کانال በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን (ከገድላት አንደበት) @kegedilatandebet27217 در تلگرام

በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን (ከገድላት አንደበት)

በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን (ከገድላት አንደበት)
ይኽ ለ3ኛ ጊዜ የተከፈተ አዲስ ቻናል ነው። በየቀኑ ገድለ ቅዱሳንና የተለያዩ አገልግሎቶች በጽሑፍና በድምፅ ይተላለፉበታል።
12,180 مشترک
1,468 عکس
32 ویدیو
آخرین به‌روزرسانی 06.03.2025 13:30

የቅዱሳን ኅሩያን፣ ከገድላት አንደበት ወቅታዊ መረጃ

ቅዱሳን ኅሩያን የአማርኛ ድምፅ ቻናል አዲስ ይዘው እንደሚገኙ የሚያዘዙ ሀይማኖታዊነትና የእምነት ጸጋ ይበልጣል። ይህ ቻናል ለዚህ ወቅት የወሰነ አዲስ ዝርዝር በሚኖርበት ጊዜ ገድለ ቅዱሳንን በጽሑፍና በድምፅ ይተላለፉበታል። በየቀኑ የሚኖሩ ትዕዛዞች እና መረጃዎች ይታወቃሉ። ቅዱሳን ኅሩያን እንዲሁም የፍትሕ እና የአስተዋል ብሄርን ይዮው የሚሰጣል ነው።

ቅዱሳን ኅሩያን ቻናል ምን ይዟል?

ቅዱሳን ኅሩያን ቻናል ከእምነት እና በመንፈሳዊ ዓይነት ጋር የተያያዘ ድምፅ እና ገለጻ ላይ ይገኛል። የቻናሉ ዋነኛ ጊዜ ለውህድ በሚገኘው ዕንቅስቃሴ የአማርኛ እና ሐዘን መሰረታዊ እንደዚህ ያለው አይነት ድምፅ ይሰጣል።

ይኽ ለ3ኛ ጊዜ የተከፈተ የውይይት እና የፍትሕ መሀይል መረጃዎች ተጨማሪ ተመልካት ይሰጣል። እነዚህ ገንቢዎች የከንቱ እና የዝማኔ ገድለ ሃይማኖታትን ይወዳድሩ ይችላሉ።

ቅዱሳን ኅሩያን አንድ የሚሰጣቸው አገልግሎት ምንድን ነው?

ቅዱሳን ኅሩያን ለመጠቀም የዝርዝር አገልግሎት አብሮትን ይሰጣል። አንዱ ዝርዝር በገድለ ቅዱሳን መሠረት የሚኖሩ እና በእምነታቸው የተነሱ የምርት ማዕከላዊ ጋር ይታወቃሉ።

እንዲሁም ዘርዝር አገልግሎታት በጽሑፍ ገበሬ ይቀርባሉ። የሚኖሩ ቅዱሳን ገድለ አይነት ዕውነታቸው ይወዳድሩ ይችላሉ።

የቅዱሳን ኅሩያን ምን የሚተላለፊ ይዘት አለው?

የቅዱሳን ኅሩያን ይዘት እንደዚህ ይሰጣል። ይህ በውይይት እና በክፍል ያሉበት ሀይማኖታቸውን ግንቦት ይወዳድሩ ይችላሉ።

ይህ ዘመናዊ ይዘት ይወዳድሩን ይብዛል እና እርግብ የብዙ ተጽእኖን ያለው ይሆን። ይገኝተህ እንደ ሀይማኖት ሞልክን የቀደም ጨዋታ ይወዳድሩ ይሆን።

ቅዱሳን ኅሩያን ምንድን ዓይነት ዝርዝር አገልግሎት አለ?

ቅዱሳን ኅሩያን ይዚህ ዓይነት ዝርዝር ይሰጣል። ይኸው ተረጃን ወደ ቅዱሳን ዙሪያ እና ዘርዝር እንደ ዘይውን በሚገኝ የወጣበትን ይወዳድሩ ይችላሉ።

ይህ ቅዱሳን ላይ ያቀርባቸው ያለው ዝርዝር አገልግሎት ኀኪም ይልቅ ይሆን። የእምነት አይነት የሚገኘው ዝርዝር ይሰጣል።

کانال تلگرام በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን (ከገድላት አንደበት)

በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን (ከገድላት አንደበት) የታሪኩን ስነስርዓት የተማሪዎችን ማስታወቂያዎችን እና ጽሑፍን ከአፈቃላይ መልእክት ማወቅ ይችላሉ ። እስካሁንም ገድላት የኅሩያን ወንድሞችን እና ሴትሞችን ለመመልከት መረጃዎች ይሰጡበታል። ብቁ ከገዳብ ልብ ውስጥ የሚደረጉትን ውይይት ሰልቦና በኮንትራቨኝ መናገር ይችላሉ።

آخرین پست‌های በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን (ከገድላት አንደበት)

Post image

በዚኽች ዕለት የካቲት 27 ቀን ያረፉት አቡነ ዓምደ ሥላሴ 28 መነኮሳትን በግፍ ገድለው ገዳሙን አጥፍተው ወደመጡበት ሲመለሱ በነበሩት የጣሊያን አውፕላኖች ላይ ይኽን ተአምር አደረጉ፦ አቡነ ዓምደ ሥላሴ ያቀኑትንና የጥንቱን ደገኛውን የገዳም ሥርዓት እንደጠበቀ የሚገኘውን ታላቁን ማኅበረ ሥላሴ አንድነት ገዳምን የደበደቡት ሁለት የጣሊያን አውፕላኖች ወደመጡበት ሲመለሱ እዛው የገዳሙ ክልል ውስጥ እንዳሉ በጻድቁ በአቡነ ዓምደ ሥላሴ ገቢረ ተአምር አውፕላኖቹ ማንም ሳይነካቸው ወድቀው ተከስክሰዋል፡፡ የአውፕላኖቹ ስብርባሪ ዛሬም ድረስ በገዳሙ ክልል ውስጥ ለምስክርነት በወደቁበት ሥፍራ ይገኛል፡፡

የጥንቱን ደገኛውን የገዳም ሥርዓት እንደጠበቀ የሚገኝ አንጋፋው ማኅበረ ሥላሴ አንድነት ገዳም ሥርዓቱና ሕጉ ጥንት እንደነበረው ነው፡፡ ገዳሙ ለመላው ኦርቶዶክሳዊ ክርስቲያን መመኪያና ለነፍስ ደኅነት በር ከፋች ሲሆን በቦታው በታላቅ ተጋድሎ የሚኖሩት አባቶችም በጸሎት አገርን ከመዓት ከመቅሰፍትና ከወራሪ ጠላት ምእመናንን በረድኤት የሚጠብቅ ታላቅ መመኪያችን ገዳም ነው፡፡

ከጌታችን ከአምላካችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በፊት በርዕሰ ገዳማት ማኅበረ ሥላሴ አንድነት ገዳም ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ቀደምት አባቶች የጌታችንን መወለዱን በተስፋ ትንቢቱን ይጠብቁ ነበር፡፡ በብህትውና ለነበሩ አባቶችን የጌታችንን መወለድ ያበሰረቻቸው ሰሳ ናት፡፡ በገዳሙ ውስጥ የነበረች አንዲት ሰሳ (ቶራ) ጌታችን በቤተልሔም በተወለደ ጊዜ በተአምራት በሰው አንደበት ‹‹ዮም ተወልደ ቤዛ ኩሉ ዓለም ዮም ተወልደ ከሣቴ ብርሃን ዮም ተወልድ መድኃኔዓለም-ዛሬ የብርሃን አምላክ የዓለም ቤዛ መድኃኔዓለም ተወለደ›› ብላ በመዝለል ልደቱን በሀገራችን አሰምታለች እርሷም በቤተልሔም ካሉ መላእክትና እረኞች ጋር በልደቱ ተደስታለች። (የገነት ምድርን ከሚያጠጡት ወንዞች አንዱ የሆነው የግዮን ወንዝንም በጌታችን ልደት ጊዜ ወደ ወተትነት እንደተለወጠ ልብ ይሏል።)

ታላቁን ማኅበረ ሥላሴ ገዳምን መሳፍንት፣ ታላላቅ ነገሥታት፣ ታላላቅ ጳጳሳት፤ የከበሩ ቅዱሳን አባቶችና ቅድሳት እናቶች መናኻሪያቸው በማድረግ የተጋድሏቸው በዓት፣ የቅድስናቸው መገኛ መጀመሪያ የዘላለም ማረፊያቸውም አድርገውታል። ለምሳሌ ከነገሥታቱ እነ ዐፄ ፋሲል፣ እነ ዐፄ ቴዎድሮስ፣ እነ ዐፄ ዮሐንስ፣ እነ ዐፄ ምኒሊክን ጨምሮ ብዙ ታላላቅ ነገሥታትም በዚህ ገዳም ሥርዓተ መንግሥትና ቅዱሳት መጻሕፍትን በመመርመር ያደጉበት ታላቅ ገዳም ነው። የመይሳው ካሳ (ዐፄ ቴዎድሮስ) ገና ከልጅነታቸው ጀምረው ፊደል ቆጥረው፣ ዳዊት ደግመው የተማሩትና ያገለገሉት በመጨረሻም በሞት ባረፉ ጊዜ የተቀበሩት በዚህ ታላቅ ገዳም ነው። ዐፄ ቴዎድሮስ "...ባደኩበትና በተማርኩበት በማኅበረ ሥላሴ ገዳም ቅበሩኝ" ብለው አስቀድመው ስለተናዘዙ በልጃቸው በመሸሻ ቴዎድሮስ አማካይነት ነው ማኅበረ ሥላሴ ገዳም የተቀበሩት።

ገዳሙን በ4ኛው መ/ክ/ዘ የነበሩት ደገኞቹ ወንድማማቾቹ ቅዱሳን ነገሥታት አብርሃ ወአጽብሓ ያስፋፉት ቢሆንም ገዳሙ ሱዳን ድንበር ላይ የሚገኝ በመሆኑ አሕዛብ እስላሞችና የውጭ ጠላቶቸ በተለያየ ጊዜ ከ7 ጊዜ በላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሰውበታል፡፡ለምሳሌ ቅዱሳን ነገሥታት አብርሃ ወአጽብሓ ያነጹትን ዮዲት ጉዲት አቃጠለችው፣ መነኮሳቱን ገድላ ቅርሱን ዘረፈች፡፡ ንጉሥ አግብዓ ጽዮን ያሠሩትን ደግሞ ግራኝ መሐመድ አጥፍቶታል፣ እርሱም መነኮሳቱን ድጋሚ ገድለ ቅርስ ዘረፈ፡፡ በኋላ በዐፄ ሠርጸ ድንግል የተሠራውን ደርቡሾች አቃጠሉት፤ በዐፄ ዮሐንስ ዘመንም (1600-1625) ሃይማኖት ተፋልሶ ገዳሙ ጠፍቷል፤ በ1877 ዓ.ም ደርቡሾች ድጋሚ ገዳሙን አቃጥለው መነኮሳቱን ገድለዋል፡፡ በዐፄ ቴዎድሮስ ዘመንም እንግሊዞች የገዳሙን ቅርሶች ዘርፈው ወስደዋል፡፡ በኋላም በተፈሪ መኮንን አልጋ ወራሽነት እቴጌ ዘውዲቱ (1909-1922) የተቃጠለውን ቤ/ክ አሠርተው ለመነኮሳቱ የሚሆን የውኃ ማጠራቀሚያ ትልቅ ታንከር አስቆፍረው ያሠሩላቸው ቢሆንም ጣልያን በ1928 በከባድ መሳሪያ በአውሮፕላን መትቶ ገዳሙንና ታንከሩን አቃጥሎታል፡፡ 28 መነኮሳትንም በግፍ ገድሏል፡፡ የፈረሰው የውኃ ታንከር ዛሬም ድረስ በምስክርነት አለ፡፡ ገዳሙን የደበደቡት ሁለት አውፕላኖችም ወደመጡበት ሲመለሱ እዛው የገዳሙ ክልል ውስጥ እንዳሉ በጻድቁ በአቡነ ዓምደ ሥላሴ ገቢረ ተአምር አውፕላኖቹ ማንም ሳይነካቸው ወድቀው ተከስክሰዋል፡፡ የአውፕላኖቹ ስብርባሪ ዛሬም ድረስ በገዳሙ ክልል ውስጥ ለምስክርነት በወደቁበት ሥፍራ ይገኛል፡፡

የማኅበረ ሥላሴን ገዳም ጻድቁ እንደመሶብ አንሥተው ለአጋዝእተ ዓለም ሥላሴ አስባርከውታል፡፡ ጻድቁ በቦታው ላይ ለ60 ዓመታት ሙሉ በፀሐይ ብቻ የበሰለ ምግብ እየተመገቡ በታላቅ ተጋድሎ ኖረው ታላቅ ቃልኪዳን ተቀብለውበታል፡፡ ዛሬ ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤ/ክ በምትገኝበት በየትኛውም ዓለም ላይ ቅዳሴ በሚቀደስበት ወቅት የማኅበረ ሥላሴ ገዳም ስሙ ሳይጠራ አይውልም፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን የቅዳሴ ሥርዓት ላይ በጸሎተ ቅዳሴ ወቅት ከቅዱስ ቁርባን በፊት ‹‹ሰላም ለክሙ ማኅበረ ሥላሴ…›› በማለት በዜማ የሚደረስ የጸሎት ክፍል አለ፡፡ ዜማውን የደረሱትና ሥርዓቱን የሠሩት ገዳሙ ካፈራቸው ታላላቅ ቅዱሳን አባቶች መካከል አንዱ የሆኑት ቅዱስ አርከ ሥሉስ ናቸው፡፡ ማኅበረ ሥላሴ አንድነት ገዳም ታላቅና ጥንታዊ ገዳም መሆኑ በዚህ ይታወቃል፡፡ በየትኛው ዓለም ላይ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ውስጥ ቅዳሴ በሚቀደስበት ሰዓት ስሙ ሳይጠራ አይውልም፡፡

አቡነ ዓምደ ሥላሴ ዐፄ ሱስንዮስ ካቶሊካውያን ደግፈው 8ሺህ የሀገራችንን ሊቃውንት በአንድ ቀን ባሳረዱ ጊዜ ንጉሡ ወዲያው ‹‹ኦርቶዶክስ ይርከስ ካቶሊክ ይንገስ›› ብሎ ያወጀበት ምላሱ ተጎልጉሎ ወጣ፡፡ እንደ አርዮስም ሆዱ አብጦ አንጀቱ ተልቶ ሊሞት ባለ ሰዓት አቡነ ዓምደ ሥላሴ አዘዞ ድረስ ሄደው ‹‹ፋሲል ይንገሥ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ትመለስ የሱስንዮስም ምላስ ይመለስ›› በማለት ተጎልጉሎ የወጣውን ምላሱን በመስቀላቸው ቢባርኩት ምላሱ ተመልሶለታል፡፡ ከዚህ በኋላ አቡነ ዓምደ ሥላሴ የዐፄ ፋሲልን ሹመትና ሃይማኖትን በአዋጅ አጽንተው ተመልሰው ወደ ገዳማቸው ማኅበረ ሥላሴ ገዳም ገብተዋል፡፡ ዐፄ ፋሲልንም የማኅበረ ሥላሴን ገዳም ግዛቱን ከሱዳን እስከ ጣቁሳ ድረስ እንዲሆን በአዋጅ ወስነው ሰጥተውት ነበር ነገር ግን ላይጠቀምበትና ላይጸና ነገር የደርግ መንግሥት የገዳሙን ሥርዓት ከማፍረሱም በላይ ርስት ጉልቱን ነጥቆ ወሰደበት፡፡ በደርቡሾች ወረራ ጊዜ እንግሊዞች አጋጣሚውን ተጠቅመው የአቡነ ዓምደ ሥላሴን ቅዱስ ገድል ዘርፈው ወስደውታል፡፡ ዛሬ በእንግሊዝ ሀገር ገድለ አቡነ ዓምደ ሥላሴ ይገኛል፡፡ ጻድቁ በዛሬዋ ዕለት የካቲት 27 ቀን ነው ያረፉት ዐፅማቸው በዚያው በመሠረቱት በማኅበረ ሥላሴ ገዳም በክብር ተቀምጧል፡፡

የአቡነ ዓምደ ሥላሴ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!

06 Mar, 07:58
973
Post image

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
የካቲት 27-ታላቁን ገዳም ማኅበረ ሥላሴን ያቀኑት ጻድቁ አቡነ ዓምደ ሥላሴ ዕረፍታቸው ነው፡፡
+ አባ አንስጣስዮስ ዕረፍቱ ነው፡፡ ይኽም ቅዱስ በትምህርቱ ዓለምን የመላ ሲሆን በታላቁ ንጉሥ በቆስጠንጢኖስ ዘመን የነበረ ነው፡፡ የከበሩ ቅዱሳን ሊቃውንት አባቶች በኒቅያ ከተማ የአንድነት ስብሰባ ባደረጉ ጊዜ በዚህ ጉባኤ ላይ ከተገኙት 318 ቅዱሳን ሊቃውንት ውስጥ የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት የሆነው አባ አንስጣስዮስ አንዱ ነው፡፡ በዚህም ጉባኤ ላይ ቅዱሳን ሊቃውንት ከሃዲ አርዮስን መክረው ዘክረው አስተምረው አልመለስ ቢላቸው ምእመናንን እንዳይበክል አውግዘው ለይተውታል፡፡

ቅዱሳን የከበሩ አባቶችም ሃይማኖትን አጽንተው ሥርዓትን ሠርተው ወደየሀገራቸው በተመለሱ ጊዜ ከኤጲስቆጶስነት ሹመት የተሻሩት ከሃድያኑ ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄዱ መስለው ወጥተው ወደ አንጾኪያ ከተማ በአንዲት አመንዝራ ሴት ዘንድ ተሰበሰቡ፡፡ ለዚህችም አመንዝራ ሴት ብዙ ገንዘብ ለመስጠት ቃል ገብተው በአባ አንስጣስዮስ ላይ በሀሰት ነገር ሠሩበት፡፡ ሴቲቱ ወደ ቤተ ክርስቲያን ከገባች በኋላ አባ አንስጣስዮስ ከእርሷ ጋር እንዳመነዘረ የወለደችውም ልጅ የእርሱ እንደሆነ አስመስላ ለካህናቱና ለሕዝቡ ሁሉ እንድትናገር አግባብተው በገንዘብ ደለሏት፡፡ እርሷም ለሕዝቡ ይህን ስትናገር ሕዝቡ አላመናትም ነበርና ‹‹አንቺ ሀሰተኛ ነሽ በዚህ ቅዱስ አባት ላይም ሀሰት ተናግረሻል፣ በከበረ ወንጌል ምለሽ ተገዝተሽ ካልተናገርሽ በቀር ቃልሽን አንቀበልም›› አሏት፡፡ እርሷም ስለገንዘብ ፍቅር በሀሰት ማለች፡፡

ከዚህም በኋላ ከሃድያኑ ለንጉሡ ነግረውና በሀሰት ከስሰው አባ አንስጣስዮስን ከመንበረ ሢመቱ ወደ አጥራክያ ደሴት አሳደዱት፡፡ በስደትም ሳለ በዚያው ዐረፈ፡፡ ነገር ግን እነዚህ ከሃድያን የክብርን ባለቤት መድኃኔዓለም ክርስቶስን ከመለኮቱ ባሕርይ ለይተው ‹ፍጡር ነው› ብለውታልና ዳግመኛም ይህንን ንጹሕና ቅዱስ አባት አባ አንስጣስዮስን ከአምንዝራ ሴት ጋር አንድ ሆነው በሀሰት በዝሙት ከስሰው አሳደውታልና እግዚአብሔር ቸል አላላቸውም፡፡ አባ አንስጣስዮስን ካሳደዱት በኋላ ያች አመንዝራ ሴት ጭንቅ በሆነ ደዌ ተያዘች፡፡ ብዙ ዘመንም ተሠቃይታ ለሞት በደረሰች ጊዜ ይህ ሁሉ መከራ የደረሰባት በከበረ ወንጌል በአባ አንስጣስዮስ ላይ በሀሰት ስለመሰከረች እንደሆነ ተገነዘበች፡፡ በአንጾኪያም ሰዎች ሁሉ ፊት ኃጢአቷን ተናግራ በደሏን አመነች፡፡ እንዲህም አለቻቸው፡- ‹‹ይህ ቅዱስ አንስጣስዮስ ከዝሙት ንጹሕ ነው፣ እነዚያ ከሃድያን ብዙ ገንዘብ ሰጥተውኝ በእርሱ ላይ ሐሰት እንድድናገር በከበረ ወንጌልም በሐሰት እንድምል አድርገውኝ ነው፡፡››
የአንጾኪያ አገር ሰዎችም ኃጢአቷን ማመኗን በሰሙ ጊዜ እጅግ አዘኑ፡፡ ካህናቱም በጸሎትና በቅዳሴ ጊዜ የአባ አንስጣስዮስን ስሙን የሚጠሩ ሆኑ፡፡ ታላቁ የቤተ ክርስቲያን ሊቅ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም አባ አንስጣስዮስን አመስግኖታል፡፡ በመታሰቢያውም ቀን ስለእርሱ ብዙ ቃላትን ደረሰ፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!
+ + +

አቡነ ዓምደ ሥላሴ:- አቡነ ዓምደ ሥላሴ የትውልድ ሀገራቸው ጎጃም ሲሆን በዐፄ ሱስንዮስ ዘመን የነበሩ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን ያደርጉ የነበሩ ገዳማዊ መነኩሴ ናቸው፡፡ ጻድቁ ማኅበረ ሥላሴን ያቀኑ ታላቅ አባት ሲሆኑ በተለይም አንድ የሚታወቁበት ትልቅ ታሪክ አላቸው፡፡ እርሱም ዐፄ ሱስንዮስ ካቶሊካውያን ደግፈው 8ሺህ የሀገራችንን ሊቃውንት በአንድ ቀን ባሳረዱ ጊዜ ንጉሡ ወዲያው ‹‹ኦርቶዶክስ ይርከስ ካቶሊክ ይንገስ›› ብሎ ያወጀበት ምላሱ ተጎልጉሎ ወጣ፡፡ እንደ አርዮስም ሆዱ አብጦ አንጀቱ ተልቶ ሊሞት ባለ ሰዓት አቡነ ዓምደ ሥላሴ አዘዞ ድረስ ሄደው ‹‹ፋሲል ይንገሥ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ትመለስ የሱስንዮስም ምላስ ይመለስ›› በማለት ተጎልጉሎ የወጣውን ምላሱን በመስቀላቸው ቢባርኩት ምላሱ ተመልሶለታል፡፡

ዐፄ ሱስንዮስ ግን ለካደበት ክህደት ቅጣቱ ነውና በመቅሰፍቱ ሳይድን በዚያው ታሞ ማቆ ማቆ ክፉ አሟሟት ሞቷል፡፡ ከዚህ በኋላ አቡነ ዓምደ ሥላሴ የዐፄ ፋሲልን ሹመትና ሃይማኖትን በአዋጅ አጽንተው ተመልሰው ወደ ገዳማቸው ማኅበረ ሥላሴ ገዳም ገብተዋል፡፡ ዐፄ ፋሲልንም የማኅበረ ሥላሴን ገዳም ግዛቱን ከሱዳን እስከ ጣቁሳ ድረስ እንዲሆን በአዋጅ ወስነው ሰጥተውት ነበር ነገር ግን ላይጠቀምበትና ላይጸና ነገር የደርግ መንግሥት የገዳሙን ሥርዓት ከማፍረሱም በላይ ርስት ጉልቱን ነጥቆ ወሰደበት፡፡

በደርቡሾች ወረራ ጊዜ እንግሊዞች አጋጣሚውን ተጠቅመው የአቡነ ዓምደ ሥላሴን ቅዱስ ገድል ዘርፈው ወስደውታል፡፡ ዛሬ በእንግሊዝ ሀገር ገድለ አቡነ ዓምደ ሥላሴ ይገኛል፡፡ ጻድቁ የካቲት 27 ቀን ያረፉ ሲሆን ዐፅማቸው በዚያው በመሠረቱት በማኅበረ ሥላሴ ገዳም በክብር ተቀምጧል፡፡

የአቡነ ዓምደ ሥላሴ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!

06 Mar, 01:17
1,267
Post image

‹‹ጌታዬ ሆይ! በሰው ፊት ክብሬን አትግለጥብኝ››

አቡነ ሀብተ ማርያም የዘውትር ጠባቂያቸው ቅዱስ ሚካኤል ካዘዛቸው በቀር ምንም አይሠሩም ነበር፡፡ ቅዱሳት መጻሕፍትንም ባነበቡ ጊዜ ኃይለ ቃሉን እየተረጎመ ምሥጢራትን ይነግራቸዋል፤ የተሰወረውንም ይገልጥላቸዋል፡፡ ከእንስሳት ጩኸት ጀምሮ ከዱር አራዊት ድምፅና እስከ አእዋፍ ቋንቋ ያለውን ያስረዳቸው ነበር፡፡

ይኸውም ቅዱስ መልአክ አንድ ቀን አቡነ ሀብተ ማርያምን ወደ ቤተ ክርስቲያን አስገብቷቸው ሥጋ ወደሙን ለመቀበል ተዘጋጅተው ሳለ ወንጌል የሚነበብበት ሰዓት ሲደርስ ያልተማረ ቄስ የክርስቶስ ጌትነቱን የምትናገር ወንጌልን ሲያነብ ‹‹ወዮሴፍ ብእሲሃ ለማርያም ጻድቅ ውእቱ›› የሚል ከቄሱ አፍ ይህን ንባብ አባታችን ሲሰሙ እጅግ ደንግጠው ወንጌል ወደሚነበብበት ስፍራ ሄደው የሚያነበውን ቄስ ገሠጹት፡፡ ‹‹ወዮሴፍሰ ፈሃሪሃ ለማርያም ጻድቅ ውእቱ በል እንጂ ብእሲሃ አትበል›› ብለው መከሩት፡፡ ቄሱም አቡነ ሀብተ ማርያም እንዳዘዙት ከስህተቱ ወደ ቀና ንባቡ ተመለሰ፡፡ ይህን ጊዜ ጌታችን ለአባታችን ድጋሚ ተገልጦላቸው ‹‹ሀብተ ማርያም ሆይ ይህን ትምህርትህን ወድጄ አመሰገንኩህ፣ የእናቴን የድንግል ማርያምን የድንግልናዋን ንጽሕና ስለ አከበርክ እኔም በመንግስተ ሰማያት ፈጽሜ አከብርሃለሁ›› አላቸው፡፡ ዳግመኛም ጌታችን ‹‹አሁንም ዮሴፍ ብእሲሃ ለማርያም የሚሉትን ሁሉ ለያቸው እንጂ አትተዋቸው፤ እንዲህ የሚል ጽሑፍም ብታገኝ እንዳይኖር እርሱን ፍቀህ ፈሃሪሃ ለማርያም የሚለውን ጻፍ›› ብሎ አባታችንን ካዘዛቸው በኋላ ሰላምታ ሰጥቷቸው ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡

አባታችንም በዚህ ጊዜ ፊታቸው ላይ ብርሃን ስለተሳለባቸውና እንደ ፀሐይ ስላበራ ሰዎችም አይተው ባደነቁ ጊዜ ወደ በዓታቸው ገቡና ጌታችንን ‹‹አቤቱ ጌታዬ ሆይ በሰው ፊት ክብሬን አትግለጥብኝ ሰውርልኝ፣ በቸርነትህም አድነኝ›› ብለው ጸለዩ፡፡እንዲህም ብለው በጸለዩ ጊዜ ፊታቸው መልኩ ተለውጦ እንደ ቀድሞው ሆነ፡፡

የአቡነ ሀብተ ማርያም የከበረች በረከታቸው ትደርብን!

05 Mar, 05:57
1,931
Post image

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
የካቲት 26-ቅዱስ ሳዶቅ ማኅበርተኞቹ ከሆኑ ሁለት ሺህ ስምንት ሰዎች ጋር በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡
+ የእግዚአብሔር ነቢይ ቅዱስ ሆሴዕ ዕረፍቱ ነው፡፡
ሰማዕቱ ቅዱስ ሳዶቅ፡- ይኽም ቅዱስ ምግባር ሃይማኖቱ ያማረ ደገኛ ክርስቲያን ነው፡፡ የከበረ ሳዶቅን ለፀሐይ ይሰግድ ዘንድ ብርህም የተባለው የፋርስ ንጉሥ አዘዘው፡፡ ቅዱስ ሳዶቅም ‹‹ፀሐይን ለፈጠራት ለዕውነተኛው አምላክ እንጂ ለዚህች ለምትታይ ፍጥረት ለሆነች ፀሐይ ልሰግድ ከእናቴ ማኅፀን አልወጣሁም›› አለው፡፡ ንጉሡም መልሶ ‹‹ለዚህች ፀሐይ አምላክ አላት እንዴ?›› ብሎ የጠቀው፡፡ ቅዱስ ሳዶቅም ‹‹ዓለምን ሁሉ የፈጠረ ዕውነተኛው አምላክ ክርስቶስ ነው›› አለው፡፡ ንጉሡም ይህን ሲሰማ እጅግ ተናዶ የቅዱስ ሳዶቅን ራስ በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ፡፡ የከበረ ቅዱስ ሳዶቅም ቆሞ ወደ እግዚአብሔር ከጸለየ በኋላ በሰይፍ ይቆርጡት ዘንድ ራሱን ዘንበል አድርጎ ሰጣቸው፡፡ እነርሱም ራሱን በሰይፍ ቆረጡትና ሰማዕትነቱን በድል ፈጸመ፡፡ ያን ጊዜም ከሰማይ ብሩህ ብርሃን በላዩ ወረደ፡፡ በዚያ ያሉ ሰዎችም ሁሉ ይህንን ለቅዱስ ሳዶቅ ከሰማይ የወረደለትን ብርሃን አይተው ‹‹እኛ ሁላችንም በቅዱስ ሳዶቅ አምላክ አምነናል፣ ክርስቲያን ነን›› ብለው ጮኸው መሰከሩ፡፡ ንጉሡም በዚህ ይበልጥ ተናዶ ሁሉንም በሰይፍ ራስ ራሶቻቸውን ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ፡፡ ያመኑትና የመሰከሩትም ሁሉም ተሰይፈው የሰማዕትነት አክሊልን በመንግሥተ ሰማያት ተቀበሉ፡፡ ቁጥራቸውም ሁለት ሺህ ስምንት ነፍሳት ናቸው፡፡ የቅዱስ ሳዶቅ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!
+ + +
ነቢዩ ቅዱስ ሆሴዕ፡- ይኽም ቅዱስ ነቢይ በአራቱ የይሁዳ ነገሥታት ዘመን በዖዝያን፣ በኢዮአታም፣ በአካዝና በሕዝቅያስ ዘመን ትንቢትን ሲናገር የኖረ ነው፡፡ በትንቢቱም ድንቆች ሥራዎችን ተናገረ፡፡ የእስራኤል ልጆችንም በክፋታቸው ገሠጻቸው፡፡ ‹‹የአመንዝራ ልጆች›› ብሎም ጠራቸው፡፡ እግዚአብሔርም ቁጣውን ከእነርሱ እንደማይመልስ ነገራቸው፡፡ ዳግመኛም ‹‹የእስራኤል ልጆች ቁጥራቸው እንደማይሰፈርና እንደማይቆጠር የባሕር አሸዋ ቢሆን ከጥቂት በቀር አይተርፉም›› አለ፡፡
ዳግመኛም አሕዛብ የሆኑ በእግዚአብሔር እንደሚያምኑ ትንቢትን ሲናገር ‹‹እኔ ወገኖቼ ያልሆኑትን እጠራቸዋለሁ፣ እነርሱም ይሰሙኛል›› አለ፡፡ ነቢዩ ሆሴዕ ዳግመኛም ስለ ጌታችን መከራ መስቀልና በከበረ ደሙ ስለመዳናችን ስለ ትንሣኤውም እንዲህ ብሎ ትንቢት ተናገረ፡- ‹‹እርሱ በመከራው ተገርፎ ያድነናል፣ ሲያድነንም በሁለተኛ ቀን ነው፡፡ በሦስተኛውም ቀን ድነን በእርሱ ፊት እንነሣለን፡፡›› ዳግመኛም እግዚአብሔርን ዐውቀን እንከተለው ዘንድ ስለሞት ሥልጣን መሻር ስለ መቃብርም መሸነፍ ትንቢትን ሲናገር ‹‹ሞት ሆይ! ይዘህ ማስቀረትህ መቃብርስ ድል መንሣትህ ወዴት ነው?›› አለው፡፡ ቅዱስ ሆሴዕ ትንቢትን እየተናገረ 70 ዓመት ኖሮ በበጎ የሽምግልናው ወቅት በሰላም ዐረፈ፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!

05 Mar, 05:56
1,706