረብለን” በሚል በመንግሥት የጸጥታ አባላትና በሕዝቡ መካከል ውጥረት መኖሩ ነው የተጠቀሰው።

የፌደራል መንግሥቱ “የአማራ ክልል መንግሥትን በኃይል ለማስወገድ የሚያሴሩ ጽንፈኛ ኃይሎች አሉ” በሚል በክልሉ የሕግ ማስከበር ዘመቻ እያደረኩኝ ነው ካለ ቆይቷል።

Anchore media አንከር ሚድያ ( በጋዜጠኛ መሳይ መኮነን)

13 Jul, 18:52


የፌደራል መንግስቱ በሰላም ስምምነቱ መሰረት ትጥቅ ያስፈታል ሲባል ህወሓትን አዲስ ጦር እንዲያደራጅ እያገዘው ነው።

አሜሪካኖች ራያ አማራ መሆኑን ተገንዝበው መመለሳቸውን የአላማጣ ከንቲባ ገልፀዋል። በአሜሪካኖቹ ራያን መጎብኘታቸው እነ ጌታቸው ረዳን ማበሳጨቱ ይታወሳል።

Anchore media አንከር ሚድያ ( በጋዜጠኛ መሳይ መኮነን)

13 Jul, 13:58


ቆቦ!

<< ራያ ቆቦ የአብይ አህመድ/ኦህዴድ መከላከያ በህዝብ ላይ በከፈተው ተኩስ ምክንያት ከባድ ውጊያ ላይ መሆናቸውን ከቦታው በደረሰን መረጃ ለማረጋገጥ ችለናል ።

Anchore media አንከር ሚድያ ( በጋዜጠኛ መሳይ መኮነን)

10 Jul, 23:57


https://www.youtube.com/watch?v=IlMdTcQnfNM