ከ1920ዎቹ ጀምሮ የእምድብር 1ኛና መለስተኛ 2ኛ ደረጃ ትም/ቤት በጉራጌ እና አካባቢው ድንቅ ምሁራንን ያፈራ፤ አንጋፋ የትምህር ማእከል በመሆንም ለብዙዎች ባለውለታ የሆነ አይን ገላጭ የትምህርት እና የእውቀት ማእከል ነው፡፡
ይህ የትምህርት እና የታሪክ ተቋም አሁን ላይ በአገልግሎት ብዛት የተጎዳና የፈራረሰ በመሆኑ መሰረታዊ ጥገና ፈልጋል፡፡
በመሆኑም ይህንን የታሪክ እና እውቀት ማእከል የሆነው የእምድብር 1ኛና መለስተኛ 2ኛ ደረጃ ትም/ቤት መልሶ ግንባታ ላማካሔድ የምክክር፣ የገቢ እና የትምህርት መርጃዎች ማሰባሰቢያ መድረክ ተዘጋጀ በመሆኑ የቀድሞ ተማዎች፤ በጎ ፍቀደኞች፣ የጉራጌ ተወላጆችና ወዳጆች፤ በሁሉም ደረጃ የሚገኙ የመንግስት ስራ ሃላፊዎች በተገኙበት ሕዳር 15 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ጀምሮ በተግባረ ዕድ ቴክኒክ ኮሌድ እንድትገኙ በበጎነት ተጋብዛችኃል፡፡
በትምህርት ልማት ላይ በጎ አሻራ ማኖር ለምትሹ እና የዚህ ት/ቤት ባለደራዎች ሁሉ በመርኃ ግብሩ ላይ በመገኘት ታሪካዊና ሞራላዊ ግዴታችሁን እንደትወጡ በአክብሮት እየጠየቅን በ0911169836 ወይም 0911879963 በመደወል የበለጠ መረጃ ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
የእምድብር 1ኛና መለስተኛ 2ኛ ደረጃ ትም/ቤት መልሶ ግንባታ አስተባባሪ ኮሚቴ
Zebidar Tube/ ዘቢዳር ቲዩብ